Dilla Don Bosco Catholic Secondary School
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
1 668
مشترکین
+124 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
ለ2018 ዓ.ም የክረምት የህፃናት ኮዲንግ ስልጠና በዚህ የጎጉል ፎርም ሊንክ ይመዝገቡ 👇
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSeoPlknHGKDI1vbqlY4yCGCQ_Baq79KLFA-5HN0OouK_M0zaQ/viewform?usp=header
⭐️በፈተና ዋዜማ እና የፈተና ጊዜ ስኬትን ለማረጋገጥ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ተግባራዊ ማድረግ ይገባል🔤➖
🔤በቂ እረፍት ማድረግ፡ አእምሮን ለማነቃቃት እና ጭንቀትን ለመቀነስ ቢያንስ ከ 7 እስከ 8 ሰዓታት የሚሆን ጥልቅ እንቅልፍ መተኛት ያስፈልጋል።
🔣የፈተና ቁሳቁስ ማሟላት፡ እስክሪብቶ፣ እርሳስ፣ ማጥፊያ፣ መለያ (ID) እና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶች አስቀድመው በቦርሳ መዘጋጀት አለባቸው።
⏰አጭር ግምገማ ብቻ ማድረግ፡
አዳዲስ ርእሶችን ለማንበብ ከመሞከር ይልቅ ቀደም ሲል የተሰሩ ማጠቃለያዎችን እና ዋና ዋና ነጥቦችን ብቻ ማየት ይበጃል።
🔤ትክክለኛ አመጋገብ፡ አእምሮ በተገቢው መንገድ እንዲሠራ ቀላል፣ ሰውነትን የሚያነቃቁ እና ጤናማ ምግቦችን መመገብ ይገባል።
🔤ስሜትን መቆጣጠር፡ የፈተና ፍርሃትን እና ጭንቀትን ለመቀነስ ከመጠን በላይ ከማሰብ መቆጠብ፣ አዎንታዊ አስተሳሰብ መያዝ እና ዘና ማለት ያስፈልጋል።
🔤የፈተና ቦታን ማወቅ፡ የፈተናው ቦታ ሩቅ ከሆነ አስቀድሞ መንገድን በመለየት ሰዓት አክብሮ ለመገኘት እቅድ መያዝ ወሳኝ ጉዳይ ነው
📌መልካም ፈተና!!
📌 መልካም ውጤት!
📌መልካም እድል!
👏👏👏👏
Register online using the following Google Form👇
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSeoPlknHGKDI1vbqlY4yCGCQ_Baq79KLFA-5HN0OouK_M0zaQ/viewform?usp=header
🚀 የልጆችዎን የክረምት እረፍት በዕውቀት ያድምቁ! 🚀
ላለፉት 5 ዓመታት ህፃናትን በኮዲንግ ስልጠና በማሰልጠን ስመ-ጥር የሆነው #ቦስኮ_ኮዲንግ_አካዳሚ (Bosco Coding Academy) በ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት ለአንድ ወር የሚቆይ ድንቅ የልጆች የኮዲንግ ስልጠና ይዞ ቀርቧል!
ቴክኖሎጂ የነገው ዓለም መሪ ነው! ልጆችዎ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ሳይሆኑ ፈጣሪ እንዲሆኑ አሁኑኑ ያስመዝግቧቸው።
📚 የሚሰጡ የስልጠና ዘርፎች፡
🖥️ ስክራች (Scratch): ለጀማሪዎች የፈጠራ እና የሎጂክ ክህሎት ማሳደጊያ
🐍 ፓይተን ፕሮግራሚንግ (Python Programming): ጠንካራ የኮዲንግ መሰረት መጣያ
🌐 ድረ-ገፅ ግንባታ (Web Development): የራሳቸውን ድረ-ገፅ የመስራት ጥበብ
🎯 የክፍል ደረጃ እና የምዝገባ ዝርዝር፡
🧑💻 የተማሪዎች ደረጃ: ከ6ኛ እስከ 10ኛ ክፍል
📅 የምዝገባ ጊዜ: ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 20 / 2018 ዓ.ም
🚀 ስልጠናው የሚጀምርበት ቀን: ሐምሌ 20 / 2018 ዓ.ም (ለአንድ ወር የሚቆይ)
📝 እንዴት ይመዘገባሉ?
ምዝገባውን በሁለት አማራጮች ማከናወን ይችላሉ፡
🌐 በኦንላይን (ከቤተዎ ሆነው): አስተያየት መስጫው ላይ ያለውን ሊንክ በመጫን መመዝገብ ይችላሉ
📍 በአካል መጥተው ለመመዝገብ: ዶን ቦስኮ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
🏢 ቦስኮ ኮዲንግ አካዳሚ - የነገውን ትውልድ በዲጂታል ክህሎት የመገንባት ጥበብ!
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር “ኤጀንቲክ መምህር ረዳት” የተሰኘ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያ አበልፅጎ በሙከራ ደረጃ ሥራ ላይ አውሏል።
Agentic AI Teacher Assistant የተባለው መተግበሪያው፣ ሙሉ በሙሉ ያለ ኢንተርኔት የሚሠራ፣ ራሱን ችሎ ውሳኔዎችን ማመንጨት የሚችል እና የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን የሥራ ጫና የሚቀንስ መሆኑ ተገልጿል፡፡
መተግበሪያው በውስጥ አቅም የበለፀገና በአካባቢያዊ ኮምፒውተር (Local Machine) ላይ በቀላሉ ተጭኖ የሚሠራ መሆኑን በሚኒስቴሩ የአይሲቲና ዲጂታል ትምህርት መሪ ስራ አስፈጻሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
መተግበሪያው በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ያሉትን መፅሐፍቶች በሙሉ ዳታሴት አድርጎ በመውሰድ፣ መፃሕፍቱን ሙሉ በሙሉ እንዲመረምርና እንዲገነዘብ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
መተግበሪያው ምን ምን ይሠራል?
➫ የትምህርት እቅድ (Lesson Plan) ያዘጋጃል፣
➫ የፈተና ጥያቄዎችና አሳይመንቶችን ያመነጫል፣
➫ ማስተማሪያ ስልቶችን (Pedagogical Strategies) በራሱ ማቀናጀት ይችላል።
መተግበሪያው በማንኛውም ላፕቶፕ ወይም ዴስክቶፕ ላይ ተጭኖ የሚሠራ ሲሆን፤ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች ተሞክሮ አጥጋቢ ውጤት ማስገኘቱ ተመላክቷል፡፡
መተግበሪያውን ለመጠቀም ምንም አይነት ወርሃዊ የኢንተርኔት ካርድ፣ የኔትዎርክ ዝርጋታ ወይም የኤአይ አጠቃቀም ክፍያ እንደማይጠይቅ በሚኒስቴሩ የአይሲቲ አማካሪ ሙሉነህ አጥናፉ (ዶ/ር) አስረድተዋል።
ከሁሉም ክልሎች ለተውጣጡ መምህራን እና የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች በመተግበሪያው አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
ምንጭ: ማህበራዊ ድረ ገፅ
New Mock Exam Web Address
👇
https://mock4.ethernet.edu.et/
+7
🏆 የእንኳን ደስ አላችሁ የምስራች! 🏆
ባለፈው ሳምንት ኢትዮጵያን ወክሎ በምስራቅ አፍሪካ የሒሳብ ውድድር ላይ በመሳተፍ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ለሆነው ለኩራታችን ማስተዋል አስራት ደማቅ የእውቅና እና የሽልማት ስነ-ስርዓት ተደረገለት! 🎉✨
በዛሬው እለት በዲላ ዶን ቦስኮ ሳሊዛውያን ማህበር (SDB) እና በትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አዘጋጅነት፣ በትምህርት ቤቱ የሰልፍ ስነ-ስርዓት ላይ ለማስተዋል የሚገባውን እውቅና ተሰጥቶታል።
በክብር እንግድነት የተገኙት የዲላ ከተማ ትምህርት ቢሮ መምሪያ ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ሆርዶፉ ለተማሪው የተዘጋጀውን የሽልማት ስጦታ (ታብሌት ኮምፒውተር እና ዘመናዊ የእጅ ሰዓት) ያበረከቱ ሲሆን፣ ለተማሪውና ለትምህርት ማህበረሰቡም አበረታች መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም ማስተዋልን ለዚህ ታላቅ የላቀ ውጤት እና ስኬት ካበቁት ውድ መምህራኑ ጋር በመሆን ደስ የሚል የማስታወሻ ፎቶግራፍ ተነስቷል።
ለማስተዋል አስራት፣ ለቤተሰቦቹ እና ለመላው የዲላ ዶን ቦስኮ ትምህርት ቤት ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ! ማስተዋል ለአገራችንም ለከተማችንም ትልቅ ኩራት ነው! 🇪🇹🥇
"ትምህርት ቤቶች እስከ ረቡዕ ዝግ ይሆናሉ" በሚል በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ እንደሆነ ተገለጸ።
"ከነገ ጀምሮ ሁሉም መደበኛ ስራዎች ይቀጥላሉ" ምርጫ ቦርድ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዛሬ ግንቦት 24/2018 ከማለዳ 12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ እንደሚገኝ ይታወቃል። በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ እና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ እንዲጠቀሙ የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት ከሚሰጡ ተቋማት በስተቀር በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ብቻ ዝግ እንዲያደርጉ ምርጫ ቦርድ ማስታወቁ ይታወቃል::
በዚህም መሰረት ከነገ ማክሰኞ ዕለት ጀምሮ መደበኛ የመንግስትና የግል ተቋማት ስራ እንደሚቀጥል ቦርዱ አመልክቷል።
በአንዳድ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች "ትምህርት ቤቶች እስከ ረቡዕ ዝግ ይሆናሉ" ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ እንደሆነ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ለኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ገልጸዋል።
ምንጭ:NBC
+2
🏆 እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ! 🏆
ኢትዮጵያን እና የዲላ ዶን ቦስኮን ስም በምስራቅ አፍሪካ መድረክ ላይ ያናኘ ታላቅ የምስራች!
🌍 በምስራቅ አፍሪካ በተካሄደው የሂሳብ ኦሎምፒያድ (East Africa Mathematics Olympiad) ውድድር ላይ ሀገራችንን ኢትዮጵያን በመወከል የተወዳደረው የትምህርት ቤታችን የ11ኛ ክፍል ተማሪ #መስተዋል_አስራት ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆኗል! 🥇✨
መስተዋል ባሳየው ድንቅ ብቃት ሀገሩን፣ ማህበረሰባችንን እና ተወዳጇን ትምህርት ቤታችንን በታላቅ ኩራት አኩርቷል።
ለዚህ ታላቅ ስኬት ለበቃው ለውዱ ተማሪያችን #መስተዋል_አስራት፣ ለተከበሩ ቤተሰቦቹ፣ ሌሊት ከቀን ለደከሙ መምህራኑ እና ለመላው የትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ፣ እንኳን ደስ አለን ማለት እንወዳለን!🎉🎈
🌟 የለፋበት ፍሬ፣ ለሁሉም ሆነ የኩራት ምንጭ! 🌟
📍 የዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን የነጻ ትምህርት ዕድል ጥሪ አቅርቧል
#Ethiopia | የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ጠንካራ ሀገራዊ የኒውክሊየር መሰረተ ልማት ለመገንባት የሚያስችሉ ከፍተኛ ባለሙያዎችን ለማፍራት ለኢትዮጵያውያን ተማሪዎችና ሰልጣኞች በሩሲያ የነጻ ትምህርት ዕድል ማመቻቸቱን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ለ2026/27 የትምህርት ዘመን በሩሲያ በሚገኙ ስመጥር የሳይንስና የምህንድስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ መማር የሚፈልጉ ብቁ አመልካቾች እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።
የሚሰጡ የትምህርት ዘርፎች በኒውክሊየር ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮሩ ሲሆን እነዚህን ዘርፎችንም ያካትታል ፡-
- Nuclear Power Engineering and Heat Physics (BSc & MSc)
- Nuclear Physics and Technology (BSc)
- Nuclear Power Plants Design, Operation and Engineering (BSc)
- Heat Power Engineering (BSc)
- Management in Technological Systems (MA)
የመወዳደሪያ መስፈርቶች ?
• ለመጀመሪያ ዲግሪ (BSc) ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት ያልበለጠ እና የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ አማካኝ ውጤታቸው 500 እና ከዚያ በላይ የሆነ።
• ለሁለተኛ ዲግሪ (MSc/MA) ዕድሜያቸው ከ30 ዓመት ያልበለጠ እና በሳይንስና ምህንድስና ዘርፍ በከፍተኛ ውጤት የተመረቁ።
ሴት አመልካቾች ለዘርፉ እንዲበረታቱ ኮሚሽኑ ጥሪ አቅርቧል።
መስፈርቱን ምታሟሉ አመልካቾች ከዛሬ ጀምሮ ባሉት 5 የሥራ ቀናት ውስጥ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን እና ደጋፊ ሰነዶቻችሁን በPDF በማዘጋጀት በኮሚሽኑ የኢሜል አድራሻ enecinfo@enec.gov.et መላክ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
ምንጭ: ከማህበራዊ ድረ ገፅ
የፈተና ስልቶች (Exam Strategies)
ፈተናን በተሳካ ሁኔታ እንዴት መውሰድ ይቻላል?
1. ፈተናው አንድ ሳምንት ሲቀረው
* ያለፉ የፈተና ሽቶችን መስራት
* የማጠቃለያ ማስታወሻዎችን መከለስ
2. ፈተናው እንደ ነገ ሆኖ ዛሬ ማታ
* የፈተና ቁሳቁሶችን (እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ) ያዘጋጁ
* የፋይዳ መታወቂያና አድሚሽን ካርድ ያደራጁ
* ሰዓት ያደራጁ
* ያለምንም ጭንቀት ዘና ብለው ይተኙ
3. በፈተና ክፍል ውስጥ (በፈተና ጊዜ)
I. ወደ ፈተና ክፍል ከገቡ በኋላ፡-
* መረጋጋትና በእርጋታ መፈተኛ ወንበር ላይ መቀመጥ
* ጭንቀትን ያስወግዱ
* የፈተና ወረቀቶች ሲሰራጩ ዘና ብለው ይተንፍሱ
II. ፈተናውን መስራት ሲጀምሩ፡-
* መመሪያዎችን (Instructions) ያንብቡ
* ጊዜን መቆጣጠር – ሰዓት እያዩ ፈተናውን መስራት
* በመጀመሪያ ቀላል የሆኑትን ጥያቄዎች ይስሩ።
* ከባድ ጥያቄ ካጋጠሞት፣ በስልታዊ ግምት አጥቁረው ሰርተው ወደሚቀጥለው ጥያቄ ይሂዱ። በፍፁም ሳያጠቁሩ ባዶ ቦታ ትተው እንዳያልፉ፡፡
* በአንድ ጥያቄ ላይ ረጅም ጊዜ አያጠፉ ምክንያቱም አጭር ጊዜ የሚወስዱ ብዙ ቀላል ጥያቄዎች አሉ።
* መጨረሻ ላይ ጊዜ ካለዎት፣ በግምት ቀብተው ያለፏቸውን ጥያቄዎች ተመልሰው ይስሩዋቸው።
* ስልታዊ ግምት 1/4ኛ መልሱን የማግኘት ዕድል አለው፡፡ ዝም ብሎ በደመነፍስ መገመት ሳይሆን ስልታዊ ግምት ይጠቀሙ፡፡
ዒድ ሙባረክ!
ለእስልምና እምነት ተከታይ ተማሪዎቻችን እና ወላጆች በሙሉ
እንኳን ለ1447ኛው ታላቁ የኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!
በዓሉ የሠላምና የፍቅር እንዲሆንላችሁ እንመኛለኝ ::
ዲላ ዶን ቦስኮ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት
ኤአይ (AI)ን እንዴት እንጠቀም ?
ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለረጅም ጊዜ እና ያለገደብ መጠቀም የሰዎችን የፈጠራ ብቃት እና ነገሮችን በጥልቀት የመመርመና የማሰብ ክህሎትን አደጋ ላይ ሊጥል እንደሚችል በቅርቡ የወጡ ተከታታይ ጥናቶች አመልክተዋል።
በዘርፉ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ሰዎች መረጃዎችን እና ውሳኔዎችን ሙሉ በሙሉ በኤአይ (AI) ላይ ጥገኞች ሆነው ማከናወን ሲጀምሩ " ኮግኒቲቭ ሰረንደር " ወይም የአእምሮን የማሰብ ስራ ለቴክኖሎጂ አሳልፎ የመስጠት ዝንባሌ ይታይባቸዋል።
ይህም አእምሮ በራሱ ጥረት መረጃዎችን የማቀናበር፣ የመተንተን እና አዳዲስ ሀሳቦችን የማመንጨት የተፈጥሮ ብቃቱ እንዲደክም ያደርገዋል።
በተለይ #ወጣቶች እና #ተማሪዎች ለተወሳሰቡ ጥያቄዎች እና ስራዎች ፈጣን ምላሽ ከኤአይ ማግኘት መልመዳቸው የራሳቸውን የአእምሮ አቅም የመጠቀም ተነሳሽነታቸውን እንደሚቀንሰው ተመራማሪዎች ያስጠነቅቃሉ።
ነገር ግን ቴክኖሎጂውን እየተጠቀሙ አእምሮን ሁል ጊዜ ንቁ፣ ብቁ እና ጤናማ አድርጎ ለማቆየት የሚረዱ በርካታ ሳይንሳዊ መንገዶች እንዳሉ ባለሙያዎች ይጠቁማሉ።
የአእምሮን የአስተሳሰብ ብቃት ላለማጣት ምን አይነት ልምዶች ማዳበር ይቻላል ?
- ከኤአይ (AI) የተገኙ ምላሾችን ወይም መረጃዎችን በቀጥታ ወስዶ ከመገልበጥ ይልቅ " ይህ መረጃ ትክክል ነው ? ምን ጎደለው ? አመክንዮአዊ ነው ? " በማለት በራስ አእምሮ መርምሮ፣ መዝኖ መጠቀም።
- ማንኛውንም ስራ፣ ጽሑፍ ወይም ፕሮጀክት ከመጀመርዎ በፊት መነሻ ሀሳቦችን እና እቅዶችን በራስ አእምሮ ማመንጨት እና ማስታወሻ መያዝ። ኤአይ ስራውን ለማስጀመር ሳይሆን የተጀመረውን ስራ ለማደራጀት ወይም ለመፈተሽ ብቻ መጠቀም።
- የፈጠራ እና የጥልቅ አስተሳሰብን የሚያነቃቁ እንደ መጽሐፍ ማንበብ፣ ስልታዊ ጨዋታዎችን መጫወት እና አዳዲስ ክህሎቶችን ያለ ቴክኖሎጂ እገዛ ለመማር መሞከር።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መረጃዎች/ስራዎችን ለኤአይ ሰጥቶ ያለ ምንም ምርመራ፣ ማስተካከያና ደጋግሞ የማንበብ ጥረት በቀጥታ #በመገልበጥ አንዳንዴም እንደራስ ስራ ማስመሰል እየተለመደ መጥቷል። ይህ በጥልቀት ሳያስቡና ሳይመራመሩ በቴክኖሎጂ ላይ ሙሉ በሙሉ ጥገኛ መሆን አእምሮን የማሰብ ስራውን እንዲተው በማድረግ፣ እውነታን የመተንተን እና የጥልቅ አስተሳሰብ ብቃትን በከፍተኛ ደረጃ እየገደለው ይገኛል ፤ ሰዎች ትንሽ ስራ እንኳን ለመስራት የማይፈልጉ ስልቹና ሰነፍ እያደረጋቸውም ነው።
ባለሙያዎች እንደሚመክሩት ኤአይ (AI) የሰውን ልጅ ሙሉ በሙሉ የሚተካ ሳይሆን እንደ ረዳት መሳሪያ ሆኖ ሊያገለግል የሚገባው ነው። ጥቅም የሚኖረውም የሰው ልጅ የራሱን የአስተሳሰብ ልዕልና ጠብቆ ሲቀጥል ብቻ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ/ም
✔️ሞዴል ፈተና መፈተን የሚያስገኛቸው ጥቅሞች:-
✅1. ያላችሁን እውቀት መመዘን እና ድክመታችሁን መለየት፡ ሞዴል ፈተናዎች በእጃችሁ ያለውን እውቀት ምን ያህል እንደሆነ ለመገምገምና የትኞቹ አካባቢዎች ላይ የበለጠ ትኩረት ማድረግ እንዳለባችሁ እንድታውቁ ያግዛሉ።
✅ ለምሳሌ፣ አንድን ሞዴል ፈተና ከሰራችሁ በኋላ በተወሰኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ደጋግማችሁ እንደተሳሳታችሁ ከተመለከታችሁ፣ በእነዚያ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ ጥናት ማድረግ ትችላላችሁ።
✅2.ከፈተና ጥያቄዎች እና የፈተና ሁኔታ ጋር መለማመድ፡ ሞዴል ፈተናዎችን መለማመድ የፈተና ጥያቄዎችን ቅርፅና አቀራረብ እንድታውቁ ይረዳችኋል። በተጨማሪም፣ በፈተና ጊዜ ሊያጋጥሟችሁ የሚችሉትን ጭንቀቶች ለመቀነስና ከፈተናው ሁኔታ ጋር እንድትላመዱ ያደርጋል።
✅3. የፈተና ጊዜ አጠቃቀም ክህሎትን ማሳደግ፡ ሞዴል ፈተናዎችን ስትሰሩ፣ ለእያንዳንዱ ጥያቄ ምን ያህል ጊዜ መመደብ እንዳለባችሁ ትማራላችሁ። ይህም በፈተናው ወቅት ጊዜያችሁን በአግባቡ እንድትጠቀሙበት ይረዳችኋል።
⭐️ ለምሳሌ፣ በአንድ ጥያቄ ላይ ብዙ ጊዜ እንደምታጠፉ ከተመለከታችሁ፣ በቀጣይ ፈተናዎች ላይ ጊዜያችሁን በአግባቡ ለመጠቀም ስልት መንደፍ ትችላላችሁ።
✅4. በራስ መተማመንን መጨመር እና የፈተና ላይ ጭንቀትን መቀነስ፡ በተደጋጋሚ ሞዴል ፈተናዎችን መስራት በራስ መተማመናችሁን ይጨምራል እንዲሁም በፈተና ጊዜ የሚሰማችሁን ጭንቀት ይቀንሳል።
✅በሞዴል ፈተናዎች ላይ ጥሩ ውጤት ስታገኙ፣ ለዋናው ፈተና የበለጠ በራስ መተማመን ይኖራችኋል።
✅5. የተማራችሁትን የማስታወስ እና የማስተዋል አቅምን መጨመር፡ ሞዴል ፈተናዎች የተማራችሁትን ነገር እንድታስታውሱና እንድትረዱ ያግዛሉ። ጥያቄዎችን ለመመለስ ስትሞክሩ፣ ቀደም ሲል ያጠኗችሁትን ርዕሰ ጉዳዮች በድጋሚ ታስታውሳላችሁ፣ ይህም ትምህርቱን በደንብ እንድትረዱት ያደርጋል።
✅6. የፈተና ጥያቄዎችን እና የተለያዩ የአጠያየቅ አይነቶችን ስልት ለማወቅ፡ ሞዴል ፈተናዎች የተለያዩ የጥያቄ አይነቶችን (ለምሳሌ፡ ምርጫ፣ እውነት ወይም ሐሰት፣ ወዘተ) እንድታውቁና ለእያንዳንዱ አይነት ጥያቄ እንዴት መልስ መስጠት እንዳለባችሁ እንድትረዱ ይረዳችኋል።
✅7. ትኩረት ማድረግ የሚያስፈልጉ ርዕሶችን እና አጠቃላይ ክለሳ ማድረግ ያለብንን ቦታዎች ለመለየት፡ ሞዴል ፈተናዎችን ከሰራችሁ በኋላ በየትኞቹ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እንደተሳሳታችሁ በመገምገም፣ በእነዚያ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ ትኩረት ማድረግ ትችላላችሁ።
✅ይህም ለፈተናው ስትዘጋጁ የትኞቹ አካባቢዎች ላይ ማተኮር እንዳለባችሁ እንድታውቁ ይረዳችኋል።
✔️በአጠቃላይ፣ ሞዴል ፈተናዎችን መፈተን እውቀታችሁን ለመገምገም፣ ለፈተናው ሁኔታ ለመለማመድ፣ ጊዜያችሁን በአግባቡ ለመጠቀም፣ በራስ መተማመናችሁን ለመጨመር እና ለዋናው ፈተና በተሻለ ሁኔታ ለመዘጋጀት ጠቃሚ ነው::
ምንጭ:
Education info Ethiopia
📢 የምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል!
ዲጂታል ኢትዮጵያን በሳይበር ደህንነት እና በቴክኖሎጂ እውቀት ለመገንባት ራዕይ ላላቸው ወጣቶች የተዘጋጀው 5ተኛው ዙር የሳይበር ታለንት ቻሌንጅ ሰመር ካምፕ የዕጩ ሰልጣኞች ምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል!
ባለፉት ዙሮች በካምፑ አልፈው ዛሬ ላይ የራሳቸውን የቴክኖሎጂ ስታርት-አፕ የመሰረቱ፣ በድሮን ቴክኖሎጂ፣ በኢምቤድድ ሲስተምስ እና በሳይበር ደህንነት ዘርፍ ሀገራዊ ችግር ፈቺ ስራዎችን እየሰሩ ያሉ የካምፑ ፍሬዎችን ተመልክተናል።
እርስዎስ የዚህ ጉዞ አካል ለመሆን ምን ይጠብቃሉ?
📅 የምዝገባ ማጠቃለያ ቀን፦ እስከ ግንቦት 17 / 2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ!
የቴክኖሎጂ እና የሳይበር ተሰጥኦ ያላቸው፣ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶች የተራዘመውን እድል ተጠቅማችሁ ፈጥናችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።
🔗 የምዝገባ ሊንክ፦ https://ctc.insa.gov.et/registration
ፈጠራችሁን ወደ ተግባር ቀይራችሁ የሀገራችሁን የሳይበር ሉዓላዊነት የምታስከብሩበት መድረክ ይጠብቃችኋል!
#INSA #CyberTalent2018 #SummerCamp #CyberSecurity #DigitalEthiopia2030 #TechTale
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
