fa
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

رفتن به کانال در Telegram

ዝም ብለህ ተቀላቀል!

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام የጥበብ ማዕድ

کانال የጥበብ ማዕድ (@yetbebmead_ab) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 932 مشترک است و جایگاه 5 411 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 116 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 932 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 25 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 604 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -23 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 2.64% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 2.10% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 419 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 334 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ዝም ብለህ ተቀላቀል!

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 26 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 932
مشترکین
-2324 ساعت
+1447 روز
+60430 روز
آرشیو پست ها
የትንሳኤ በዓል እንዴት አለፈ ቤተሰቦች?!

"እኔን ግን ያደክመኛል!!" ስትለኝ እያፅናናዋት መስሎኝ ለካ ሁሌ ለመስማት ብቻ አየሞከርኩ ነበር፤ በድካም ውስጥ ሁናችሁ፣ ፈተና ውስጥ ወድቃችሁ ሌላ ሰው ልክ እንደ እኛ መታመሙ ያቀለው ይመስል "አ
"እኔን ግን ያደክመኛል!!" ስትለኝ እያፅናናዋት መስሎኝ ለካ ሁሌ ለመስማት ብቻ አየሞከርኩ ነበር፤ በድካም ውስጥ ሁናችሁ፣ ፈተና ውስጥ ወድቃችሁ ሌላ ሰው ልክ እንደ እኛ መታመሙ ያቀለው ይመስል "አንቺ ብቻ አይደለሽም፣ሁሉም ሰው የሚኖረው ስቃይ አለው" መባል ማበርታት ሚመስለን ብዙዎቻችን ነን፤ አንዳንዱን ግን ያደክመዋል፣ ሁሉም ሚኖረው ህመም አለው፣ ችግር ውስጥ የገባ ሰው መጀመሪያ ሚፈልገው ከልብ መረዳትን ነው፣ ቀድሞ ፈራጅ አለመሆንን ነው።🍂 @NEKU_TEWLD10 @NEKU_TEWLD10

ብዙ የሚያወራ ሰው ተገማች ይሆናል። ተገማች ሰው ደግሞ በቀላሉ ይናቃል በጥቂቱ ስትናገር ግን ሰዎች ስለ አንተ ለማወቅ ይጓጓሉ ክብርህም ይጨምራል ራስህን ለማስረዳት በሞከርክ ቁጥር ጥፋተኛ ወይም ደካማ ትመስላለህ። ብቁ ሰው ራሱን አያብራራም ስራው እንዲናገርለት ያደርጋል። 📕ርዕስ:-48ቱ የስልጣን ህጎች

ፈሪ ብትሆን እራሱ የአንዳንድ ሙዚቃዎች ሐይል ልክ እንደ ህንድ ፊልም ነው! በጥይት ማንጠባጠብ እንድትችል ራሱ ያደርግሃል።

እንስሳቱማ የስጋቸውን አይቶ የማናየው ክንፍ ተሰጣቸው መሰል በየጣሪያው ሆኗል ጋጣቸው! አልወርድም ማለቷ ፖለቲካ እንዳይሆንባት ብቻ እንጂ…

"ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ? ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም::"(ሉቃ 24፥5) እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱሰ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በስላም አደረሳችሁ የጥበብ ማዕድ ቤተሰቦች::

፡ ውድ የዚህ ቻናል ቤተሰቦች ዛሬ ለየት ባለ መልኩ የግጥም ውድድር ልናካሂድ ከተፍ ብለናል፡፡ በመሆኑም ሁላችሁም መወዳደር ትችላላችሁ፡፡ 👉መወዳደር የምትፈልጉ ግጥማችሁን ከእሁድ ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ እስከ ማክሰኞ ከምሽቱ 3:00 ድረስ መላክ ትችላላችሁ፡፡👇              ••••••••••••••••••••••••••                     @abu1219                        @amen1995                  •••••••••••••••••••••••••• 👉በተመቻችሁ ሀሳብ መፃፍ ትችላላችሁ፡፡ 👉 100% Vote     🎁1ኛ ለወጣ የ150 ብር ካርድ     🎁2ኛ ለወጣ የ100 ብር ካርድ     🎁3ኛ ለወጣ የ50 ብር ካርድ 👉ግጥሙ የራሳችሁ መሆን እንዳለበት እያሳሰብን ውድድሩ ረቡዕ ከምሽቱ 2:00 ተጀምሮ እሁድ ማለትም በዳግማ ትንሳኤ ከምሽቱ 3:00 ይጠናቀቃል፡፡ 👉ውድድሩ የሚካሄድበት ቻናል ሊንክ        https://t.me/Yetbebmead_ab                    መልካም እድል🙏          

#ትንሣኤ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ ! " በዚህ የለም ፤ እርሱ እንደተናገረው ተነሥቷል "   በማቴዎስ ወንጌል ፥ " እነሆ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ ወርዶአልና ፤ ቀርቦም በመቃብሩ አፍ ላይ ድንጋይዋን አንከባሎ በላይዋ ተቀመጠ፡፡ መልኩም እንደ መብረቅ ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበር፡፡ እርሱንም ከመፍራት የተነሣ መቃብሩን የሚጠብቁ ታወኩ ፤ እንደ በድንም ሆኑ፡፡ መልአኩ መልሶ ሴቶቹን እንዲህ አላቸው፥ ' እናንተስ አትፍሩ ፤ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንደምትሹ አውቃለሁና፡፡ በዚህ የለም ፤ እርሱ እንደ ተናገረው ተነሥቶአል ' " ተብሎ እንደተጻፈው መድኃኒዓለም ብርሃንን ተጎናጽፎ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን በክብር ተነሥቶአል፡፡ መልካም የትንሣኤ በዓል ! በዓሉ የሰላምና የፍቅር ይሆን ዘንድ እንመኛለን !

ያቀባብራል ወይ በናፍቆት ወዳጅን ቢሰጡት ፈተና 🥺🎧
ያቀባብራል ወይ በናፍቆት ወዳጅን ቢሰጡት ፈተና 🥺🎧

የ #ኢትዮጵያ ብር እና የ #ደቡብ_ሱዳን ፓውንድ በዓለም ላይ ደካማ አፈጻጸም ካሳዩ የመገበያያ ገንዘቦች ተርታ ተመደቡ‼️ ድከሙ ሲለን እንጂ ለኛ በአሞሌ ጨው መገበያየት ነበር የሚሻለን!
የ #ኢትዮጵያ ብር እና የ #ደቡብ_ሱዳን ፓውንድ በዓለም ላይ ደካማ አፈጻጸም ካሳዩ የመገበያያ ገንዘቦች ተርታ ተመደቡ‼️ ድከሙ ሲለን እንጂ ለኛ በአሞሌ ጨው መገበያየት ነበር የሚሻለን!

ኣንዳንድ ቀን ኣለ ኣይመሽ ወይ ኣይነጋ ወቅቱን ያልጠበቀ ሚደምን በበጋ ኣይበርድ ኣይሞቅ ነገር ስሜት ያናጥባል በምኞት ኣሳስሮ በሃሳብ ያሰጥማል ከኣንዱ ሲመለጥ ካንዱ ያላትማል ቀን  በሰው ሲሳለቅ እንዲው ያለምንም.. ያደክማል ጫጫታ ያደክማል ግርግር እራስን ሲያገኙ ካልጠበቁት መንደር ያደክማን ሃሳቡ ውል ኣልባ ጭንቀቱ ኣልፎ ለሚረሳ ግዜ መሰዋቱ ይቅር ብቻ... ይቅር ይለፍ ኣናወራም ሰሚ ወዳጅ ከራስ በላይ ኣናገኝም እንዲህ ሆነን በቀን ስላቅ እድሜያችንን እንዳማጥነው ወይ ኣያልፈን ወይ ኣናልፈው.. meron.

እኔን ሶስት ሰዎች ይገርሙኛል ። ሁለቶቹ የሰሩት ስህተት ተመሳሳይ ሁኖ አንደኛው በፀፀት ራሱን ያጠፋበትና ሁለተኛው ደግሞ ተፀፅቶ በንስሃ የተመለሰበት ነው ። ከነዚህ ሶስት ሰዎች አንዱ አስቆሮቱ ይሁዳ ነው :-  ይሁዳ እየሱስን በ 30 ዲናር ሸጠ ከዚያ በኋላ የእየሱስን መገረፍና ስቃይ አይቶ ተፀፀተ ። ህሊናው ወቀሰው ,,, የህሊናን ክስ የምናሸንፈው ለሰራነው / ላደረግነው ስህተት ይቅርታ በመጠየቅና በመናዘዝ ነው  ። እዚህ ጋር የፊዮዶር ዲዮቶቪዮስኪን ንግግር ላስገባ "  ክፉ ነገር ብትሰራ ልብህ ይቀጣሃል እውነተኛ ሰላም ከንስሃ ይመጣል "  ይላል ። ይሁዳ እውነተኛ ሰላሙን ባለማግኘቱ ራሱን አጥፍቷል ። ሁለተኛው ጴጥሮስ ነው :- ጴጥሮስም መምህሩን እየሱስን ክዶታል ያውም ሶስት ግዜ ። ግን የጴጥሮስ ስህተት ክህደት ቢሆንም እሱ ግን ከስህተቱ የተመለሰው ከ እየሱስ ጋር አይን ለ አይን በተያዩ ግዜ እየሱስ " ትክደኛለህ " ያለው ቃል #ትዝ ብሎት ነው ። ከስህተቱም የተመለሰው አልቅሶ ኃጢአቱን በመናዘዙ ነው ። አዚህ ጋር አንድ ነገር ያዙልኝ 👌 የህሊና ክስ የሚቀደደው ይቅርታን በመጠየቅና በመናዘዝ ነው ። ሶስተኛው ቶማስ ነው :-ቶማስ  ስህተት ሰርቷል ልላቹ አይደለም የሱን ጭንቅላት ላደንቅ እንጂ ።  ከደቀ መዝሙሮቹ  ሁሉ የሚገርመኝ በምን መሰላቹ :- አንድ ቀን ሰብኮም ሆነ በሽተኞችን ፈውሶ አለማወቁ ነው ። ጠያቂና ጠርጣራ ነው ። እየሱስ ከሞት ተነስቶ በመካከላቸው ቁሞ " ሰላም ለእናንተ ይሁን "ሲል  እየሱስ መሆኑን ጠርጥሮ የተወጋሀውን ቦታ ካላየሁ እና ካልዳሰስኩ  አላምንም ሲል እየሱስ ዳስሶ እንዲያየው ፈቀደና " ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለ "  ( ዮሐ 20: 29 ) የቶማስ ሁኔታው ጠርጣራነቱ የሚገርም ነው ።        ✍ Henok

The Passion Of The Christ በአማርኛ.avi1048.83 MB

አምላካችሁን ዘመናዊነታችሁ ውስጥ ለምን ትፈልጉታላቹ? ጥንታዊነት ውስጥስ መፈለጉ ለምን ኋላቀርነት ይመስላችኋል??!      በመዘመናቹ ውስጥ ስለምን እንደ ኑሮዓቹ የፈጠራቹ አብሯቹ እንደሚዘምን ይሰማችኋል?        የጊዜ ጌታ!

📌#ታላቅ_ፍቅር_ተገለጠ። ❤️ ————————————————- በሰው ልጆች ታሪክ ያልተመዘገበና ከሰውኛ ፍቅር የጠለቀ ታላቅ ፍቅር የዛሬ 2000 አመት በቀራኒዮ ተራራ መስቀል ላይ ተገለጠ።  ኃጢአተኞች ፣በደለኞችና ጠላቶች በነበርንበት ጊዜ በፍፁም ፍቅሩ የወደደንና ሕይቱንም አሳልፎ የሰጠን አንድ ንጹህ ተገኝ። በኃጢአታችን መገረፍ፣መሰቃየትና መሞት የሚገባን እኛ ሆነን ሳለ የማይገባው ኢየሱስ የእኛን ሞት ሞተ እኛን ለማዳን በእኛ ፈንታ ምራቅ  ተተፋበት፣ተገረፈ፣ተሰቃየ፣በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞተ፤ኃጢአታችንን፣ እርግማናችንን፣ነውራችንን ሁሉ አስወገደልን። ኢየሱስ ክርስቶስ ንጽህ ደሙን አፍስሶ፣ቅዱስ ሥጋውን ቆርሶ ውድ ሕይወቱን ስለእኛ ፍቅር አሳልፎ በመስጠት መውደዱን፣ፍቅሩን በቀራኒዮ አደባባይ ላይ ሲገልጥልን ጭራሽ በእግዚአብሔር እንደተቀሰፈ፣እንደተቸገር ፣እንደተመታ ተቆጠረ። እርሱ አብዝቶ ቀረበን ፤ምንም የሚወደድ ነገር ሳይኖረን እርሱ ግን ወደደን።በሰማይ ያለውን የክብሩን ዙፋን ትቶ ስለእኛ ፍቅር ሲል እንደ ኃጢአተኛ፣እንደ ወንበዴ፣እንደ ምናምንቴ ተቆጠረ።በእውነት ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ የገለጠው ፍቅር ከአዕምሮ ያልፋል። 👉 ነብዩ ኢሳይያስ በትንቢት ስለመሲሁ ፍቅር ሲናገር፦ ኢሳይያስ 53 ፣6፤ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ። 7፤ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም:: እንኳን ለጌታችን ለመድሀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ።

ፀሎተ ሐሙስ፤ ሕፅበተ እግር❤️‍🩹

አውቶብሱ (በእውቀቱ ስዩም) ይሄ የሀያላን አገር ጦርነት፥ ከራይድ ተጠቃሚነት ወደ ህዝብ ትራንስፖርት ተገልጋይነት አሸጋገረኝ፤ ባለፈው በቀበና የሚያልፈውን አውቶበስ ጃንሜዳ ላይ ፥ ኢብሳ ህንጻ አጠገብ ከሚገኘው ፌርማታ ላይ ጠበቅሁት፤ አውቶብሱ ያረጀና የታከተ ነው፤ የእድገት በህብረት ዘማቾችን ከሽሮሜዳ እስከ ቦረና በማመላለስ ስራ የጀመረ አንጋፋ አውቶብስ መሆኑን አረጋግጫለሁ ፤ በተጠረመሰ ቁጥር እየበየዱ ፥ ሲዝግ ቀለም እየቀቡ ፥ እስከዛሬ እንዲያገለግል አስገድደውታል፤ ፍሬቻው በነበረበት ቦታ የለም፤ ማታ ማታ ሹፌሩ በፍሬቻው ቦታ ፋኖስ ያንጠለጥልበታል፤ ከቂጡ ላይ የተለጠፈ ያንበሳ ስእል አለ፤ (ከ”ከመቀመጫው ላይ “ ልል ነበር አውቶብሰ አይቀመጥም) ስእል እንደሚከሳ ያወቅሁት በዚህ አንበሳ ነው፤ ያንበሳው ጎፈር ብንን ብሎ ሰውነቱም ተቆሻምዶ አንበጣ መስሏል፤ አውቶብሱ እንደ አምሳ እግር ነው የሚያዘግመው፤ ራስህን ለመግደል አቅደህ ፊቱ ላይ ብትደቀን አይሳካልህም ፤ እንኩዋን የመዳጥ የመገፍተር አቅም የለውም ፤ ከጭስ ማውጫው ውስጥ የሰንደል የምትመስል ቀጫጫ ጢስ እየተመዘዘች ትወጣለች፤ እኔ የኩባ ሲጋር ሳጨስ ከዚህ የተሻለ፥ ፊቴን ከአበዳሪ እይታ የሚጋርድ ወፍራም ጭስ አወጣለሁ፤ አይ ጊዜ! እንዲያ በራይድ እንዳልተንደላቀቅሁ፥ የዶንኪሾቴን ፈረስ የመሰለ አውቶብስ ልፈናጠጥ ነው፤ ፌርማታው ላይ ሲደርስ በሩ ተከፈተ፤ ግን በሩ ላይ ራሱ አምሳ ሰው ቆሟል ፤ ተጨማሪ ተሳፋሪ ቀርቶ አየር ለማስገባት የሚሆን ቦታ የለም፤ ያም ሆኖ ፌርማታው ላይ ሰፍሮ የቆየ ህዝብ ለመግባት መጋደል ጀመረ፤ እኛ ተሳፋሪዎች ለመግባት ስንጋደል፥ ሹፌሩ ጋቢና ውስጥ ሆኖ እንደ ግልያዳተር እያየ ይዝናናብናል፤ በኛ በኩል ባለው በር ላይ የቆሙትን ተሳፋሪዎች ተባብረን ስንገፋቸው አንድ ዘንግ የሚያቆም ቦታ ተገኘ፤ የተገፉት ተሳፋሪዎች የት ገቡ?ጥቃቱ ስለመረራቸው በወድያኛው መስኮት ዘልለው ያመለጡ ይመስለኛል፤ ኪሴ ውስጥ ያለውን ሞባይል ይዘርፉኝ ይሆን ብየ ሰጋሁ፤ ግን በዚህ ሁኔታ ውስጥ ኪስ ማውለቅ የሚችል ሰው መሸለም ይገባዋል፤ምክንያቱም እዚህ አውቶብስ ውስጥ እጅህ ያንተ አይደለም፤ እንዴት እንደገባ ባይታወቅም እጅህን አጠገብህ ባለው ሰውየ ብብት ውስጥ ታገኘዋለህ ” አባ መውረጃየ ደርሷል ፤ እጄን ልትመልስልኝ ትችላለህ ‘ ማለት ይጠበቅብሀል፤ አንድ ወጣት ከፊትለፊቴ ይታየኛል፤ ከእግሩ ስር የተቀመጡትን አዛውንት ፥ “ አባ፤ ወንበሩን ሊለቁልኝ ይችላሉ ?” አላቸው፤ ሽማግሌው የሆነ ነገር ሊናገሩ ሲሉ፤ የአንድ አልፎሂያጅ ተሳፋሪ ፥ጋቢ ግንጣይ አፋቸው ላይ አረፈ፤ “ እናንተ በደናው ጊዜ ደልቷችሁ ኖራችሁዋል ፤ እስቲ አንዳንዴ እንኩዋ ለኛ ትንሽ የምቾት እድል ስጡን “ አለ ወጣቱ፤ ሽማግሌው አፋቸው ውስጥ የቀረውን የጋቢ ብናኝ እንደ ጉሽ ጠላ ትፍ ትፍ በለው ለርግማን ተዘጋጁ፤ ይህን ጊዜ፥ ወጣቱ አመለጠው፤ ለነገሩ አምልጦት ሳይሆን በፈቃዱ ለቀቀው፤ ዓላማው ግልጽ ነበር፤ ሲፈሳ ካጠገቡ ያሉት ተሳፋሪዎች ካውቶብሱ ይወርዳሉ ብሎ አስቦ ነበር ፤ ሽማግሌው ግን ተናገሩ፤ “ እንኩዋን ብትፈሳ ብታራ ራሱ አንወርድም ! ይሄ ህዝብ ባንተ የሸንኮራ ፈስ ቀርቶ በሙሰሎኒ የመርዝ ጋዝ እንኳ አልተበገረም! ፈሳም" ካውቶብሱ ወረድሁና ናፍጣ ለማስቀዳት በተደረደሩት መኪኖች ጀርባ ቡታጋዜን ይዠ ተሰልፍኩ፤

፡ ጅራፍ ይጮሃል          ፈትሉ ሆኖ መንታ ድምጽ እያፈነ     ከቆሳዩ በላይ ሀዘን እየገታ ፡ ጧ ይላል ሰውነት      ጧ ይላል ጠብታ             የደም እንጥፍ'ጣፊ ቆሞ የሚገ'ርፈው    በጭቃኔ ዝሎ አይመስልም ግን ጠፊ!        አቡ(አላዛር ቴዎድሮስ)

“ስለ እኔ ስትል ምራቅ የተፉብህን ፊትህን አሳየኝ እኔም የኃጢአቴን እድፍ በዕንባዬ አጥበው ዘንድ።” ​ይህ የአበው ልባዊ ጸሎት የሚነግረን ትልቁ እውነት በጌታ ሕማም ውስጥ የእኛን መዳን ብቻ ሳይሆን የእርሱን ወደር የለሽ ትሕትና ጭምር ነው። ጌታ በጲላጦስ አደባባይ ለግርፋት ጀርባውን ሲሰጥ ፊቱ ላይ ምራቅ ሲተፋበትና በራስጌው ላይ የሾህ አክሊል ሲደፋበት ዝም ማለቱ አቅም አጥቶ ሳይሆን የእኛን የትዕቢት ቁስል በትሕትናው ለመፈወስ ነው። ​ በዚህ በሰሙነ ሕማማት ወቅት እርሱ ስለ እኛ የተቀበለውን ውርደት ስናስብ እኛ ደግሞ በውስጣችን ያለውን የኩራት ግንብ ልናፈርስ ይገባል። አበው እንደሚሉን "ጌታ ለግርፋት የሰጠው ጀርባው ለእኛ መጠጊያ ግንብ ሆኖናል በፊቱ ላይ የተተፋው ምራቅም የእኛን የነፍስ እድፍ ቀድሷል።" ​ ስለዚህ ይህ ጊዜ የሐዘን ብቻ ሳይሆን የፍቅር መማሪያ ወቅት ነው። ጌታን የምንመስለው በዕውቀት ብዛት ወይም በንግግር ጌጥ ሳይሆን እርሱ እንዳደረገው ዝቅ ብለን ለሌሎች ፍቅርን ስንሰጥና በትሕትና ስንመላለስ ነው። ፊትህን ወደ እርሱ አዙር እርሱም በቁስሉ ይፈውስሃል በሕማሙም ሕይወትን ይሰጥሃል። ​ያብጽሓነ ለብርሃነ ትንሣኤሁ! 🙏🙏

አየህ የኔ እግዜር ያንተ ልጅ እንዲህ ነኝ ሌላው አባቴ ምን አይነት ፍቅር ነው እኔን በእድሜ በጤና ለዚህ አውዳመት ለትንሳኤህ ያደረስከኝ ብሎ የፍቅርና የደስታ እንባ ሲያለቅስ እኔም በተራዬ ጌታ ሆይ ምን አድርጌህ ነው ደሞ ለአሁኑ አውዳመት ያደረስከኝ 🥺 ከረከሰው ሞት ለኔ አተህ ነው ብዬ አማርራለሁ 😔 አየህ እኔ ልጅህ እች ሴት ነኝ ትናንትም ዛሬም ነገም ደሞ ካልሞትኩኝ የምማፀንህ ሰው እያልኩኝ ግደለኝ ያንተ ልጅ እንዲህ ነኝ 🥺😔😔