fa
Feedback
አቤል ተፈራ በላይ

አቤል ተፈራ በላይ

رفتن به کانال در Telegram
3 067
مشترکین
-124 ساعت
-57 روز
-6230 روز
آرشیو پست ها
እንኳን ለአባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ፍልሰተ አጽም ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ! የቅዱስ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ጸሎት "...  አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የመንግስተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ትቼ ወጣሁ ጌታዬ ሆይ እንግዲህ ለችግረኛው ለእኔ ያላንተ ረዳት የለኝም ለደካማው ለኔ ያላንተ የሚያፅናናኝ የለኝም ከመውደቅም ያለንተ የሚያነሳኝ የለኝም ላዘንኩ ለእኔም ካላንተ የሚያረጋጋኝ የለኝም ለደሃው ለእኔ ያለንተ መጠጊያ የለኝም አቤቱ ፊትህን እሻለሁ ያንተን ፊት እሻለሁ ፊትህን ከኔ አትመልስ አምልኮትህን ፈለግኩ አታሳፍረኝ ረዳት ሁነኝ እንጂ አትጣለኝ ..." ገድለ ተክለ ሃይማኖት ም.29 ❤️

እመቤታችን የተወለደችበት መታሰቢያ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ ከሞቀው ቤታችን ወጥተን ድንኳን በመጣል ወደ ውጭ እንወጣለን የሚያሳዝነው ነገር ግን ድንኳኖቻችን በዝማሬ መድመቅ ሲገባቸው እኛ ግን የልደቷን ባለቤት በማይመጥን መልኩ የዘፈን ዳንኪራ ቦታ እናደርጋቸዋለን። አካባቢያችሁን ቃኝታችሁ እስቲ ንገሩኝ ተወዳጆች ተሳስቻለሁ ? በየመንደሩ በዚህ የተነሳ ድኅነት የሚገኝባት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እና ክብሯ ይጎድፋል። በዓላቶቻችን ሁሉ የጌታን ክብር የመግለጥ አባቶቻችን እስከ ሙሉ መንፈሳዊ ሞገሳቸው ቢሰጡንም እኛ ግን የኃጢአት እና የዓለማዊነት ፍላጎታችን መፈጸሚያ የርኩሰት ሜዳ እያደረግናቸው መሆኑ ሲታይ ያሳዝናል።

ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው። ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም። ሉቃስ ፳፬:፭ እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን ­ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ትንሣኤው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና  አደረሰን­።🙏

ኢየሱስ_ቃል_በቃል_አምላክ_ነኝ_አምልኩኝ_ያለው_የቱ_ጋር_ነው_Where_Did_Jesus_Say_I_Am.mp315.26 MB

"መሬት ረገጥኩሽ መልሼ ቀልሼ፤ ኋላ እታረቃለሁ ሙሉ አካሌን ክሼ።" አለ ባለ ዘለሰኛው! ዘንድሮስ መሬትም ናት እንደ ሰው ከፋችብን💔 በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባን ወረዳ በተከሠተው የመ
"መሬት ረገጥኩሽ መልሼ ቀልሼ፤ ኋላ እታረቃለሁ ሙሉ አካሌን ክሼ።" አለ ባለ ዘለሰኛው! ዘንድሮስ መሬትም ናት እንደ ሰው ከፋችብን💔 በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባን ወረዳ በተከሠተው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቍጥር ከ102 በላይ ኾኗል💔 በተለያዩ ገዳማት ያሉ መናንያን መነኰሳትና የአብነት ተማሪዎች እንዲኹም ኦርቶዶክሳዊው የገጠር ማኅበረሰብ በተጠናና በታቀደ መዋቅር በከባድ የጦር መሣሪያ እያለቀ ነው💔 በተፈጥሮም ኾነ በሰው ሠራሽም አደጋ በየቦታው ያረፉ የወገኖቻችንን ነፍስ ይማርልን! ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ይስጥልን። (ለእኛ ለተረኞች ደግሞ የንስሓ ጊዜ ያድርግልን!!! የአበውን ቃል አስታውሱ! ጦርነት፣ ረኀብ፣ መቅሠፍት ወረርሽኝ (በሽታ) ገና ወደፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ገና ለቀጣዮቹ 2 ዓመታት ያህል እጅግ እየከፋ እንደሚሔድ አበው የተናገሩትን አንርሳ! መፍትሔው ንስሓ ነው። የምድሩ ቢቀር ከሰማዩ ከቅዱሳኑ ርስት የተለየን እንዳንኾን።)

ዛሬ የተፈጸመው ነገር ያሳዝናል አባ አይናለም የወልድያ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ትናት ማታ በሁለት ጥይት ተመተው ተገድለዋል። ማታ በግምት ከ2:30 - 3 ሰዓት ጥይት ተመተው ሰው በሰዓቱ ባለመድረሱ የተነሳ ደማቸው ፈሶ ነፋሳቸው ተለይታ ጠዋት ሬሳቸው ተገኝቷል። የወልድያ ምዕመናን ልብ የሰበረ ጉዳይ ሁኗል።

ቲክቶክ በክርስትና እይታ ክፍል 1 (1).mp39.16 MB

04_የኤፌሶን_መልእክት_ምዕራፍ_አራት_1.pdf0.77 KB

03_የኤፌሶን_መልእክት_ምዕራፍ_ሦስት_ጥናት.pdf0.90 KB

02_የኤፌሶን_መልእክት_ምዕራፍ_ሁለት_ጥናት.pdf0.71 KB

پیام صوتی02:18

01_የኤፌሶን_መልእክት_ምዕራፍ_አንድ_ጥናት.pdf0.71 KB

پیام صوتی06:31

پیام صوتی01:52