1 560
مشترکین
-224 ساعت
-17 روز
-1630 روز
آرشیو پست ها
1 560
ለቅድመ አንደኛ (K.G) እና አንደኛ ደረጃ ለምታስተምሩ ወላጆች ብቻ (የመጽሀፍት ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች)
ለመጨረሻ ጊዜ!
የመማሪያ መጽሐፍት ክፍያ ከነሐሴ 18 እስከ ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም፣ ከ2፡30 – 6፡00 ሰዓት ድረስ በአካል በመቅረብ በካሽ ብቻ እንድትከፍሉ እናሳውቃለን።
ይህንን የመጨረሻ ዕድል ሳያመልጣችሁ፣ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ክፍያውን እንድታጠናቅቁ እያሳወቅን ከተጠቀሰው ጊዜ ውጪ የግዢ ሂደቱ ስለሚጠናቀቅ እና ዝግ ስለሚሆን በተጠቀሰው ጊዜ ክፍያውን በማጠናቀቅ ከሌላ ገበያ ያለውን አላስፈላጊ ተጨማሪ ወጪና መጉላላት እንድትቆጠቡ እናሳስባለን።
ማስታወሻ ክፍያው በካሽ ገቢ ብቻ የሚደረግ ነው የባንክ Deposit አይቻልም
ት/ቤቱ
1 560
ለኢያሱ ቅርጫፍ አስኮ ፕሮግረስ ወላጆች/ አሳዳጊዎች በሙሉ
የመማሪያ መፅሀፍት ክፍያን ይመለከታል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ት/ቢሮ ከ KG-8 ክፍል ላሉ ተማሪዎች የተማሪ መማሪያ መፅሀፍት አዘጋጅቶ በየት/ቤቶች ከወላጆች ክፍያ እንዲሰበሰብ እና በዚሁ መልክ መፅሀፍቶቹን ለሁሉም ተማሪ ተደራሽ ለማድረግ አቅዷል። ሆኖም ይህን አጋጣሚ እንድትጠቀሙ በየት/ት ደረጃው ለጠቅላላ መፅሀፍት የሚመጣውን የሂሳብ መጠን ከምዝገባ ክፍሉ በመውሰድ ክፍያውን እስከ ሰኞ ነሀሴ 4/2018 ዓ.ም እንድትፈጽሙ እያሳሰብን ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ት/ቤቱ ለከፈሉ ተማሪዎች ግዢ የሚፈጸምበት እና የሚያከፋፍልበት ጊዜ መሆኑን እየገለፅን በተቀመጠው ጊዜ በመክፈል ተጠቃሚ እንድትሆኑ እና ይህን እድል ጊዜው አልፎበት ለአላስፈላጊ ተጨማሪ ወጪዎች እና እንግልት እንዳትዳረጉ እናሳስባለን።
ት/ቤቱ
1 560
19/11/2018
ጥብቅ ማሳሰብያ
በ2018 ዓ.ም ልጆቻችሁ 6ኛ ክፍል እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ላስፈተናችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች በሙሉ።
የ2019 ዓ.ም የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከተጀመረ ሳምንታት ያለፉ መሆኑ ይታወቃል ።
ሆኖም በአሁን ሰዓት የእነዚህ ክፍል ምዝገባ ከአለን የክፍል ብዛት እና የክፍሉ የመያዝ አቅም በላይ ተመዝጋቢዎች እየተመዘገቡ ስለሆነ የነዚህን ክፍሎች ምዝገባ አጠናቅቀን ምዝገባውን ልንዘጋ እየተገዳድን ነው ::
በዚህም መሠረት በልዩ ሁኔታ ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ነገ ሐምሌ 20 /2018 ዓ.ም ከ6ኛ ወደ 7ኛ እንዲሁም ከ8ኛ ወደ 9ኛ ተዘዋውረው ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች በአስቸኳይ እንድታስመዘግቡ ት/ቤቱ በጥብቅ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ በተባለው ጊዜ ውስጥ ወላጆች ኃላፊነት ወስዳችሁ በማስመዝገብ ያልተገባን መጉላላት እንድታስቀሩ በጥብቅ እናሳስባለን!
ት/ቤቱ
1 560
ሐምሌ 14/2018
ዉድ የነባር ተማሪዎች ወላጅ(አሳዳጊዎች)
በወላጆች/በአሳዳጊዎች ጥያቀ መሠረት ለ ሁለት ቀን ተራዝሞ የነበረው የነባር ተማሪዎች ምዝገባ (ነገ ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም ) የሚጠናቀቅ መሆኑን እየገለፅን እስካሁን ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች በነገው እለት እንድታስመዘግቡ በድጋሚ እናሳውቃለን።
ማሳሰብያ: ከሐምሌ 15/2018 ዓም በኋላ በሚኖሩን ጥቂት ክፍት ቦታዎች በመጠባበቅ ላይ ያሉትን የአዲስ ተማሪዎች ምዝገባ የምንጀምር መሆኑን እናሣውቃለን።
ት/ቤቱ
1 560
ዉድ የነባር ተማሪዎች ወላጅ(አሣዳጊዎች)
የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 1_ ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም ሲካሄድ እንደነበረ ይታወቃል።ነገር ግን በዛሬው እለት የነባር ተማሪዎችን ምዝገባ ለማጠናቀቅ ት/ቤቱ ከጠዋቱ 2 ሠዐት እስከ 9 ሠዐት ሰፊ እርብርብ ብናደርግም በርካታ ወላጆች ልጆቻቸውን በወቅቱ ባለማስመዝገባቸው ከፍተኛ መጨናነቅ ተፈጥሮ ነበር። ስለሆነም እስከአሁን ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች ለመጨረሻ ግዜ ሐምሌ 14 እና15/2018 ምዝገባ የምናካሂድ መሆኑን እንገልፃለን።
ማስታወሻ ሰኞ ሐምሌ 13/2018 አጠቃላይ የመምህራንና ሠራተኞች ስብሰባ ስለምናካሂድ በሁሉም ቅርንጫፎቻችን ምዝገባና የክረምት ትምህርት የማይኖር መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።
ት/ቤቱ
1 560
ዉድ የነባር ተማሪዎች ወላጅ(አሳዳጊዎች)
የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ነገ (አርብ ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም ) የሚጠናቀቅ መሆኑን በድጋሚ እየገለፅን እስካሁን ልጆቻችሁን ያላስመዘገባችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች በነገው እለት እንድታስመዘግቡ በድጋሚ እናሳውቃለን።
ማስታወሻ : ለነገ ብቻ ምዝገባ እስከ ቀኑ 9:00 ሰዓት የሚቆይ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።
ት/ቤቱ
1 560
ዉድ የነባር ተማሪዎች ወላጅ(አሣዳጊዎች)
የነባር ተማሪዎች ምዝገባ አርብ ሐምሌ 10/2018 ዓ.ም የሚጠናቀቅ መሆኑን በድጋሚ እየገለፅን በመጨረሻው ቀን ከሚፈጠረው አላስፈላጊ መጨናነቅ ልጆትን ቀድመው እንዲያስመዘግቡ በድጋሚ እናሣውቃለን።
ት/ቤቱ
1 560
ለነባር ተማሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ መሟላት ያለባቸው
1️⃣*ሁለት 3*4 ጉርድ ፎቶ
2️⃣* የተማሪ የፋይዳ ቁጥር (FAN)
3️⃣* የእናትና የአባት/ አሳደጊዎች
የፋይዳና የቀበሌ መታወቂያ
ፎቶ ኮፒ
4️⃣* የተማሪ ኦርጂናል ስርተፍኬት
