3 067
مشترکین
-124 ساعت
-57 روز
-6230 روز
آرشیو پست ها
3 067
እንኳን ለአባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ፍልሰተ አጽም ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ !
የቅዱስ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ጸሎት
"... አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የመንግስተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደተከፈተ ትቼ ወጣሁ ጌታዬ ሆይ እንግዲህ ለችግረኛው ለእኔ ያላንተ ረዳት የለኝም ለደካማው ለኔ ያላንተ የሚያፅናናኝ የለኝም ከመውደቅም ያለንተ የሚያነሳኝ የለኝም ላዘንኩ ለእኔም ካላንተ የሚያረጋጋኝ የለኝም ለደሃው ለእኔ ያለንተ መጠጊያ የለኝም አቤቱ ፊትህን እሻለሁ ያንተን ፊት እሻለሁ ፊትህን ከኔ አትመልስ አምልኮትህን ፈለግኩ አታሳፍረኝ ረዳት ሁነኝ እንጂ አትጣለኝ ..."
ገድለ ተክለ ሃይማኖት ም.29 ❤️
3 067
እመቤታችን የተወለደችበት መታሰቢያ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ ከሞቀው ቤታችን ወጥተን ድንኳን በመጣል ወደ ውጭ እንወጣለን የሚያሳዝነው ነገር ግን ድንኳኖቻችን በዝማሬ መድመቅ ሲገባቸው እኛ ግን የልደቷን ባለቤት በማይመጥን መልኩ የዘፈን ዳንኪራ ቦታ እናደርጋቸዋለን። አካባቢያችሁን ቃኝታችሁ እስቲ ንገሩኝ ተወዳጆች ተሳስቻለሁ ?
በየመንደሩ በዚህ የተነሳ ድኅነት የሚገኝባት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እና ክብሯ ይጎድፋል። በዓላቶቻችን ሁሉ የጌታን ክብር የመግለጥ አባቶቻችን እስከ ሙሉ መንፈሳዊ ሞገሳቸው ቢሰጡንም እኛ ግን የኃጢአት እና የዓለማዊነት ፍላጎታችን መፈጸሚያ የርኩሰት ሜዳ እያደረግናቸው መሆኑ ሲታይ ያሳዝናል።
3 067
ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው። ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም። ሉቃስ ፳፬:፭
እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ትንሣኤው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።🙏
3 067
"መሬት ረገጥኩሽ መልሼ ቀልሼ፤
ኋላ እታረቃለሁ ሙሉ አካሌን ክሼ።" አለ ባለ ዘለሰኛው! ዘንድሮስ መሬትም ናት እንደ ሰው ከፋችብን💔
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባን ወረዳ በተከሠተው የመሬት መንሸራተት እና የጎርፍ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቍጥር ከ102 በላይ ኾኗል💔
በተለያዩ ገዳማት ያሉ መናንያን መነኰሳትና የአብነት ተማሪዎች እንዲኹም ኦርቶዶክሳዊው የገጠር ማኅበረሰብ በተጠናና በታቀደ መዋቅር በከባድ የጦር መሣሪያ እያለቀ ነው💔
በተፈጥሮም ኾነ በሰው ሠራሽም አደጋ በየቦታው ያረፉ የወገኖቻችንን ነፍስ ይማርልን! ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ይስጥልን።
(ለእኛ ለተረኞች ደግሞ የንስሓ ጊዜ ያድርግልን!!! የአበውን ቃል አስታውሱ! ጦርነት፣ ረኀብ፣ መቅሠፍት ወረርሽኝ (በሽታ) ገና ወደፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ገና ለቀጣዮቹ 2 ዓመታት ያህል እጅግ እየከፋ እንደሚሔድ አበው የተናገሩትን አንርሳ! መፍትሔው ንስሓ ነው። የምድሩ ቢቀር ከሰማዩ ከቅዱሳኑ ርስት የተለየን እንዳንኾን።)
3 067
ዛሬ የተፈጸመው ነገር ያሳዝናል አባ አይናለም የወልድያ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ትናት ማታ በሁለት ጥይት ተመተው ተገድለዋል።
ማታ በግምት ከ2:30 - 3 ሰዓት ጥይት ተመተው ሰው በሰዓቱ ባለመድረሱ የተነሳ ደማቸው ፈሶ ነፋሳቸው ተለይታ ጠዋት ሬሳቸው ተገኝቷል።
የወልድያ ምዕመናን ልብ የሰበረ ጉዳይ ሁኗል።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
