fa
Feedback
መንፈሳዊ ግጥም ብቻ

መንፈሳዊ ግጥም ብቻ

رفتن به کانال در Telegram

በዚህ ቻናል ላይ በየቀኑ ኦርቶዶክሳዊ ግጥሞችን ያገኛሉ ለአስተያየትና ግጥም እንዲፖሰትላችሁ የምትፈልጉ ለመላክ @Solasc12 @Solasc13 @Mgetem_group ኦርቶዶክሳዊ ጥቅሶች ብቻ @Ortho_quotes

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام መንፈሳዊ ግጥም ብቻ

کانال መንፈሳዊ ግጥም ብቻ (@mgetem) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 27 276 مشترک است و جایگاه 2 689 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 219 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 27 276 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 28 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -287 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 0 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 19.38% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.43% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 286 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 481 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 25 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
በዚህ ቻናል ላይ በየቀኑ ኦርቶዶክሳዊ ግጥሞችን ያገኛሉ ለአስተያየትና ግጥም እንዲፖሰትላችሁ የምትፈልጉ ለመላክ @Solasc12 @Solasc13 @Mgetem_group ኦርቶዶክሳዊ ጥቅሶች ብቻ @Ortho_quotes

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 29 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

27 276
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-457 روز
-28730 روز
آرشیو پست ها
እርዳኝ ጌታዬ @Mgetem በሚያልፈው ፈተና የማታልፈውን በታናሽ ነገር አንተ ታላቁን ምስጋንን ትተው ከንፈሮቼ እንዳላማርር በአፌ ስቼ  እርዳኝ ጌታዬ የሆነብኝ ነገር ሁሉ ሊያበረታኝ ለኔ ሆነ አምናለሁ ወድቆ አይወድቅም ክርስቶስ አንተን ያመነ በውድቀቴ በሀዘኔ ይታየኝ ጌታ ማዳንህ ብርታት ስጠኝ የኔ ጌታ በእሳት መሃል ላመስግንህ ትዕግስት የለው ሰውነቴ ይቸኩላል  እስኪፈጸም የፈለገው ካልሆነለት ማመስገንን አልለመደም ምክንያት አለህ የኔ ጌታ ሥሕተት አይደል ስትከለክል በደስታዬ ብቻ ሳይሆን በሀዘኔም  ነህ ትክክል ለዘላቂ ድህነቴ ለጊዜው ነው ስትቀጣኝ እንዳልጠፋ አሰበህ ነው ወደኸኝ ነው ስትቆጣኝ ከቅድስናህ እንድካፈል ከክብርህ እንዳልጎድል አሳምመኽ ልታድነኝ ሠጠተኸኝ ነው በጎ እድል  እርዳኝ ጌታዬ ለክፉ አይሁን ልመናዬ አቅም ስጠኝ ልጠብቅህ መልስ  እስኪያገኝ  ጥያቄዬ ✍️ እሸቱ አበባው http://t.me/Mgetem http://t.me/Mgetem http://t.me/Mgetem

እርዳኝ ጌታዬ በሚያልፈው ፈተና የማታልፈውን በታናሽ ነገር አንተ ታላቁን ምስጋንን ትተው ከንፈሮቼ እንዳላማርር በአፌ ስቼ  እርዳኝ ጌታዬ የሆነብኝ ነገር ሁሉ ሊያበረታኝ ለኔ ሆነ አምናለሁ ወድቆ አይወድቅም ክርስቶስ አንተን ያመነ በውድቀቴ በሀዘኔ ይታየኝ ጌታ ማዳንህ ብርታት ስጠኝ የኔ ጌታ በእሳት መሃል ላመስግንህ ትዕግስት የለው ሰውነቴ ይቸኩላል  እስኪፈጸም የፈለገው ካልሆነለት ማመስገንን አልለመደም ምክንያት አለህ የኔ ጌታ ሥሕተት አይደል ስትከለክል በደስታዬ ብቻ ሳይሆን በሀዘኔም  ነህ ትክክል ለዘላቂ ድህነቴ ለጊዜው ነው ስትቀጣኝ እንዳልጠፋ አሰበህ ነው ወደኸኝ ነው ስትቆጣኝ ከቅድስናህ እንድካፈል ከክብርህ እንዳልጎድል አሳምመኽ ልታድነኝ ሠጠተኸኝ ነው በጎ እድል  እርዳኝ ጌታዬ ለክፉ አይሁን ልመናዬ አቅም ስጠኝ ልጠብቅህ መልስ  እስኪያገኝ  ጥያቄዬ ✍️ እሸቱ አበባው

🖥"የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ " በመምህር ዲያቆን ዘላለም ታዬ  👇👇 https://youtu.be/tzerWs__Kgg

🖥 እጅግ ድንቅ ስብከት ዲያቆን ዘላለም ታዬ  "የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ " 👇👇 https://youtu.be/tzerWs__Kgg https://youtu.be/tzerWs__Kgg https://youtu.be/tzerWs__Kgg

ወልድ እናቱን ላከ መዳን ላልወደዱት፥ ባይዋጥላቸው፤ ለእኛ ለም'ናምን፥ ይህ ቀን ግን ልዩ ነው። የአብራካቸው ክፋይ፥ የእያቄም ወሐና፤ ታስደምም ነበረ፥ በውበት ቁንጅና። ፃህፍት እንደሚሉት፥ በሾለ ብዕራቸው፤ ሁለንተናሽ ውብ ነው፥ ሰሎሞን እንዳለው፤ እንደ ቅዱስ አፍሬም፣ እንደ ህርያቆስ፤ ፅፎ እንደማይደክመው፥ እንደአባ ጊዮርጊስ፤ እሷን የነገሩን፥ ሙሽራ ብለው ነው።              ~~~ የታደለች እናት፥ ንፅህት የተባለች፤ በአምላክ ህሊና፥ ታስባ የኖረች፤ አለም ሁሉ እንዲድን፥ ግንቦት 1መጣች፤ እሰይ ደስ ይበለን፥ ማርያም ተወለደች።              ~~~ ግንቦት 1 ልዩ ነው፥ የተወደደ ቀን፤ ወልድ እናቱን ላከ፥ እኛን ሊታረቀን። ልጇ ነው አምላኳ፥ እሷ የምታዘው፤ አምላክ ሁኖ ልጅ ነው፥ አቤት የሚል ምነው። ውሃን የሚቀይር፥ በደልን የሚሸር፤ ሞትን ድል የነሳ፥ ያልያዘው መቃብር፤ የፍጥረትን ጌታ፥ ያቀፈች በክብር፤ የያዕቆብ መሰላል፥ ናት የሙሴ በትር፤ ስሟ የሚጣፍጥ፥ የሁለት ቃል ጥምር፤ ያም ከሰማይ ሲሆን፥ ማር ደግሞ ከምድር፤ ወልዳ ድንግል የሆነች፥ ያረገች በክብር፤ ማርያም ልደቷ ነው፥ ደስታችን እናብስር። ድንግል ልደቷ ነው፤ ደስ ብሎን እናክብር።              ~~~ መላኩ ከሰማይ፥ ደስ ይበልሽ ያላት ፅንስ ከማህፀን፥ በደስታ የዘለለላት ከድንግል ማርያም ውጭ፥ እስኪ ሌላ ማናት? እንዳለች ንገሩኝ፥እስኪ እኔም ልወቃት፤ ግን በፍፁም የለም፥ ከዚህ ሁሉ ፍጥረት።              ~~~ በ3አመት ወጥታ፥ ከእናት ከአባቷ ቤት፤ ቤተመቅደስ ኖረች፥ ለ12 ዓመት። ከቤተ መቅደሱ፥ ከትህትና ጋር፤ መሶብወርቅ ሰራች፥ በወርቅና በሐር። የሚያስፈልገውን፥ ለቤተ መቅደሱ፤ ስታዘጋጅ ኖረች፥ እስከሚመጣ እሱ። ቀርቦ ለለመናት..... ስሟ መድኃኒት ነው፥ ረሀብን ያጠፋል፤ ስለእመብርሃን ሲል፥ ተሜ ያውቅበታል፤ በድንግል ስም ብሎ፥ አኩፋዳው ይሞላል።              ~~~ አይሁድ አህዛቡ፥ ብሎም መናፍቁ.... ስለድንግል ምስጢር፥ ያልተዋጠላቸው፤ ዛሬም ሳይድኑ አሉ፥ ልቦና ይስጣቸው። ገብርኤል ተገልጦ፥ ምስጢር እስኪነግራት፤ ብትሰጣቸው ድንግል፥ ማርያም ንፅህት፤ መቅደሳችን አሉ፥ የአይሁድ ሞኝነት። የአይሁድኮ ድካም፥ የእነሱ ቂልነት፤ ስሞን እስኪፈራ፥ አጣመዋል ትንቢት። ስምኦን ተጨንቆ፥ ድንግል በድንግልና፤ ወንድ ልጅን ወልዳ፥ አለም ይድንና። ብዬ እናገራለሁ፥ በጨካኞቹ ፊት፤ ከዚህ ተሳስቷል፥ የኢሳያስ ትንቢት። ኢሳያስ ቢሳሳት፥ እኔ አልሳሳትም፤ ሴት ብዬ ልቀይ፥ የድንግልን እትም። ብሎ ቢልም ቅሉ፥ ስምኦን በድፍረት፤ መልአኩ ተላከ፥ የእግዜርን አሰራር እንዳይበክልብት።              ~~~ መቼም ከሳጥናኤል፥ መልካም ነገር የለም፤ ሲያስወቅሳት ኖረ፥ ሔዋንን ዘላለም። ከይሴኮ ተንኮሉ፥ የከይሴኮ ክፋት፤ አፉን አለስልሶ፥ አስወጣቸው ገነት፤ እግዜር ተቀይሞ፥ በጥንዶቹ ስህተት፤ የሚያማልድ ጠፍቶ፥ ገነትን የሚከፍት፤ እነ አዳም ኑረዋል፥ ሽህ ዘመን በግዞት።              ~~~ ሰፊው ቤት ቢዘጋ፥ በመጀመሪያዋ እናት፤ ሔዋን ስትወቀስ፥ ለብዙ ሽ ዓመታት፤ ድንግል ተወለደች፥ ማልዳ ምታስከፍት። ዳግማዊቷ ሔዋን፥ አምላኳን ወለደች፤ ዳግም ወደሲኦል፥ ልጆቿ እንዳይገቡ... በቀኙ ቆማለች፥ ማርልኝ እያለች። እንኳንም ተወለድሽ፥ ጠላት ደስ አይበለው፤ መርገም የተፋቀው፥ በደል የተሻረው፤ በድንግል ማርያም ልጅ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ነው።              ~~~ ብላቴናዋ እናት እግረ ተከል፥ ልጇን ክፋ እንዳይነካባት ወደግብፅ ወረደች፥ ገብርኤል እየመራት ። ስንጠይቅ ሰሎሜን፥ መልስ እንደሰጠችን፤ አረጋዊው ስሞን፥ ደግሞ እንደነገረን፤ የበረሀው ጉዞ፥ ከባድ ነበር አሉን።              ~~~ ስለአንድያ ልጇ፥ ብዙ ግፍን ያየች፤ ከ3 ዓመት በላይ፥ በረሃ ያደረች፤ ያች ብላቴና ድንግል፥ ማርያም ነች። ዳዊት በመዝሙሩ፥ እንደዘመረልሽ፤ ፅዮን እልሻለሁ፥ የንጉሱ እናት ነሽ። አንችን ለማወደስ..... ቃላት ባፈላልግ ፈፅሞ ባጣልሽ፤ ከመላእክት ቋንቋ፥ አንድ ተዋስኩልሽ፤ ደስ ይበልሽ አልኩሽ፥ እንኳንም ተወለድሽ።  (2)              ~~~ እኔ እምልሽ ድንግል፥ አንዴ ልጠይቅሽ፤ ያየሁት በመፅሐፍ፥ ዶኪማስ ቤት ሂደሽ፤ ወይኑ ሲያልቅባቸው፥ ከልጅሽ ጠይቀሽ፤ ጋኑን ወይን አስሞላሽ። በላየ ሰብእ እንኳን፥ ብዙ ነፍስን በልቶ፤ በአንቺ ስም ሲለምን.... ለአንዱ የእኔ ቢጤ፥ ጥርኝ ውሃ ሰጥቶ፤ ገነት እንደገባ፥ አንብበናል ጎልቶ።     እና አንዲህ ከሆነ.... ልጅሽን ስትጠይቂው፥ አለ አምቢ የሚልሽ? በበረሃው እንኳን፥ ኖሯል ሲታዘዝሽ፤ አንቺ የወለድሽው፥ ጌታሽ ካከበረሽ፤ ልደትሽን ልናከብር፥ መጥተናል ከደጅሽ፤ እስከ መጨረሻው፥ አማለጃችን ነሽ እኛ እኖድሻለን፥ እንኳንም ተወለድሽ። እንወድሻለን!!! እንኳን  አደረሰን አደረሳችሁ https://youtube.com/@awdemihretzetewahdo?si=ssYLKSzRnD3AOtzx https://youtube.com/@awdemihretzetewahdo?si=ssYLKSzRnD3AOtzx

እንኳን ደስታን ወደ ዓለም ይዞ ለመጣ ተናፋቂው ለድንግል ማርያም ልደት አደረሳችሁ!!! 👇👇👇👇👇👇 https://youtube.com/@awdemihretzetewahdo?si=ssYLKSzRnD3AOtzx

እንኳን አደረሳችሁ @Mgetem በሐኪ ማርያም ማርያም ዘገነት ኮል። ዕፀ ጳጦስ ዕፀ ጳጦስ መዝገቡ ለቃል። ድንግል ማርያም የሱፍ አበባ ትባላለች። የሱፍ ተክሉ እሾሃም ሲሆን አበባው እሾህ የለውም። ድንግል ማርያምም መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ከነበረባቸው የሰው ልጆች የተገኘች መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለባት ንጽሕት ናት። ድንግል ማርያም ሶምሶን ከሞተ አንበሳ ያገኛትን የማር ወለላ ትመስላለች። በመርገም ከነበሩ የተገኘች መርገም የሌለባት ንጽሕት ናትና። ድንግል ማርያም ሙሴ ባያት ዕፀ ጳጦስ ትመሰላለች። እሳተ መለኮትን በሥጋ ስትፀንስ እሳተ መለኮት አላቃጠላትም። ለጨለማው ዓለም የሚያበራ ብርሃንን የያዘችልን መቅረዝ ናት። ለተራበው ዓለም ዘለዓለማዊ ሕይወትን የሚሰጥ ምግብን ይዛልን የመጣች መሶበ ወርቅ ናት። የሕይወት ፍሬን የወለደችልን የሕይወት ዛፍ ናት። በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ። © በትረ ማርያም አበባው  🔤🔤🔤🔤🔤🔤🔤🔤🔤 👇👇👇👇👇👇 https://youtube.com/@awdemihretzetewahdo?si=ssYLKSzRnD3AOtzx

ልደታ ለማርያም 📎❤ @Mgetem በግንቦት አንድ ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች። እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኅነት የሆነባት ናት፡፡ ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ። በዚያ ወራት የመካኖች መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና፡፡ እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር፡፡ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ሐሳባቸውን ተመለከተ፡፡ ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው፡፡ በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ፤ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት። ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች። ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገነች። የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች፡፡ ከዚህም በኋላ ይህችን የከበረች ሕፃን ፀንሳ ወለደች። ስሟንም ‹ማርያም› ብላ ሰየመቻት። ትርጓሜውም ‹እመቤት› ነው። ‹ደግሞም ሀብታና ስጦታ› ማለት ነው፡፡ በእውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ሁላችን በእርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነትን ያገኘንባት ናትና። የሥጋና የነፍስ መድኃኒት የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ለዘለዓለሙ ይኑር፤ አሜን፡፡ ከመጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ግንቦት t.me/Mgetem t.me/Mgetem t.me/Mgetem

የቆሎ ተማሪ @Mgetem ........................ ግዕዙን ለማወቅ ቅኔ ማህሌቱን ታሪክ ወግ ባህሉን  ሊያስቀጥል ያባቱን ቁምጣውን አጥልቆ  ኩታውን ደርቦ ደግሞም ይለምናል እንዲሠጠው ዳቦ ስለ እመብርሃን ስለ አዛኝቷ ይኸው መጥቻለሁ አለሁ ከዛች ቦታ እማዬ  እናቴ  እንዳስለመድሽኝ ቁራሺቷን ዳቦ በጠላ ስጪኝ እያለ ቢለምን ከበራፍ ላይ ሁኖ አያፍርም ነበረ በእርሷ ተማፅኖ ጠላውን በጣሳ ቂጣውን በሰፌድ ተብሎ ይሠጣል ቢሆንህ ለመንገድ ሲሄድ ሲገሰግስ ሲሄድ በየዋርካው ደግሞም ይለምናል ቢሆን ለማደሪያው የቆሎ ተማሪው ተርቦ ቢጠይቅ የቆሎ ተማሪው ተጠምቶ ሲጠይቅ ተስፋው ቅኔ ሁኖ አያቅም ዘር ብሔር ይጣደፋል እንጂ ሠጪውን ለማክበር። http://t.me/Mgetem http://t.me/Mgetem ተጨማሪ ግጥም እንለቃለን 👇👇👇👇👇 https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE

ልደታ ለማርያም 📎❤ @Mgetem በግንቦት አንድ ቀን አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች። እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኅነት የሆነባት ናት፡፡ ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ፡፡ ሁለቱም ልጅ በማጣት ሲያዝኑ ኖሩ። በዚያ ወራት የመካኖች መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና፡፡ እነርሱም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልዱ ነበር፡፡ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ሐሳባቸውን ተመለከተ፡፡ ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኅነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው፡፡ በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ፤ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት። ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች። ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገነች። የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ለእግዚአብሔር ስለትን ተሳለች፡፡ ከዚህም በኋላ ይህችን የከበረች ሕፃን ፀንሳ ወለደች። ስሟንም ‹ማርያም› ብላ ሰየመቻት። ትርጓሜውም ‹እመቤት› ነው። ‹ደግሞም ሀብታና ስጦታ› ማለት ነው፡፡ በእውነት የዓለሙ ሁሉ እመቤት ሁላችን በእርሷ ሰማያዊ ሀብት ልጅነትን ያገኘንባት ናትና። የሥጋና የነፍስ መድኃኒት የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷም ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ለዘለዓለሙ ይኑር፤ አሜን፡፡ ከመጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ግንቦት t.me/Mgetem t.me/Mgetem t.me/Mgetem

እናቱ እናቴ - ልደትሽ ልደቴ ! (በመላኩ አላምረው) @Mgetem + + + ለእናትነት ክብር - እርሱ ከመረጠሽ በዮሐንስ በኩል - ለእኔ ከተሰጠሽ እኔም እርሱን ጌታ - ብዬ ከተቀበልሁ ማዳኑን አምኜ - በሕጉ ስር ከዋልሁ እናቱን እናቴ - ብየ ለመቀበል... ጥያቄ ልደርድር? ለምን? እንዴት? ልበል? + + + ልጅሽ በምድር ላይ - ሥጋሽን በመልበስ አዳምን ሊያድነው - ለእኛም ጽድቅን ሊያወርስ የረገጠው መሬት - የቆመበት ቦታ ከቤተልሄም ዋሻ - እስከ ጎለጎታ ቅዱስ ከተባለ - ውሎ ያደረበት ልዩ ክብር ካለው - የተሰቀለበት... አንችማ እናቱ - ማህፀን ዓለሙ የሰውነት ልኩ - ሥጋውና ደሙ እንዴት አትከብሪ!? እንዴት አትቀደሽ!? እንዴት አትወደጅ!? እንዴት አትወደሽ!? + + + እንኳንስ ለእኔና... ለእርሱም ለጌታችን - ፈጣሪ ለሆነ እናቱ መባልሽ - ይህ እውነት ከሆነ እናቴ መሆንሽ - እንዴት አልታመነ??? + + + በሥጋ ያይደለ - በረቀቀ መንፈስ እናቴ ሆነሽኝ - ያንችን ክብር ብወርስ ይሄንን መታደል - እንዴት እገፋለሁ? እናቱ እናቴ ነሽ! - ተቀብየሻለሁ!!! + + + ፈጣሪን ልትወልጅው - አምላክን ልታ’ዥው ሰማይና ምድር የማይወስኑትን - በእቅፍሽ ልትይዥው ከድንግልና ጡት - ወተት ልታጠቢው የዓለሙን መጋቢ... ከደኃ ማጀትሽ - ሲራብ ልትመግቢው እናት አባትሽን - ከእስር ልታስፈቺ የክፋትን አባት - በፍቅር ልትረቺ ከሀና ከኢያቄም - የተወለድሽ አንቺ እናትና ድንግል - ንግሥትና አገልጋይ ሰማየ ሰማያት - ጽርሐ አርያም ሆይ! የአንቺ ግሩም ልደት - ለእኔም ነው ልደቴ የጥምቀት መሥራቹ - ልጅሽ ነው አባቴ ዳግም የተወለድሁ - ከውኃና መንፈስ ባንቺ መወለድ ነው - የአዳም ተስፋው ሲደርስ ሕይወት የሆነልን - የልጅሽ ሥጋና ደም ከአንቺው ነው የነሳው - ከላይ አልወረደም ዝም ማለት ያልቻልኩት - ለዚህ ነው ድፍረቴ ልጅሽ ሕይወቴ ነው ! እናቱ እና ነሽ - ልደትሽ ልደቴ + + + + ቅድስተ ቅዱሳን - ንጽሒተ ንጹሐን ማሕጸኑ ለጽድቅ - እናቱ ለብርሃን ሰማየ ሰማያት - ታናሽ ብላቴና ከእያቄም ወሀና - ተወለደሻልና ዓለም ብርሃን አየ - ውስጥሽ ባለው ፀሐይ አዳም ቀና አለ - ተስፋ ብርሃኑን ሊያይ ፍጥረታት በሙሉ - ከሰማይ ከምድር በደስታ ተመሉ - ልደትሽ ሲነገር ተወለደሻልና - የፀሐይ እናቱ ጽርሃሐ-አርያም ሆንሽ - ብላቴናይቱ ! + + + + (፡›አበው ስለክብርሽ - ቃላት አጠራቸው ስለ ደም ግባትሽ - ምሳሌ ጠፋቸው እኔ ግን ደፋሩ - እዘባርቃለሁ ባልበሰለ ብዕር - ቃላት እመርጣለሁ በተንሸዋረረ ዓይን - ክብርሽን አያለሁ ምልጃሽን እያሰብሁ - በተስፋ እኖራለሁ‹፡) + + + የብርሃን እናቱ - የፀሐይ ምሥራቁ የአዳም ሙሉ ተስፋ - የሰይጣን መብረቁ ስለ አንቺ መወለድ - ዓለም ተፈጠረ ስለ አንቺ መወለድ - የሰው ልጅ ከበረ አዳምና ዘሩ - በኃጢአት ቢረክሱ በአንቺ መወለድ - ግን በክብር ነገሡ በአንቺ ልዩ ልደት - አዳም አምላክ ሆነ በአንቺ ልዩ ልደት - ክብራችን ገነነ በአንቺ ልዩ ልደት - ዲያብሎስ ታሰረ በአንቺ ልዩ ልደት - ባሪያ መሆን ቀረ እኔም ደፋር ሆንኩኝ - ፍርሃት ተሰወረ ባዶው አዕምሮዬ - ክብርሽን ነገረ፡፡ + + + ሰማይና ምድር - ልደትሽን ሲያከብሩ ሊቃውንት ሲቀኙ - መላእክት ሲዘምሩ ክብርሽን ተማምነው - በምልጃሽ ያደሩ በምህረት ቃል ኪዳን - ለክብር ሲጠሩ እንደልጅነቴ ለእኔም - እንዲደርሰኝ እንባሽን አስታውሶ - ልጅሽ እንዲምረኝ ዝም ማለት ያልቻልኩት - ለዚህ ነው ድፍረቴ የአንቺ መወለድ ነው - የጽድቅ መሠረቴ ልጅሽ ሕይወቴ ነው ! እናቱ እናቴ ነሽ - ልደትሽ ልደቴ፡፡ + + + http://t.me/Mgetem http://t.me/Mgetem ተጨማሪ ግጥም እንለቃለን 👇👇👇👇👇 https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE

የልደታን ግጥሞች በድምፅ/በቪዲዮ  እንለቃለን ❤️ ሰብስክራይብ እያደረጋችሁ ጠብቁን 🥰 👇👇👇👇👇👇👇 https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE

#የአምላክ_እንባ (በላይ በቀለ ወያ) @Mgetem . . ከላይ ከሰማያት... በሰው ተበድሎ ፤ ፈጣሪ ያለቅሳል ከታች ያለ ፍጥረት... "ዝናብ ጣለ" ብሎ ፤ ምድሪቱን ያርሳል። ወራትን ጠብቆ፤ ርሀቡን አስታግሶ የሀገሬ ገበሬ... በፈጣሪ እንባ ነው ፤ የሚበላው አርሶ። እንዲያው በተለምዶ፤ ዝናብ የምንለው ትእግስት አጠራቅሞት... ለወራት የቆየ ፤ የአምላክ እንባ ነው። ።።። ከማንባቱ በፊት... ማዘኑን ሊያረዳ፤ ሰማይ ጠቁሮ ሳለ፤ ፈጣሪ ሲቆጣ... ትውልድ ያማትባል፤ "መብረቅ" ነው እያለ። የሀገሬ ገበሬ..... ሰማዩን እያየ፤ ምድሪቱን ያርሳል የገበሬው በሬ... ሳር ሳሩን እያየ፤ ከገደል ይደርሳል በፈጣሪ እንባ በሰው ልጆች ደባ የታረሰ መሬት... ስንዴና እንክርዳዱን፤ባንድ ላይ ያበቅላል ከላይ ከሰማያት... ስንዴን ከእንክርዳዱ ፤ሊለይ ይታገላል ከታች ያለ ፍጥረት ርሀቡን ሊያስታግስ ስንዴና እንክርዳድን፤ ደባልቆ ይበላል። ።።። ለእንደገና ክረምት ለእንደገና በደል ፣ ለእንደገና ለቅሶ የሀገሬ ገበሬ…… ሰማይ ሰማይ ያያል፤ ደረቅ መሬት አርሶ። ።፣ ከላይ ከሰማያት. የፈጣሪ እናት ልጇን ለማባበል ፤ ፈገግ ትላለች ከታች ያለች እናት... "ፀሐይ ወጣ"ብላ ፤ ብቅል ታሰጣለች። እንዲያው በተለምዶ፤ ፀሀይ የምንላት ልጇን ለማባበል…. ብርሀን የሰጠች፤ የአምላክ እናት ናት። t.me/Mgetem t.me/Mgetem t.me/Mgetem

Powered by @Manybot

የልደታን ግጥሞች በድምፅ/በቪዲዮ እንለቃለን ❤️ ሰብስክራይብ እያደረጋችሁ ጠብቁን 🥰 🫴🫴🫴🫴🫴🫴🫴🫴 https://youtube.com/@awdemihretzetewahdo?si=ssYLKSzRnD3AOtzx

#አልችልም_አስችለኝ @Mgetem እየደነገጠ እየፈራ ልቤ አንድነት አቅቶት ቅጥልጥል ሃሳቤ ኮሽ ባለ ቁጥር እየፈራች ነፍሴ አስጨንቀዋለሁ ራሴን በራሴ አይኖቼ ተስፋዬን ማየት ተስኗቸው እግሮቼ ጉዞዬን መጓዝ አቅቷቸው ይቅበዘበዛሉ መሪ ጠፍቶባቸው ዝም ባለ ጎጆ ጭጭ ባለ ሌሊት ጩኸት ይሰማኛል ምንም በሌለበት የሚያሳርፍ ጌታ እንዳለኝ ይወቀው የሚያስጨንቀኝን አምላኬ አስጨንቀው አንተ ድረስና የጭንቄን ውል ፍታ አልችልም አስችለኝ እንዳልጠፋ ጌታ ! 👇👇👇 https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE

#አማኑኤል_አፈረሰበት_እቅዱን @Mgetem የሰው ዘር ቀዳሚ ጠላት ለዓለም የሐሰት አባት የአዳምን ኃጢአት መስራች በሰዎች ውድቀት ተደሳች የሐዘን ቤቶችን ለመስራት ተኝቶ አያውቅም በእውነት በደምና እንባ እያራሰ በሰው አጥንት እየማሰ የሞትን መሰረት በመጣል የኃጢአት ምሰሶ በመትከል እጅግ ብዙ ዘመናት ትግሏል የሞቱን መውጊያ ለመንቀል ምክንያተ ድኂን ናት ድንግል የአዳምን እዳ ለማስወገድ ሥጋን ለበሰ እግዚአብሔር ወልድ አማኑኤል ሰው በመሆን ክፉ ተግባሩን የሰይጣንን አፈረሰበት ዕቅዱን፡፡ ________ https://t.me/Mgetem https://t.me/Mgetem https://t.me/Mgetem https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE

ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ | ናና አማኑኤል 👇👇👇 https://youtu.be/W9Tl9i4vdgE