fa
Feedback
Abdu & Hasu

Abdu & Hasu

رفتن به کانال در Telegram

Abdulhak & Hasenet <የኢቅራእ ቢስሚ ረቢከ /አንብብ በጌታህ ስም/ ትውልዶች እንጂ ፣ የኢቅራእ /የአንብብ / ትውልዶች አይደለንም።> አላህ ያወቅነውን የምናሳውቅ ፣ ባወቅነው ደግሞ የምንጠቀም ያድርገን። አሚን!! For any comment ⇄ @ABDU_EMRE

نمایش بیشتر
4 616
مشترکین
-324 ساعت
-237 روز
-12730 روز
آرشیو پست ها
#ጊዜው_ደርሷል 1448ኛው አ.ሂ እነሆ ገብቷል! ዓመቱ የዓለም የኃይል ሚዛን (የፖለቲካና የጂኦፖለቲካ መዋቅር) የሚቀየርበት፣ የድሮዎቹ ኃያላን የሚዳከሙበትና አዳዲስ ኃይሎች የሚወጡበት የሽግግር ወቅት ይሆናል። ይህ ውጥረትና መናወጥ ምድርን በፍትህ ለመሙላት ለሚመጣው መለኮታዊ ለውጥ መንገድ ጠራጊ ነው ተብሎ ይታመናል። ሼሆቹ እነዚህን ክስተቶች የሚናገሩት ሰውን ለማስፈራራት ሳይሆን፣ መንፈሳዊ ዝግጅት እንዲያደርግ ነው። ለዚህ ዓመት የሚከተሉትን ሶስት ነገሮች አጥብቁ ይላሉ፦ 1. ኢስቲግፋር (ምህረት መለመን) 2. ኡዝላህ (ራስን ከጩኸት ማራቅ) 3. ሱህባህ (ከመልካሞች ጋር መሆን)፦ በዚህ የፈተና ዘመን ብቻውን የሚጓዝ ሰው ይበላል፤ ስለዚህ ልባቸው ከፈጣሪ ጋር ከተገናኘ መልካም ሰዎችና መሻኢኮች ጋር መጣበቅ። ባጭሩ ሼሆቹ የዚህን ዓመት ፍሰት ሲያጠቃልሉት፦ "ውጫዊው ዓለም በከፍተኛ ፍጥነት ይናወጣል፣ ይለወጣልም፤ ነገር ግን በልቡ ውስጥ የአላህን ፍቅርና ሰላም የገነባ ሰው ማዕበሉ አይነካውም" ይላሉ። በዚህ ዓመት ልቡን አጥብቆ፣ በእውነተኛ ስሜትና እምነት ዱዓእ ለሚያደርግ ሰው ምላሹ በጣም በፍጥነት እንደሚመጣ ይናገራሉ። በተለይ የተበደሉ ሰዎች፣ ምስኪኖችና የልብ ስብራት ያላቸው ሰዎች ጸሎት ምድርን የመለወጥ ኃይሉ ከፍተኛ የሚሆንበት ዓመት ነው። *ደግ ምንሰማበትና ምናይበት አመት ያድርግልን! #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ የዑስማኒያ ታሪክ ጸሐፊና ተጓዥ ኤቭሊያ ቸለቢ በጉዞ ማስታወሻቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፦ ሱልጣን ሙራድ 4ኛ ልክ እንደሌሎቹ የኦቶማን ሱልጣኖች፣ የተራ ሰው ልብስ ለብሰው፣ በሌሊት የሕዝቡን ሁኔታ መፈተሽ ያዘወትሩ ነበር። አንድ ቀን ሌሊት ሱልጣኑ ከታማኝ አገልጋዩ ጋር ሆኖ በኢስታንቡል ታዋቂው የንግድ ማዕከል አቅራቢያ ሲያልፍ፣ በአንድ ትንሽ ሱቅ ውስጥ መብራት በርቶ ይመለከታል። ወደ ሱቁ ጠጋ ሲሉ፣ አንድ በጣም ረጋ ያለ፣ ሽበት የበዛበትና ፊቱ በብርሃን የተሞላ ጫማ ሰፊ ብቻውን ተቀምጦ ጫማ ሲሰፋ ያገኙታል። ሱልጣኑና አገልጋዩ ተራ መንገደኛ መስለው ወደ ሱቁ ገቡና «ሰላም ላንተ ይሁን አባት ሆይ፣ በዚህ ሌሊት ምን እየሰሩ ነው?» አሉ። ሽማግሌው ቀና ብለው ተመለከቱ፤ የሚገርመው፣ ሱልጣኑ ልብሱን ቀይሮ የመጣ ቢሆንም፣ ገና ሲያዩት ማንነቱን አውቀው ነበር። ሽማግሌውም ፈገግ አሉና «ሰላም ላንተም ይሁን ሱልጣኔ! እንኳን ደህና መጣህ። እኔ የአላህን ሲሳይ ፍለጋ ጫማ እየሰፋሁ ነው» አሉ። ሱልጣን ሙራድ በማንነቱ መታወቅ እጅግ ደነገጠ። ወዲያውም ይህ ሰው ተራ ጫማ ሰፊ እንዳልሆነ ተረዳ። ሱልጣኑ በክብር ተቀምጦ ከሽማግሌው ጋር ማውራት ጀመረ። በጨዋታቸው መሃል፣ ሽማግሌው ጫማውን በሰፉ ቁጥር፣ «ያ ኸድር... ያ ኸድር...» እያሉ ይተነፍሱ ነበር። ሱልጣኑ ይህንን ሲሰማ በጥንቃቄ ተመለከታቸውና እንዲህ አለ፦ «አባት ሆይ! "ያ ኸድር" እያልክ ትጠራለህ። ለመሆኑ ኸድርን (ዐ.ሰ) አይታችሁ ታውቃላችሁ? ወይስ ዝም ብላችሁ ነው ስሙን የምታነሱ?» ጫማ ሰፊው ሽማግሌ መርፌቸውን አስቀመጡና ወደ ሱልጣን ሙራድ 4ኛ ቀረብ ብለው ፈገግ አሉ፦ «ሱልጣን ሆይ! አንዳንድ ሰዎች ኸድርን ለማግኘት እድሜያቸውን ሙሉ በተራራና በባህር ዳርቻ ይፈልጉታል። ነገር ግን ኸድር አንዳንድ ጊዜ በየቀኑ ወደ ሱቃቸው እየመጣ አጠገባቸው እንደሚቀመጥ አያውቁም። ለምሳሌ አሁን እኔ "ያ ኸድር" ባልኩ ቁጥር፣ እርሱ እዚህ አጠገቤ ተቀምጦ መርፌውን ሲያቀብለኝ ይታየኛል» አሉ። ሱልጣኑ ይህንን ሲሰማ በሰውነቱ ላይ የደስታና የፍርሃት ስሜት ፈሰሰ። ወዲያውኑ ሽማግሌውን በጥብቅ ተመልክቶ «እባክህ ያ ሰይዲና! አንተ እራስህ ኸድር ነህ አይደል?» ብሎ እጁን ሊስም ተጠጋ። ሽማግሌው ግን እጃቸውን ሳቡና፦ «አይደለሁም ሱልጣኔ፣ እኔማ የኸድር ምስኪን ወዳጁ ነኝ። እርሱ ግን አሁን ከዚህ ሱቅ ወጥቶ ወደ ባህር ዳርቻው ሄዷል» አሉት። ሱልጣን ሙራድ 4ኛ ከዚያ ሱቅ የወጣው የዱንያ ንግሥና ከተራው ጫማ ሰፊ መንፈሳዊ ደረጃ ጋር ሲነጻጸር ምን ያህል ኢምንት እንደሆነ ተረድቶ ነበር። አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሐመድ! አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር! #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

#ለይለተል_ጁሙኣ ታዋቂው የኦቶማን ተጓዥ እና የታሪክ ጸሐፊ እቭሊያ ቸለቢ ገና የ20 ዓመት ወጣት እያለ፣ ልቡ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፍቅር የተቃጠለ እና ሁልጊዜም እርሳቸውን በህልሙ ለማየት የሚናፍቅ ስስ ልብ የነበረው ወጣት ነበር። በኢስታንቡል ከተማ ይኖር በነበረበት ወቅት፣ በአንድ የተባረከ የጁምዓ ምሽት (ለይለተል ጁምዓ) ሌሊቱን ሙሉ ቁርዓን ሲቀራ፣ ሰለዋት ሲያወርድና እያለቀሰ ዱዓ ሲያደርግ አደረ። በለሊቱ መጨረሻ ላይ እዚያው ቁርዓኑ ላይ እንዳለ እንቅልፍ ወሰደው። እቭሊያ ቸለቢ በህልሙ እራሱን በኢስታንቡል ከተማ በሚገኘው በታዋቂው "አሂ ቸለቢ መስጂድ" ውስጥ አገኘው። መስጂዱ በሰው የተሞላ ቢሆንም፣ በውስጡ ያሉት ሰዎች በሙሉ መላእክት፣ ታላላቅ ሶሃቦችና ሰማዕታት ነበሩ። መላው መስጂድ በብርሃን (ኑር) ተሞልቷል። በድንገት ከመስጂዱ ሚህራብ (የሶላት መሪው ቦታ) አጠገብ ፍጹም ብርሃን የሆኑት ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በግርማ ሞገስ ተቀምጠው ተመለከተ። ሰሃባው ሰዕድ እብኑ አቢ ወቃስ (ረ.ዐ) እቭሊያ ቸለቢን እጁን ይዞ ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፊት አቀረበው። ወጣቱ እቭሊያ ቸለቢ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ግርማ ሞገስና ውበት ፍጹም ተደንቆ፣ ልቡ በደስታና በፍርሃት እየመታች እግራቸው ስር ወደቀ። ከመምጣቱ በፊት በለይለተል ጁምዓ ሲያለቅስ የነበረው ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) "የእርስዎን አማላጅነት (ሸፋዐት) እፈልጋለሁ" ለማለት ነበር። ነገር ግን በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፊት በቆመ ጊዜ፣ በደስታና በድንጋጤ ብዛት አንደበቱ ተሳሰረ። "ሸፋዐት ያ ረሱለላህ" ማለት ሲገባው፣ በአፉ የመጣውና የተናገረው እንዲህ ነበር፡ "ሰያሀት ያ ረሱለላህ!" (የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ጉዞ/ጉብኝትን እሻለሁ!) ታላቁ ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የወጣቱን መሳሳትና የልቡን ንፅህና ተመልክተው በደማቅ ሁኔታ ፈገግ አሉ። ከዚያም የተሳሳተውንም ያልተሳሳተውንም አጣምረው እንዲህ አሉት፦ "አላህ ሁለቱንም ይስጥህ! ሸፋዐቴም (አማላጅነቴም)፣ ሰያሀትህም (ጉዞህም) ይስጥህ፤ የአለምን ድንቆች የምታይበትና የምትመሰክርበት ረጅም እድሜ ይስጥህ!" አሉት። በመቀጠልም በቦታው የነበሩት ሶሃቦች በሙሉ ለእቭሊያ ቸለቢ ዱዓ አደረጉለት። ከህልሙ በደስታና በዕንባ ተውጦ ሲነቃ፣ ያ የተባረከ የአርብ ምሽት ህልም የሕይወቱ መመሪያ እንደሆነ ተረዳ። ከዚህ የለይለተል ጁምዓ መናም በኋላ፣ እቭሊያ ቸለቢ ከኢስታንቡል በመነሳት በመላው የኦቶማን ግዛት፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ (መካ እና መዲናን ጨምሮ) ለ50 ዓመታት ያህል ተጓዘ። ያየውንና የታዘበውን ሁሉ "ሰያሀት ናሜ" (የጉዞ ማስታወሻ) በሚባለው ታዋቂ የ10 ጥራዝ መጽሐፉ ውስጥ አሰፈረው። በጁሙኣ የአባባ ሰለዋት ስጦታ <اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مَركَز الأَنْبِيَاءُ وَالأَوْلِيَاءُ ، وَآلِهِ وَصَحْبِهِ أُولِي الْفَضْلِ وَالأَتْقِيَاءِ.> #መደድ_ያአላህ! #ሸፈኣት_ያረሱሉሏህ! #ሂመት_ያአባራሙዝ! @abduftsemier @abduftsemier

أهل المودة في فناء جالو إلى أن وصلوا في الجهات سارو اللهم صلى على محمد (٢) مدينة النور وأرباب الصفا

#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ ሱልጣን አብዱልሀሚድ በጣም አስቸጋሪና የሀገር ህልውና የሚወሰንበት ዲፕሎማሲያዊ ቀውስ በገጠማቸው ቁጥር፣ ወደ ግል መስገጃ ክፍላቸው (ኸልዋ) ይገቡና ረጅም ሰዓት ይቆያሉ። በአንድ ወቅት፣ አንድ የቅርብ አገልጋያቸው በሩ ላይ ቆሞ ሳለ፣ ሱልጣኑ በክፍሉ ውስጥ ከሌላ ሰው ጋር በዝቅተኛ ድምፅ ሲነጋገሩ ይሰማል። ነገር ግን ወደ ክፍሉ የገባ ምንም ሰው አልነበረም። በኋላ ላይ ሱልጣኑ ከክፍሉ ሲወጡ ፊታቸው በደስታ በርቶ ነበር። አገልጋዩ ደፍሮ «ሱልጣኔ ሆይ! ብቻዎን ሆነው ማንኑን እያማከሩ ነበር?» ብሎ ጠየቃቸው። ሱልጣኑም ፈገግ ብለው፦ «በዚህ የጭንቅ ሰዓት ዑስማኒያን ብቻዋን የማይተዋትና በአላህ ፍቃድ መመሪያ ይዞልኝ የሚመጣው ሰይዲና ኸድር ነበረ። እርሱ አሁን የመጣው የፈረንሳይንና የእንግሊዝን ተንኮል እንዴት እንደምሰብር ሊነግረኝ ነው» በማለት ምስጢሩን ገልጠውለታል። በሌላ ጊዜ የጁምዓ ሶላት ከተሰገደ በኋላ፣ ሱልጣን አብዱልሀሚድ ከሕዝቡ ጋር ሰላምታ እየተለዋወጡ ሳለ፣ አንድ በጣም ያረጀ ልብስ የለበሰ፣ አይኑ ገርመም የሚያደርግ ሽማግሌ ወደ ሱልጣኑ ቀረበ። ሽማግሌው የሱልጣኑን እጅ በጥብቅ ይዞ ሰላም ካላቸው በኋላ፣ በጆሯቸው ጠጋ ብሎ «የአላህ አደራ በአንተ ላይ ይሁን፣ በፅናት ቁም!» አላቸው። ሱልጣኑ የሰውየውን እጅ በያዙበት ቅጽበት፣ በሰውነታቸው ላይ ልዩ የመንፈስ እርካታና ሙቀት ተሰማቸው። ሰውየው ሰይዲና ኸድር መሆናቸውን ወዲያውኑ የተረዱት ሱልጣኑ፣ እጃቸውን ሳይለቁ «ዱዓእ አድርጉልኝ ያ ሰይዲና» አሏቸው። ሽማግሌውም ፈገግ ብለው «አላህ ካንተ ጋር ነው» ካሉ በኋላ፣ ወደ ህዝቡ መሃል ገብተው በአንድ ቅጽበት ተሰውሩ። ሱልጣን አብዱልሀሚድ በ1909 ዓ.ም (በምዕራባውያንና በሀገር ውስጥ ተንኮለኞች ሰበብ) መፈንቅለ መንግስት ሲደረገባቸውና ዑስማኒያ ወደ መፍረስ በተቃረበችበት ወቅት፣ በኢስታንቡል የነበሩ ታላላቅ አውሊያዎች (ለምሳሌ እንደ ሸይኽ ዛፊር ያሉ) በህልማቸውና በከሽፋቸው ያዩትን ታሪክ እንዲህ ሲሉ ዘግበውታል፦ «ሱልጣኑ ከስልጣን በወረዱበት ሌሊት፣ ሰይዲና ኸድር በኢስታንቡል ባህር ዳርቻ ላይ ቆመው በከፍተኛ ሃዘን ሲያለቅሱ ታዩ። "ዛሬ የዑስማኒያ መንፈሳዊ ጋሻ ተሰበረ፣ ለኢስላም ኡማ የሚያለቅሰው የአላህ ወዳጅ ወደቀ" እያሉ አዝነዋል።» "O yüce Osmanlılara selam olsun!" "ሰላም ለታላቆቹ ዑስማኖች!"✋ *አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ መርከዚል አንቢያዕ ወል አውሊያዕ! *አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር! #አባ_ደዋም #እነሆ_አዲሱ_ዘመን! @abduftsemier @abduftsemier

#101_አመታት_ያለ_ኸሊፋ💔   ታላቁ ኸሊፋ የፍልስጤም ጠበቃ የኡስማኖች ሱልጣን አብዱልሀሚድ ሁልጊዜ የኸሚስ ምሽት (የጁሙዓ ለሊት) ሲመጣ የመንግስትን ስራዎች በሙሉ ያቆሙና ለሊቱን በሰለዋት፣ በዚክርና በሰላት ያሳልፉ ነበር። "ይህ ለሊት የአላህና የመልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) ብቻ ነው" በማለት። አንድ የጁሙዓ ለሊት ግን በሚቀጥለው ቀን ጠዋት መውጣት ያለበት እጅግ አስቸኳይና የኡማውን ደህንነት የሚመለከት ውሳኔ ነበረ። ሱልጣኑ ለሊቱን በዒባዳ አሳልፈው በሰለዋት ተመስጦ ላይ ሳሉ እንቅልፍ ይወስዳቸዋል። በህልማቸውም ነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) ያያሉ። የአላህ መልእክተኛም (ሰ.ዐ.ወ) ፈገግ ብለው እንዲህ አሏቸው፦ <"ልጄ አብዱልሀሚድ ሆይ! ዛሬ በጁሙዓ ለሊት በእኔ ላይ የምታወርደው ሰላዋት ደርሶኛል። የኡማው ጉዳይ አያስጨንቅህ፣ ወደ ስራህ ተመለስ፤ እኛ ከጎንህ ነን።"> ሱልጣን አብዱልሀሚድ በከፍተኛ ድንጋጤና ደስታ ከህልማቸው ባነኑ፤ ወዲያውኑ በእኩለ ሌሊት ፓሻውን አስጠሩት። ፓሻው በለሊት መጠራታቸው አስደንግጦቸው ሲመጡ፣ ሱልጣኑ ሰነዱን አውጥተው ፈረሙበት። ሱልጣኑ እያለቀሱ ለፓሻው እንዲህ አሉት፦ "ይህንን ሰነድ የፈረምኩት በራሴ ፍላጎት አይደለም፤ የጁሙዓ ለሊት ባለቤት የሆኑት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፈርመው ስላሉኝ ነው!" ይህንን ሲሰሙ በጋራ እያለቀሱ ለሊቱን በሰለዋት አደሩ። *ሱልጣኑ የጁሙዓ ለሊት ሲገባ ቀኑን ሙሉ በውዱእ ለመቆየት ይጥሩ ነበር። ሌላው ቀርቶ ከእንቅልፋቸው ሲነቁ ውዱእ ለማድረግ እስከሚሄዱ ድረስ መሬቱን በባዶ እግራቸው እንዳይረግጡ ከአልጋቸው አጠገብ ያለውን አፈር ታያሙም ያደርጉበት ነበር። *በጁሙዓ ለሊት ከመካና መዲና የሚመጡ ደብዳቤዎች ካሉ፣ ሌላውን የመንግስት ስራ አቁመው እነዚያን ቅዱሳን ቦታዎች ለማክበር ሲሉ ደብዳቤዎቹን በቆሙበት ሆነው ያነቡ ነበር። "O yüce Osmanlılara selam olsun!" "ሰላም ለታላቆቹ ዑስማኖች!"✋     በጁሙኣ የአባባ ሰለዋት ስጦታ <اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مَركَز الأَنْبِيَاءُ وَالأَوْلِيَاءُ ، وَآلِهِ وَصَحْبِهِ أُولِي الْفَضْلِ وَالأَتْقِيَاءِ.> በእነዚህ 101 አመታት ሙስሊሙ አለም ጭንቅላት እንደሌለው ሰው ሆኖል። በቃቹ ይበለን! #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

#ሂ_ባባ በቻይና የእስልምና ታሪክ ውስጥ የቃዲሪያ ጠሪቃን እና ማህበረሰቡን በመንፈሳዊ እውቀት ያነፁ ታላቅ መሪ ናቸው። በቻይና ሙስሊሞች ዘንድ «ሂላል አል-ዲን» ወይም በሰፊው «ሂ ባባ» እየተባሉ በታላቅ አክብሮት ይጠራሉ። ሂ ባባ ስማቸው ጪ ጂንግዪ (祁静) ሲሆን፤ የተወለዱት በ1656 እ.ኤ.አ. በኪንግ ስርወ-መንግስት ዘመን በጋንሱ ግዛት በሊንዢያ ከተማ ነው። ከተማዋ በታሪኳ በርካታ ሙስሊሞች የሚኖሩባት እና «የቻይናዋ መካ» እየተባለች የምትጠራ ስፍራ ናት። ሂ ባባ ገና በወጣትነታቸው በዒባዳ የጠነከሩ እና ጥልቅ የሆነ መንፈሳዊ ጥማት የነበራቸው ሰው ነበሩ። በወቅቱ በመካከለኛው እስያ እና በቻይና መካከል የነበረውን የሐር ንግድ ተከትለው የሚመጡ ታላላቅ መሻይኾችን በማግኘት እውቀት ለመቅሰም ከፍተኛ ጥረት ያደርጉ ነበር። የሂ ባባ ህይወት ሙሉ በሙሉ የተቀየረው በ1672 እ.ኤ.አ. ታላቁን መምህር ኸውጃ አፋቅ በተገናኙ ጊዜ ነበር። ኸውጃ አፋቅ ከመካከለኛው እስያ (ከካሽጋር) ተነስተው እስልምናን ለማስተማር ወደ ዢኒንግ መጥተው ነበር። ሂ ባባ ወደ መምህሩ ዘንድ በመቅረብ የሱፊያ መንገድን በጥልቀት ተማሩ። ኸውጃ አፋቅ የሂ ባባን ታማኝነት፣ ትህትና እና የውስጥ ንፅህና በመመልከት የቃዲሪያን መንገድ በቻይና እንዲመሩ እና እንዲያስፋፉ ኢጃዛ (መንፈሳዊ ፈቃድ) ሰጧቸው። ይህ ክስተት የቃዲሪያ ጠሪቃ በቻይና መሬት ላይ በይፋ ስር እንዲሰድ ማዕዘን ድንጋይ ሆነ። ሂ ባባ መንገዱን ሲመሩ የነበራቸው አቀራረብ ከሌሎቹ የቻይና ሱፊ መሪዎች እጅግ የተለየ እና ማራኪ ነበር፦ ሂ ባባ በዱንያዊ (አለማዊ) ክብርና ስልጣን ላይ ምንም ፍላጎት አልነበራቸውም። ተከታዮቻቸውም ጊዜያቸውን በጸጥተኛ ዚክር (ኸፊይ) እና በቁርዓን ንባብ እንዲያሳልፉ ይመክሩ ነበር። በመላው ሰሜን ምዕራብ ቻይና እየተዘዋወሩ በርካታ ሙሪዶችን አፍርተዋል። እነዚህ ሙሪዶች በኋላ ላይ ጦሪቃን በተለያዩ የቻይና ግዛቶች አስፋፍተዋል። ሂ ባባ በ1719 እ.ኤ.አ. በተወለዱባት ሊንዢያ ከተማ አረፉ። የእሳቸው ማረፍ ተከታዮቻቸውን እጅግ ያሳዘነ ቢሆንም፥ የእሳቸው መንፈሳዊ መገኘት ግን አልጠፋም። ከተለያዩ የቻይና ክፍሎች የሚመጡ ሙስሊሞች የእሳቸውን መቃብር ለመጎብኘት እና ዱዓ ለማድረግ ወደዚህ ስፍራ ይመጣሉ። በአሁኑ ጊዜም የሂ ባባ ስም ሲነሳ የቻይና ሙስሊሞች የሚዘክሩት የእሳቸውን ትህትና፣ ሰላማዊነት እና እስልምናን በቻይና ባህል ውስጥ በጥበብ የማስረፅ ችሎታቸውን ነው። *በቻይና ከቃዲሪያ ውጪ ነቀሽበንዲያ፤ ኩብራዊያን .. የመሳሰሉ ጦሪቃዎች ይገኛሉ። #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ በአንድ የቱርክ መንደር ውስጥ የሚኖር በጣም ደግና አላህን ፈሪ ገበሬ ነበር። ሁልጊዜም ዱዓ ሲያደርግ “ያ አላህ! የሰይድና ኸድርን ፊት ሳላይ እንዳትገለኝ፣ አንዴ እንኳ ቤቴ መጥቶ ማዕዴን እንዲባርክልኝ አድርግ” እያለ ይማጸን ነበር። በአንድ የብርድ ወራት፣ አንድ በጣም የቆሸሸ፣ ልብሱ የተቀደደና የሚያስጠላ ሽታ ያለው ደሃ አረጋዊ መጥቶ በሩን አንኳኳ። ገበሬውና ባለቤቱ ግን ምንም ሳይጸየፉ በፍቅር ተቀብለው፣ እግሩን አጥበው፣ ካላቸው ምርጥ ምግብ አቅርበው አስተናገዱት። አረጋዊውም መግቦቱን አክብሮ ዱዓ አድርጎላቸው ሄደ። ​በነገታውም በተመሳሳይ ሰዓት፣ ሌላ በጣም ተሳዳቢ፣ ቁጡና ክፉ የሚናገር ለማኝ መጣ። ገበሬው አሁንም በትዕግስት አስተናግዶት ሸኘው። በሦስተኛው ቀንም ሌላ እንግዳ መጥቶ አስተናገዱ። ​በዚያው ሰሞን ገበሬው በህልሙ አንድ ታላቅ መሪ አገኘና “ያ አላህ፣ ይሄን ያህል ዘመን ኸድርን አሳየኝ እያልኩ ስለምንህ ለምን አልመጣልኝም?” ብሎ ጠየቀ። በህልሙ የተገለጠው መሪም ሳቅ አለና፦ ​“የመጀመሪያው ቀን የመጣው ኸድር ነበረ፤ የቤታችሁን ንጽሕናና ቸርነት አየ። ​በሁለተኛው ቀን የመጣውም ኸድር ነበረ፤ የእናንተን ትዕግስትና ስነ-ምግባር ፈተነ። ​በሦስተኛው ቀንም የመጣው ኸድር ነበረ፤ በረከቱን ጥሎላችሁ ሄደ። #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

#አራጁ ይህችን የቁስ አለም አልፈልጋትም፤ ጀነትንም አይደለም ምፈልገው፤ ከውሰርን አይደለም ምመኘው፤ የምፈልገው አንተን ብቻ ነው። ጠዋፍ አደረግን ከሰላታችን ቂብላ፤ የኢብራሂም ግቢ ሩህ የምትሞላ፤ ከሶፋ መርዋ ሀጀራ ስትሮጥ በጭንቀት፤ በሶምሶማ ስሮጥ እኔም ለመጥራራት፤ አበበ ትዝ ቢለኝ ሩጫዬን አቀለጥኩት፤ ከኢስማኢል እጅም ዋንጫ ተቀበልኩት፤ ደሞ ስጠጣው ያንን ጣፋጭ ዘምዘም፤ እጅግ መጣፈጡ ነፍስን ያድሳል ለዘላለም። ደሞ ከአረፋ ተራራ በ9 ኛው ቀን ከጫፉ ወጥቼ፤ የመላኢካን ጥሪ የጌታን ውዳሴ ሰምቼ፤ ያረብ እያልኩት እንባዬን ዘርቼ፤ አቤት ያ አብዲ ሲለኝ መቋቋም አቃተኝ፤ የኔ ከሪም በእዝነቱ አካቦ አቀፈኝ፤ ለሊቱን ለማደር ሀጃጁ ሲታደም፤ ምቾቱ የእንቅልፍ እንዲህ አይነገርም፤ ደሞ የኢዱ ቀን ኡዱሂያ ሲታረድ፤ ኢስማኢል አለኝ ሙክቱን እረድ፤ ጅብሪልን ጠየቅኩት ሙክት ስጠኝ ብዬ፤ እሱም እየሳቀ ኢስማኢልን ሳታርድ ለምንብዬ? ነፍሳቸውን ለሚያርዱት ሽልማቱ ምንድነው? አሁን ሀቅ ብለሀል ሙክቱን አመጣው፤ ቢስሚላሂ ተብሎ ሊፀዳ ታረደ፤ የነብሳያችን ቆሻሻ ከእንግዲህ ተወገደ፤ እንዲህ እያልን በብዙ ነጎድን፤ ከሩሁ አለም ከሀጅ ተመለስን። @abduftsemirr @abduftsemier

#ሁለቱ_ነገስታት ዛሬ የሰይዲና ኸድርና ሰይዲ ኢልያስ (ዐሰ) በአረፋ ዲዋን የሚመሩበት የጉባዔ እለት ነው። ታላቁ ሸይኽ ኢብን አቢ እንደሚያብራሩት፣ የሰይድና ኸድርና የሰይድና ኢልያስ መገናኘት የሁለት ዓለማት መገናኘት ነው። -ሰይድና ኸድር የባጢን (የምስጢር እውቀት) መገለጫ አድርገው ይመስሏቸዋል። ሰይድና ኢልያስን ደግሞ የ"ዛሂር" (የሸሪዓው እውቀት) ጠባቂ አድርገው ያዩዋቸዋል። ሰይድና ኸድርና ሰይድና ኢልያስ የሚመሩት ታላቅ የመንፈሳዊ አካላት ጉባኤ ለሚመጣው ዓመት በምድር ላይ ስላለው ሰላም፣ በረከት፣ የዝናብ መዝነብና የሰዎች ሲሳይ (ርዝቅ) ዱዓ ይደረጋል፣ ውሳኔዎችም ይተላለፋሉ። ሼህ ናዚም ስለዚህ ቀን እንደገለጹት፣ በዚህ ዕለት በሰይድና ኸድርና በሰይድና ኢልያስ መሪነት ታላቅ መንፈሳዊ ስብሰባ (ዲዋን) ይደረጋል። በዚህ ስብሰባ ላይ የነቅሸበንዲያ ሰንሰለት መሻይኾች በሙሉ ይሳተፋሉ። እሳቸው «በዚህ ዕለት አላህ ለሰው ልጆች የሚሰጠውን እዝነት፣ ሲሳይ (ርዝቅ) እና ጥበቃ የሚከፋፍሉት እነሱ ናቸው፤ ስለዚህ ልባችሁን ሰብስባችሁ ዱዓ አድርጉ» ይሉ ነበር። ሼህ መህሙድ ኢፈንዲ፣ በዚህ ዕለት ሌሊቱን በሰላት (በተሃጁድ) ማሳለፍ፣ ጧት ላይ ሰደቃ መስጠት፣ እና የአላህን በረከት መለመን እንደሚገባ ያስተምራሉ። በተለይም በቱርክ ውስጥ በዚህ ዕለት ሰዎች ምኞታቸውንና ዱዓቸውን በወረቀት ጽፈው ከሮዝ (የጽጌረዳ) ዛፍ ስር የማስቀመጥ ባህል ስላላቸው፣ ሼህ መህሙድ «ምክንያቱ ሰይድና ኸድር በሮዝ ዛፎች አቅራቢያ ስለሚዘዋወሩና ለዱዓችሁ አሚን እንዲሉ ስለሚፈለግ ነው፤ ነገር ግን ዋናው ነገር ዱዓው ከአላህ መሆኑን ማመንና ልብን ማጥራት ነው» ብለዋል። *ከጉባዔውም ከትልቆቹም ያገናኘን! #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

ሰይዲና ኸድር (ኺዝር) ቱርክ መድህ.mp34.18 MB

#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ በአባሳውያን ዘመን የነበረው ታዋቂው ኸሊፋ ሀሩን ረሺድ ለድሆች ገንዘብ ማደል ይወድ ነበር። አንድ ቀን በከተማዋ ያሉ ድሆችን በሙሉ ሰብስቦ ወርቅ ሲያድል፣ አንድ ለየት ያለ ለማኝ ይመጣል። ​ለማኙ ወርቁን ከተቀበለ በኋላ፣ ለሀሩን ረሺድ እንዲህ አለው፦ "አንተ የሰጠኸኝ ወርቅ ለዛሬ ብቻ ነው የሚሆነኝ። እውነተኛ ሀብትና በረከት ከፈለግክ ግን 'የኸድርን ችሮታ' ፈልግ" አለው። ​ንጉሡ ሰይድና ኸድርን ለማግኘትና ያንን በረከት ለመጠየቅ ከፍተኛ ጉጉት አደረበት። እሳቸውን ለማግኘትና የሚያገናኘው ሰው ፍለጋ ብዙ ሞከረ፤ ​ከእለታት አንድ ቀን፣ ንጉሡ በቤተ-መንግሥቱ የአትክልት ስፍራ ውስጥ ብቻውን እያለ፣ አንድ አትክልተኛ የሚመስል ሰው አገኘ። ሰውየው መሬቱን በዱላው ሲነካው፣ የደረቀው መሬት ወዲያውኑ ለምለም ሆኖ ፍራፍሬዎችን አፈራ። ኸሊፋው ያ ሰው ሰይድና ኸድር መሆናቸውን አውቆ በታላቅ ትህትና "ከችሮታህ ስጠኝ" ሲል ተማፀነ። ሰይድና ኸድር ግን እንዲህ አሉት፦ "እውነተኛ ሀብት መሬትን ወደ ወርቅ መቀየር አይደለም። እውነተኛው ሀብት አላህ በሰጠህ ነገር ላይ 'በረከትን' (በረካ) ማድረግ እና በውስጥህ የሚገኘው 'የእርካታ ሀብት' (ቀናዓህ) ነው። ያ እኛ የገነባናው ግንብ ስር የነበረው የወርቅ ሀብትም ቢሆን ለአባታቸው ደግነት ሲባል አላህ ለየቲሞቹ የጠበቀላቸው የችሮታው ምልክት ነው" አሉትና ተሰወሩ። "ያኸድር ለተበደሉት ድረሱ፤ ለተጨነቁት አስደሱ፤ ለሙሪድ ሁሉ እንደ ዝናብ ፍሰሱ።" #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

#ለይለተል_ጁሙኣ ከዚህ አለም ያለፉ ዘመዳሞች፣ የወዳጆችና የሷሊሆች ነፍሳት በጁሙኣ ለሊት በአንድ ታላቅ ጉባዔ "መጅሊስ" ላይ ይሰበሰባሉ። እርስ በእርስ እየተጎበኙ በምድር ላይ የነበራቸውን መልካም ትውውቅና ፍቅር ያድሳሉ። በዚህ ስብስብ ላይ፣ በቅርብ ቀናት ውስጥ ከምድር ወደ በርዘክ ዓለም የተሸጋገሩ አዳዲስ ነፍሳት ካሉ ትልቅ ትኩረት ይሰጣቸዋል። ቀድመው የሞቱት ዘመዶቹ አዲሱን መጪ በመክበብ በምድር ላይ ስላስቀሯቸው ልጆቻቸው፣ የትዳር አጋሮቻቸውና የቅርብ ወዳጆቻቸው ሁኔታ በጥልቀት ይጠይቁታል። አዲሱ መጪ "እገሌ እኮ ሃብታም ሆኗል፣ እገሊትም አግብታለች" እያለ የምድርን ዜና ሲነግራቸው ታላቅ ደስታ ይሆንላቸዋል። ነገር ግን ስለ አንዱ ዘመዳቸው ጠይቀውት "እሱ እኮ ከእኔ በፊት ነው የሞተው" የሚል ምላሽ ከሰጣቸው፣ ነፍሳቱ በእጅጉ ያዝናሉ። "ወደ እኛ አልመጣም ማለት ወደ ሌላኛው (ወደ ቅጣት) መንገድ ወስደውታል" በማለት ስለዚያ ሰው ይከፋሉ፣ ይጸጸታሉ። በጁሙዓ ቀን የሙታን ነፍሳት ወደ ምድራዊው ዓለም፣ በተለይም ወደ ቀድሞ ቤታቸውና ወደ ዘመዶቻቸው በር ላይ በመቆም በሕይወት ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ይመለከታሉ። ቤተሰቦቻቸው በቁርኣን፣ በሶለዋትና ሰደቃ ተጠምደው ካገኟቸው ነፍሳቱ ታላቅ ሰላምና ደስታ ይሰማቸዋል። በተቃራኒው ቤተሰቡ በዱንያ ጨዋታና በዝንጉነት ውስጥ ከሆኑ ነፍሳቱ እያዘኑና "እኛ ካለፍንበት የሞት መንገድ ተማሩ" እያሉ ይመለሳሉ። ኢማም አል-ገዛሊ በታዋቂው "ኢሕያኡ ዑሉሙዲን" በተሰኘው መጽሐፋቸው፦ "ሙታን በሕይወት ያሉ ወዳጆቻቸውን ዱዓና ሶደቃ ልክ ሕያው ሰው ስጦታን እንደሚናፍቀው አጥብቀው ይናፍቃሉ። የጁሙዓ ሌሊት ሲሆን መላእክት የሕያዋንን ዱዓና ምፅዋት በብርሃን ሳህኖች ላይ አድርገው ለሙታኑ ያቀርቡላቸዋል። በዚህ ጊዜ ስጦታ የደረሰው ነፍስ ልክ በምድር ላይ ያለ ሰው በስጦታ እንደሚደሰተው ሁሉ እጅግ በጣም ይደሰታል፤ ጎረቤቶቹ የሆኑት ሌሎች ነፍሳትም እንኳን ደስ አለህ እያሉ ያከብሩታል።" ታላቁ ሸይኽ ሐሰን አል-በስሪ ስለዚሁ ጉዳይ ሲናገሩ፦ "የጁሙዓ ሌሊትና ቀኗ ለአኼራ ሰዎች በዓላቸው ናት። በዚህች ዕለት አላህ ለነፍሳት የሚሰጠው ነጻነትና እርስ በእርስ የመጎብኘት ዕድል በሌላ ቀን አይሰጥም። በምድር ላይ ያላችሁ ሰዎች ሆይ! በሩቅ ሀገር ያለን ዘመዳችሁን በስጦታ እንደምታስቡት ሁሉ፣ በበርዘክ ዓለም ያሉ ወላጆቻችሁንም በዚህች ሌሊት በሶለዋትና በዱዓ አስቧቸው። የእናንተ መዘንጋት ለእነሱ ታላቅ የብቸኝነት ስብራት ነውና።" ታላቁ ዐሪፍ ሱፍያን አሥ-ሠውሪ ደግሞ የጁሙዓን ሌሊት በተመለከተ፦ "አንድ አማኝ ለሞቱት ዘመዶቹ የሚያደርገው ዱዓ፣ በጨለማ ቤት ውስጥ ለተቀመጠ ሰው ፋኖስ ይዞ የመግባት ያህል ነው። ቀብራቸውን ያበራላቸዋል፣ የጠበበውንም ያሰፋላቸዋል። በተለይ በለይለተል ጁሙዓ የሚደረግ ዱዓ መላእክት በቀጥታ ስሙንና የአባቱን ስም ጠርተው 'ይህ ከልጅህ ከእገሌ የተላከልህ ብርሃን ነው' ብለው የሚያስረክቡት ልዩ ክብር ነው።" ታላቁ ዓሊም ኢማም ኢብን አል-ቀይም "ኪታቡ ሩሕ" በተባለው ዝነኛ መጽሐፋቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፦ "ሙታን የጁሙዓን ቀንና ሌሊት በሚገባ ያውቃሉ። እንዲያውም በምድር ላይ ያሉ አዕዋፋትና እንስሳት ሳይቀሩ የጁሙዓ ቀን መቃረቡን አውቀው እንደሚፈሩት ሁሉ፣ የበርዘክ ሰዎችም ይህችን ዕለት በታላቅ ጉጉት ይጠብቋታል። ምክንያቱም በዚች ዕለት ከምድር የሚመጣላቸው መንፈሳዊ ረድኤትና ስጦታ እጅግ የበዛ በመሆኑና ከቀደሙት ወዳጆቻቸው ጋር በሰፊው የሚገናኙባት በመሆኗ ነው።" የአባባ የጁሙኣ ስጦታ اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ! አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ! #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

#አላህን_በመናም_ማነጋገር እዚሁ መንደር በዚህ ጉዳይ ብዙ ሲባል ሰምተናል፤ ለእነርሱ መልስ ሳይሆን እውነታውን በጥቂቱ እንወያያለን። አላህን በህልም ማየት በአቅልም (በአእምሮ) በሸሪዓም የሚቻል መሆኑ የተረጋገጠ ነው። ለዚህም ዋናው መረጃ ነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) “ጌታዬን በላቀና ባማረ መልኩ አየሁት” (ጃሚዐ ቲርሚዚ ቁጥር 3235) ብለዋል። ኢማሙ አህመድና ኢማሙ ጦበራኒይ ይህንን ሀዲስ በተለያየ መንገድ ዘግበውታል። ይህ በጣም ወሳኝ ነጥብ ነው፤ አላህን በህልም ማየት ሲባል ከአላህ ባህሪያት (ጽዱነት) ጋር በሚስማማ መልኩ እንጂ ፍጡራንን በሚመስል መልኩ አይደለም። *አላህ ቅርጽ፣ ቀለም፣ ቦታ ወይም አቅጣጫ የለውም። ስለዚህ በህልም የሚታየው አላህ በባሪያው ልብ ውስጥ የጣለው የባህሪያቱ ነጸብራቅ (ተጀሊ) ነው። ኢማም አል-ገዛሊ “ኢሕያኡ ኡሉሚዲን” በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ እንደሚያብራሩት፣ የሰው ልጅ ልብ እንደ መስታወት ነው። የሰውየው ልብ ከዱንያ ፍቅርና ከወንጀል በጠራ ቁጥር፣ በህልሙ የሚያየው መለኮታዊ መገለጫ (ተጀሊ) ይበልጥ እውነተኛና ንጹህ ይሆናል። አንድ ሰው አላህን በግርማዊነቱ (ጀላል) ወይም በደግነቱና (ጀማል) ሊያየው ይችላል። ታዋቂው ታቢዒይ እና የህልም ፈቺው መሐመድ ኢብኑ ሲሪን አላህን በህልም ማየትን እንደሚከተለው ይፈታሉ፡ *አንድ ሰው አላህን በህልሙ ካየና አላህም ምሕረትን፣ ጀነትን ወይም መልካም ነገርን ቃል ከገባለት፣ ያ ህልም እውነት ነው፤ ሰውየውም ፍጻሜው ያማረ ይሆናል። ኢማም አህመድ ሀንበሊ (ረዐ) አላህን በህልማቸው ከአንድ መቶ ጊዜ በላይ እንዳዩት ይናገራሉ። ሸይኽ አብዱልቃድር አል-ጂላኒ፣ “አል-ፉዩዳት አር-ረባኒያ” በተሰኘው መጽሐፍ ላይ፣ አላህን በህልማቸው አይተው እንደተነጋገሩና አላህም የመንፈሳዊ መንገድ መመሪያዎችን እንደሰጣቸው ተናግረዋል። ታላቁ ቢያዚድ አል በስጧሚ በአንድ ወቅት አላህን በህልማቸው አይተውት “ጌታዬ ሆይ! ወደ አንተ መድረሻው መንገድ ምንድነው?” ብለው ጠየቁት። አላህም “ነፍስህን (ስሜትህን) ትተህ ና፤ ወደ እኔ ትደርሳለህ” እንዳላቸው ይተርካሉ። ታላቁ ዐሪፍ ኢማሙ ሻዚሊይ፣ አላህ በህልምም ሆነ በንቃት ልባቸው ላይ የሚጥለውን መገለጥ (ተጀሊ) በሰፊው ያስተምሩ ነበር። ታላቁ የፊቅህ ሊቅ ኢማም አቡ ሐኒፋ አላህን በህልማቸው አንድ መቶ ጊዜ እንዳዩት ይገልፃሉ። ከባግዳድ ታላላቅ መሻኢኾች አንዱ የሆኑት ሸይኽ ማዕሩፍ ከርኺ ሁልጊዜ በመንፈሳዊ መሳጥ ውስጥ እንደሆኑ ገልፀዋል። ሸይኽ ዙን-ኑን አል-ምስሪ አላህን በመናም አይተው ስለ ልብ ንጽህና እና ስለ እውነተኛ ፍቅር (መሐባ) ያወጉበትን "ሪሳለቱል ቁሸይሪይ" ላይ ተገልፆል። ሸይኽ ሰሪይ አስ-ሰቀጢይ እሳቸውም አላህን በመናም በማየትና መለኮታዊ ተግሣጽና መመሪያዎችን በመቀበል፣ ነፍስን እንዴት መግራት እንደሚቻል ለደቀመዛሙርቶቻቸው ያስተምሩ ነበር። ኢብኑ አረቢ (ሸይኹል አክበር) አላህን በመናም ብቻ ሳይሆን በንቃት (በከሽፍ) ጭምር መለኮታዊ ተጀሊያትን (መገለጦችን) እንደሚያዩ በኪታቦቻቸው ላይ አስፍረዋል። ሸይኽ አሕመድ አል-ፋሩቂ አስ-ሲርሃንዲ በህንድ የነቅሸበንዲያ ጠሪቃ ታላቅ መሪ፤ በመናምና በከሽፍ መለኮታዊ ባህሪያትን (ተጀሊያት) በማየት ረገድ እጅግ ጥልቅ የሆኑ ማብራሪያዎችን “መክቱባት” በተሰኘው ታዋቂ ኪታባቸው ላይ አስፍረዋል። ሸይኽ ኒዛሙዲን አውሊያእ (ደህሊ - ህንድ)፦ የቺሽቲያ ጠሪቃ መሪ ሲሆኑ፣ በመናማቸው አላህ ዘንድ ትልቅ መቃም (ደረጃ) እንደተሰጣቸውና የልባቸው መስታወት መለኮታዊ ምስጢራትን ለማየት እንደበቃ ተናግረዋል። አዚዝ ማሕሙድ ሁዳዪ፦ በኢስታንቡል የሚገኙ የጀልወቲያ ጠሪቃ መስራችና ታላቅ ወሊይ ናቸው። በህልማቸው መለኮታዊ መመሪያዎችንና የምስራቾችን በመቀበል፣ በዘመኑ ለነበሩት የኦቶማን ሱልጣኖች ጭምር መንፈሳዊ መካሪ ነበሩ። ኢስማዒል ሐቂ አል-ቡርሰዊ፦ “ሩሑል በያን” የተሰኘውን ታዋቂ ተፍሲር የጻፉ ታላቅ ሊቅ ናቸው። ቁርአንን በሱፊያ እይታ ሲተረጉሙ፣ ራሳቸው በመናምና በከሽፍ ያዩዋቸውን መለኮታዊ ምስጢሮችና ተጀሊያቶች እያጣቀሱ ነው። ሸይኽ ሐሰን ወድ ሐሱነህ፦ በመናማቸው ከመለኮታዊው ዓለም ጋር የነበራቸው ትስስርና መለኮታዊ ግርማን የማየት ተሞክሮአቸው በሱዳን የሱፊያ ታሪክ መጽሐፍ (“ጦበቃት ወድ ዶይፍ”) ላይ ጠቅሰዋል። ሰይድ ቡሽራ ሰይዱል ባዕ(ገቲይ) ከአላህ በመናም ስላገኙት መገለጥና ከሽፍ አብራርተዋል። ሱልጣኑል አውሊያ የቁባ አባ ሰይድ ቡሽራ አብሬትይ ባዑ ሳኒ በየጊዜው ከጌታቸው ጋር ስለነበራቸው መገለጥ ገልፀዋል። ሸይኻችን ሰይድ አባራሙዝ አብሬትይ ስለዚሁ ነገር በሚስባሀቸው ላይ እንዲህ ሲሉ ይናገራሉ። "አላህ ከባሮቹም የፈለገውን ሰው በዚህች ዓለም (ዱንያ) ያለምንም መዘግየትና መቀደም ዛቱን ይገልጣል።" #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

Repost from N/a
#አላህን_በመናም_ማነጋገር እዚሁ መንደር በዚህ ጉዳይ ብዙ ሲባል ሰምተናል፤ ለእነርሱ መልስ ሳይሆን እውነታውን በጥቂቱ እንወያያለን። አላህን በህልም ማየት በአቅልም (በአእምሮ) በሸሪዓም የሚቻል መሆኑ የተረጋገጠ ነው። ለዚህም ዋናው መረጃ ነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) “ጌታዬን በላቀና ባማረ መልኩ አየሁት” (ጃሚዐ ቲርሚዚ ቁጥር 3235) ብለዋል። ኢማሙ አህመድና ኢማሙ ጦበራኒይ ይህንን ሀዲስ በተለያየ መንገድ ዘግበውታል። ይህ በጣም ወሳኝ ነጥብ ነው፤ አላህን በህልም ማየት ሲባል ከአላህ ባህሪያት (ጽዱነት) ጋር በሚስማማ መልኩ እንጂ ፍጡራንን በሚመስል መልኩ አይደለም። *አላህ ቅርጽ፣ ቀለም፣ ቦታ ወይም አቅጣጫ የለውም። ስለዚህ በህልም የሚታየው አላህ በባሪያው ልብ ውስጥ የጣለው የባህሪያቱ ነጸብራቅ (ተጀሊ) ነው። ኢማም አል-ገዛሊ “ኢሕያኡ ኡሉሚዲን” በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ እንደሚያብራሩት፣ የሰው ልጅ ልብ እንደ መስታወት ነው። የሰውየው ልብ ከዱንያ ፍቅርና ከወንጀል በጠራ ቁጥር፣ በህልሙ የሚያየው መለኮታዊ መገለጫ (ተጀሊ) ይበልጥ እውነተኛና ንጹህ ይሆናል። አንድ ሰው አላህን በግርማዊነቱ (ጀላል) ወይም በደግነቱና (ጀማል) ሊያየው ይችላል። ታዋቂው ታቢዒይ እና የህልም ፈቺው መሐመድ ኢብኑ ሲሪን አላህን በህልም ማየትን እንደሚከተለው ይፈታሉ፡ *አንድ ሰው አላህን በህልሙ ካየና አላህም ምሕረትን፣ ጀነትን ወይም መልካም ነገርን ቃል ከገባለት፣ ያ ህልም እውነት ነው፤ ሰውየውም ፍጻሜው ያማረ ይሆናል። ኢማም አህመድ ሀንበሊ (ረዐ) አላህን በህልማቸው ከአንድ መቶ ጊዜ በላይ እንዳዩት ይናገራሉ። ሸይኽ አብዱልቃድር አል-ጂላኒ፣ “አል-ፉዩዳት አር-ረባኒያ” በተሰኘው መጽሐፍ ላይ፣ አላህን በህልማቸው አይተው እንደተነጋገሩና አላህም የመንፈሳዊ መንገድ መመሪያዎችን እንደሰጣቸው ተናግረዋል። ታላቁ ቢያዚድ አል በስጧሚ በአንድ ወቅት አላህን በህልማቸው አይተውት “ጌታዬ ሆይ! ወደ አንተ መድረሻው መንገድ ምንድነው?” ብለው ጠየቁት። አላህም “ነፍስህን (ስሜትህን) ትተህ ና፤ ወደ እኔ ትደርሳለህ” እንዳላቸው ይተርካሉ። ታላቁ ዐሪፍ ኢማሙ ሻዚሊይ፣ አላህ በህልምም ሆነ በንቃት ልባቸው ላይ የሚጥለውን መገለጥ (ተጀሊ) በሰፊው ያስተምሩ ነበር። ታላቁ የፊቅህ ሊቅ ኢማም አቡ ሐኒፋ አላህን በህልማቸው አንድ መቶ ጊዜ እንዳዩት ይገልፃሉ። ከባግዳድ ታላላቅ መሻኢኾች አንዱ የሆኑት ሸይኽ ማዕሩፍ ከርኺ ሁልጊዜ በመንፈሳዊ መሳጥ ውስጥ እንደሆኑ ገልፀዋል። ሸይኽ ዙን-ኑን አል-ምስሪ አላህን በመናም አይተው ስለ ልብ ንጽህና እና ስለ እውነተኛ ፍቅር (መሐባ) ያወጉበትን "ሪሳለቱል ቁሸይሪይ" ላይ ተገልፆል። ሸይኽ ሰሪይ አስ-ሰቀጢይ እሳቸውም አላህን በመናም በማየትና መለኮታዊ ተግሣጽና መመሪያዎችን በመቀበል፣ ነፍስን እንዴት መግራት እንደሚቻል ለደቀመዛሙርቶቻቸው ያስተምሩ ነበር። ኢብኑ አረቢ (ሸይኹል አክበር) አላህን በመናም ብቻ ሳይሆን በንቃት (በከሽፍ) ጭምር መለኮታዊ ተጀሊያትን (መገለጦችን) እንደሚያዩ በኪታቦቻቸው ላይ አስፍረዋል። ሸይኽ አሕመድ አል-ፋሩቂ አስ-ሲርሃንዲ በህንድ የነቅሸበንዲያ ጠሪቃ ታላቅ መሪ፤ በመናምና በከሽፍ መለኮታዊ ባህሪያትን (ተጀሊያት) በማየት ረገድ እጅግ ጥልቅ የሆኑ ማብራሪያዎችን “መክቱባት” በተሰኘው ታዋቂ ኪታባቸው ላይ አስፍረዋል። ሸይኽ ኒዛሙዲን አውሊያእ (ደህሊ - ህንድ)፦ የቺሽቲያ ጠሪቃ መሪ ሲሆኑ፣ በመናማቸው አላህ ዘንድ ትልቅ መቃም (ደረጃ) እንደተሰጣቸውና የልባቸው መስታወት መለኮታዊ ምስጢራትን ለማየት እንደበቃ ተናግረዋል። አዚዝ ማሕሙድ ሁዳዪ፦ በኢስታንቡል የሚገኙ የጀልወቲያ ጠሪቃ መስራችና ታላቅ ወሊይ ናቸው። በህልማቸው መለኮታዊ መመሪያዎችንና የምስራቾችን በመቀበል፣ በዘመኑ ለነበሩት የኦቶማን ሱልጣኖች ጭምር መንፈሳዊ መካሪ ነበሩ። ኢስማዒል ሐቂ አል-ቡርሰዊ፦ “ሩሑል በያን” የተሰኘውን ታዋቂ ተፍሲር የጻፉ ታላቅ ሊቅ ናቸው። ቁርአንን በሱፊያ እይታ ሲተረጉሙ፣ ራሳቸው በመናምና በከሽፍ ያዩዋቸውን መለኮታዊ ምስጢሮችና ተጀሊያቶች እያጣቀሱ ነው። ሸይኽ ሐሰን ወድ ሐሱነህ፦ በመናማቸው ከመለኮታዊው ዓለም ጋር የነበራቸው ትስስርና መለኮታዊ ግርማን የማየት ተሞክሮአቸው በሱዳን የሱፊያ ታሪክ መጽሐፍ (“ጦበቃት ወድ ዶይፍ”) ላይ ጠቅሰዋል። ሰይድ ቡሽራ ሰይዱል ባዕ(ገቲይ) ከአላህ በመናም ስላገኙት መገለጥና ከሽፍ አብራርተዋል። ሱልጣኑል አውሊያ የቁባ አባ ሰይድ ቡሽራ አብሬትይ ባዑ ሳኒ በየጊዜው ከጌታቸው ጋር ስለነበራቸው መገለጥ ገልፀዋል። ሸይኻችን ሰይድ አባራሙዝ አብሬትይ ስለዚሁ ነገር በሚስባሀቸው ላይ እንዲህ ሲሉ ይናገራሉ። "አላህ ከባሮቹም የፈለገውን ሰው በዚህች ዓለም (ዱንያ) ያለምንም መዘግየትና መቀደም ዛቱን ይገልጣል።" #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

#መገርገቢያ   በአንድ መንደር ውስጥ የሚኖር፣ ኑሮው እጅግ የጠበበበት ግን ደግሞ በአብሬቶች ፍቅር የሰከረ አንድ አናፂ ነበር። ይህ ሰው ምንም እንኳን ድሃ ቢሆንም፣ በየሳምንቱ ማክሰኞ ሲመጣ ያለችውን ጥቂት ሳንቲም ሰብስቦ ለቤተሰቡና ለጎረቤቶቹ "ይህ ለሼሆች ክብር ነው" በማለት ሰደቃ ያደርግ ነበር።   አንድ ቀን ግን ሁኔታዎች ተቀየሩ። አናፂው የሚሰራው ስራ አጣ፣ ቤቱ ውስጥ የሚበላ ነገር ጭራሽ ጠፋ። የመገርገብያ ቀን ደረሰ፤ ነገር ግን ለቤተሰቡም ሆነ ለሰደቃው የሚሆን ምንም ነገር አልነበረውም። በጣም አዘነ፣ ልቡ ተሰበረ። "ነገ እንዴት የለመድኩትን የፍቅር ግብዣ ላደርግ ነው?" ብሎ ተከዘ።     አናፂው ወደ መስጊድ ሄዶ ዒሻ ሰግዶ ሲመለስ፣ በመንገድ ላይ አንድ የሚያብረቀርቅ ድንጋይ አገኘ። ወርቅ መሰለውና ደስ ብሎት ወደ ቤት ይዞት ሄደ። ለባለቤቱ ሰጣትና "አላህ ለመገርገብያ በረከት የላከው ነው፣ ነገ ሸጠን ለቤተሰባችንም ለዱኣችንም የሚሆን እናደርጋለን" አላት።     በዛው ለሊት አናፂው በህልሙ ሼሆችን ሰይድ አባራሙዝን ያያል፤ ፈገግ ብለው እንዲህ አሉት፡ "አንተ ስለ እኔ ስትል የለመድከውን ኸይር ስራ አልተውክም፣ አላህም ካልጠበቅከው ቦታ ሰጥቶሃል" አሉት። አናፂው ሲነቃ ድንጋዩ በእውነትም ውድ የሆነ ጌጥ ሆኖ አገኘው። ነገር ግን ትልቁ ተአምር ከዚያ ቀን በኋላ ቤቱ በበረካ ተሞላ፤ ስራም በየቦታው እየመጣለት የዛ አካባቢ ትልቅ ባለሀብት ሆነ። #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier

ኪብሪቱል አሕመር! pdf የዙልሂጃ ስጦታ! @abduftsemier

ኪብሪቱል_አሕመር!_የአባባ_የሰለዋት_ኪታብ!_አብዱ_ኤምሬ_1.pdf152.95 MB

ኪብሪተል አሕመር! የዙልሂጃ ስጦታ! @abduftsemier

#አስሩ_ቀናት ​ነቢያችን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በዙል ሂጃህ አስር ቀናት ውስጥ የሚሰሩ መልካም ስራዎች በሌላ በማንኛውም ጊዜ ከሚሰሩ ስራዎች ይልቅ በአላህ ዘንድ ይበልጥ የተወደዱ መሆናቸውን አስተምረዋል። ​ሰሃባዎችም፦ "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን ?" ብለው ጠየቁ። ነቢያችንም (ሰ.ዐ.ወ)፦ "አዎ፣ በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሃድም ቢሆን አይበልጠውም፤ በነፍሱና በገንዘቡ ወጥቶ (ተዋግቶ) እዚያው የቀረ ሰው ሲቀር።" (ቡኻሪ) ታላቁ የነቅሸበንዲያ መሪ መውላና ሼህ ናዚም አል-ሐቃኒ፣ ሀጅ ሁለት አይነት ነው፤ አንደኛው የአካል ሀጅ ሲሆን፣ ሁለተኛው እና ጥልቁ  የልብ ሀጅ ነው። “አካላቸው መካ የደረሱት ካዕባን ዞሩ፤ ልባቸው ወደ አላህ የቀረበው ግን የዐሪፎች ሀጅ ነው፤ ምክንያቱም እነሱ የካዕባን ጌታ በልባቸው ይዞራሉ” ይላሉ። አሪፎቹ በቁርአን የተማለባቸውን አስሩን የዙልሂጃህ ቀናት (ሊያሊን ዐሽር) እንደ ታላቅ የውይይትና የፍቅር (ሱሕባ) ወቅት ያዩታል።  በእነዚህ ቀናት ምላስ በዚክር (በላኢላሀ ኢለላህ - ተህሊል) መርጠብ አለበት። ታላቁ ጋውስ ሼህ አብዱልቃድር አል-ጂላኒ በኪታባቸው ላይ እንዳሰፈሩት፣ በእነዚህ አስር ቀናት ውስጥ የሚደረግ እያንዳንዱ መልካም ስራ፣ ዚክር እና ፆም የሰውን ልጅ መንፈሳዊ ማዕረግ (መቃም) በፍጥነት ያሳድጋል። ይህ ጊዜ አላህ ለባሮቹ የከፈተው ልዩ የፍቅር ማዕድ ነው። ሼሀችን የወንጀላችን ሳሙና የሆኑት አባራሙዝ በዐረፋ ቀን ሲቆሙ፣ ፍፁም ጸጥታ ውስጥ ይሰምጡ ነበር። ለነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እና ለአላህ በነበራቸው ክብር የተነሳ ጨርሶ ሳይንቀሳቀሱ በዝምታ (አደብ) ይቆሙ ነበር። በዐረፋ ቀን መላው ዓለም ነጭ ለብሶ ሲያለቅስ፣ የሰውን ልጅ ምስኪንነት እና የአላህን ፍፁም ጌትነት (ሩቡቢያህ) ያስተውላሉ። ታቢዒዩ ሰዒድ ኢብኑ ጁበይር፦ የዙልሂጃህ አስር ቀናት ከገቡ፣ ማንም ሰው ሊወዳደረው በማይችል መልኩ ሌሊቱን በሶላት፣ ቀኑን በፆም ይተጉ ነበር። "በእነዚህ አስር ቀናት መብራታችሁን አታጥፉ (ሌሊቱን በዒባዳ አሳልፉ)" ይሉ ነበር። ኢማም አል-ገዛሊ በታላቁ ኪታባቸው "ኢሕያኡ ዑሉሙ ዲን" ላይ ስለ ዙልሂጃህ አስር ቀናት ስነ-ስርዓት በጥልቀት አብራርተዋል። በእነዚህ ቀናት የሚደረግ ፆም እና ሰደቃ የተለየ መንፈሳዊ ብርሃን አለው። ገዛሊ ሰዎችን ሲመክሩ፦ "እነዚህ ቀናት የአላህ ልዩ ስጦታዎች የሚታደሉባቸው በመሆናቸው፣ ልባችሁን ከዱንያ ጭንቀት አፅድታችሁ ተቀበሏቸው።" የሱፊዮቹ ሱልጣን ባየዚድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀጅ ለማድረግ መካ በደረሱ ጊዜ እንዲህ አሉ፦ "መጀመሪያ መካ ስደርስ ካዕባውን ብቻ አየሁ። ሁለተኛ ጊዜ ስሄድ የካዕባውን ጌታ አየሁ። ሶስተኛ ጊዜ ስሄድ ግን ካዕባውም ሆነ ጌታው ሳይሆኑ ሁሉም ነገር በእርሱ ፍቅር ውስጥ ጠፍቶ (ፈናእ ሆኖ) አየሁ።" ሰይዱ ጧዒፋ ኢማም ጁነይድ እንዲህ ይላሉ፦ በእነዚህ ቀናት (በተለይ በዐረፋ ቀን) ባሪያው በአላህ ፊት ሲቆም ፍፁም በሆነ ማነስ፣ ምስኪንነት እና ከስህተቱ ለመታረም እንደሚፈልግ ባሪያ መሆን አለበት። በዙልሂጃህ 10ኛው ቀን (በዒድ) እንስሳ ማረድ በራሱ ትልቅ ሚስጥር አለው። ታላቁ ገጣሚ መውላና ጀላሉዲን ሩሚ እንዲህ ይላልሉ-    "የእንስሳውን ጉሮሮ በካራ ከመቁረጥህ በፊት፣ በውስጥህ ያለውን የእኔነት፣ የትዕቢት፣ የቀናተኝነት እና የስስት ነፍስህን እረደው። እውነተኛው መስዋዕትነት ይሄ ነው!" *አሏሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ አሽረፈል ሙርሰሊን! #አባ_ደዋም @abduftsemier @abduftsemier