Abdu & Hasu
الذهاب إلى القناة على Telegram
Abdulhak & Hasenet <የኢቅራእ ቢስሚ ረቢከ /አንብብ በጌታህ ስም/ ትውልዶች እንጂ ፣ የኢቅራእ /የአንብብ / ትውልዶች አይደለንም።> አላህ ያወቅነውን የምናሳውቅ ፣ ባወቅነው ደግሞ የምንጠቀም ያድርገን። አሚን!! For any comment ⇄ @ABDU_EMRE
إظهار المزيد4 467
المشتركون
-1024 ساعات
-447 أيام
-12730 أيام
أرشيف المشاركات
4 467
#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
ታላቁ የፋርስ ገጣሚ ሃፊዝ ሺራዚ ገና ወጣት ሳለ በሺራዝ ከተማ ውስጥ በአንድ ዳቦ ቤት ውስጥ ሊጥ አብኪ እና ጋጋሪ ሆኖ ይሰራ ነበር። ከእለታት በአንዱ ቀን በአቅራቢያው ለሚገኝ አንድ ባለጸጋ መኖሪያ ቤት ዳቦ ለማድረስ በሄደበት ወቅት፣ "ሻካ-ነባት" የምትባል እጅግ ውብ የሆነች የባለጸጋውን ልጅ በአጋጣሚ ያያታል። ሃፊዝ በመጀመሪያ እይታ በእሷ ፍቅር እብድ ሆነ። ነገር ግን እሷ የሀብታም ልጅ፣ እሱ ደግሞ ደሃ በመሆኑ እሷን ማግኘት ፍጹም የማይታሰብ ህልም ነበር።
በሺራዝ ከተማ ውስጥ አንድ የታወቀ እምነት ነበር፤ እሱም፡- "አንድ ሰው 'ባባ ኩሂ' በተባለው ተራራ ላይ ለ40 ተከታታይ ቀናትና ሌሊቶች ጸልዮ ካደረ፣ ሰይድና ኸድር ይገለጥለታል። ሃፊዝ ፍቅሩን ለማግኘት ሲል ይህንን ከባድ ተጋድሎ ለመጀመር ወሰነ። በየቀኑ በዳቦ ቤት ውስጥ ስራውን ይሰራና፣ ሌሊት ሌሊት ወደ ባባ ኩሂ ተራራ እየወጣ እስከ ንጋት ድረስ በጸሎትና በለቅሶ ያሳልፍ ነበር። ይህንን ለ39 ቀናት በትጋት ቀጠለ። በ40ኛው ምሽት ላይ ሃፊዝ በከፍተኛ ድካም እና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆኖ ሳለ፣ በድንገት ተራራው በብርሃን ተሞላ። በአይን ሊታይ የማይችል ውበት ያለው፣ አረንጓዴ የለበሰና ረጅም ነጭ ፂም ያለው ሽማግሌ ከፊቱ ቆመ። ኸድርም ወደ ሃፊዝ ቀረብ ብለው በደግነት፡ "የልብህን መሻት አውቃለሁ፤ ለአርባ ቀናት ያሳየኸው ታማኝነትና ጽናት ተቀባይነት አግኝቷል። በዚህ ጊዜ ኸድር ለሃፊዝ መለኮታዊ የሆነ የብርሃን ጽዋ (አንዳንዶች የጀነት ወይን ይሉታል) አቀረበለት። ሃፊዝ ከጽዋው በተጎነጨ ጊዜ በአእምሮውና በልቡ ውስጥ የነበረው ምድራዊ መጋረጃ ተቀደደ።
የኸድርን መለኮታዊ መጠጥ እንደቀመሰ፣ የሃፊዝ ልብ በአንድ ጊዜ ተቀየረ። የ"ሻካ-ነባት" ምድራዊ ውበት፣ ከመለኮታዊውና ከፈጣሪ ፍቅር ውበት ጋር ሲነጻጸር በጣም ኢምንት ሆና ታየችው። "እኔ የምፈልገው ይህንን የፈጣሪን ፍቅር፣ የዓለማትን ምስጢርና ጥበብን ነው" አሉ ሺራዚ። ኸድርም በሃፊዝ ምርጫ እጅግ ተደስተው፡ "የማይጠፋ የጥበብና የቅኔ ምንጭ ተሰጥቶሃል፤ ከአሁን በኋላ አንተ 'ሊሳን አል-ገይብ' (የስውሩ ዓለም አንደበት) ተብለህ ትጠራለህ" ብለው ዱኣ አደረጉለት።
*ሃፊዝ ከተራራው ወርዶ ወደ ሺራዝ ከተማ ሲመለስ፣ እስከዚያ ቀን ድረስ አንድም መስመር ግጥም መጻፍ የማይችለው ወጣት፣ በአንደበቱ እጅግ ጥልቅና ረቂቅ የሆኑ መለኮታዊ ግጥሞችን ማዝነብ ጀመረ። የሺራዝ ሊቃውንት ሳይቀሩ በእሱ ግጥሞች ጥልቀት ተደነቁ።
*ሻካ-ነባት ራሷ በኋላ ላይ በሃፊዝ መንፈሳዊ ታላቅነትና ውበት ተማርካ ወደ እሱ መጣች አገባት።
ሀፊዝ በዲቫኑ (የግጥም ስብስቡ) ላይ ስለ ኸድር እና ስለ "ህይወት ውሃ" እየጠቀሰ፣ ያንን የለውጥ ምሽት በምስጢራዊ ቃላት ያወሳል።
ታላቁ የፋርስ ገጣሚ ፈሪዱዲን አጣር የከተማዋ ትልቅ ፋርማሲስት
የመድኃኒትና የሽቶ ቀማሚ ሀብታም ነጋዴ ነበር። አጣር በሱቁ ውስጥ ተቀምጦ ሳለ አንድ ድሃ ደረሳ (መንፈሳዊ መንገደኛ) ወደ ሱቁ ይመጣል። ድሃው ሰው የአጣርን ሀብትና በምድራዊ ስራ መጠመድ አይቶ በጥልቅ ትንፋሽ ተከዘ። አጣርም ተናዶ "ለምን አትሄድም?" አለው።
ድሃው ሰውም፡ "እኔማ እጄ ላይ ካለችው ከዚች የምግብ ሳህን በስተቀር ምንም የለኝም፤ ከዚህ ዓለም መውጣት (መሞት) ለእኔ በጣም ቀላል ነው። አንተ ግን በዚህ ሁሉ ሀብትና ንብረት ተከበህ እንዴት ልትሞት እንደምትችል ሳስበው አዝንልሃል" አለው።
አጣርም ፡ "ለመሆኑ አንተ ከዚህ ዓለም እንዴት ነው የምትወጣው?" አለው። ድሃው ደረሳም ወዲያውኑ የያዛትን ሳህን ተንተርሶ መሬት ላይ ተኛ፣ "አላህ!" አለና በዚያው ቅጽበት ነፍሱ ወጣች።
አጣር ምድራዊ ህይወቱን ትቶ ወደ መንፈሳዊው ዓለም ከገባ በኋላ፣ ለዓመታት በጥልቅ ጸሎትና ተጋድሎ ውስጥ አሳለፈ። በሰይዲና ኸድር መሪነትም ከመለኮታዊው ደጃፍ ደረሰ።
አጣር በግጥሞቹ ውስጥ ስለ ሰይዲ ኸድር ሲያነሳ እንዲህ ይላል፡- "የኸድርን መንገድ የተከተለ ሰው፣ መጀመሪያ ራሱን ማጥፋት (ከምድራዊ ፍላጎት መራቅ) አለበት። ያኔ የህይወት ውሃን ከምንጩ ይጠጣል።"
*አላሁመ ሷሊ አላ ሰይድና ወሀቢቢና ሙሐመድ ፤ ወአላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#ለይለተል_ጁሙኣ
ከመውላና ጀላሉዲን ሩሚ ድንቅ ድንቅ የመስነቪ ታሪኮች መካከል፣
አንድ ጁሙኣ ለይል ነቢዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) በበረሃ ውስጥ ሲጓዙ፣ አንድ ምስኪን እረኛ ብቻውን ቆሞ ወደ አላህ ሲጸልይ ተመለከቱት። እረኛው ልቡ በፈጣሪ ፍቅር ተነክቶ፣ እጆቹን ወደ ሰማይ ዘርግቶ ይማጸን ነበር፦
"አምላኬ ሆይ! የት ነህ? ልምጣና ልብስህን ልስፋልህ? ፀጉርህን ላበጥርልህ? ጫማህን ልጠገንልህ?... ጌታዬ ሆይ! ብትታመም እያስታመምኩህ እግርህን ባሸሁልህ... ማታ ማታ የሚጠጣ ወተት አቅርቤልህ ብርድ እንዳይመታህ ብርድ ልብስ ባለበስኩህ... አንተ የኔ ማር፣ የኔ ውድ ጌታ!"
ነቢዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) የእረኛውን ንግግር ሲሰሙ በጣም ደነገጡ። ወደ እረኛው ጠጋ አሉና በቁጣ እንዲህ አሉት፦ "አንተ ሰው! ይህ የምትናገረው ነገር ምንድነው? አላህ እኮ ልብስ፣ ጫማ፣ ወተትም ሆነ እንክብካቤ አያስፈልገውም! እርሱ ከምንም ነገር የተፈጠረ አይደለም፣ አይታመምም፣ አይራብም። ይህ የምትናገረው ንግግር ክህደት (ኩፍር) ነው! አሁኑኑ ዝም በል!"
ምስኪኑ እረኛ የነቢዩ ሙሳን ንግግር ሲሰማ ልቡ በድንጋጤና በሀዘን ተሰበረ። ራሱን ዝቅ አድርጎ፣ እያለቀሰና እየተቆጨ ዋሽንቱንና በጎቹን ትቶ ወደ በረሃው እያለቀሰ ሮጦ ጠፋ።
እረኛው እንደሄደ፣ አላህ (ሱ.ወ) ለነቢዩ ሙሳ በወህይ (ራዕይ) እንዲህ አላቸው፦
"ሙሴ ሆይ! እረኛውን ባሪያዬን ከእኔ ለምን አራቅኸው? አንተን ወደ ምድር የላኩህ ሰዎችን ወደ እኔ እንድታቀርብልኝ ነው ወይስ ባሮቼን ከእኔ እንድታርቅብኝ? እኔ ወደ ውጫዊው ንግግርና ቃላት አልመለከትም። እኔ የምመለከተው ወደ ልብና ወደ ውስጣዊው ቅንነት ነው። ያ እረኛ ቃላቶቹ ስህተት ቢኖርባቸውም፣ ልቡ ግን በንጹህ ፍቅር ተሞልቶ ነበር። አንተ ውጫዊውን ስርዓት ተመልክተህ የልቡን ፍም አጠፋኸው!"
ነቢዩ ሙሳ (ዐ.ሰ) ይህንን መለኮታዊ ወቀሳ ሲሰሙ እጅግ ተጸጸቱ። ወዲያውኑ እረኛውን ፍለጋ ወደ በረሃው ሮጡ። በረሃውን አቋርጠው፣ አቧራ ለብሰው ሲፈልጉት ቆይተው በመጨረሻም እረኛውን በረሃ ውስጥ በለቅሶ ተደፍቶ አገኙት።
ሙሳም ወደ እረኛው ቀረቡና፦ "የምስራች! አላህ ወቀሰኝ። ምንም ሳትጨነቅ ልብህ በፈቀደው፣ በፍቅርህ በለመደው ቋንቋና ቃላት ፈጣሪህን መማጸን ትችላለህ። ያንተ ንጹህ ልብ በአላህ ዘንድ ተቀባይነት አለው" አሉት።
እረኛውም ግንባሩን ቀና አድርጎ ፈገግ አለና እንዲህ አለ፦ "ሙሳ ሆይ! ያንተ ወቀሳ መጀመሪያ ልቤን ሰብሮት ነበር፤ ነገር ግን ያ ስብራት ወደ ጥልቅ መንፈሳዊ ደረጃ አሻገረኝ። አሁን ከቃላት ባለፈ የፈጣሪዬን ብርሃን በልቤ ማየት ጀምሬያለሁ" አላቸው።
መውላና ሩሚ በመቀጠል እንዲህ ይላሉ፦ "አላህ ዘንድ ዋጋ ያለው የተሽቆጠቆጡ ቃላት መደርደር ሳይሆን፣ የተሰበረና በቅንነት የተሞላ ልብ ነው።"
በጁሙኣ የአባባ ሰለዋት ስጦታ
<اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مَركَز الأَنْبِيَاءُ وَالأَوْلِيَاءُ ، وَآلِهِ وَصَحْبِهِ أُولِي الْفَضْلِ وَالأَتْقِيَاءِ.>
*"አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ መርከዚል አንቢያዕ ወል አውሊያዕ፤ ወአሊሂ ወሷህቢሂ ኡሊል ፈድሊ ወል አትቂያዕ።"
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#የአእዋፋት_ጉባኤ
ፈሪዱዲን አታር በ12ኛው ክፍለ ዘመን የኖረ ታላቅ የፋርስ (ኢራን) ሱፊ ገጣሚ እና ፈላስፋ ነው። የእሱ ድንቅ ስራ የሆነው "የአእዋፋት ጉባኤ" (መናጢቀ ጠያር) በዓለም ስነ-ጽሁፍ ውስጥ እጅግ በጣም ጥልቅ እና ውብ ከሆኑ መንፈሳዊ ምሳሌያዊ ታሪኮች ነው።
"አንድ ቀን በዓለም ላይ ያሉ ወፎች ሁሉ በአንድ ላይ ተሰበሰቡ። ንጉስ የሌለው ህዝብ ሰላምና ስርዓት አይኖረውም በሚል መሪ የሚሆን ንጉስ መፈለግ እንዳለባቸው ተስማሙ። በዚህ ጊዜ ሁድድ ወደ መድረክ ወጣች፤ በጥበቧ የምትታወቅ፣ የንጉስ ሱለይማን መልእክተኛ የነበረች እና የዓለማትን ምስጢር የተረዳች ወፍ ናት። እንዲህ አለች፦
"እኔ ንጉሳችሁን አውቀዋለሁ፤ ስሙም ሲሙርግ ይባላል። የሚኖረውም ከዓለም ዳርቻ ባለ፣ እሳታማና አስፈሪ በሆነው በቃፍ ተራራ ላይ ነው። እሱ ለእኛ በጣም ቅርብ ነው፣ እኛ ግን ከእሱ በጣም የራቅን ነን። እሱን ለማግኘት ግን የሞትና የህይወትን መንገድ ማለፍ አለብን!"
ሁድሁድ የጉዞውን አስቸጋሪነት ስትገልጽላቸው፣ እያንዳንዱ ወፍ የራሱን ምድራዊ ምቾትና ድክመት እያነሳ ማምለጫ ሰበብ መደርደር ጀመረ።
*የለሊት ወፍ፦ "እኔ የሮዝ (የጽጌረዳ) አበባ ፍቅረኛ ነኝ። ያለ እሷ ውበት መኖር አልችልም። ጽጌረዳን ጥዬ ወደዚያ አስፈሪ ጉዞ አልሄድም" አለች።
*በቀቀን፦ "እኔ ለዘላለም የሚያኖርኝን የህይወት ውሃ (የእድሜ ማራዘሚያ) ነው የምፈልገው። ይህ ውብ ቤቴ ይበቃኛል፤ ረጅሙን መንገድ አልፈልግም" አለች።
* ፒኮክ፦ "እኔ ቀድሞ የጀነት ወፍ ነበርኩ። በሰይጣን መታለሌ ምክንያት ነው ወደ ምድር የተጣልኩት። እኔ የምፈልገው ወደ ጀነት መመለስ ብቻ ነው፤ የሲሙርግ ንጉስነት አያሳስበኝም" አለች።
* ዳክዬ፦ "እኔ ያለ ውሃ መኖር አልችልም። ውሃ ህይወቴ፣ መስገጃዬና መታጠቢያዬ ነው። በየብስ ላይ ረጅም መንገድ መጓዝ አልችልም" አለች።
*ጉጉት፦ "እኔ ሰዎች የሚኖሩበትን ቦታ አልወድም። የምኖረው በፈራረሱ ቤቶች ውስጥ ውድ ሀብት ፍለጋ ነው። ይህንን ፍለጋዬን ትቼ አልመጣም" አለች።
በመጨረሻም በሁድሁድ ንግግር የተነሳሱት በሺዎች የሚቆጠሩ ወፎች ክንፋቸውን ዘርግተው ወደ ቃፍ ተራራ በረሩ። ነገር ግን መንገዱ እጅግ አስፈሪ ነበር። በየመንገዱ ረሃብ፣ ጥም፣ ሙቀትና ቅዝቃዜ አደቀቃቸው። ከሰባቱ ሸለቆዎች ሲያልፉ፦
1)የፍለጋ ሸለቆ: ምኞትንና ቁሳዊ ፍላጎትን ትቶ እውነትን በጽናት መፈለግ መጀመር።
2)የፍቅር ሸለቆ: አእምሮንና አመክንዮን ወደ ጎን አድርጎ በፍቅር መቃጠል።
3)የእውቀት ሸለቆ: ዓለምን በውጫዊ መልክዋ ሳይሆን በውስጣዊ ምስጢሯ መረዳት።
4)የነጻነት/የመላቀቅ ሸለቆ: ከምድራዊ ትስስር እና ከዓለማዊ ስጋቶች ሙሉ በሙሉ መላቀቅ።
5)የአንድነት ሸለቆ: በፍጥረት ሁሉ ውስጥ ያለውን መለኮታዊ አንድነት ማየት፤ "እኔ" እና "አንተ" የሚለው መለያየት መጥፋቱ።
6)በ"የድንቅ ሸለቆ"፦በመለኮታዊው ውበት ተደንቆ ግራ መጋባትና ራስን መርሳት። በዚ ሸለቆ ላይ አእምሯቸውን ስተው መንገድ የሳቱ ብዙ ነበሩ።
በየሸለቆው ፍርሃት ሲጠናባቸው፣ አንዳንዶቹ ወደ ኋላ ተመለሱ፤ ሌሎቹ በድካም ሞቱ፤ የተወሰኑት ደግሞ በበረሃው አውሬዎች ተበሉ።
7)የሞትና የህይወት ሸለቆ: "እኔነትን" ሙሉ በሙሉ አጥፍቶ በመለኮታዊው ውቅያኖስ ውስጥ መሞት።
በመጨረሻም፣ ከአዝማሪዎቹ፣ ከጀግኖቹና ከቆንጆዎቹ ወፎች መካከል በህይወት ተርፈው የሲሙርግ ቤተመንግስት ደጃፍ ላይ የደረሱት 30 ወፎች ብቻ ነበሩ። ላባቸው ረግፏል፣ ክንፋቸው ቆስሏል፣ በረሃብና በስቃይ ሰውነታቸው አልቋል። የቤተመንግስቱ በር ጠባቂ መጀመሪያ ላይ አናገራቸው፦ "እናንተ እነማን ናችሁ? እዚህ ምን ትፈልጋላችሁ? ሲሙርግ የእናንተን መሰል ደካማ ፍጥረታት አይፈልግም፤ ሂዱ ተመለሱ!" አላቸው።
ወፎቹ ግን ማልቀስ ጀመሩ። "እኛ እዚህ የምንሞት ቢሆንም እንኳ ከደጃፉ አንንቀሳቀስም" አሉ። ይህንን ፍጹም እጅ መስጠትና ጽናት ሲያይ፣ በር ጠባቂው በሩን ከፈተላቸው። ወደ ውስጥ ሲገቡ ታላቅ ብርሃን ፈነጠቀባቸው። አንድ መጽሐፍ ተሰጣቸው፤ መጽሐፉን ሲያነቡት በጉዞው ላይ ያሳለፉትን ስቃይ፣ የሰሩትን ስህተትና ህይወታቸውን በሙሉ የያዘ መስተዋት ሆነባቸው።
በመጨረሻም ወደ ዙፋኑ ሲመለከቱ ምንም አይነት አካላዊ ወፍ አላዩም። ያዩት ነገር ቢኖር የራሳቸውን ነጸብራቅ ብቻ ነበር።
*በዚያ የነበረውን መለኮታዊ ብርሃን ሲመለከቱ እነሱ ራሳቸው ሲሙርግ መሆናቸውን ተረዱ። ወደ ዙፋኑ ሲመለከቱ ግን ዙፋኑ ላይ ያለውና እነሱ አንድ ሆኑ።
በዚህ ጊዜ አንድ ድምፅ እንዲህ አላቸው፦
"እናንተ የመጣችሁት 30 ወፎች ሆናችሁ ነው፤ በመስተዋቱም ላይ የታየው 30 (ሲ-ሙርግ = 30 ወፍ ማለት ነው) ነው። ብዙ ሆናችሁ ብትመጡ ኖሮ እዚህ የምታዩትም ብዙ ነበር። ይህ የእናንተ እውነተኛ ማንነት መስተዋት ነው።"
ይህ ምሳሌ፦ በምድራዊ ፍቅርና ስሜት፤ በሀይማኖታዊ ስነስርአት ብቻ ተወስነው ውስጣዊ ጥልቀትን የማይፈልጉ፤ ፈጣሪን ለፀጋው (ለጀነት ምቾት) ብቻ እንጂ ፍቅሩን የማይረዱ፤ ለውጥን የሚፈሩ፤ በቁሳዊ ሀብት ፍለጋ የታወሩ፤ እንዲሁም ለጌታቸው ፍቅር ሁሉን የሚተዉትን ሰዎች ይወክላል።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
በአንድ ወቅት ታላቁ ዐሪፍ ቢሽር አል-ሀፊ በባግዳድ ጎዳናዎች ላይ ባዶ እግራቸውን እየተጓዙ ሳለ፣ አንድ የማያውቁትና ፊቱ በኑር (በብርሃን) የተሞላ እንግዳ ሽማግሌ መንገድ ላይ ያገኛሉ። ሽማግሌው ወደ ቢሽር በመምጣት ስማቸውን ጠርቶ ሰላምታ አቀረበ።
ሽማግሌው ሰው ለቢሽር እንዲህ አለ፦ "አንተ ቢሽር ሆይ! አንተ በምድር ላይ ብቻ ሳይሆን በሰማይ መላእክት ዘንድም የምትታወቅ የላቅክ የአላህ ወዳጅ ነህ" አላቸው።
ቢሽርም በንግግሩ ተገርሞ "የአላህ ወዳጅ ሆይ! እባክህ ማንነትህን ንገረኝ?" ሲል ጠየቀ። ሽማግሌውም ፈገግ ብሎ፦ "እኔ ወንድምህ ኸድር ነኝ" አሉ።
ቢሽር ሰይዲና ኸድር መሆናቸውን ሲያውቅ እጅግ ደነገጠ፤ በደስታም ተሞሉ። ከዚያም "ሰይዲና ኸድር ሆይ! እባካችሁ ለአላህ ስም ስትሉ ዱዓ አድርግልኝ" አላቸው። ሰይዲና ኸድርም እጃቸውን ወደ ሰማይ አንስተው፦ "አላህ ሆይ! ለአንተ ያለውን መታዘዝ አግኝቶታልና የአንተን መውደድ (ሪዷን) ጨምርለት፣ ለአንተ መስራቱንም አግኝቶታልና በደረጃው ላይ ማዕረግን ጨምርለት" ብለው ዱዓ አደረጉለት። ከዚህ ክስተት በኋላ ቢሽር በመንፈሳዊ ደረጃቸው ላይ ከፍተኛ እድገት አገኙ።
*አላሁመ ሷሊ አላ መርከዚል አንቢያዕ ወል አውሊያዕ!
*አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ ሰይድ ዩኑስ ኤምሬ ሸይኻቸውን ታፕዱክ ለ40 አመት ካገለገሉ በኋላ፣ "እኔ ምንም ለውጥ አላመጣሁም፣ መንፈሳዊ ብስለት ላይ አልደረስኩም" በሚል የከንቱነት ስሜት ተጭኖቸው ሀድራውን ጥለው ወጥተው ሲጓዙ መንገድ ላይ ከሰባት የላቁ አውሊያኦች (ደጎች) ጋር ይገናኛሉ። ምሽቱ የጁሙዓ ለይል ነበር፤ እያንዳንዱ ወሊይ በየተራ ዱዓ ሲያደርግ፣ ከተሰወረው ዓለም (ገይብ) እጅግ ጣፋጭ ምግብ ይወርድላቸዋል። ተራው ወደ ዩኑስ ሲደርስ ጨነቃቸው። እጃቸውን ወደ ሰማይ ዘርግተው እንዲህ አሉ፡ "ጌታዬ ሆይ! እኔ ማነኝና ነው የምለምንህ? ነገር ግን እነዚህ ደጋግ ባሮችህ በተማፅኑህና ይህንን ጸጋ በሰጠሃቸው ሰው ስም፣ እኔንም በዚያው ታላቅ ስም ማረኝ፣ አታሳፍረኝ" ብለው ዱዓ አደረጉ።
በዚያኑ ቅጽበት ከቀደሙት ይልቅ እጥፍ የሆነ ማዕድ ወረደ። አውሊያኦቹ ተደንቀው "በማን ስም ነው የለመንከው?" አሉት። ዩኑስም "ቅድሚያ እናንተ በማን ስም እንደለመናችሁ ንገሩኝ" አላቸው። እነሱም፡ "እኛስ በአናቶሊያ ምድር የሚገኘው የታፕዱክ ኤምሬ ደረሳ የሆነው ዩኑስ በሚባል የላቀ ባሪያ ስም (በእሱ ደረጃ) ነው የለመንነው" አሉት።
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ!
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
በቴህራን በተካሄደው የአያቶላ አሊ ኻሜኒ (ረ) የስንብት ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢራን መንግሥት የአገራት የዲፕሎማቲክ ልዑካን ቡድኖች ወደ አስከሬኑ ሲጠጉ የተነበበው ቁርኣን አንቀጽ (አያህ)
ቻይና፦ አል-ዒምራን (3:126) — “አላህም (ይህንን እርዳታ) ለእናንተ ብስራት እንድትሆንና ልቦቻችሁም በእርሱ እንዲረኩ እንጂ ለሌላ አላደረገውም። ድልም ከአሸናፊው ጥበበኛው አላህ ዘንድ እንጂ ከሌላ አይደለም።”
ሩሲያ፦ አል-ቀሰስ (28:83) — “ይህች የመጨረሻይቱ ዓለም (ገነት) በምድር ላይ ትዕቢትንና ጥፋትን ለማይፈልጉ ሰዎች እናደርጋታለን፤ መልካም ፍጻሜም ለጠባቂዎቹ (ለጻድቃኑ) ነው።”
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE)፦ አል-ማኢዳህ (5:51) -- “እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አይሁዶችንና ክርስቲያኖችን ረዳቶች (ወዳጆች) አድርጋችሁ አትያዙ፤ ከፊላቸው ለከፊሉ ረዳቶች ናቸውና። ከእናንተም ውስጥ ወዳጅ የሚያደርጋቸው ሰው እርሱ ከእነሱ ነው። አላህ አመጸኞችን ሕዝቦች አይመራም።”
የአውሮፓ አገራት ተወካዮች፦ ሱራህ ኢብራሂም (14:42) -- “አላህንም እነዚያ በደለኞች ከሚሰሩት ነገር ዘንጊ አድርገህ አታስበው፤ የሚያቆያቸው (የሚቀጣቸው) ዓይኖች በድንጋጤ ለሚፈጡበት ቀን ብቻ ነው።”
ሳውዲ አረቢያ፦ አል-ኢምራን (3:13) -- “በእርግጥ በነዚያ በተገናኙት ሁለት ጭፍሮች ውስጥ ለእናንተ አስደናቂ ምልክት አለ። አንደኛይቱ ጭፍራ በአላህ መንገድ ላይ የምትጋደል ስትሆን ሌላኛይቱ ደግሞ ከሃዲዎች ነበሩ... አላህም በራሱ እርዳታ የሚሻውን ሰው ይደግፋል።”
ሊባኖስ፦ አን-ኒሳእ (4:66) — “እኛም በእነርሱ ላይ ‘ነፍሶቻችሁን ግደሉ ወይም ከአገሮቻችሁ ውጡ’ ማለትን በጻፍንባቸው (በደነገግንባቸው) ኖሮ ከእነርሱ ጥቂቶቹ እንጂ አይሰሩትም ነበር...”
ሃማስ፦ አል-አሕዛብ (33:23) — “ከምእመናን ውስጥ በአላህ ላይ በእርሱ የገቡትን ቃል የፈጸሙ ወንዶች አሉ። ከእነርሱም ስለቱን (ሰማዕትነትን) የጨረሰ አለ፤ ከእነርሱም ገና የሚጠባበቅ አለ። (ቃል ኪዳናቸውን) ምንም መለወጥን አለወጡም።”
ሒዝቦላህ፦ ሱራህ አል-ማኢዳህ (5:56) -- “አላህንና መልክተኛውን እነዚያ ያመኑትንም ወዳጅ የሚያደርግ ሰው (የአላህ ጭፍራ ነው)፤ የአላህም ጭፍራዎች እነሱ በእርግጥ አሸናፊዎች ናቸው።”
የመን ሐውቲዎች፦ አል-ፈትሕ (48:29) — “ሙሐመድ የአላህ መልዕክተኛ ነው፤ እነዚያም ከእርሱ ጋር ያሉት (ምእመናን) በከሃዲዎች ላይ የበረቱ፣ በመካከላቸው አዛኞች ናቸው...”
ቱርክ፦ አን-ኒሳእ (4:95) —“ምእመናን ከሆኑት ሰሪዎች (ተዋጊዎች) ውስጥ ያለ ጉዳት (ቤት) ተቀማጮቹና እነዚያ በአላህ መንገድ ላይ በገንዘቦቻቸውና በነፍሶቻቸው የሚጋደሉት አይስተካከሉም። አላህ በገንዘቦቻቸውና በነፍሶቻቸው የሚጋደሉትን ከተቀማጮቹ በደረጃ አበለጠ...።”
የኢራቅ ታጣቂዎች፦ አል-ዒምራን (3:169–170) -- “እነዚያንም በአላህ መንገድ የተገደሉትን ሙታን አድርገህ አታስብ፤ ይልቁንም እነሱ በጌታቸው ዘንድ ሕያዋን ናቸው፤ ሲሳይንም ያገኛሉ። አላህ ከችሮታው በሰጣቸው ነገር ተደሳቾች ሲሆኑ...”
ሶሪያ፦ አል-ኢስራእ (17:5) -- “ከሁለቱ መጀመሪያይቱ (የማጥፋት) ጊዜ በመጣ ጊዜ በናንተ ላይ ኃያላን የሆኑ ባሮቻችንን እንሰድባችኋለን፤ በቤቶችም መካከል ይመላለሳሉ (ይበረብራሉ)፤ ፍጻሜውም የሚፈጸም ቃል ኪዳን ነበረ።”
ፓኪስታን እና አፍጋኒስታን፦ አል-ሁጁራት (49:10) -- “ምእመናን ወንድማማቾች ናቸው፤ በመካከላቸውም አስታርቁ፤ አላህንም ፍሩ፣ ይታዘንላችሁ ዘንድ።”
*አላህ ለዘመኑ ግፍኞችና በደለኞች መድሀኒት የሆኑትን ሰይድ መህዲ አ.ሰ ያምጣልን! አሚን!
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ ወሊይ ዘኑን አል-ሚስሪ ቀ.ሲ በጁሙዓ ለይል ከካይሮ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ አንድ ጭር ባለ በረሃማ መንገድ ላይ ብቻቸውን ይጓዙ ነበር። ሌሊቱ እጅግ ቀዝቃዛና ጨለማ ነበር። ሸይኹ ልባቸውን በዝክርና በሶለዋት ሞልተው እየተጓዙ ሳለ፣ ድንገት በዚያ ጭለማ ውስጥ አንድ የሚያስፈራ ትልቅ ድምፅ ሰሙ። ድምፁን ተከትለው ጠጋ ሲሉ፣ አንድ ትልቅ አንበሳ መሬት ላይ ወድቆ በከፍተኛ ህመም ሲጮኽና ሲያቃስት ተመለከቱ። ተራ ሰው ቢሆን በፍርሃት ይሸሻል፤ ዘኑን ግን ፍጥረታትን በሙሉ በራህመት ስለሚያዩ ወደ አንበሳው በጥንቃቄ ቀረቡ። ሲመለከቱት፣ የአንበሳው እግር ውስጥ ትልቅና ስለታም እሾህ ገብቶ ቆስሎና አብጦ አገኙት።
ዘኑን አል-ሚስሪ "ይህ በዚህች በተባረከች የጁሙዓ ለይል አላህ የላከብኝ የፈተና ማዕድ ነው" አሉ። ወዲያውኑ ቢላዋቸውን አውጥተው፣ በአላህ ስም እሾሁን ከአንበሳው እግር ላይ በጥንቃቄ ነቀሉለት። ቁስሉንም ከልብሳቸው ላይ ቀደው ጨርቅ አሰሩለት። አንበሳው ወዲያውኑ ከህመሙ ሲገላገል፣ በሚያስገርም ሁኔታ ሰይዲን ሊጎዳቸው አልሞከረም። ይልቁኑ ራሱን መሬት ላይ አድርጎ፣ በትልቅና በሚያስተጋባ ድምፅ መጮኽ ጀመረ።
በዚያ ሰዓት፣ አላህ ለዘኑን አል-ሚስሪ የመንፈሳዊ ከሽፍ (መገለጥ) ከፈተላቸው። የአንበሳው ጩኸት በልባቸው ውስጥ እንዲህ ሲል ተሰማቸው፦
"ያ አላህ! ይህ የአንተ ወዳጅ በዚህች የጁሙዓ ለይል ለእኔ አዘነልኝ፣ ከህመሜም ፈወሰኝ። አንተም በዚህች ምሽት የልቡን ጭንቀት በሙሉ አስወግድለት፣ ወደ አንተ የሚወስደውንም የመጨረሻውን የመክፈቻ በር ክፈትለት።"
አንበሳው ዱዓውን አድርጎ በጨለማው በረሃ ውስጥ ተሰወረ። ዘኑን አል-ሚስሪ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሆነው ወደ ሰማይ ሲመለከቱ፣ የሰማይ በሮች በሙሉ ተከፍተው የራህመትና የኑር መጋረጃ ሲወርድ ተመለከቱ። ልባቸው ከዚህ በፊት ደርሳበት የማታውቀው ጥልቅ የሆነ መለኮታዊ እውቀትና ፍቅር (ማዕሪፋ) ውስጥ ሰጠመች።
እሳቸው ራሳቸው ስለዚያች ሌሊት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦
"በእውቀቴና በኢባዳዬ ብዛት ያላገኘሁትን ትልቅ መንፈሳዊ ከፍታና ከሽፍ፣ አላህ በዛች ጁሙዓ ለይል በአንድ ምስኪንና በታመመ ፍጡር ላይ እንዳዝን በማድረጉ ሰበብ ብቻ ሰጠኝ።"
*"በምድር ላሉት እዘኑ፣ በሰማይ ያለው ያዝንላችኋል" የሚለው የነቢዩ (ﷺ) ቃል ማሳያ ነው።
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ!
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
Repost from Abdu & Hasu
#ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ ወሊይ ዘኑን አል-ሚስሪ ቀ.ሲ በጁሙዓ ለይል ከካይሮ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ አንድ ጭር ባለ በረሃማ መንገድ ላይ ብቻቸውን ይጓዙ ነበር። ሌሊቱ እጅግ ቀዝቃዛና ጨለማ ነበር። ሸይኹ ልባቸውን በዝክርና በሶለዋት ሞልተው እየተጓዙ ሳለ፣ ድንገት በዚያ ጭለማ ውስጥ አንድ የሚያስፈራ ትልቅ ድምፅ ሰሙ። ድምፁን ተከትለው ጠጋ ሲሉ፣ አንድ ትልቅ አንበሳ መሬት ላይ ወድቆ በከፍተኛ ህመም ሲጮኽና ሲያቃስት ተመለከቱ። ተራ ሰው ቢሆን በፍርሃት ይሸሻል፤ ዘኑን ግን ፍጥረታትን በሙሉ በራህመት ስለሚያዩ ወደ አንበሳው በጥንቃቄ ቀረቡ። ሲመለከቱት፣ የአንበሳው እግር ውስጥ ትልቅና ስለታም እሾህ ገብቶ ቆስሎና አብጦ አገኙት።
ዘኑን አል-ሚስሪ "ይህ በዚህች በተባረከች የጁሙዓ ለይል አላህ የላከብኝ የፈተና ማዕድ ነው" አሉ። ወዲያውኑ ቢላዋቸውን አውጥተው፣ በአላህ ስም እሾሁን ከአንበሳው እግር ላይ በጥንቃቄ ነቀሉለት። ቁስሉንም ከልብሳቸው ላይ ቀደው ጨርቅ አሰሩለት። አንበሳው ወዲያውኑ ከህመሙ ሲገላገል፣ በሚያስገርም ሁኔታ ሰይዲን ሊጎዳቸው አልሞከረም። ይልቁኑ ራሱን መሬት ላይ አድርጎ፣ በትልቅና በሚያስተጋባ ድምፅ መጮኽ ጀመረ።
በዚያ ሰዓት፣ አላህ ለዘኑን አል-ሚስሪ የመንፈሳዊ ከሽፍ (መገለጥ) ከፈተላቸው። የአንበሳው ጩኸት በልባቸው ውስጥ እንዲህ ሲል ተሰማቸው፦
"ያ አላህ! ይህ የአንተ ወዳጅ በዚህች የጁሙዓ ለይል ለእኔ አዘነልኝ፣ ከህመሜም ፈወሰኝ። አንተም በዚህች ምሽት የልቡን ጭንቀት በሙሉ አስወግድለት፣ ወደ አንተ የሚወስደውንም የመጨረሻውን የመክፈቻ በር ክፈትለት።"
አንበሳው ዱዓውን አድርጎ በጨለማው በረሃ ውስጥ ተሰወረ። ዘኑን አል-ሚስሪ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሆነው ወደ ሰማይ ሲመለከቱ፣ የሰማይ በሮች በሙሉ ተከፍተው የራህመትና የኑር መጋረጃ ሲወርድ ተመለከቱ። ልባቸው ከዚህ በፊት ደርሳበት የማታውቀው ጥልቅ የሆነ መለኮታዊ እውቀትና ፍቅር (ማዕሪፋ) ውስጥ ሰጠመች።
እሳቸው ራሳቸው ስለዚያች ሌሊት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦
"በእውቀቴና በኢባዳዬ ብዛት ያላገኘሁትን ትልቅ መንፈሳዊ ከፍታና ከሽፍ፣ አላህ በዛች ጁሙዓ ለይል በአንድ ምስኪንና በታመመ ፍጡር ላይ እንዳዝን በማድረጉ ሰበብ ብቻ ሰጠኝ።"
*"በምድር ላሉት እዘኑ፣ በሰማይ ያለው ያዝንላችኋል" የሚለው የነቢዩ (ﷺ) ቃል ማሳያ ነው።
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ!
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ ወሊይ ዘኑን አል-ሚስሪ ቀ.ሲ በጁሙዓ ለይል ከካይሮ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ አንድ ጭር ባለ በረሃማ መንገድ ላይ ብቻቸውን ይጓዙ ነበር። ሌሊቱ እጅግ ቀዝቃዛና ጨለማ ነበር። ሸይኹ ልባቸውን በዝክርና በሶለዋት ሞልተው እየተጓዙ ሳለ፣ ድንገት በዚያ ጭለማ ውስጥ አንድ የሚያስፈራ ትልቅ ድምፅ ሰሙ። ድምፁን ተከትለው ጠጋ ሲሉ፣ አንድ ትልቅ አንበሳ መሬት ላይ ወድቆ በከፍተኛ ህመም ሲጮኽና ሲያቃስት ተመለከቱ። ተራ ሰው ቢሆን በፍርሃት ይሸሻል፤ ዘኑን ግን ፍጥረታትን በሙሉ በራህመት ስለሚያዩ ወደ አንበሳው በጥንቃቄ ቀረቡ። ሲመለከቱት፣ የአንበሳው እግር ውስጥ ትልቅና ስለታም እሾህ ገብቶ ቆስሎና አብጦ አገኙት።
ዘኑን አል-ሚስሪ "ይህ በዚህች በተባረከች የጁሙዓ ለይል አላህ የላከብኝ የፈተና ማዕድ ነው" አሉ። ወዲያውኑ ቢላዋቸውን አውጥተው፣ በአላህ ስም እሾሁን ከአንበሳው እግር ላይ በጥንቃቄ ነቀሉለት። ቁስሉንም ከልብሳቸው ላይ ቀደው ጨርቅ አሰሩለት። አንበሳው ወዲያውኑ ከህመሙ ሲገላገል፣ በሚያስገርም ሁኔታ ሰይዲን ሊጎዳቸው አልሞከረም። ይልቁኑ ራሱን መሬት ላይ አድርጎ፣ በትልቅና በሚያስተጋባ ድምፅ መጮኽ ጀመረ።
በዚያ ሰዓት፣ አላህ ለዘኑን አል-ሚስሪ የመንፈሳዊ ከሽፍ (መገለጥ) ከፈተላቸው። የአንበሳው ጩኸት በልባቸው ውስጥ እንዲህ ሲል ተሰማቸው፦
"ያ አላህ! ይህ የአንተ ወዳጅ በዚህች የጁሙዓ ለይል ለእኔ አዘነልኝ፣ ከህመሜም ፈወሰኝ። አንተም በዚህች ምሽት የልቡን ጭንቀት በሙሉ አስወግድለት፣ ወደ አንተ የሚወስደውንም የመጨረሻውን የመክፈቻ በር ክፈትለት።"
አንበሳው ዱዓውን አድርጎ በጨለማው በረሃ ውስጥ ተሰወረ። ዘኑን አል-ሚስሪ ግን በዚያው ቦታ ላይ ሆነው ወደ ሰማይ ሲመለከቱ፣ የሰማይ በሮች በሙሉ ተከፍተው የራህመትና የኑር መጋረጃ ሲወርድ ተመለከቱ። ልባቸው ከዚህ በፊት ደርሳበት የማታውቀው ጥልቅ የሆነ መለኮታዊ እውቀትና ፍቅር (ማዕሪፋ) ውስጥ ሰጠመች።
እሳቸው ራሳቸው ስለዚያች ሌሊት ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦
"በእውቀቴና በኢባዳዬ ብዛት ያላገኘሁትን ትልቅ መንፈሳዊ ከፍታና ከሽፍ፣ አላህ በዛች ጁሙዓ ለይል በአንድ ምስኪንና በታመመ ፍጡር ላይ እንዳዝን በማድረጉ ሰበብ ብቻ ሰጠኝ።"
*"በምድር ላሉት እዘኑ፣ በሰማይ ያለው ያዝንላችኋል" የሚለው የነቢዩ (ﷺ) ቃል ማሳያ ነው።
የአባባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، صَلَاةً تَرْزُقُنَا بِهَا الْخُلُقَ النَّفِيسَ، يَا رَحْمَانُ يَا قُدُّوسُ!
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሀመድ፤ ወአላ አሊ ሰይዲና ሙሀመድ ሷላተን ተርዙቁና ቢሃል ኹሉቀ ነፊስ ያረህማኑ ያቁዱስ!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
ሼህ አብዱልኻሊቅ አል-ጉጅዱዋኒ ገና በወጣትነት ዕድሜያቸው ቁርአንን እና የሸሪዓ እውቀቶችን እያጠኑ። አንድ ቀን በቁርአን ውስጥ ያለውንና ስለ ውስጣዊ/ሚስጥራዊ ዚክር (የልብ ዚክር) የሚናገረውን የጌታችንን ቃል ያነባሉ፡-
“ጌታህን በነፍስህ ውስጥ በጭምትነትና በፍርሃት... ጥዋትና ማታ አውሳው፤ ከዘንጊዎችም አትሁን።” (ሱረቱል አዕራፍ፡ 205)
ወጣቱ አብዱልኻሊቅ በዚህ አንቀጽ ላይ በጥብቅ አሰላሰሉና መምህራቸውን እንዲህ ሲሉ ጠየቁ፡-
“ይህ ዚክር እንዴት ነው የሚደረገው? በድምፅ (በምላስ) ካደረግኩት ሰዎች ይሰሙኛል፣ ይህ ደግሞ ለይዩልኝ ሊዳርገኝ ይችላል። በልቤ ብቻ ካደረግኩት ደግሞ ሰይጣን የሰውን ልጅ የደም ስር ተከትሎ ስለሚዘዋወር በልቤ የማስበውን ያውቅብኛል። ታዲያ ፍጹም ሚስጥራዊ እና ሰይጣንም ሆነ ሰው የማያውቅበትን ዚክር እንዴት ማድረግ እችላለሁ?”
መምህራቸውም “ልጄ ሆይ፣ ይህ የላቀ መለኮታዊ እውቀት ነው፤ አላህ ከፈለገ ከቅዱሳን ባሮቹ በአንዱ በኩል ይገልጥልሃል” አሏቸው።
ብዙም ሳይቆይ፣ ወጣቱ አብዱልኻሊቅ በሶላት ላይ እያሉ ፍጹም መንፈሳዊ ድባብ ተፈጠረ። በወቅቱ የነበሩት ታላቁ መሪ ሰይድና ኸድር (ዐ.ሰ) በአካል ተገለጡላቸው። ሰይድና ኸድርም ለአብዱልኻሊቅ መንፈሳዊ አባትና መሪ እንደሚሆኑ በመግለጽ፣ ያንን የፈለጉትን ሚስጥራዊ ዚክር ሊያስተምሯቸው መጡ። ሰይድና ኸድር ወጣቱን አብዱልኻሊቅን ይዘው ወደ አንድ የውሃ ኩሬ ሄዱ። ከዚያም በውሃው ውስጥ እንዲጠልቁና እዚያ ውስጥ ሆነው ትንፋሻቸውን አፍነው፣ ምላሳቸውን ከላንቃቸው ጋር አጣብቀው በልባቸው “ላ ኢላሀ ኢልለላህ፣ ሙሐመዱ ረሱሉላህ” እያሉ እንዲያወሱ አዘዟቸው።
ይህ ዚክር “ኸፊ” (ፍጹም ሚስጥራዊ) ይባላል። በውሃ ውስጥ ትንፋሽን አፍኖ የሚደረግ በመሆኑ፡- ምላስ አይንቀሳቀስም (ሰዎች አይሰሙትም)፣ ትንፋሽ አይወጣም (የሰውነት እንቅስቃሴ ስለማይታይ ሰይጣንም የተደበቀውን መንፈሳዊ ብርሃን በቀላሉ ሊሰርቅ አይችልም)።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#ለይለተል_ጁሙኣ
ሰይዱ ጧኢፋ ኢማም ጁነይድ በአንድ የጁሙዓ ሌሊት በባግዳድ መስጂድ ውስጥ ዒባዳ እያደረጉ ሳለ፣ አንድ ዓይነ ስውር ምስኪን ሰው ወደ መስጂዱ ይገባል። ይህ ሰው በጣም ፍጹም በሆነ ፍቅር (ሸውቅ) ሆኖ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ላይ ሰለዋት ያወርዳል።
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ، طِبِّ الْقُلُوبِ وَدَوَائِهَا، وَعَافِيَةِ الأَبْدَانِ وَشِفَائِهَا، وَنُورِ الأَبْصَارِ وَضِيَائِهَا، وَعَلَى آلِهِ وَصَحْبِهِ وَسَلِّمْ.
"አላሁመ ሷሊ ወሰሊም ዓላ ሰይዲና ሙሐመዲን፣ ጢቢል ቁሉቢ ወደዋኢሃ፣ ወዓፊየቲል አብዳኒ ወሺፋኢሃ፣ ወኑሪል አብሷሪ ወዲያኢሃ፣ ወዓላ አሊሂ ወሷሕቢሂ ወሰሊም"
ይህ ሰለዋት እጅግ ልብ የሚነካና ጥልቅ የሆነ የፍቅር መግለጫ ያለው ነው። ኢማም ጁነይድ የሰውየውን ሰለዋት ሲሰሙ፣ በልባቸው ውስጥ ለየት ያለ መንፈሳዊ ስሜት ይሰማቸዋል፤ በሰውየው ላይ ያለው የአላህ እዝነትና ብርሃንም ይታያቸዋል።
በዚህ ጊዜ ኢማም ጁነይድ ወደ ሰውየው ጠጋ አሉና፡-
"አንተ የአላህ ባሪያ ሆይ! ይህ የምታወርደው ሰለዋት እጅግ አስደናቂ ነው፤ ይህንን ሰለዋት ማን ነው ያስተማረህ?"ሲሉ ይጠይቁታል።
ሰውዬም ፈገግ አለና እንዲህ አላቸው፡-
"አቡል ቃሲም ሆይ! እኔማ ዕውርና ደካማ ሰው ነኝ። ነገር ግን በአንድ የጁሙዓ ሌሊት በህልሜ ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) አየኋቸው። ወደ እሳቸው ጠጋ ብዬ 'የአላህ መልእክተኛ ሆይ! እኔ ዓይኔ የማያይ ምስኪን ነኝ፤ አላህ ዘንድ ትልቅ ደረጃ የሚያሰጠኝን ሰለዋት ያስተምሩኝ' አልኳቸው። እሳቸውም ይህንን ሰለዋተ ኑራኒያ አስተማሩኝ። ከዚያን ቀን ጀምሮ በየጁሙዓው ሌሊት ይህንን ሰለዋት ሳወርድ፣ የነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) መንፈሳዊ ቅርበትና ብርሃን አይለየኝም" አላቸው።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#የድል_ቀን
አሹራ ቀን (ሙሀረም 10) ላይ የተከሰቱትን ታላላቅ መለኮታዊ ድሎች፦
* የነቢዩላህ ኣደም (ዐ.ሰ)፦ አላህ ንስሐቸውን የተቀበለውና ይቅርታ ያደረገላቸው በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ኑህ (ዐ.ሰ)፦ ታላቁ የጥፋት ውሃ ጎርፍ አብቅቶ፣ እርሳቸውና አማኞች የነበሩበት መርከብ በ“ጁዲ” ተራራ ላይ በሰላም ያረፈችው በዚህ ዕለት ነው።
* የነቢዩላህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ)፦ ነቢዩላህ ኢብራሂም የተወለዱትም በዚህ ቀን ሲሆን፥ ከናምሩድ እሳት ውስጥ በተጣሉ ጊዜ አላህ እሳቱን ቀዝቃዛና ሰላም (በርደን ወሰላማ) አድርጎ ያዳናቸው በዚህ ዕለት ነው።
* የነቢዩላህ ሙሳ (ዐ.ሰ)፦ ፈርዖንና ግፈኛው ሰራዊቱ በባህር ውስጥ የሰጠሙበት፣ ሙሳና የኢሥራኢል ልጆች ግን ባህሩ ተከፍሎላቸው በሰላም የተሻገሩበትና ከባርነት ነፃ የወጡበት ታላቁ የድል ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ዩሱፍ (ዐ.ሰ)፦ በወንድሞቻቸው ምቀኝነት ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ከተጣሉ በኋላ፣ ከአላህ በረከት ጋር ከጉድጓዱ የወጡበት እንዲሁም ከዓመታት በኋላ ከግብፅ እስር ቤት የተፈቱበት ቀን ነው።
*የነቢዩላህ ያዕቆብ (ዐ.ሰ)፦ ከልጃቸው ከነቢዩ ዩሱፍ መለየት የተነሳ አልቅሰው ጠፍቶ የነበረው ዓይናቸው (ዕይታቸው) በአላህ ፈቃድ የተመለሰላቸውና ብርሃን ያገኙበት በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ አዩብ (ዐ.ሰ)፦ አላህ ሙሉ ጤንነታቸውንና ያጡትን ሀብት የመለሰላቸው በአሹራ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ዩኑስ (ዐ.ሰ)፦ በአሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ሆነው ካደረጉት ጥልቅ ዚክርና መማጸን በኋላ፣ አላህ ከአሳው ሆድ በሰላም ያወጣቸውና ወደ ምድር የመለሳቸው በዚህ ዕለት ነው።
* የነቢዩላህ ሱለይማን (ዐ.ሰ)፦ አላህ ለነቢዩ ሱለይማን ታላቅ የሆነውንና ማንኛውንም ፍጡር (ሰውን፣ ጂንንና ንፋስን) የሚገዛበትን ንግሥናና ስልጣን የለገሳቸው በዚህ ቀን ነው።
*የነቢዩላህ ዳውድ (ዐ.ሰ)፦ አላህ ለነቢዩ ዳውድ ያደረገላቸውን ትልቅ ይቅርታና ወንጀላቸውን የማራቸው ዕለት።
* የነቢዩላህ ዒሳ (ዐ.ሰ)፦ ጠላቶቻቸው ሊገድሏቸውና ሊሰቅሏቸው ባሴሩ ጊዜ፣ አላህ ከእነሱ ተንኮል ጠብቆ ወደ ሰማይ ያነሳቸው በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ እድሪስ (ዐ.ሰ)፦ አላህ በቁርኣን ውስጥ “ከፍተኛም ስፍራ አነሳነው” (መርየም፡ 57) በማለት የገለጸውና ነቢዩላህ እድሪስን ወደ አራተኛው ሰማይ ከፍ ያደረገበት ዕለት።
* የነቢዩላህ ሹዐይብ (ዐ.ሰ)፦ ነቢዩላህ ሹዐይብ ለህዝቦቻቸው ጥመትና መከራ ካላቸው ከባድ ሀዘን የተነሳ አልቅሰው ዓይናቸው ጠፍቶ የነበረ ሲሆን፣ አላህ ሙሉ ዕይታቸውን የመለሰላቸው በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ሁድ (ዐ.ሰ)፦ አላህ አመጸኞቹን የ“ዓድ” ህዝቦች በብርቱና አውዳሚ ንፋስ ባጠፋበት ወቅት፣ ነቢዩ ሁድንና አብረዋቸው የነበሩትን አማኞች ከጥፋት ያዳነበት ዕለት አሹራ ነው።
* የነቢዩላህ ሷሊህ (ዐ.ሰ)፦ ታላቋ ግመል (የአላህ ተአምር) በድንጋይ ውስጥ የወጣችበት እንዲሁም ሰሙዶች ግመሏን ካረዱ በኋላ የመጣባቸውን የመብረቅና የጩኸት ቅጣት ተከትሎ ነቢዩ ሷሊህና ሙስሊሞች የዳኑት በዚህ ቀን ነው።
* የነቢዩላህ ሎጥ (ዐ.ሰ)፦ የሰዶም (የሎጥ ህዝቦች) ከተማ ከመገልበጧና የድንጋይ ዝናብ ከመዝነቡ በፊት፣ አላህ ነቢዩ ሎጥንና ቤተሰቦቻቸውን ሌሊቱን በሰላም ያስወጣበትና ያዳነበት ዕለት እንደሆነ ይገለጻል።
* የነቢዩ ሙሐመድ ﷺ፦ አላህ በቅዱስ ቁርዐን ሱራ ፈትህ (48:2) "አላህ ከወንጀልህ ያለፈውንና የሚመጣውንም ለአንተ ሊምርልህ፣ ጸጋውንም በአንተ ላይ ሊሞላልህ፣ ቀጥተኛውንም መንገድ ሊመራህ (ይህን ታላቅ ድል አጎናጸፈህ)።"
በማለት የተናገረለትን ታላቅ የምህረትና የክብር አክሊል ለነቢያችን ﷺ ያረጋገጠበት ዕለት ነው።
የተሰውፍ ሊቃውንት (መሻኢኾች) እንደገለጹት፣ አላህ ይህንን ዓለም በውጫዊ ነገሥታት ብቻ ሳይሆን በውስጣዊ አውሊያኦቹ (በመንፈሳዊ መዋቅር ወይም ዲዋን) ያስተዳድራታል። ይህ መዋቅር ደግሞ በየዓመቱ በአሹራ ሌሊትና ቀን ትልቅ ሽግግር ያደርጋል።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#ሹማምንት
በተሰውፍ ውስጥ የመንፈሳዊ መሪዎች እና የወሊዮች (አውሊያኦች) መንፈሳዊ የሹመት ደረጃ በዝርዝር እንደሚከተለው ነው፦
1. ቁጥብ፦ በአንድ ዘመን በአለም ላይ አንድ ቁጥብ ብቻ ሲኖር የበላይ መሪ ነው። የአለም መንፈሳዊ ምሰሶ ነው፤ መለኮታዊ እዝነት፣ ኑር (ብርሃን) እና ሲሳይ ወደ አለም የሚፈስሰው በእሱ ልብ አማካኝነት ነው።
2. ኢማመይን፦ ሁለት ሲሆኑ ከቁጥቡ ቀጥሎ ያሉ የግራና የቀኝ ረዳቶች ናቸው።
*የቀኙ ኢማም፦ የማይታየውንና የመንፈሳዊውን አለም (ዓለመል መለኩት) ይቆጣጠራል።
*የግራው ኢማም፦ የሚታየውንና ቁሳዊውን አለም (ዓለመል ሙልክ) ይከታተላል። ቁጥቡ ሲያልፍ በቦታው የሚተካው ይህ የግራው ኢማም ነው።
3. አውታድ፦ ቁጥራቸው አራት ሲሆኑ የአለም አራቱ ማዕዘናት ምሰሶዎች ናቸው። እያንዳንዱ አውታድ በአራቱ የአለም አቅጣጫዎች (ምስራቅ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ) ተመድበው በየአቅጣጫው ያለውን ሰላምና ሚዛን የመጠበቅ አደራ አለባቸው።
4. አብዳል፦ ብዛታቸው አርባ ሲሆን፤ በአለም ላይ በረከትና እዝነት እንዲወርድ፣ ጦርነትና መቅሰፍት እንዲከላከል ሌሊትና ቀን የሚጸልዩ ናቸው። አንዱ ሲሞት ሌላው ወዲያው ስለሚተካ "አብዳል" (ተለዋዋጮች) ተባሉ። መሪያቸው ሰይዲ ኸድር አሰ ናቸው።
5. ኑቀባእ፦ ብዛታቸው ሰላሳ ሲሆን የሰዎችን ውስጣዊ ማንነት፣ የልብ ሚስጥር እና የተንኮል ሀሳቦችን የመለየት ልዩ መንፈሳዊ እውቀት ተሰጥቷቸዋል።
6. ኑጀባእ፦ ሰባ የሚደርሱ ሲሆን፤ የሰዎችን ከባድ ሸክምና ችግር በመሸከም፣ ሰዎችን በማስታረቅ እና ሰብአዊ እርዳታዎችን በመንፈሳዊው መንገድ በማቅለል ላይ የተሰማሩ ናቸው።
7. አኽያር፦ እስከ 500 ይደርሳሉ ሁልጊዜ በመልካም ስራ ላይ የተሰማሩ፣ ከክፉ ነገር የራቁ እና ዱአቸው ፈጣን ምላሽ የሚያገኝ ታላላቅ ወሊዮች ናቸው።
8. አብራር፦ ቁጥራቸው በውል አይታወቅም። መላ ህይወታቸውን ለዒባዳ እና ሰዎችን ለመርዳት የሰጡ፣ ልባቸው ከቂምና ከምቀኝነት የጠራች ወሊዮች ናቸው። በአለም ላይ የሚከሰቱ አብዛኞቹን በጎ ነገሮች በዱዓቸው ይደግፋሉ።
9. አምድ ወይም ዐሙድ፦ ብዛታቸው 360 ነው። በእያንዳንዱ የአለም ክፍል ተበትነው የሚኖሩ፣ የሰዎችን እምነትና መንፈሳዊ ጥንካሬ ልክ እንደ አምድ ደግፈው የሚይዙ ታላላቅ ባሮች ናቸው።
10. ኡመላእ ፦ በቁጥር አይገደቡም፤ እነዚህ በአላህና በፈጣሪ መካከል። ያሉትን ሚስጥራት ጠባቂዎች ናቸው። ሸሪዓን በትክክል በመተግበር እና ለሰዎች በማስተማር ይታወቃሉ።
11. አምሳል፦ በጣም ብዙ ናቸው። "ምሳሌዎቹ" ማለት ነው፤ በህዝብ መካከል እየኖሩ በመልካም ስነ-ምግባራቸው፣ በትህትናቸውና በቁጥብነታቸው ለሌላው ሰው አርአያና ምሳሌ የሚሆኑ አማኞች ናቸው።
12. ሷሊሒን፦ እነዚህ ግዴታ የሆኑትን የእምነት ስራዎች በትክክል የሚተገብሩ፣ ከተከለከሉ (ሀራም) ነገሮች ሙሉ በሙሉ የሚርቁ እና በሰዎች መካከል በደግነታቸው የሚታወቁ አማኞች ናቸው። ለሌላው ደረጃ መሸጋገሪያ የመጀመሪያው መሰላል ተደርገው ይወሰዳሉ።
13. ቃኒቲን፦ ለፈጣሪ ትዕዛዝ ፍጹም ተገዢ የሆኑ፣ በኢባዳ ላይ ረጅም ጊዜ የሚያሳልፉ እና ውስጣዊ ትህትና ያላቸው (ኹሹዕ ያላቸው) ባሮች ናቸው።
14. ሻኪሪን፦ በደስታም ሆነ በመከራ ጊዜ አምላካቸውን ከማመስገን የማይቦዝኑ፣ ፈጣሪ በሰጣቸው ጥቂት ነገር የሚረኩ (ቃኒዕ የሆኑ) ናቸው።
15. ሳቢሪን፦ በመከራ፣ በበሽታ ወይም በችግር ጊዜ ፍጹም ትዕግስትን የሚያሳዩ፣ በፈጣሪ ውሳኔ (ቀዷ ወቀድር) ላይ የማይማረሩ እና በትዕግስታቸው ምክንያት መንፈሳዊ ጥንካሬን የሚያገኙ ናቸው።
16. ሙእሚኒን፦ በልባቸው ውስጥ እውነተኛ እምነት (ኢማን) ያላቸው፣ ነገር ግን አሁንም ድረስ ከራሳቸው ነፍስና ስሜት ጋር የሚታገሉ፣ ጥፋት ሲያጠፉ ወዲያውኑ ተውበት (ንስሀ) የሚያደርጉ አጠቃላይ ሙስሊሞች ናቸው።
#አፍራድ፦ ከጠቅላላው የሪጃሉል ጋይብ (የማይታየው አለም ሰዎች) መዋቅር እና ህግጋት ውጪ የሆኑ፣ ቀጥታ ከአላህ ብቻ ትዕዛዝ የሚቀበሉ በጣም ጥቂትና ነጻ የሆኑ ታላላቅ ነቢያትና ወሊዮች የሚገኙበት ደረጃ ነው። ከነዚህ ውስጥ ኸድር (ዐ.ሰ) እና ነቢዩ ኢልያስ (ዐ.ሰ) ይገኙበታል።
ማሳሰቢያ፦ እነዚህ ሁሉ መንፈሳዊ መሪዎች እራሳቸውን ደብቀው፣ ዝናን ሳይፈልጉ፣ በተራ ህዝብ መካከል ተደባልቀው የሚኖሩ በመሆናቸው በተራ አይን በቀላሉ አይታወቁም። መዋቅሩ የአለምን መንፈሳዊ ሰላምና ስነ-ስርዓት ለመጠበቅ በአላህ ፍቃድ የሚሰራም ነው።
#መገርገቢያ
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#የሰይዱና_ኸድር_ቅዳሜ
"ቢስሚላሂ ማሻአላህ፣ ላ የሱቁል ኸይረ ኢለላህ። ቢስሚላሂ ማሻአላህ፣ ላ የሥሪፉ ሱአ ኢለላህ። ቢስሚላሂ ማሻአላህ፣ ማ ካነ ሚን ኒዕመቲን ፈሚነላህ። ቢስሚላሂ ማሻአላህ፣ ላ ሐውላ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ።"
(በአላህ ስም አላህ የሻው ይሆናል፤ መልካም ነገርን ከአላህ በስተቀር ማንም አይሰጥም። በአላህ ስም አላህ የሻው ይሆናል፤ መጥፎ ነገርን ከአላህ በስተቀር ማንም አይመልሰውም። በአላህ ስም አላህ የሻው ይሆናል፤ ማንኛውም ጸጋ ከአላህ ዘንድ ነው። በአላህ ስም አላህ የሻው ይሆናል፤ ከአላህ በስተቀር ምንም ብልሃትና ኃይል የለም።)
ይህንን ዚክር ጠዋትና ማታ 3 ወይም 7 ጊዜ ማለት ሰይድና ኸድርን ለመገናኘት ይረዳል።
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#ለይለተል_ጁሙኣ
ታላቁ ታቢዒይ ጣዉስ ኢብኑ ከይሳን (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
አንድ የጁሙዓ ምሽት በመካ በካዕባ አጠገብ ሳለሁ፣ በአለባበሱ በጣም ደሃና ምስኪን የሆነ፣ የጉዞ ድካም ያለበት ሰውዬ አየሁ። ሰውየው ወደ መቃሙ ኢብራሂም ተጠጋና የሌሊት ሶላት መስገድ ጀመረ።
ሶላቱን ጨርሶ ሱጁድ ወረደ። ጣዉስ እንዲህ ይላሉ፡ "ለመሆኑ በዚህ በተባረከ ሌሊት ምን እያለ ዱዓ እንደሚያደርግ ለመስማት ጆሮዬን ጠጋ አደረግኩ።"
ሰውየው በሱጁድ ላይ ሆኖ በዕንባ እየታጠበ አራት አጫጭር ቃላትን ብቻ በተደጋጋሚ ይል ነበር፡
"إِلَهِي عُبَيْدُكَ بِبَابِكَ.. سَائِلُكَ بِبَابِكَ.. فَقِيرُكَ بِبَابِكَ.. مِسْكِينُكَ بِبَابِكَ"
"ጌታዬ ሆይ! ይኸው ትንሽ ባሪያህ በደጅህ ቆሟል.. ጠያቂህ በደጅህ ቆሟል.. ድሃህ በደጅህ ቆሟል.. ምስኪንህ በደጅህ ቆሟል (ማረኝ፣ ስጠኝ)።"
ጣዉስ ይላሉ፦ "እነዚህን ቃላት ደጋግሞ ሲል ልቤ ተነካ። ከዚያን ቀን ጀምሮ እኔም በሕይወቴ ማንኛውም ከባድ ጭንቀት ሲገጥመኝ፣ በለይለተል ጁሙዓ ሌሊት ሱጁድ ወርጄ ይህችን ዱዓ ማድረግ አልተውኩም። ያደረግኳት ጊዜም አላህ ጭንቀቴን ሳይፈታው ቀርቶ አያውቅም!"
የአበባ የጁሙኣ ሰለዋት ስጦታ
اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وَعَلَى كُلِّ نَبِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا أَبِي بَكْرٍ وَعَلَى كُلِّ وَلِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُمَرَ وَعَلَى كُلِّ تَقِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عُثْمَانَ وَعَلَى كُلِّ سَخِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا عَلِيٍّ وَعَلَى كُلِّ رَضِيٍّ، وَعَلَى سَيِّدِنَا جِبْرِيلَ وَعَلَى كُلِّ مَلَكٍ (عَشْرَ مَرَّاتٍ).
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#ጊዜው_ደርሷል
1448ኛው አ.ሂ እነሆ ገብቷል! ዓመቱ የዓለም የኃይል ሚዛን (የፖለቲካና የጂኦፖለቲካ መዋቅር) የሚቀየርበት፣ የድሮዎቹ ኃያላን የሚዳከሙበትና አዳዲስ ኃይሎች የሚወጡበት የሽግግር ወቅት ይሆናል። ይህ ውጥረትና መናወጥ ምድርን በፍትህ ለመሙላት ለሚመጣው መለኮታዊ ለውጥ መንገድ ጠራጊ ነው ተብሎ ይታመናል።
ሼሆቹ እነዚህን ክስተቶች የሚናገሩት ሰውን ለማስፈራራት ሳይሆን፣ መንፈሳዊ ዝግጅት እንዲያደርግ ነው። ለዚህ ዓመት የሚከተሉትን ሶስት ነገሮች አጥብቁ ይላሉ፦
1. ኢስቲግፋር (ምህረት መለመን)
2. ኡዝላህ (ራስን ከጩኸት ማራቅ)
3. ሱህባህ (ከመልካሞች ጋር መሆን)፦ በዚህ የፈተና ዘመን ብቻውን የሚጓዝ ሰው ይበላል፤ ስለዚህ ልባቸው ከፈጣሪ ጋር ከተገናኘ መልካም ሰዎችና መሻኢኮች ጋር መጣበቅ።
ባጭሩ ሼሆቹ የዚህን ዓመት ፍሰት ሲያጠቃልሉት፦ "ውጫዊው ዓለም በከፍተኛ ፍጥነት ይናወጣል፣ ይለወጣልም፤ ነገር ግን በልቡ ውስጥ የአላህን ፍቅርና ሰላም የገነባ ሰው ማዕበሉ አይነካውም" ይላሉ።
በዚህ ዓመት ልቡን አጥብቆ፣ በእውነተኛ ስሜትና እምነት ዱዓእ ለሚያደርግ ሰው ምላሹ በጣም በፍጥነት እንደሚመጣ ይናገራሉ። በተለይ የተበደሉ ሰዎች፣ ምስኪኖችና የልብ ስብራት ያላቸው ሰዎች ጸሎት ምድርን የመለወጥ ኃይሉ ከፍተኛ የሚሆንበት ዓመት ነው።
*ደግ ምንሰማበትና ምናይበት አመት ያድርግልን!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
የዑስማኒያ ታሪክ ጸሐፊና ተጓዥ ኤቭሊያ ቸለቢ በጉዞ ማስታወሻቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፦ ሱልጣን ሙራድ 4ኛ ልክ እንደሌሎቹ የኦቶማን ሱልጣኖች፣ የተራ ሰው ልብስ ለብሰው፣ በሌሊት የሕዝቡን ሁኔታ መፈተሽ ያዘወትሩ ነበር። አንድ ቀን ሌሊት ሱልጣኑ ከታማኝ አገልጋዩ ጋር ሆኖ በኢስታንቡል ታዋቂው የንግድ ማዕከል አቅራቢያ ሲያልፍ፣ በአንድ ትንሽ ሱቅ ውስጥ መብራት በርቶ ይመለከታል። ወደ ሱቁ ጠጋ ሲሉ፣ አንድ በጣም ረጋ ያለ፣ ሽበት የበዛበትና ፊቱ በብርሃን የተሞላ ጫማ ሰፊ ብቻውን ተቀምጦ ጫማ ሲሰፋ ያገኙታል።
ሱልጣኑና አገልጋዩ ተራ መንገደኛ መስለው ወደ ሱቁ ገቡና «ሰላም ላንተ ይሁን አባት ሆይ፣ በዚህ ሌሊት ምን እየሰሩ ነው?» አሉ። ሽማግሌው ቀና ብለው ተመለከቱ፤ የሚገርመው፣ ሱልጣኑ ልብሱን ቀይሮ የመጣ ቢሆንም፣ ገና ሲያዩት ማንነቱን አውቀው ነበር። ሽማግሌውም ፈገግ አሉና «ሰላም ላንተም ይሁን ሱልጣኔ! እንኳን ደህና መጣህ። እኔ የአላህን ሲሳይ ፍለጋ ጫማ እየሰፋሁ ነው» አሉ። ሱልጣን ሙራድ በማንነቱ መታወቅ እጅግ ደነገጠ። ወዲያውም ይህ ሰው ተራ ጫማ ሰፊ እንዳልሆነ ተረዳ። ሱልጣኑ በክብር ተቀምጦ ከሽማግሌው ጋር ማውራት ጀመረ። በጨዋታቸው መሃል፣ ሽማግሌው ጫማውን በሰፉ ቁጥር፣ «ያ ኸድር... ያ ኸድር...» እያሉ ይተነፍሱ ነበር።
ሱልጣኑ ይህንን ሲሰማ በጥንቃቄ ተመለከታቸውና እንዲህ አለ፦ «አባት ሆይ! "ያ ኸድር" እያልክ ትጠራለህ። ለመሆኑ ኸድርን (ዐ.ሰ) አይታችሁ ታውቃላችሁ? ወይስ ዝም ብላችሁ ነው ስሙን የምታነሱ?» ጫማ ሰፊው ሽማግሌ መርፌቸውን አስቀመጡና ወደ ሱልጣን ሙራድ 4ኛ ቀረብ ብለው ፈገግ አሉ፦ «ሱልጣን ሆይ! አንዳንድ ሰዎች ኸድርን ለማግኘት እድሜያቸውን ሙሉ በተራራና በባህር ዳርቻ ይፈልጉታል። ነገር ግን ኸድር አንዳንድ ጊዜ በየቀኑ ወደ ሱቃቸው እየመጣ አጠገባቸው እንደሚቀመጥ አያውቁም። ለምሳሌ አሁን እኔ "ያ ኸድር" ባልኩ ቁጥር፣ እርሱ እዚህ አጠገቤ ተቀምጦ መርፌውን ሲያቀብለኝ ይታየኛል» አሉ።
ሱልጣኑ ይህንን ሲሰማ በሰውነቱ ላይ የደስታና የፍርሃት ስሜት ፈሰሰ። ወዲያውኑ ሽማግሌውን በጥብቅ ተመልክቶ «እባክህ ያ ሰይዲና! አንተ እራስህ ኸድር ነህ አይደል?» ብሎ እጁን ሊስም ተጠጋ። ሽማግሌው ግን እጃቸውን ሳቡና፦ «አይደለሁም ሱልጣኔ፣ እኔማ የኸድር ምስኪን ወዳጁ ነኝ። እርሱ ግን አሁን ከዚህ ሱቅ ወጥቶ ወደ ባህር ዳርቻው ሄዷል» አሉት። ሱልጣን ሙራድ 4ኛ ከዚያ ሱቅ የወጣው የዱንያ ንግሥና ከተራው ጫማ ሰፊ መንፈሳዊ ደረጃ ጋር ሲነጻጸር ምን ያህል ኢምንት እንደሆነ ተረድቶ ነበር።
አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ ሰይዲና ሙሐመድ!
አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
#ለይለተል_ጁሙኣ
ታዋቂው የኦቶማን ተጓዥ እና የታሪክ ጸሐፊ እቭሊያ ቸለቢ ገና የ20 ዓመት ወጣት እያለ፣ ልቡ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፍቅር የተቃጠለ እና ሁልጊዜም እርሳቸውን በህልሙ ለማየት የሚናፍቅ ስስ ልብ የነበረው ወጣት ነበር። በኢስታንቡል ከተማ ይኖር በነበረበት ወቅት፣ በአንድ የተባረከ የጁምዓ ምሽት (ለይለተል ጁምዓ) ሌሊቱን ሙሉ ቁርዓን ሲቀራ፣ ሰለዋት ሲያወርድና እያለቀሰ ዱዓ ሲያደርግ አደረ። በለሊቱ መጨረሻ ላይ እዚያው ቁርዓኑ ላይ እንዳለ እንቅልፍ ወሰደው። እቭሊያ ቸለቢ በህልሙ እራሱን በኢስታንቡል ከተማ በሚገኘው በታዋቂው "አሂ ቸለቢ መስጂድ" ውስጥ አገኘው። መስጂዱ በሰው የተሞላ ቢሆንም፣ በውስጡ ያሉት ሰዎች በሙሉ መላእክት፣ ታላላቅ ሶሃቦችና ሰማዕታት ነበሩ። መላው መስጂድ በብርሃን (ኑር) ተሞልቷል።
በድንገት ከመስጂዱ ሚህራብ (የሶላት መሪው ቦታ) አጠገብ ፍጹም ብርሃን የሆኑት ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በግርማ ሞገስ ተቀምጠው ተመለከተ። ሰሃባው ሰዕድ እብኑ አቢ ወቃስ (ረ.ዐ) እቭሊያ ቸለቢን እጁን ይዞ ወደ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፊት አቀረበው።
ወጣቱ እቭሊያ ቸለቢ በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ግርማ ሞገስና ውበት ፍጹም ተደንቆ፣ ልቡ በደስታና በፍርሃት እየመታች እግራቸው ስር ወደቀ። ከመምጣቱ በፊት በለይለተል ጁምዓ ሲያለቅስ የነበረው ነብዩን (ሰ.ዐ.ወ) "የእርስዎን አማላጅነት (ሸፋዐት) እፈልጋለሁ" ለማለት ነበር።
ነገር ግን በነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ፊት በቆመ ጊዜ፣ በደስታና በድንጋጤ ብዛት አንደበቱ ተሳሰረ። "ሸፋዐት ያ ረሱለላህ" ማለት ሲገባው፣ በአፉ የመጣውና የተናገረው እንዲህ ነበር፡ "ሰያሀት ያ ረሱለላህ!" (የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ጉዞ/ጉብኝትን እሻለሁ!)
ታላቁ ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የወጣቱን መሳሳትና የልቡን ንፅህና ተመልክተው በደማቅ ሁኔታ ፈገግ አሉ። ከዚያም የተሳሳተውንም ያልተሳሳተውንም አጣምረው እንዲህ አሉት፦ "አላህ ሁለቱንም ይስጥህ! ሸፋዐቴም (አማላጅነቴም)፣ ሰያሀትህም (ጉዞህም) ይስጥህ፤ የአለምን ድንቆች የምታይበትና የምትመሰክርበት ረጅም እድሜ ይስጥህ!" አሉት።
በመቀጠልም በቦታው የነበሩት ሶሃቦች በሙሉ ለእቭሊያ ቸለቢ ዱዓ አደረጉለት። ከህልሙ በደስታና በዕንባ ተውጦ ሲነቃ፣ ያ የተባረከ የአርብ ምሽት ህልም የሕይወቱ መመሪያ እንደሆነ ተረዳ።
ከዚህ የለይለተል ጁምዓ መናም በኋላ፣ እቭሊያ ቸለቢ ከኢስታንቡል በመነሳት በመላው የኦቶማን ግዛት፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አፍሪካ እና በመካከለኛው ምስራቅ (መካ እና መዲናን ጨምሮ) ለ50 ዓመታት ያህል ተጓዘ። ያየውንና የታዘበውን ሁሉ "ሰያሀት ናሜ" (የጉዞ ማስታወሻ) በሚባለው ታዋቂ የ10 ጥራዝ መጽሐፉ ውስጥ አሰፈረው።
በጁሙኣ የአባባ ሰለዋት ስጦታ
<اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى مَركَز الأَنْبِيَاءُ وَالأَوْلِيَاءُ ، وَآلِهِ وَصَحْبِهِ أُولِي الْفَضْلِ وَالأَتْقِيَاءِ.>
#መደድ_ያአላህ!
#ሸፈኣት_ያረሱሉሏህ!
#ሂመት_ያአባራሙዝ!
@abduftsemier
@abduftsemier
4 467
أهل المودة في فناء جالو
إلى أن وصلوا في الجهات سارو
اللهم صلى على محمد (٢)
مدينة النور وأرباب الصفا
4 467
#የሰይዲና_ኸድር_ቅዳሜ
ሱልጣን አብዱልሀሚድ በጣም አስቸጋሪና የሀገር ህልውና የሚወሰንበት ዲፕሎማሲያዊ ቀውስ በገጠማቸው ቁጥር፣ ወደ ግል መስገጃ ክፍላቸው (ኸልዋ) ይገቡና ረጅም ሰዓት ይቆያሉ። በአንድ ወቅት፣ አንድ የቅርብ አገልጋያቸው በሩ ላይ ቆሞ ሳለ፣ ሱልጣኑ በክፍሉ ውስጥ ከሌላ ሰው ጋር በዝቅተኛ ድምፅ ሲነጋገሩ ይሰማል። ነገር ግን ወደ ክፍሉ የገባ ምንም ሰው አልነበረም። በኋላ ላይ ሱልጣኑ ከክፍሉ ሲወጡ ፊታቸው በደስታ በርቶ ነበር። አገልጋዩ ደፍሮ «ሱልጣኔ ሆይ! ብቻዎን ሆነው ማንኑን እያማከሩ ነበር?» ብሎ ጠየቃቸው። ሱልጣኑም ፈገግ ብለው፦ «በዚህ የጭንቅ ሰዓት ዑስማኒያን ብቻዋን የማይተዋትና በአላህ ፍቃድ መመሪያ ይዞልኝ የሚመጣው ሰይዲና ኸድር ነበረ። እርሱ አሁን የመጣው የፈረንሳይንና የእንግሊዝን ተንኮል እንዴት እንደምሰብር ሊነግረኝ ነው» በማለት ምስጢሩን ገልጠውለታል።
በሌላ ጊዜ የጁምዓ ሶላት ከተሰገደ በኋላ፣ ሱልጣን አብዱልሀሚድ ከሕዝቡ ጋር ሰላምታ እየተለዋወጡ ሳለ፣ አንድ በጣም ያረጀ ልብስ የለበሰ፣ አይኑ ገርመም የሚያደርግ ሽማግሌ ወደ ሱልጣኑ ቀረበ። ሽማግሌው የሱልጣኑን እጅ በጥብቅ ይዞ ሰላም ካላቸው በኋላ፣ በጆሯቸው ጠጋ ብሎ «የአላህ አደራ በአንተ ላይ ይሁን፣ በፅናት ቁም!» አላቸው። ሱልጣኑ የሰውየውን እጅ በያዙበት ቅጽበት፣ በሰውነታቸው ላይ ልዩ የመንፈስ እርካታና ሙቀት ተሰማቸው። ሰውየው ሰይዲና ኸድር መሆናቸውን ወዲያውኑ የተረዱት ሱልጣኑ፣ እጃቸውን ሳይለቁ «ዱዓእ አድርጉልኝ ያ ሰይዲና» አሏቸው። ሽማግሌውም ፈገግ ብለው «አላህ ካንተ ጋር ነው» ካሉ በኋላ፣ ወደ ህዝቡ መሃል ገብተው በአንድ ቅጽበት ተሰውሩ።
ሱልጣን አብዱልሀሚድ በ1909 ዓ.ም (በምዕራባውያንና በሀገር ውስጥ ተንኮለኞች ሰበብ) መፈንቅለ መንግስት ሲደረገባቸውና ዑስማኒያ ወደ መፍረስ በተቃረበችበት ወቅት፣ በኢስታንቡል የነበሩ ታላላቅ አውሊያዎች (ለምሳሌ እንደ ሸይኽ ዛፊር ያሉ) በህልማቸውና በከሽፋቸው ያዩትን ታሪክ እንዲህ ሲሉ ዘግበውታል፦ «ሱልጣኑ ከስልጣን በወረዱበት ሌሊት፣ ሰይዲና ኸድር በኢስታንቡል ባህር ዳርቻ ላይ ቆመው በከፍተኛ ሃዘን ሲያለቅሱ ታዩ። "ዛሬ የዑስማኒያ መንፈሳዊ ጋሻ ተሰበረ፣ ለኢስላም ኡማ የሚያለቅሰው የአላህ ወዳጅ ወደቀ" እያሉ አዝነዋል።»
"O yüce Osmanlılara selam olsun!"
"ሰላም ለታላቆቹ ዑስማኖች!"✋
*አላሁመ ሷሊ ወሰሊም አላ መርከዚል አንቢያዕ ወል አውሊያዕ!
*አላሁመ ሷሊ አላ ሰይዲና ኸድር!
#አባ_ደዋም
#እነሆ_አዲሱ_ዘመን!
@abduftsemier
@abduftsemier
