Daily Meditation
رفتن به کانال در Telegram
ሂድና በ "ሰሊሆም" መጠመቂያ ታጠብ አለው ትርጓሜውም "የተላከ"ማለት ነው። ስለዚ ሄዶ ታጠበ እያየም መጣ። ዬሀ 9:7 and said to him, "Go,wash in the pool of "SILOAM" (which means "sent"). so he went aweywashed and come back seeing. jon 9:7 ለማንኛዉምሀሳብአስታያየት @yenemrchaeysus 👆👆👆👆
نمایش بیشتر1 139
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-57 روز
-2030 روز
آرشیو پست ها
1 138
🩸ሴት ሆይ 🗣
👇👇
1⃣ ከአልማዝና እንቁ ሁሉ😲 ውድ አልፎም የበላይ ሆነሽ ስለምን ገንዘብና ወርቅ ያታላልሻል ስለምንስ ወርደሽ ትገኛለሽ⁉️
2⃣ በሴትነትሽ በክብርም በመፈጠርሽ ብቻ ልትኮሪና🙋 ዘና ብለሽ መኖር ሲገባሽ ስለምን👉 ራስሽን የበታች አድርጎ መቁጠር አስፈለገ 🤷♂❓
3⃣ አለባበስሽ ቅድስናሽ👍 መሆኑን ዘንግተሽ ይልቅስ ስለምንስ ሰውነትሽን/ ገላሽን አደባባይ ላይ መግለጥ ተገቢ ሆኖ ተገኘ⁉️🤔
4⃣ ብልህ፣ አዋቂ፣ ጭምት፣ ኩሩ ሴት ሆነሽ ሳለ የቀረበሽ ወንድ ሁሉ ለምን ያታልልሻል😡❓
5⃣ ከአመፃው አለም መለየትና በቅኑ መንገድም መጓዝ ሲገባሽ እንዴት🤷♂ አልባሌ ቦታ ተገኝተሽና ዋጋሽን ዝቅ ታደርጊያለሽ🤔⁉️
6⃣ ውበት እግዚአብሔርን መፍራት ሆኖ ሳለ ስለምን በመዋቢያ ምርቶች ላይ #እምነትሽን ትጥያለሽ⁉️
"ውድ ነሽና እንደ ውድ ሁኚ!!"
1 138
⚠️ አጭር ምክር!!👂
🔘 በፈገግታ ተቀበይ 🙋♀
👇👇
#ሰው በእርሷ ሕይወት ላይ #ዋጋ ብሎም #ስፍራ እንዳለው #የተረዳች ያቺ ሴት እንዴት ያለች እድለኛ ትሆን‼️ ከራሷ አልፋ ለሌላው በረከት ናትና ።
በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ ብታልፍ የሰው ጉዳይ #ግድ ስለሚላት🤔 ከራሷ ነገር ወጥታ #በፈገግታ ልብን #ትመልሳለችና። ያቺ ልባም ሴት በመከራ እየተጓዘች እንኳ ፊቷን ሰው ላይ አትጥልም በፈገግታ ተቀብላ በመፍትሄ ትሸኘዋች። 🙋♀
ልብ በይ 👉 ሰው ወደ አንቺ ሲወጣ አስቀድመሽ በደስታ ፈገግ ብለሽ ተቀበይው ፊት አትንሺው ለዛ ሰው #ያቺ ፈገግታ ሕይወቱ ላይ ምን ለውጥ እንደሚያመጣ አታውቂምና‼️
በአንድ ፈገግታ #ያዘነ ሊፅናና፣ #ሸክም ያለው ቀሎት የሚሰማውን ሊያወራ ይችላል🤷♀። ለሰው ጊዜና ቦታ ይኑርሽ ለአንዲት ነፍስ ግድ ካለለሽ የግል ሩጫሽ ነገ ይጥልሻል😳።ከራስ ጊዜ ቀንሶ ዋጋም ቢሆን ከፍሎ ለሰው ጊዜ መስጠት እንዴት መልካም ነው።
በምንም ሁኔታ ውስጥ ሁኚ ሰውን በፈገግታ ተቀበይ ፊትሽን አታጨማጂው። 👉 #የበደለሽ ሰው እንኳ ቢሆን ምከሪው #ጥፋቱን ንገሪው እንጂ በዝምታ ብቻ አትለፊው ትጎጃለሽና።
⚠️ ታዲያ አስተውይ #በፈገግታ ተቀበይ ማለት #ባህሪ አትለይ ወይም #አትመርምሪ ማለት አይደለም ለሕይወትሽ የማይበጀውን #ትቆርጫለሽ። ግን ፈገግ ብለሽ ሰው አስተናግጂ ተቀበይም ፊትን አትንሺ። 🙏
ሁሉም ለራሱ እየተሯሯጠ ባለበት በዚህ ዘመን ለሰው ፈገግ ማለት ሰውን መቀበል በረከት ነው። ፈገግ ማለት መገልፈጥ አልያም ማፌዝ አይደለም🤔 ሰውን #ለመስማት #ደስታን ለማካፈል #መልካሙን መንገድ ለመጠቆም ለማጽናናት #ዝግጁ መሆን ማለት ነው። 🙏
⚠️ ይበልጥ ደግሞ ፍሬ እንድታፈሪ በእግዚአብሔር ቃል እውቀት ራስሽን ሙይ🙏
1 138
🩸 ትዳር...🧖♂🧖♀..‼️
👇👇
🙋♂ ትዳር በስሜታዊነት ተገፋፍተሽ የምገቢበት አይደለም👉 የግል፣ የቤተሰተብ፣ የማህበረሰብ ጥያቄዎችን ለመመለስ ብለሽ ራስሽን እራስሽን እንዳታጪ ተጠንቀቂ‼️
🙋♂ ትዳር ፉክክር አይደለም። አስተዋይ ሴት ሁኚ ለጊዜያዊ ደስታ ብለሽ ነገሽን አታስጨንቂ ተረጋጊ ዙሪያሽን ተመልከቺ በፉክክር እረፍት የለም ‼️
🙋♂ ትዳር ሰርግ አይደለም ከአንድ ቀን ደስታ የዘለለ ሕይወት እንጂ። ንቁ ሴት ሁኚ ስለ ነገ የታባቱ ተብሎ የሚገባበት ሁሉ ነገር የሚፈስበት አይደለም ትዳር👉የሚጠይቅ የሚያገባው አቤት የሚል ነገ ከፊት አለና😳‼️
"አትቸኩይ ግን አትዘግይ፤ አትፍጠኚ ግን እንደ እግዚአብሔር ቃልና ድምፅ በፍጥነት ተራመጂ !!" 🐅
🙋♂ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደን አንቺም አክብሪ ደንታ ቢስ "ይሁና የታባቱ🤷♀⁉️" ከሚሉት ወገን አትሁኚ ትዳር ተቋም ነውና ራስሽ ላይ በደምብ ስሪ ሃላፊነት አለውና
🙋♂ መልካም በመሰለው ሳይን መልካም ብቻ በሆነው ነገር ሁሉ ራስሽን አብቂ #ቅድስና፣ #አለባበስ፣ ንግግር፣ ተግባቦት፣ ጥበብ ፣ #መንፈሳዊ ሕይወት ትጋት በእነዚህ ሁሉ ራስሽን አሰልጥኚ መልካሙንም አድርጊ🙏
1 138
⚠️የጥንቃቄ መልዕክት⚠️
የ ብዙ ሰዎች ቴሌግራም መጠለፉን ተመልክቻለው...ይህንንም የተረዳሁት ያለ ዕነርሱ ፍቃድ የሚላኩ ሊንኮች ሰሞኑን በርከት ብለው እኔ ዘንድ ስለደረሱ ነው።በዚህ አጋጣሚ "ፎቶአችሁን እዚህ website ላይ አይተን ነው ብለው የሚልኩላችሁን ማንኛውንም አይነት ሊንክ አትክፈቱ።እናንተም ተመሳሳይ የመጠለፍ እጣ ይደርሳችኋል...በዚህ ሳምንት ብቻ በርከት ያሉ የተጠለፉ ሰዎች ስላየሁኝ እንድትጠነቀቁ ነው።ማንም ቢልክ እዳትከፍቱ እነሱ ተጠልፈው ነው!
1 138
🔘 አይኖችሽ ወዳዩት ሁሉ ልብሽ ብሎም እግሮችሽ እንዳይሮጡ አጥብቆ የሚጠብቅሽ 👇
👉 34 እንዳስተውል አድርገኝ፥ ሕግህንም እፈልጋለሁ፤ በፍጹም ልቤም እጠብቀዋለሁ።
'መዝሙረ ዳዊት 119'
🔘 ከድካም ከውድቀት ማግስት ብርታትና መነሳት እንዳለ የሚጠቁምሽ 👇
👉14 እግዚአብሔር በቃሎቹ የታመነ ነው፥ በሥራውም ሁሉ ጻድቅ ነው፤ እግዚአብሔር የተፍገመገሙትን ሁሉ ይደግፋቸዋል፥ የወደቁትንም ያነሣቸዋል።
'መዝሙረ ዳዊት 145:'
🔘 እንዴት እንደ ልባም ሴት ሆነሽ መመላለስ እንዳለብሽ ሹክ የሚልሽ 👇
👉መፅሐፈ ምሳሌ ምዕ 31: 10-31
🔘 ምን ያክል ውድ እንደሆንሽ የሚነግርሽ 👇
👉10 ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል። 'መጽሐፈ ምሳሌ 31'
🔘 የቷ ሴት እንደምትመሰገን ምን ስራዏቿም መልካምን እንደሚከፍላት አልፎም ውበት ማለት ምን ማለት እንደሆነ የሚያሳስብሽ 👇
👉30 ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች። 'መጽሐፈ ምሳሌ 31'
🔘 በምን መንገድ አንደበትሽን መክፈት እንዳለብሽ የሚጠቁምሽ 👇
👉13 አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ።
'መዝሙረ ዳዊት 34:'
🔘 ራስን መግዛት ሰውነትሽም የራስሽ እንዳልሆነ በስጋሽም የፈጠረሽን ጌታ ልታከብሪ እንደሚገባ የሚያስተምርሽ 👇
👉19-20 ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
'1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:19-20'
🔘 አለባበስሽ ቅድስና እንደሆነ የሚያስገነዝብሽ 👇
👉ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ።
'1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:4'
🔘 ሰነፍ ሴት እንዳትሆኚ የሚመክርሽ 👇
👉1 ብልሃተኛ ሴት ቤትዋን ትሠራለች፤ ሰነፍ ሴት ግን በእጅዋ ታፈርሰዋለች። 'መጽሐፈ ምሳሌ 14:'
🔘 ባልሽ የቤቱ ራስ እንደሆነ ልታከብሪው ልትታዘዢው እንደሚጠባ በረከትም ፍሬም በዚያ መንገድ እንደሆነ ይሀው የሚልሽ 👇
👉እንዲሁም፥ እናንተ ሚስቶች ሆይ፥ ከባሎቻችሁ አንዳንዱ ለትምህርት የማይታዘዙ ቢኖሩ፥ በፍርሃት ያለውን ንጹሑን ኑሮአችሁን እየተመለከቱ ያለ ትምህርት በሚስቶቻቸው ኑሮ እንዲገኙ ተገዙላቸው።
'1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:1-2'
⚠️ ትህትና በክብር ዝቅ ባለበት በዚህ ዘመን እግዚአብሔር የሚፈልጋት አይነት ያቺን ትሁት ልባም ሴት እንድትሆኚ የሚመክርሽ 👇
🔘ህያው የእግዚአብሔር ቅዱሱ ቃል ነውና አንቺ ሴት 👇
🔘 ራስሽን በእግዚአብሔር ቃል እውቀት ሙይ አእምሮሽና ልብሽ👉 #እረፍት #ደስታ #ቀናውንም መንገድ ይከተላሉና
በዘመናዊነት በስልጣኔ #ዋጋዋን የረሳች ያቺን ወደ ሞት የምትመራ አይነት #ሰነፍ ሴት ከመሆን እግዚአብሔር ይጠብቃችሁ ዘንድ ይህ ለእናንተ መልካም ምኞቴ ነው🙏
⚠️ #እንደጊዜው #እንደፋሽኑ #እንደሁኔታው ሳይሆን መኖርስ እንደ #እግዚአብሔር ቃል 🙏
1 138
♦️ ሴቶችም… 👇
👇👇
1⃣ የተከበሩ 🙏
🔺 አንቺ👉 ክብር ያለሽ ሴት ነሽ👍 ማለትም ተራ አይደለሽም❌ ነገር ግን ሰውም እግዚያብሄርም የሚያከብርሽ በሰራሽው ስራ ነው🤷♂ ስለዚህ ክብር እንዳለሽ አውቀሽ መኖር ያንቺ ድርሻ ነው በተራ😳 ነገር ውስጥ የምታልፊና ቀለሽም የምትገኚ ከሆነ ችግሩ ከአንቺ😔 ነው "ክብር ያለሽ ሴት ነሽ አትቅለይ"💪
2⃣ ሐሜተኞች ያልሆኑ ❌
ከንፈርሽ የተፈጠረው👉" መልካምን ወሬ ለማውራትና ለመናገር ነው እንጂ🤔 በሐሜት ክፋ ሃሳብን ሰው ላይ ለመዝራት አይደለም🙅♂" ጓደኛሽን በጀርባ የምታሚ አትሁኚ ይሄ ያንቺ ባህሪ አይደለም😔 ይልቁኑ የጠሉሽን የሰደቡሽን ክፋትንም ያደረጉብሽን😡 በከንፈርሽ ብቻ ሳይሆን ከልብሽ መርቂ እግዚያብሄር በዚህ ደስ ይሰኛልና🙏
3⃣ ልከኞች 💁
በልክና በመጠኑ የምትኖሪ ሁኚ🙏 ብዙም ከፍ አትበይ ደግሞም አትውረጂ የምታደርጊውን ሁኑ ማስተዋልን እየተመረኮዥሽ ከውኚ😲 በጣም ከፍ ካልሽ ጌታን ልትፈታተኚ ዝቅም ካልሽ ልታጉረመርሚ😡 ስለምትችይ "በመጠኑ ኑሪ"🙏
" እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤"
1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 5:8
4⃣ በነገር ሁሉ የታመኑ🙋
ተስፋ እንድትቆርጪ አልተፈቀደልሽም❌ ይልቁኑ በእምነት እንድትበረቺ ግን ስልጣን ተሰጥቶሻል😍 ስለዚህ በምንም ሁኔታ ውስጥ ብታልፊ እምነትሽን አትጪ "እምነተሽ የነገሽ መሰረት ነውና"🙏
ከላይ👆 ያሉትን አራቱን መስፈርቶች እንደ ልባም ሴት ልታሟዪ🤷♂ የግድ ነው በረከትሽ ያለው በእነዚህ ውስጥ ነውና🙏
1 138
👋 እንዴት አደራችሁ ልባሞች👋
ሁሌም በውሎሽ መልካም ነገርን ለማድረግ በመልካም መንገድም ለመሄድ አስበሽ ተነሺ🙋♀ ቅንነት፣ ዝቅ ባይነት፣ ልጋስነት፣ ታዛዥነት ፍቅርም በተሞላ መንፈስ ከቤት ውጪ🚶♀ ትላንት ያስቀየሙኝ ሰዎች አሉ ብለሽ ዛሬም በጥላቻና በድብርት ስሜት አትውጪ❌ ም/ቱም ዛሬ ሌላ ቀን ነዋ ጌታ በጨመረልሽ ሌላ ቀን ላይ ያንን እርግፍ አድርገሽ ጥለሽ የዛሬ ውሎሽን በደስታ ጀምሪ ለነዛም ሰዎች ዛሬም ቅንነትሽን ፍቅርሽን አሳዪ 👍
የአንድ ቀን በህይወትሽ ላይ መጨመር የዋዛ አይደለም❌ ብዙዎች ይህችን ቀን ናፍቀዋት ላያዯት ተሰናብተዋል😔 ብዙዎች በህይወታቸው የአንድ ቀን ጭማሪ ጉዳይ ሳይገባቸው በማይገባቸው ስፍራ ውሎው ባክነዋል🤦♀ ስለዚህ ይህ የአንድ ቀን ጭማሪ ጉዳይ ይግባሽና እያንዳንዱን ሰዓት እያንዳንዱንም ደቂቃ እግዚያብሄርን በመፍራት በቅድስና ዝቅ በማለት አሳልፊው🙏 የዛሬው ቀን እንዱሁ በነፃ የተሰጠው ሰው በተመረቀለት ቀን ላይ ቆሞ ጨማሪውን ያመሰግናል🛐
እግዚያብሄርን በመፍራት በቅድስና🙏፣ በትህትና፣ በልጋስነትም ደግሞም ፍቅር በተሞላው መታዘዝ👍 አልፎም እግዚያብሄርን ስለ ሀሉ እያመሰገናችሁ የዛሬውን ቀን ታሳልፉ ዘንድ ይህ ምክሬ ነው መልካም ውሎ🙏
1 138
🩸አዎን እስካልሞታችሁ ድረስ የመኖር የመነሳት የመመለስ ተስፋ አላችሁ 🙋♂
🩸አዎን በምሕረት ከተፍገመገሙበት መቆም ከወደቁበት መበርታት አለ 🙋♂
🩸አዎን ከትላንት የተሻለ ነገ አለ አስቀያሚውን ትላንት የምትበቀሉበት 🙋♂
🩸አዎን በለቅሶ ብቻ የማያበቃ በብዙ ሳቅ የተሞላ ነገ አለ 🙋♂
👉 #ድቅቅ ብላችኃል አዎን #መጠንከር ትችላላችሁ በራሳችሁ ላይ ተስፋ #ቆርጣችኃል አዎን ተስፋ ማድረግ ትችላላችሁ #በሕይወት አይደላችሁ🤷♂!? ታዲያ ተስፋችሁን ማን #ነጠቀ⁉️
👉 " አይዞአችሁ በምህረት የሚቀጠል ሕይወት አለ ያልተበላሸ ነገ ተስፋ ያለው
1 138
10 ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል።
'መጽሐፈ ምሳሌ 31:10'
🔹አንቺ ብቻ በእግዚአብሔር መንገድ ሂጂ እንጂ 👉 በረከት ነሽ ደግሞም ምንጭ ግራ ለተጋቡ ለብዞዎች ደራሽ ፣ ለባልሽ ኩራት፣ ፍሬያማ ትውልድን የምታፈሪ፣ በሰማዩም በምድሩም የምትባረኪ ሴት ላትሆኚ የሚከለክልሽ ፈፅሞ የለም🤷♂ ብቻ አንቺ በእግዜሩ መንገድ በቅድስና ሂጂ ወደ ጌታም ተመለሺ። " ሴት ሁኚ!! "
1 138
# ክፍል ሁለት 2⃣
🩸Cohabitation/ በመፅሐፍ ቅዱስ ቅኝት!!
ቅዱሱ መፅሐፍ ሳይጋቡ cohabit/ አብሮ ስለመኖር የማይደግፍ ብዙ ሃሳቦችን ያነሳል፤ አንድ መሆን ያለው በጋብቻ ውስጥ ብቻ መሆኑን ያስረግጣል አስቀድሞውኑ የእግዚአብሔር ፈቃድ ያም ስለሆነ 👇
"ስለዚህ ሰው ከአባቱና ከእናቱ ተለይቶ ከሚስቱ ጋር ይጣመራል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ" ዘፍ 2 ፥ 24
አንድነት አብሮ መኖር ያለው እግዚአብሔር በፈቀደው ህጋዊ ጋብቻ ውስጥ ብቻ ነው። #cohabitation ያልተቀደሰ ሃሳብ ነው እንኳን አንድ ወንድና አንዲት ሴት ሳይጋቡ አንድ ላይ መኖር ቀርቶ የተለያየ ቤት እንኳ ሆነው ቢጠራሩ ለብቻቸው ምን ያክል ለሥጋ ፈቃድ ለመገዛት ቅርብ እንደሆኑ መገመት አያዳግትም ሰው ብረት ለበስ አይደለምና። ራሴን ጠብቄ ኖራለሁ አይታሰብም👉 "ካልተቀደሰ ሕይወት የተቀደሰ ፍሬ ማግኘት አይቻልምና‼️" 👇
" መጋባት በሁሉ ዘንድ ክቡር መኝታውም ንፁሕ ይሁን ፤ ሴሰኞችና አመንዝራዎች ግን እግዚአብሔር ይፈርድባቸኋል " ወደ ዕብ 13 ፥ 4
" ከዝሙት ሽሹ። ሰው የማሰራው ሁሉ ከአካሉ ውጪ ነው፤ ዝሙትን የሚፈፅም ግን በገዛ አካሉ ላይ ኃጥአት ይሰራል " 1ቆሮ 6 ፥ 18
ከብዙ በጥቂቱ ቅዱሱ ቃል ይህን ይላል ሳይጋቡ አብሮ መኖር ለምን ኃጥአት እንደሚያጋልጥ። 👇
" ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኵሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ፤ "
' ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5 ፥ 3'
⚠️ አጭር ማጠቃለያ ምክር👇
🔘 ሳይጋቡ አብሮ መኖር የጌታ ፈቃድ ካልሆነ የትኛውም #ምክንያት መስሎ የሚቀመጥ አብሮ ለመኖር ሳይጋቡ ያ ክፉ ሃሳብ ፅንስ ነው ኃጥአትን የሚወልድ።ባለማወቅ የጀመራት ተመለሱ ሌሎቻችሁ ንቁ!! እስከጋብቻ ቀን ድረስ ተቆጠቡ አብሮ መኖር ቀርቶ ጭር ያለ ቦታ አልያም ቤት ውስጥ አትጠራጠሩ❌ ። ሳይጋቡ ከጋ መጋባትን እንደ ምርጫ አትቁጠሩ #normal አይደለምና 🙏
🔘 አንዳንዴ በነፃነት የሚደረግ ያ መልሶ ባሪያ ስለሚያደርግ የሚጠቅመውንና የሚጎዳውን ለዩ እንደ ጌታ ቃል ነሩ
🔘 በይበልጥ በዚህ ሴቶች የሕይወት #ጥያቄዎቻቸውን ለመመለስ ብሎም ሌሎች #ለትዳር አንድ እርምጃ መስሏቸው ያገቡበታል። አንቺ ግን ንቂ #normal ነው እየተባለ ብዙ ኃጥአት የሚሰራበት ዘመን ነውና 👉 " ለመወሰን ሁለቴ አስተውይ ማስተዋል የጌታ ቃል ምን ይላል ብሎ መየትም ነውና፣ ማስተዋል የራስ አንዳልሆኑ ማወቅ ነው፣ ማስተዋል ነገን ማየት ነውና፤ ዘመኑን መርምሪ "
⚠ ክፉውን ተቃወሚ ከመልካም ነገር ጋር ተባበሪ 👉 " ከማናቸውም ዐይነት ክፉ ነገር ራቁ። " 1ተሰ 5 ፥ 22
" በቀን እንደምንመላለስ በአግባቡ እንመላለስ። " ሮሜ 13 ፥ 13
1 138
አንድ ወንድና አንዲት ሴት ሳይጋቡ አብረው መኖር ይችላሉ ወይ?
💁♀አዎ መኖር ይችላሉ! ግን ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት በፍፁም ተቀባይነት የሌለው እንዲሁም በኛም ስርአት ነውር የሆነ ተግባር ነው።
በእርግጥ ዘመን አመጣሽ ስልጣኔ መስሎ የመጣብን ትውልድን ወደ ማይሆን እሳቤ ይዞ እየሔደ ያለ ነገር ነው። ይህ ግን ሁለቱን ሰዎች ወዳልሆነ ነገር የመምራት እድሉ ብዙ ነው፤ like ባልተጋቡ ሰዎች መሐል ግንኙነት እንዲፈጠር በር ከፋች መሆኑ ዋናው ነው, also ያ ኑሮ ከልተመቻቸው ትተው መሔድ እንደሚችሉ እንዲያስቡ ይሆናል so የትዳር ዋናው አላማ ደግሞ እስከ ፍፃሜ አብሮ በችግርም በደስታም መኖር እና እንደ ሀሳቡ መመላለስ ነው።
ሳይጋቡና ቃልኪዳን ሳይኖር የገቡበት ነገር ደግሞ በምን አገባኝነት እንዲሁም በችላባይነት ውሳኔዎችን ለመስጠት ያቻኩላል። ልባም ሴት በክብር ተሸልማ፣ እስከመጨረሻ የሚወዳትን ሰው በቃልኪዳን ሀላፊነት ወስዳ ጌታዋንም ራስዋንና ቤተሰቧንም ምታከብርና ምታስከብር ናት!
"የጌታን ሀሳብ ጥያቄ ውስጥ ሚከት ትዳር ትርፉ ዘመንን ማስበላት ነው!" ትዳሩ ቀርቶ ጌታ ቢከብር እና በኛ ደስ ቢለው ትርፋችን የዘላለም ህይወት ነው።
ከትዳር በፊት አብሮ መኖርን የሚሰብክ ክፉ ሀሰተኛ ዘመን አመጣሽ የተባረከ ትዳርን ጠል የሆነ ውሸት ነው። አንስማው። በጥቂት፣ ሞኝነት በሚመስል የታመንለት አባት በከበረ ነገር ሊሾመን እንጂ እንዋረድ ዘንድ አይደለም።
ከ ተሊሌ
1 138
ሰላም እንዴት ናችሁ ልባሞች🖐
የመጀመሪያው ጥያቄ ሳይጋቡ አብሮ መኖር ምን ችግር አለው የሚል ነው ?
መጋባት ወይም ደግሞ ትዳር መመስረት ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን መመለስ ይኖርብናል ምክንያቱም የትዳርን አላማ እና ግብ ካላወቅን ብዙ ስለምንስት ማለት ነው።
ትዳር የቤተ ክርስቲያን እና የክርስቶስ ምሳሌ ነው። እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የሰጠው የበረከት ቦታ ነው ። እግዚአብሔር የባረከው ደግሞ የተቀደሰ ቦታ ነው ። ትዳርን እንዲሁ እኛ ስለፈቀድን ወይም ደግሞ ስለተዋደድን ብቻ የምንጀምር ከሆነ
1 : እግዘብሔርን እናሳዝናለን
2 : እሱ የቀደሰውንና የባረከውን ነገር እናረክሰዋለን
3 : ሰላማችንን እናጣለን በጊዜው ግን ደስተኛ የሆንን ይመስለናል
ትዳር አግብቶ ከመውለድ ወይም ደግሞ ንብረት ከማፍራት ያለፈ የእግዚአብሔር ደስታና ሀሳብ የሚፈፀምበት ቦታ ነው ። ትዳርን አክብረን ከያዝነው በቅድስና ደግሞ እግዚአብሔርን በመፍራት ኖረን ከጠበቅንና በእርሱ ጊዜ ወደ ትዳር ከገባን እግዚአብሔር ያከብረናል !!!! ነገር ግን ቃሉን ትተን ቸልም ብለን የራሳችንን ሀሳብ አስቀድመን በሄድንበት መንገድ ሁሉ ብዙ ዋጋ እንከፍላለን ።
ስለዚህ እህቶቼ እግዚአብሔር ይረዳናል እኛም በተቻለ መጠን እራሳችንን እየገዛን በቅድስና መኖር ይሁንልን ደግሞ እኛ ክርስቲያኖች ነን ስንሞሸር የሚያምርብን በአባታችን ቤት ነው
ከእህታቹ ከኤደን
1 138
Photo እና video ዝም ብለሽ አትፓስቺ 😳🙄
"ለክርስቲያን" ሴቶች በየ social media በየ Instagram በየ Facebook የምትለቂው photo እና video አላማው ምንድነው..? እይታ እና አድናቂ አገኘው ብለሽ የምትፓስቺው ነገር በኅላ የማትወጪው ነገር ውስጥ ሊያስገባሽ ይችላል.😳🥺
ስለዚህ ምን አይነት መልህክት እያስተላለፍኩ ነው..?
አለባበሴ፣እንቅስቃሴዬ እግዚአብሔርን ያከብራል ወይ..? የሚለው ሀሳብ ላይ ትኩረት ይኑርሽ..
የምታደርጊውን ሁሉ በማስተዋል አድርጊ.
ከዛ እመኚኝ እህቴ ብዙ ታተርፊያለሽ 🙌
ውድ እህቴ🥰
ለሰዎች የመሰናከያ ምክንያት ሳይሆን የመታነጻቸው ምክንያት ለመሆን እራስሽ ላይ ስሪ🙌🥰
ከ ረድኤት
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
