cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ወአማኑኤል ቤተክርስቲያን

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
257
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

#ማስታወቂያ የዩቲዩብ ቻናል መግዛት ለሚፈልግ ማንኛውም ሰው #Watch_houre > 6000+ #View >280k+ #Subscriber >3400+ #Monetization on ይህንን የዩቲዩብ ቻናል መግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው +25198822340 ወይም @habmisget ማናገር ይችላል የማቴገዙ ጊዜችን አታጥፉ እውነተኛ ገዥ ብቻ አናግሩን
نمایش همه...
#መጽሐፍቅዱስ [በአንድ ተራራማ ስፍራ እርሻ በማረስ ከልጅ ልጁ ጋር የሚኖር አንድ ሽማግሌ ነበር፡፡ ይህ ሽማግሌ ዘወትር ፀሐይ ብርሃኗን ስትፈነጥቅ እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱስን ያነባል፡፡ የልጅ ልጁ የአያቱን ተግባር ይከታተል ስለነበር እሱም ያያቱን ፈለግ በመከተል ጠዋት ጠዋት እየተነሳ መጽሐፍ ቅዱን ማንበብ ጀመረ፡፡](https://t.me/+EdNOvg5AOZU3OTc0 አንደ ቀን ታድያ አያቱን “አባባ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ እየሞከርኩ ነበር፡፡ ነገር ግን ልረዳው አልቻልኩም ደግሞም አንብቤ እንደጨረስኩ ወዲያውኑ እረሳዋለሁ እናም እንድረዳውና እንዳልረሳው ምን ማደረግ አለብኝ?” ሲል ጠየቀ፡፡ [ሽማግሌው ምንም ድምጽ ሳያሰሙ “ከሰሉን ወደ ምድጃው ጨመሩና እንካ ይሄን የከሰል ቅርጫት ይዘህ ወንዝ ውረድና ውሃ ይዘህልኝ ተመለስ” አሉት፡፡ ልጁ ትዛዙን ለመፈጸም ወደወንዝ ወርዶ ውሃውን ይዞ ሊመለስ ቢመክርም ቅርጫቱ ውሃውን እያንጠባጠበ ቤት ከመድረሱ በፊት ፈሶ አለቀበት፡፡ ሽማግሌው የልጁን ሁኔታ እያስተዋሉ “አሁን ለሁለተኛ ጊዜ ይዘህ ስትመጣ ግን ፈጠን ፈጠን ብለህ ተመለስ ብለው” ድጋሜ ላኩት፡፡ አሁንም ልጁ እንደተነገረው በፍጥነት ውሃውን ቀድቶ ሊመለስ ቢሞክርም ቤቱ ሳይደርስ ውሃው ፈሶ አለቀበት፡፡ አያቱንም “በቅርጫት ውሃ ማምጣት ስለማይቻል ሌላ መያዥ ይስጡኝና ላምጣ” ሲል ጠየቀ፡፡ ሽማግሌ አያቱም “እኔ የምፈልገው የቅርጫት ውሃ ነው፡፡ ጠንክረህ ባለመሞከርህ ነው ፈሶ ያለቀብህ” በማለት እንደገና ላኩት፡፡ በዚህ ጊዜ ልጁ በቅርጫት ውሃን ማምጣት እንደማይቻል ቢያውቅም ለአያቱ ታዛዥነቱን ለማሳየት ከበፊቱ ፈጥኖ ለማምጣት ሲሞክር ውሃው ፈሶ ስላለቀበት ባዶውን ቅርጫት እያሳየ “ተመልከት አባባ! እዲሁ ነው የምደክመው እንጅ እኮ ጥቅም የለውም” አለ፡፡](https://t.me/+EdNOvg5AOZU3OTc0) ከዚህ ጊዜ ምልልስ በኋላ ሽማግሌው “እስኪ ቅርጫቱን ተመልከተው” አሉት፡፡ ልጁ ቅርጫቱን ሲመለከት ከዚህ በፊት የማያውቀው ቅርጫት ይመስል ቅርጫቱ የተለየ ሆነበት የከሰል መያዣ እያለ በጅጉ የቆሸሸ ነበር፡፡ አሁን ግን ሙልጭ ብሎ ጸድቷል፡፡ ውስጡን ሲመለከተው ከመንጻቱ የተነሳ የበፊቱ ቅርጫት አልመስለው አለ፡፡ [ስለዚህ ልጄ መጽሐፍ ቅዱስን ስታነብ የሚሆነው እደሱ ነው፡፡ ላትረዳው ትችል ይሆናል ወይም ደግሞ ያነበብከውን ሁሉንም ነገር ላታስታውሰው ትችል ይሆናል ዳሩ ግን ባነበብክ ቁጥር ለውጨኛው የሚተርፍ ውስጣዊ ንጽህና እያመጣህ መሆኑን አትዘንጋ የመንፈስ ሥራ እንደዚህ ነው በማለት አስተማሩት፡፡](https://t.me/+EdNOvg5AOZU3OTc0) (ከምስጋናው ግሸን ወልደ አገሬ) ይከታተሉን👇 @mekraabaw በዩቲዩብ ለመከታተል👇 https://youtu.be/Hb86WTpY94I
نمایش همه...
ቻናላችን ለመቀላቀል
ኦርቶዶክሳዊት ምክር ለማግኘት
ምክረ አበው -Mekra_@b`q
🔺በዩቱዩብ ለማግኘት subscribe ያድርጉ🔺
🔴عاجل الحرب العالمية
#ጀሃድ_አወጁ!!☝️☝️☝️ ሁላችሁም ኦርቶዶክሳዊያን ይሄነን ቮይስ ስሙ!☝️ እኛ እራሳችሁን እንድትጠብቁ እና እንድትጠነቀቁ እንጅ ግደሉ ሚል አምላክ ስለሌለን እንደ እነሱ ገጀራ አናነሳም! የክርስቲያን ዝርያት በሙሉ የተዋሕዶ ልጅ ሆነ ፕሮቴስታንት የሆነ ሁሉ ይዳረስ ይስማ በክርስቲያን ላይ በሙሉ ነው እያወጁ ያሉት! ማንኛውም ሰው በቴሌግራም አካውንት ላለው ኦርቶዶክስ በሙሉ ሸር ያድርግ!!! ለበለጠ መሰል መረጃዎች በቴሌግራም ሊንኩን በመጫን ተ #ዲ ን እሱባለው✍(ሥሙር) ¶¶¶ ልዩ ልዩ የሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትምህርቶች ፣መዝሙሮችን ፣ ግጥሞችን የሚፈልጉትን የመፅሐፍ ቅዱስን ቃል ያገኛሉ • • • • ለመቀላቀል ለሌላም ሰው ለማጋራት👇👇👇 🇪🇹ኢትዮጵ🇪🇹 @KIDUS017
نمایش همه...
3.80 KB
★ መረቡን ከታንኳይቱ በስተቀኝ ጣሉ ★ ስምዖንና ጓደኞቹ ዓሣ አጥማጆች ናቸው። ሌሊቱን ሙሉ ሲያጠምዱ አድረው አንድ ዓሣ እንኳን ሳይይዙ ነጋባቸው። ባዶ መረባቸውን እያጠቡ እያለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እነርሱ መጣ። አስተምሮ ከጨረሰ በኋላ ስምዖንን : "ወደ ጥልቁ ፈቀቅ በል መረቦቻችሁንም ለማጥመድ ጣሉ" አለው። ስምዖን ከአምስት ዓመቱ ጀምሮ ዓሣ ሲያጠምድ ያደገ የሃምሳ አምስት ዓመት ጎልማሳ ነው። ሆኖም "ጥርሴን የነቀልኩበት ሙያ ነው" ብሎ ሳይመፃደቅ "አቤቱ ሌሊቱን ሁሉ አድረን ስንደክም ምንም አልያዝንም። ነገር ግን በቃልህ መረቦቹ እጥላለሁ" አለ። የጌታን ትእዛዝ አክብረው ወደ ጥልቁ ፈቀቅ ብለው መረባቸውን ሲጥሉ እጅግ ብዙ ዓሣ ያዙ ፣ መረቦቻቸውም ተቀደዱ። በሌላ ታንኳ የነበሩት ጓደኞቻቸውን እንዲያግዙአቸው ጠሩአቸው። ታንኳው እስኪሠጥም ድረስ መረቡ በዓሣ ተሞላ። ይህንን ተአምር ያዩ ሁሉ ሲደነቁ ስምዖን ጴጥሮስ ግን ጌታችንን ፈራው። በዚህ ትልቅ ባሕር ውስጥ ያለውን መርምሮ ካወቀ በእኔ ልብ ውስጥ ያለውን ኃጢአትማ እንዴት ያውቅብኝ ይሆን? ብሎ ተጨነቀ ፣ የረከሰ ሕይወቱን አስቦ ራሱን ተፀየፈ። ከኢየሱስ ጉልበት ላይ ወድቆ "ጌታ ሆይ እኔ ኃጢአተኛ ነኝና ከኔ ተለይ" አለው። ጌታ ግን "አትፍራ ከእንግዲህ ወዲህ ሰውን የምታጠምድ ትሆናለህ" አለው። ያቺ ዕለት ስምዖን ጴጥሮስና ጓደኞቹ ጌታ ባዘዛቸው መሠረት መረብ እየጣሉ ዓሣ ማጥመድ የጀመሩባት ዕለት ሆነች። (ሉቃ 5:3) ይህ ከተፈፀመ ከሦስት ዓመታት በኋላ ጌታችን በመስቀል ተሰቅሎ ሞቶ ከተነሣ በኋላ ትንሣኤውን ሙሉ በሙሉ ያላመኑት ስምዖን ጴጥሮስና ጓደኞቹ ዓሣ ለማጥመድ ወደ ባሕር ሔደው ነበር። ጌታችን በዚህ ጊዜ ከመካከላቸው ተገኝቶ "አንዳች የሚበላ አላችሁ?" አላቸው። እነርሱም የለንም አሉት። ይህን ጊዜ "መረቡን በታንኳይቱ በስተቀኝ ጣሉት ታገኙማላችሁ" አላቸው። መረቡን ሲጥሉ ከዓሣው ብዛት የተነሣ ሊጎትቱት አቃታቸው። (ዮሐ 21:6) በጌታ ትእዛዝ ዓሣ ሁለት ጊዜ የሚጠመድባት ይህች መረብ በዓሣ የተመሰልን እኛን የሰበሰበች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት። በመጀመሪያው ዙር ዓሣ የማጥመድ ሥራ የተካሔደው "ወደ ጥልቁ በመሔድ ነበር" ቤተ ክርስቲያን ከዚህች ዓለም ባሕር ውስጥ ብዙዎችን አጥምዳለች። በዚህ ዓለም በኃጢአት ዐዘቅት ውስጥ ጠልቀው የገቡትን ሰዎች ሳይቀር መረብዋ ቤተ ክርስቲያን ወደ ጥልቁ ፈቀቅ ብላ አጥምዳ ሰብስባለች። በዚህ ነፍሳትን የማጥመድና ወደ መረቡ የማስገባት ሥራ ላይ የተመደቡት እነቅዱስ ጴጥሮስ ቢሆኑም ከዓሣዎቹ ብዛት የተነሣ ለብቻቸው ሊወጡት አልቻሉም። ስለዚህ በሌላ ታንኳ የነበሩ ጓደኞቻቸውን ጠርተው መረቡን በዓሣ ሞሉት። እነዚህ በረዳትነት የተጠሩት የሐዋርያት ጓደኞች ምእመናንን ከዓለም ጥልቅ ውስጥ በትምህርት እየሳቡ ወደ መረቧ ቤተ ክርስቲያን ሲያስገቡ የኖሩ አርድእት ፣ ሐዋርያውያን አበው ፣ ሊቃውንትና ካህናት ናቸው። በጴጥሮስና በመሰሎቹ ትጋት ዛሬ ቤተ ክርስቲያን በብዙ ዓሣዎች ተሞልታለች። ዓሣዎቹ በበዙ ጊዜ መረቡ ተቀድዶ ነበር። እንደዚሁም ኃጢአተኛውን ከጻድቁ ክፉውን ከደጉ ሳትለይ ከሁሉም ዓይነት የሰበሰበችው ቤተ ክርስቲያን በየጊዜው በዓሣዎቿ ብዛት ብዙ የመቀደድ ፈተና ገጥሟታል። አንዳንድ ዓሣዎች ከባሕር ከወጡ በኋላ ወደ ባሕር ለመመለስ ሲታገሉ ፣ አንዳንዶቹ ባሕር ውስጥ እያሉ እንደሚዋኙት ሊዋኙ ሲሞክሩ ፣ አንዳንድ ዓሣዎች መረብ ውስጥ ገብተው ሲፋለሙ መረቡን ቀድደውት ነበር። የእኛዋ መረብ ቤተ ክርስቲያንም ይህ ዓይነቱ በዓሣዎቿ ጦስ የመቀደድ ችግር ሁሌ እንደገጠማት እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ትቆያለች። ይህ ሁሉ ችግር ግን ጌታችን ዳግም እስኪመጣ ድረስ ነው። ወደነ ቅዱስ ጴጥሮስ ድጋሚ መጥቶ መረቡን ጣሉ ያለው ጌታ ስለ ቤተ ክርስቲያንም ይህን ማለቱ አይቀርም። እስቲ ሁለተኛውን የዓሣ ማጥመድ ሥራ አስተውለን እናንብበው። መጀመሪያ "ወደ ጥልቁ ጣሉ" ያለው ጌታ ከትንሣኤ በኋላ ግን "በስተቀኝ ጣሉ" ብሏል። ከጥልቁ ብዙ ዓሣዎች የሰበሰበችው መረብ ቤተ ክርስቲያን ጌታ ዳግም ሲመጣ ድጋሚ ዓሣ ትሰበስባለች። ያን ጊዜ ግን የምትሰበስበው "በስተቀኝ" ብቻ ነው። በዓሣዎችዋ ብዛት ስትቀደድ የኖረችው ቤተ ክርስቲያን ከትንሣኤ በኋላ ግን ዓሣዎችዋ ብዙ ቢሆኑም እንኳን አትቀደድም። ምክንያቱም ጌታ "በስተቀኝ ጣሉ" እንዳለው ከትንሣኤ በኋላ ወደ መረቡ የሚገቡት ጌታ አስቀድሞ በቀኙ ያቆማቸው ቅዱሳን ሰማዕታት ምእመናን ናቸው። ቅዱሳን ደግሞ የቱንም ያህል በቁጥር ቢበዙ መረብዋ እንድትቀደድ አያደርጉም። ጌታችን ዳግም መጥቶ መረብዋን ቤተ ክርስቲያን በሚያስጥልበት ጊዜ በስተቀኝ ሆነው ከሚገቡት ከነቅዱስ እስጢፋኖስ ፣ ከመጥምቁ ዮሐንስ ጋር ፣ ከሁሉም ቅዱሳን ሰማዕታት ጋር ለመገኘት ያብቃን። ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ 👇👇👇👇👇 @mekra_abaw
نمایش همه...
🔴 ምክረ አበው MEKRA ABAW™

#አባቶችን_ጠይቅ_ይነግሩሃል ● ጠቢብ ከሰነፍ ጋር ቢጣላ፥ ሰነፍ ወይም ይቈጣል ወይም ይስቃል፥ ደምን ለማፍሰስ የሚሹ ሰዎች ፍጹሙን ሰው ይጠላሉ፥ ደግሞም የቅኑን ሰው ነፍስ ይሻሉ። ሰነፍ ሰው ቍጣውን ሁሉ ያወጣል፤ ጠቢብ ግን በውስጡ ያስቀረዋል። ○ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕ. 29 ○ ሀሳብ ካላችሁ @habmisget

የፋሲካሰላምታአሰጣጥትርጉም ምሕዛል ወቃለ ባሕ ዘትንሣኤ Paschal troparion & Greeting ✍ (ለትንሣኤ የተቆነጠረ ሐሳብ) ሀገርኛው የዘውትር ሰላምታችን ሰላም ላንተ ይኹን👋 ጠላትኽን ያውድቅ ቢሰኛኽን ያርቅ! 🙏 በሚል መነሻ ስብሐተ እግዚአብሔር የሚታከልበት ምኞት መግለጫና ምስጋና ማቅረቢያ ነው! የሰላምታው መንገድ ደግሞ በሦስት ሂደት (በቃል በእጅና በአንገት) የሚከወን ነው። 🤝 መጨባበጥ (ተራክቦተ እድ ፣ ፅብጠት፣ ተጻብሖ) ☞ በእጅ የሚፈጸም ፦ በመጨባበጥ handshake በመተቃቀፍ hugging አልያም በጉንጭ በመሳሳም cheek kissing ይፈጸም የነበረውን በቀደሙቱ ዘንድ “አምኃ ቅድሳት” holy kiss & kiss of peace ⇨ ἐν ἁγίω φιλήματι, και φιλί της ειρήνης እየተባለ የሚጠራው መንገድ ነው! በዚኽ አጋጣሚ በወቅቱ ጉዳይ መጨባበጥ መተቃቀፍና መሳሳም ለወረርሽቹ በፍጥነት መዛመት ምክንያት መሆናቸውን አውቀን #አካላዊፈቀቅታ|ን በመጠበቅ በበሽታው የምናልፍ ሳንሆን በሽታውን የምናሳልፍ ነገንም የምናይ እንድንሆን በተከታዮቹ መንገዶች ሰላምታ የምንለዋወጥ ይሁን! 🙇 "እጅ መነሳሳት" (እማኄ) ☞ ባንገት፣ በወገብና በጕልበት የሚፈጸም ነው 🙋 የሰላምታ ቃል መለዋወጥ (በቃለ ተአምኆ) ሰላምታ በንግግር በመለዋወጥ የሚፈጸም ዋናዎቹ ናቸው! ወደ ተቆነጠረው ሐሳብ እንለፍ ተዝካረ ትንሣኤው በሚታሰብበት ዐባይ ፋሲካ ፶ ዕለት በቤተክርስቲያናችን የሚፈጸም የተለየ ሰላምታና የዜማ ድጋም አመላለስ አለ የጌታችን ተዝካረ ትንሣኤ በቤተክርስቲያናችን ሰፊ ቦታና ትርጉም ያለው በመሆኑ የዓመት ሢሦው (⅓) ነገረ ፋሲካን የሚያስታውስ ነው (የፋሲካ ጾም ⁵⁵ እና ዘመነ ትንሣኤ⁵⁰) በቅዳሴው መግቢያ መስዋእቱ ከቤተልሔም ወደ ቤተ መቅደስ ሲመጣ ከትንሳኤው እስከ በዓለ ፶ ጊዜው የተለየ መሆኑን ለማሳወቅ "እመቦ ብእሲ… " በሚለው መግቢያ ፈንታ "ሃሌ ሉያ ዮሴፍ ወኒቆዲሞስ ገነዝዎ ለኢየሱስ በሰንዱናት ለዘተንሥአ እሙታን በመንክር ኪነ ⇨ ሃሌ ሉያ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ድንቅ በሚሆን ጥበብ ከሙታን ተለይቶ የተነሣ ኢየሱስን በበፍታ ገነዙት፡፡" የሚል መልእክት በዜማ ይደርሳል! ከዚኽ ውጪ ምሕዛል ዘትንሣኤ ወይም «የፋሲካ አመላለስ» ያልነው Paschal troparion እና ቃለ ባሕ ዘትንሣኤ «የፋሲካ ሰላምታ» ያልነው Paschal Greeting ከወትሮው በተለየ መንገድ ይፈጸማል። ሁለቱም በልሳነ ጽርእ (ግሪክ) #ክሪስቶስ_አኔስቲ / Χριστὸς ἀνέστη እየተባለ ይጠራል ① #ምሕዛል_ዘትንሣኤ Paschal troparion የፋሲካ አመላለስ በእርግጥ ምሕዛል አልያም ምስትሕዛል የሚባለው በድጓው ሊቃውንቱ የሚያስተዛዝሉት ዜማ ድጋም ሲሆን መነሻውን ድጓ ያደረገው በቅዳሴው ክፍል የምናገኘው ይኽ የተዝካረ ትንሣኤ ምስትሕዛል፦ «ህየንተ ዝውእቱ ጊዜ ባርኮት እምትንሣኤ እስከ በዓለ ፶ » በሚል የገባ ሦስት ጊዜ ደጋግመን በመቀባበል የምናደርሰው " ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ ⇝ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ሞቶ ሞትን አጠፋው በመቃብር ላሉ የዘላለም ዕረፍት የሚሆን ሕይወትን ሰጠ " በሌሎች ምሥራቃውያን (Eastern ) እና ጽባሓውያን (Orientals) ዘንድም በእጅጉ የተለመደ ነው! በግሪክ ፓስካል ትሮፓርዮን አልያም χριστος ανεστη የሚባል በዜማ የሚደርስና የዘመነ ሐዋርያት ጭምር ጥንታዊ መገለጫ አለው ተብሎ የሚታመን ነው። Χριστὸς ἀνέστη ἐκ νεκρῶν, θανάτῳ θάνατον πατήσας, καὶ τοῖς ἐν τοῖς μνήμασι, ζωὴν χαρισάμενος! የንባባዊ ፍቺው አማርኛ ትየባ (transliteration) ደግሞ ይኽን ይመስላል! ክርስቶስ አኔስቲ ኤክ ኔክሮኒ ፣ ታናቶ ታናቶን ፓቲሳስ፣ ኬቲስ ኤን ቲስ ሚ’መሲ፣ ዞይን ካሪዛሜኖስ በትርጉሙም የእኛው " ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ ⇝ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ሞቶ ሞትን አጠፋው በመቃብር ላሉ የዘላለም ዕረፍት የሚሆን ሕይወትን ሰጠ " ካለው ጋር አቻ ፍቺ አለው Christ is risen from the dead, Trampling down death by death, And upon those in the tombs, Bestowing life! ② #ቃለባሕዘትንሣኤ Paschal Greeting «የፋሲካ ሰላምታ» በሓ ወይም ባሕ የሚባለው የሰላምታ የቡራኬ ቃል ፍሥሓ ሰላም የሚለውን የሚገልጥ ነው! በቤተክርስቲያናችን አበው መምህራንም ቅድመ ቃለ እግዚአብሔር ፣ ድኅረ ቃለ ቡራኬ ለ፶ው ዕለት ከምእመናን ጋር የሚለዋወጡት ሰላምታ ነው! ከዚያም አልፎ ምእመናንም ከምእመናን ጋር የትንሳኤውን የምሥራች ለማብሰርና መልካም ምኞት ለመግለጥ ያውሉታል። አቀራረቡ በአመላለስ አገባብ የሚከወን ሲሆን ሰላምታ ሰጪና ሰላምታ ተቀባይ ይኽን ይለዋወጣሉ፤ በኢትዮጵያዊቷ የተዋህዶ ቅድስት ቤተክርስቲያናችም ከ6ኛው ምዕተ ዓመት አንስቶ አገልግሎት ላይ መዋሉን መረጃዎች ይገልጣሉ። በቅዱስ ያሬድ ምዕራፍ (ዘመወድስ) ውስጥ በፍታሕ ሊተ ሥር በመሪና ተመሪ የሚቀርብ ዛሬ ለፋሲካ ሰላምታ የምንገለገልበት የትንሣኤው ምስክርነት ቃል አለ። እንዲህ ይላል ፦ ☞ ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ፣ በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን ፣ አሠሮ ለሰይጣን ፣ አግዓዞ ለአዳም ፣ ሰላም ፣ እምይእዜሰ ፣ ይኩን ፣ ሰላም! ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፣ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ፣ ሰይጣንን አሠረው፣ አዳምን ነጻ አወጣው ፣ ሰላም፣ ከዛሬ ጀምሮ ፣ ይሁን ፣ ሰላም በመቀባበል እንዲህ ተጽፏል ☞ Christ is risen from the dead! ☜ By the highest power and authority! ☞ He chained Satan! ☜ Freed Adam! ☞ Peace! ☜ Henceforth! ☞ Is! ☜ Joy and Peace! ☞ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን! ☜ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን! ☞ አሰሮ ለሰይጣን! ☜ አግዐዞ ለአዳም! ☞ ሰላም! ☜እምይእዜሰ! ☞ ኮነ! ☜ ፍስሐ ወሰላም! ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ ዲያብሎስን አሰረው አዳምን ነጻ አወጣው፤ሠላም ከዛሬ ጀምሮ ሰላም ሆነ..... See more👇👇 [@mekra abaw
نمایش همه...
ቻናላችን ለመቀላቀል
ኦርቶዶክሳዊት ምክር ለማግኘት
ምክረ አበው -Mekra_@b`q
የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) ማግባት ስትፈልግ አስቀድመህ ጸልይ፤ አሳብህን ለእግዚአብሔር ንገረው፡፡ እግዚአብሔር መርጦ እንዲሰጥህ ለምነው፡፡ ጭንቀትህን ኹሉ በእርሱ ላይ ጣለው፡፡ አንተ እንደዚህ እርሱ እንዲመርጥልህ የምታደርግ ከኾነም፥ አክብረኸዋልና እርሱም ለአንተ በጎ የትዳር አጋርን በመስጠት ያከብርሃል፡፡ ስለዚህ በምታደርገው ነገር ኹሉ ሽማግሌህ እርሱ እግዚአብሔር እንዲኾን ዘወትር ጠይቀው፡፡ አስቀድመህ እንደዚህ ካደረግህም፥ ወደ ትዳር ከገባህ በኋላ ፍቺ አይገጥምህም፡፡ ሚስትህ ሌላ ሰውን አትመኝም፡፡ በሌላ ሴት እንድትቀናም አታደርግህም፡፡ በመካከላችሁ [ለክፉ የሚሰጥ] ጠብና ክርክር አይኖርም፡፡ ከዚህ ይልቅ ታላቅ የኾነ ሰላምና ፍቅር በመካከላችሁ ይሰፍናል፡፡ እነዚህ ካሉ ደግሞ ሌሎች በጎ ምግባራትን፣ ትሩፋትን ለመፈጸም አትቸገሩም፡፡ #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ ምክረ አበው ጋብቻ ለሚፈጽሙ ሁሉ ሼር እናድርግ 👇👇👇👇👇 @mekra_abaw @mekra_abaw
نمایش همه...
ሕማማት ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ሰሙነ ሕማማት የጾመ ሁዳዴ የመጨረሻው ሳምንት፤ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማም የሚታሰብበት፤ ካህናትና ምእመናን በአጸደ ቤተክርስቲያን ተሰብስበው የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ የሚያዜሙበት፤ ግብረ ሕማም በመባል የሚታወቀውን መጽፍ የሚያነቡበትና የሚሰሙበት፤ በነግህ፣ በሠልስት፣ በስድስት፣ በተሰዓት /ዘጠኝ /ሰዓት፣ በሰርክ /በዐስራ አንድ/ ሰዓት እየመላለሱ የሚሰግዱበትና የሚጸለዩበት ልዩ ሳምንት ነው ከሆሳዕና ማግስት እስከ ትንሳኤ። በዚህ ሳምንት በተለይ ካህናት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ ምክንያቱም ጌታችን የደረሰበትን መከራና ስቃይ እንዲሁም የሰው ልጅ ፭ ሺ ፭ መቶ ዘመን በጨለማ ግዞት ይኖር እንደነበር ለማዘከርም ጭምር ነው። የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራና ሕማም በጽኑ እንድናስበው ያስተማሩን ሐዋርያት ናቸው። ለእነርሱም የነገራቸው ደግሞ ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ሰሙነ ሕማማት የጌታችንን ሕማማት ከማሰብ ጋር በየዕለቱ በርካታ ድርጊቶች መፈጸማቸውን የምናስታውስበት ሳምንት ነው፦ 📖ሰኞ መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል፦ በዚህ ዕለት ጌታችን ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ ቅጠል ያለባትን በለስ ተመልክቶ ወደ በለሲቱ ቢቀርብ ከቅጠል በቀር ምንም ነገር ባለማግኘቱ “ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ምንም ካንቺ ፍሬ አይበላ” ማር ፲፩፥፲፬ በማለት ስለረገማት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ ይባላል። አንጽሖተ ቤተመቅደስ ይባላል፡- ጌታ ወደ ቤተመቅደስ ሄዶ በቤተመቅደሱ የሚሸጡትን እና የሚለውጡትን “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች” ማቴ ፳፩፥፲፫ በማለት ከቤተመቅደስ ገርፎ አስወጥቷቸዋልና። 📖ማክሰኞ የጥያቄ ቀን ይባላል፦ ሰኞ ዕለት በቤተመቅደስ ሲሸጡ እና ሲለውጡ የነበሩትን ሁሉ እየገረፈ በማባረሩ ምክንያት ለሰው ልጅ ሹመትንና ስልጣንን የሰጠ ጌታ “በምን ስልጣን ይህንን ታደርጋለህ?” ማቴ ፳፩፥ ፳፫ ተብሎ በፈሪሳውያን ተጠይቋልና የጥያቄ ቀን ይባላል። የትምህርት ቀን ይባላል፡- በዚህ ዕለት በቤተመቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረም የትምህርት ቀን ይባላል። ሉቃ ፳፩ ፥፳፰ ፣ ማር ፲፪፥፪። 📖ረቡዕ ምክረ አይሁድ ይባላል፦ ረቡዕ እለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ወቅቱ የፋሲካን በዓል የሚያከብሩበት ቀን በመሆኑ እና ብዙ ህዝብም ጌታን ይከተለው ስለነበር ሁከት እንዳይነሳ ስጋት ነበራቸው ። ነገር ግን ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጣቸው ስለነገራቸው ሉቃ ፳፪፥፩-፮ ጭንቀታቸው ተወግዶ በጌታ መያዝ ተስማምተዋል። የመልካም መዓዛ ቀንም ይባላል፡- ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በሰምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯ የመዓዛ ቀን ይባላል። የእንባ ቀን ይባላል፡- ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ እፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አርሳለችና ማር ፲፬፥፱ የእንባ ቀን ይባላል። 📖ሐሙስ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል፦ ጌታችን ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ ሲጸልይ በማደሩ ማቴ ፳፮፥፴፮ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል። የምስጢር ቀን ይባላል፡- ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምስጢር ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል። የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል፡- መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም ድህነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ ሉቃ ፳፪፥፳ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል። የነጻነት ሐሙስ ይባላል፡- ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም ዮሐ ፲፭፥ ፲፭ የነጻነት ሐሙስ ይባላል። 📖ዓርብ የስቅለት ዓርብ ይባላል፦ ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና ማቴ ፳፯፥፴፭ የስቅለት ዓርብ ይባላል። መልካሙ ዓርብ ይባላል፡- ከጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ የወንጀለኛ መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል ጌታችን በደሙ ቀድሶ የምህረት፣ የሕይወት አርማ፣ የዲያቢሎስ ድል መንሻ ስላደረገው፤ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል። 📖ቅዳሜ ቀዳም ስዑር ትባላለች ፦ ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረች ቅዳሜ ይባላል። ለምለም ቅዳሜ ይባላል፡- ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጤማ እስከ ትንሣኤ ለሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል። ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል፡- ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ያረፈበት ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ስራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዶ ሲኦልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ የነበሩትን ነፍሳት የዘላለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል። አምላካችን በረድኤት ጠብቆ ለብርሐነ ትንሳኤው ያድርሰን! አሜን https://t.me/dnhayilemikael
نمایش همه...
አድኅነነ እግዚኦ እስመ ሃልቀ ሔር

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @DnIsraelYeArsemaLije

9/08/14 ዓ.ም መዝሙር ዘሆሳዕና "ወእንዘ ሰሙን" ✝ በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚሰበክ ምስባክ። ዲ/ን - ዕብ 9÷11- ፍ ም ን/ዲ - 1ጴጥ 4÷1-12 ን/ካ - ግብ፡ሐዋ 28÷11-ፍ ም የዕለቱ_ምስባክ - መዝ 8÷2 እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ በእንተ ጸላኢ ከመ ትንሥቶ ለጸላኢ ወለገፋዒ ትርጒም፦ ጠላትን ለማሳፈር ቂመኛንና ግፈኛንም ለማጥፋት ከህፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ:: ወንጌል፦ ዮሐ 5÷11-31 ቅዳሴ: ዘጎርጎርዮስ በቴሌግራም 👇 @mekra_abaw በዩቲዩብ ማግኘት ለምትፈልጉ https://www.youtube.com/channel/UCfWtKqb7qsxjXey4kN_tykg?sub_confirmation=1
نمایش همه...
393355556.mp31.17 MB
ይህንን ቪድዮ ስታይ የግቢ ላይፍ ይናፍቅሐል የእመቤታችን ጽዋ በዚህ መልኩ አሳልፈነዋል ቻናላችንን ሰብስክራይ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑኑ Please like share and subscribe 👇👇👇👇 https://youtu.be/oJ6RC3vgxc4
نمایش همه...
እውነተኛው ሰላም ያለው ከቤትህ ነው University of Gondar የጽዋ መርሃ ግብር #ክራር_መዝሙር #subscribe

እውነተኛው ሰላም ያለው ከቤትህ ነው University of Gondar የጽዋ መርሃ ግብር #ክራር_መዝሙር #subscribeሰብስክራይብ ቀማድረግ ቤተሰብ ሁኑንUoG university of Gindar freshman Orthodox mezmur በገና ዝማሬ...

یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.