cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
1 951
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-47 روز
-1830 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡- #ሰኞ #ማዕዶት_ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡ #ማክሰኞ #ቶማስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29 #ረቡዕ #አልአዛር_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ #ሐሙስ #አዳም_ሐሙስ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ #አርብ #ቅድስት+ቤተክርስቲያን_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡ #ቅዳሜ ቅዱሳት_አንስት_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡ #እሁድ #ዳግም_ትንሳኤ_ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
نمایش همه...
#ትንሣኤ #ልቡና ዛሬ የትንሣኤ በዓልን እያከበርን ነው። ትንሣኤ ማለት መነሣት ማለት ነው። ብዙዎቻችንም እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን እያልን ነው። ፖለቲከኛውም፣ ሰባኪውም፣ ጳጳሱም፣ ዘፋኙም፣ አርቲስቱም፣ አክቲቪስቱም ሁሉም እንኳን አደረሳችሁ እያለ ነው። ጌታ ተነሣ ስንል እኛም ትንሣኤ ልቡናን መነሣት አለብን። ፖለቲከኞች በቂም በቀል እና በሴራ መቃብር ውስጥ ሆናችሁ እንኳን አደረሳችሁ ብትሉን ራሳችሁን የምትዋሹ ትሆናላችሁ። ከመቃብር ውጡ። ትንሣኤያችሁን ሐዋርያት ይመልከቱት። በመቃብር ሆነን ስለ ትንሣኤ ብናወራ አያምርብንም። ። ኑ በሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደተነሣ እኛም ትንሣኤ ልቡናን እንነሣ። የዘረኝነት፣ የውሸት፣ የጥላቻ፥ የበቀል፣ የሐሜት፣ የከንቱ ውዳሴ፣ የትዕቢት፣ የራስ ወዳድነት መቃብርን ፈንቅለን እንውጣ። ኑ እንነሣ። ስንነሣ ደግሞ ልባችን ብርሃንን ይሞላዋል። ችግሮቻችን ሁሉ ከእኛ በታች ነበሩ። ነገር ግን ትንሣኤ ልቡናን ባልተነሡ ሰዎች ምክንያት እንደ ተራራ የገዘፉ ሆኑብን። ኑ በትንሣኤው እንነሣ። በአፋችሁ እንኳን አደረሳችሁ እያላችሁን በልባችሁ ግን ቀጣይ ዓመት እንዳንደርስ እየገደላችሁን ከሆነ ይሁዳነት ነው። ይሁዳ በአፉ ሰላም እያለ ነው ጌታን የሸጠው። ሁሉም ከተንኮልና ከሽንገላ መቃብር ይውጣ እና የፍቅር ትንሣኤን ይነሣ። © በትረ ማርያም አበባው https://t.me/dnhayilemikael🌿
نمایش همه...
ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn

ፋሲካ አልባ ፋሲካ ለሃምሳ ቀናት ጾመን ደርሰን ከኀዘን አጽናፍ በስግደት በለቅሶ ከርመን ቆመን ከሰቆቃ ጫፍ እንደ ሐዲስ ኪዳንናዊ ሰው ከርመን ወንጌል ስናጠና እግዚኦ መሐረነ ጌታ ብለን ጮኸን ሆሳዕና ሕማምህ መከራህ አልፎ ትንሣኤህ ሲመጣ ፋሲካ ልክ እንደ ኦሪት ሰው ሆንን ሮጥን እንስሳ ፍለጋ እንደ ክርስቲያኖች ወግ ሥጋህንበልተን እንደመዳን በግና ዶሮ ልናሳድድ ሔድን ወደ ብሉይ ኪዳን ስንት ሰዓት ልቁረብ ማለት ትተን የእርዱ ነገር አስጨነቀን ከትንሣኤህ ዕለት ቆመን የልብ ትንሣኤ ራቀን የመቃብርህን ውጪ ቆመው ደጅ ደጁን ከጠበቁ ሕያው ጌታ መሆንህን ክብርህን ጭራሽ ካላወቁ ከሮማውያን ወታደሮች በምን ተለየን እኛ ሥጋህን ተቀብለን ካልሆነን የነፍስ መዳኛ ከቶ እንዴት ይከበራል ወደ አንተ ሳይቀርቡ ትንሣኤ? ለእኛ አልነበረም ወይ ያ ዕንባ ያ ሁሉ ኤሎሄ ኤሎሄ የከበረው ሥጋህ ዛሬ በእኛ ውስጥ ካልተቀበረ ምኑን ትንሣኤ ተበሰረ ምኑን ፋሲካ ተከበረ? ይቅር በለን ጌታችን ሆይ በዶሮ ሥጋ ላከበርንህ የሥጋችንን ስናሳድድ በትንሣኤህ ቀን ለቀበርንህ በሞትህ ሙት ያስነሣህ ሆይ እኛንም አስነሣን ዛሬ ደርቀን አንቅር በኃጢአት አድርገን የትንሣኤህ ፍሬ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ቀዳም ስዑር ሚያዝያ 2016 ዓ.ም. https://t.me/dnhayilemikael🌿
نمایش همه...

1
✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ            አሜን ✍“ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ፤ ተነሥቶአል እንጂ በዚኽ የለም" 📖ሉቃ 24፥5 #ክርስቶስ_ተንስአ_እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን፤ #አሠሮ_ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፤ #ሰላም፤ እምይእዜሰ፤ #ኮነ፤ ፍሥሐ ወሰላም።     ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥       ድርሳን ዘበዓለ ፋሲካ     ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥ ✍ "እግዚአብሔርን የሚያምንና የሚወድ ቢኖር፤ እርሱ በዚህ  አንፀባራቂና የደስታ በዓል ደስ ይበለው" ✍ "ብልህ አገልጋይ ቢኖር፤ እርሱ ወደ ጌታው ሐሴት ገብቶ ዕልል ይበል፤ በጾም የደከመ ቢኖር፤ አሁን ደመወዙን ይቀበል፡" ✍ "በመጀመሪያው ሰዓት ወደ አምላኩ የቀረበ ቢኖር፤ ዛሬ ሽልማቱን ይውሰድ" ✍ "በሦስተኛው ሰዓት የመጣ ቢኖር፤ እርሱ በዓሉን በምስጋና ያክብር፤ በስድስተኛው ሰዓት የደረሰ ቢኖር፤ አይጎድልበትምና አይጠራጠር፤ እስከ ዘጠነኛ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፤ ሳይጠራጠር ይቅረብ፤ እስከ ዐሥራ አንደኛዋ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፤ ስለ መዘግየቱ አይደንግጥ፤ ጌታ ቸር ነውና፤ በመጨረሻ የመጣውንም እንደ መጀመሪያው አድርጐ ይቀበሏልና" ✍ "በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ለመጣው ከመጀመሪያው ሰዓት አንሥቶ ሲደክም ከነበረው ጋራ እኩል ይሰጧልና፤ መጨረሻ ለመጣው ጌታ ምሕረቱን ይለግሰዋል፤ መጀመሪያ ለመጣውም ያስብለታል፡፡ ✍ "ለአንደኛው ይሰጠዋል፤ ለሌላኛውም ጸጋውን ያድለዋል፤ ለአንደኛው መልካም ምግባሩን ይቀበልለታል፤ ለሌላኛውም መልካም ፍቃዱን ይቀበልለታል፤ ለአንዱ ምግባሩን ያከብርለታል፤ ለሌላኛውም በቅን ልቡና የሚያደርገውን ጥረት ያደንቅለታል" ✍ "ስለዚህ ኹላችሁም ወደ ጌታችሁ ደስታ ግቡ፤ ፊተኞች ኋለኞችም ሆይ እኩል ደመወዛችሁን ተቀበሉ፤ ባለጸጐች ድኾችም ሆይ በአንድነት ዘምሩ" ❖ እናንተ ብርቱዎች ደካሞችም ሆይ በዓሉን አክብሩት፡፡ ✍እናንተ የጾማችሁ መጾም ያልቻላችሁም ሆይ ዛሬ ላይ ደስ ይበላችሁ፤ መሠዊያው ሙሉ ነውና ኹሉም በማዕዱ ደስ ይበለው፤ ፍሪዳው የሰባ ነውና አንድ ሰው ስንኳ እንደ ተራበ እንዳይሔድ፤ ኹላችንም የእምነት በዓሉን እንካፈል፤ ከቸርነቱና ከፍቅሩ ሀብትም እንቋደስ፡፡ ✍ማንም ስለ ድኽነቱ አይዘን፤ ኵላዊቷ መንግሥት ተገልጣለችና፤ ማንም በኃጢአቱ አያንባ፤ ከመቃብሩ የይቅርታ ብርሃን ተንቦግቧልና፤ ማንም ሞትን አይፍራ የመድኃኒታችን ሞት ከዚህ ነጻ አውጥቶናልና፤ ለእርስዋ በመታዘዝም ጌታ አጥፍቷታልና፡፡ ✍በሞቱ ሞትን ገደለው፤ ወደ ሲዖል በመውረድ ሲዖልን በዘበዘው፤ ኢሳይያስም አሰምቶ እንደ ተናገረ ሲዖል ከጌታችን ጋር ፊት ለፊት ተገናኘች፤ ❖ መረራትም ከንቱ አድርጓታልና መረራት ❖ ሸንግሏታልና መረራት ❖ ሽሯታልና መረራት ❖ ነፍሳትን ይዛ እንዳታስቀር አስሯታልና መረራት ❖ መቃብር የዕሩቅ ብእሲ ሥጋ አገኘሁ ብላ ዋጠችው፤ስትውጠው ግን እግዚአብሔር ኾኖ አገኘችው መረራትም ❓ሞት ሆይ መውጊያህ ወዴት አለ ❓ሲዖል መቃብርም ሆይ ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ ❖ ክርስቶስ ተነሣ፤ ❖ ሞት ሆይ አንተም ጠፋህ ❖ ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ ❖ ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ ❖ ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች ❖ ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች ❖ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቿልና፡፡ ❖ ለእርሱም ክብርና ጽንዕ ዛሬም ዘወትርም እስከ ዘለዓለሙ ድረስ ይኹን ✍ "ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሐጺባ በደመ ክርስቶስ" 👉"ምድር ጸዳች ሐሴት አደረገች በክርስቶስ ደም በእውነት ታጠበች" እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን መልካም በዓል ✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" 📖ምሳ 1፥33 📌ምንጭ ✍ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ እንደፃፈው ✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝💚💛❤️✝ 🙏 ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ፤ እኔም ለእናንተ ከአዘጋጀው በኃዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ      ✍"ልብህን በእርጋታ አኑረው፤ የሁሉም መጨረሻ እና የሁሉም አገልጋይ ለመሆን በጣም ትጋ ለከንቱ ንግግር ዘገምተኛና ሰነፍ ሁን፤ ነገር ግን የቅዱሳት መጻህፍትን ቃል በማወቅ በመስማት ድኅነትን የሚሰጡ ናቸውና ብልህ ሁን" 📚ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ                ወስብሐት ለእግዚአብሔር                               ይቆየን  ───────────                     Channel  🧲  https://t.me/dnhayilemikael🌿         FB https://t.me/dnhayilemikael🌿
نمایش همه...
ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn

1
የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያምገዳም ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት ተከናወነ ! ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክሃይማኖት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በመገኘት የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት አከናውነዋል። ዕለተ ሐሙስ እንደሚታወቀው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፍጹም ትህትና የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበበት ከሐዋርያት ጋር ግብር የገባበትና የክርስትና ሕይወት ማኅተም የሆነውን ምስጢረ ቁርባን ያከናወነበት ዕለት ነው። ስነ ሥርዓቱም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ቆሞሳት ፣ ካህናት እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ሃይማኖታዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ ተከናውኗል ። ምንጭ ተዋሕዶ ሚዲያ
ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ    ╭═══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ═══╮     የመሰረተ ተዋሕዶ ሰንበት ትምህርት ቤት መገናኛ ብዙሃን                ➡️      መሰረተ ሚዲያ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇      ቻነሉን share በማድረግ መሠረተ ሚዲያ አብረን እናሳድግ 👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም አድራሻ ⤵️ ⤵️ ⤵️ ⬇️═https://t.me/Meseretemedia
نمایش همه...
👍 1 1
የሰሙነ ሕማማት ዕለታት ስያሜዎች ፩ .ዕለተ ሰኑይ መርገመ በለስ፡- ጌታችን የሆሣዕና ዕለት ቢታንያ አድሮ በማግስቱ ከቢታንያ ሲወጣ ተራበ፤ በመንገድም ሲያልፍ ቅጠል ያላት በለስን ከሩቁ ተመለከተ፡፡ ወደ በለሲቱም በቀረበ ጊዜ ከቅጠል በቀር አንዳች ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ያንጊዜም ‹‹ከእንግዲህ ወዲህ ለዘለዓለም ከአንቺ ፍሬ የሚበላ አይኑር›› ሲል በለሲቱን ረገማት፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ይህንን ሰሙት፡፡ በዚህም ምክንያት ይህች ዕለት በለሲቱ የተረገመችባት ቀን ናትና መርገመ በለስ ተብላ ትጠራለች፡፡ (ማር.፲፩፥፲፩-፲፬) በዚህ አገላለጽ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ስትሆን ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባር ነው፡፡ መድኃኒታችን ክርስቶስ ከእስራኤል ፍቅርን፣ ሃይማኖትን፣ ምግባርን ፈልጎ አላገኘባቸውም፡፡ እስራኤል፦ ሕዝበ እግዚአብሔር፣ የአብርሃም ዘር መባልን እንጂ የአብርሃምን ሥራ በመሥራት በምግባር በሃይማኖት ጸንተው መኖር አይፈልጉምና ደግ ሰው አልተገኘባቸውም፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በለስ የተባለች ኦሪት ናት፡፡ ኦሪት በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛትም አማናዊ ድኅነትን የምታሰጥ ሆና አላገኛትም፡፡ ይሁን እንጂ በእርሷ ድኅነት ባይገኝባትም ‹‹ኦሪትና ነቢያትን ከመፈጸም በቀር ልሽር አልመጣሁም ልፈጽም እንጂ›› በማለት ሕገ ኦሪትን ፈጽሟታል፡፡ ከዚህም ባሻገር በለስ የተባለች ኃጢአት ናት፡፡ የበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነች ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አግኝቷታል፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣል፤ ቆይቶ ግን ይመራል፤ ኃጢአትም ሲሠሩት ለጊዜው ደስ ያሰኛል ኋላ ግን ያሳዝናል፡፡ በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚለውም በአንቺ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ የሚቀር አይኑር ሲል ነው፡፡ በለሲቱ ስትረገም ፈጥና መድረቋም በአዳም ምክንያት ያገኘን በደል በእርሱ እንደጠፋልን ለመግለጽ ነው፡፡
https://t.me/dnhayilemikael🌿
نمایش همه...

1
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿✍#ሆሳዕና_ማለት_ምን_ማለት_ነው ?? 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 #በሆሳዕና_ለምን_ቀለበት_እናስራለን ? #በሆሳዕና_ጌታችን_ለምን_በአህያ_ላይ_ተቀመጠ #በሆሳዕና_ለምን_ዘንባባ_አነጠፉ ? ................................................................ እና ሌሎች በደንብ ይነበብ ሼር! => ሆሳዕና ማለት ምን ማለት ነው?? ሆሳዕና ማለት፦ የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው:: 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 => በሆሣዕና ዕለት በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ ነው?? 1.ጌታ ለአዳም የሰጠው ቃል ኪዳን ለማስታወስ፡-ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድነሃለሁ ያለውን የተስፋ ቃል ለማስታወስ፡፡ 2.ጌታ ለእመቤታችን የገባላትን ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው። 3.ጌታ ለእስራኤላውያን የሰጣቸው ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው። 4.ጌታ ለአዳም ከሰይጣን ግዛት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ እኛም ከሰይጣን ግዛት ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ከክፋት ከኃጢአት አውጣን ማረን ለንስኃ ሞት አብቃን ከቤትህ አትለየን እንደ ቸርነትህ ይቅር በለን ስንል ለጌታ ዳግም ላናጠፋ ቃል የምንገባበት ነው፡፡ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 => ጌታችን በዕለተ ሆሳዕና ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም?? ትንቢቱንና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ " አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል።(ትንቢተ ዘካርያስ 9:9) => በአህያ መቀመጡ፦ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 •ትህትናን ለማስተማር •የሰላም ዘመን ነው ሲል •ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና በየዋህነት ለሚኖሩ ምዕመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 •አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ ብለው ነው የሚሄዱት፤በቀላሉ ትወጣበታለህ፤በቀላሉ ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ። => ጌታችን ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ዘባባ የመነጠፉ ሚስጢር የምን ምሳሌ ነው??? 1.ዝንባባ፡- ይስሃቅ በተወለደ ጊዜ ደስ ብሎት አብርሃምን ዘንባባ ይዞ እግዚአብሔር አመስግነዋል፡፡ 2.ዝንባባ ደርቆ እንደገና ሂይወት ይዘራል፡- የደረቀ የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡ 3.ዝንባባ የሰላም ምልክት ነው፡- የሰላም አምላክ ነህ ሲሉ ነው። 4.ዝንባባ የደስታ መግለጫ ነው፡- አንተ ደስ የምታሰኝ ሃዘናችንም የምታርቅልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡ 5.ዝንባባ እሾሃማ ነው፡- አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡ 6.ዝንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጂ፡፡ ጌታም አንተ ባህሪህን የማይመረመር ነው ሲሉ ነው፡፡ ህዝቡ ከልብሳቸው ሌላ ስንት አይነት ቅጠንል አነጠፉለት ምን ምን?? 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 => ልብሳቸውን ማንጠፋቸው፡- ለክብሩ መግለጫ ነው፡፡ ሌሎችም ሦስት አይነት ቅጠል አነጠፉለት ዘንባባ፤የቴመር ዛፍ፤የወይራ ዛፍ አነጠፉለት፡፡ => ትልቅዋ አህያ በምን ትመሳለለች ውርን ጭለዋስ??? ትልቅዋ አህያ የኦሪት ምሳሌ ነው። 1.ትልቅዋ አህያ ሸክም የለመደች ናት ህገ ኦሪትም የተለመደች ህግ ናትና፡፡ 2.የእስራኤል ምሳሌ ነው፡-ትልቅዋ አህያ ሸክም እንደለመደች ሁሉ እስራኤልም ህግ ለመፈጸም በህግ ለመራመድ የለመዱ ናቸው፡፡ 3.የአዳም ምሳሌ ነው፡- አዳም ሸክም የበዛበት ነበርና። 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ውርጭላዋ 1.በህገ ወንጌል ትመሰላለች፡-ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ ክርስቶስ የመሰረታት የሰራት አዲስዋ ህግ ናትና፡፡ 2.በአህዛብ ትመሰላለች፡-ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች አይደለችም እንዲሁም አህዛብም ህግህን የመቀበል የመቀበል የለመደ አይደሉም፡፡ ለህግህ አዲስ ናቸውና፡፡ 3.የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡- የዓለም ሸክም አቅልላለችና በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ ምክንያታችን ጌታን የተሸከመች ንጽህት እንከን የሌላት እናት ናትና፡፡ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ።።።።ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።። ።።።።። ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።። ።።።።። ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።። 🌿https://t.me/dnhayilemikael🌿
نمایش همه...
5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።     1, 🛑አላማ     2 ,🛑እምነት     3,🛑ጥረት     4 🛑ጥንቃቄ      5🛑ጽናት =>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው። ❇️9ኙ የቅድስና መንገዶች❇️ ፩👉ሃይማኖት ፪👉ጾም ፫👉ጸሎት ፬👉ስግደት ፭👉ምጽዋት ፮👉ፍቅር ፯👉ትህትና ፰👉ትዕግስት ፱👉የዋህነት ✝ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል።         (ቅዱስ መቃርስ ) https://t.me/dnhayilemikael
نمایش همه...
ኑ ቃለ እግዚአብሔርን እንማማር

#መሰረታዊ_የቤተክርስቲያን_ክርስቲያን_ትምህርት / #የተለያዩ_ተከታታይ_ትምህርት ' #ስንክሳር_የቅዱሳን_ገድል_በየዕለቱ ! #ስዕለ_አድህኖ ! #ምስባክ #የየበአላቱ_ዋዜማና_ሥርተ_ማህሌት #መዝሙር #ግጥም #ለመናፍቃን_ጥያቄ_መልስ እና የተለያዩ የቤተክርስቲያን ዶግማና ቀኖና የጠበቁ ሌሎች መንፈሳዊ ጽሁፎች ይለቀቁበታል Administration @zearsema_dn

1
ሮሜ 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁹ ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን። ክፉውን ነገር ተጸየፉት፤ ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ፤ ¹⁰ በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ እርስ በርሳችሁ ተከባበሩ፤ ¹¹ ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤ ¹² በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ፤ ¹³ ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤ እንግዶችን ለመቀበል ትጉ። ¹⁴ የሚያሳድዱአችሁን መርቁ፥ መርቁ እንጂ አትርገሙ። ¹⁵ ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ። ¹⁶ እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ፤ የትዕቢትን ነገር አታስቡ፥ ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ። ልባሞች የሆናችሁ አይምሰላችሁ። ¹⁷ ለማንም ስለ ክፉ ፈንታ ክፉን አትመልሱ፤ በሰው ሁሉ ፊት መልካም የሆነውን አስቡ። ¹⁸ ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ። ¹⁹ ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና። ²⁰ ጠላትህ ግን ቢራብ አብላው፤ ቢጠማ አጠጣው፤ ይህን በማድረግህ በራሱ ላይ የእሳት ፍም ትከምራለህና። ²¹ ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ።
نمایش همه...