ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር️
መጽሐፍትን በጥሩ ዋጋ እንገዛለን እንሸጣለን! ገፁን ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን ያስፉት 📚📚 አድራሻችን አዲስአበባ 0991001450
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር️
کانال ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር️ (@bookworlds1) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 10 550 مشترک است و جایگاه 3 627 را در دسته کتب و رتبه 3 156 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 10 550 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 05 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -96 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -6 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 14.48% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً N/A% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 1 528 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 0 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 20 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“መጽሐፍትን በጥሩ ዋጋ እንገዛለን እንሸጣለን!
ገፁን ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን ያስፉት 📚📚
አድራሻችን አዲስአበባ
0991001450”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 06 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته کتب تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 06 سپتامبر | 0 | |||
| 05 سپتامبر | 0 | |||
| 04 سپتامبر | 0 | |||
| 03 سپتامبر | 0 | |||
| 02 سپتامبر | +6 | |||
| 01 سپتامبر | +3 |
| 2 | እርስዎ አልሳሉትም እባክዎት ይሄንን ስዕል የሳለውን ሰው ይንገሩኝ...እያለች ብትለምናቸውም ልጁ የሰጣቸው ማስጠንቀቂያ ነበርና ሊነግሯት አልፈለጉም።
መለመኑ ሲሰለቻት አንድ ሃሳብ መጣላትና ያንን ሀሳብ መጠቀም ፈለገች። አባቷን ቀለምና ቡርሽ እንዲያስመጣላት ጠየቀችው።
አባቷም የምትፈልገውን አይነት ቀለምና ቡርሽ እንዲሁም ለስዕል የሚያገለግል ነገር ሁሉ አስመጣላት።
አሁን አለች ልዕልቷ...አሁን እርስዎ ከሆኑ ስዕሉን የሳሉት አለች ወደ ሽማግሌው ዞራ ፣ ፈረሱም ይሄው ሜዳውም ይሄው ...እኔን ይሳሉኝ። እውነትም እኔን በደንብ አድርገው ከሳሉኝ የእስከዛሬዎቹን ስዕሎች እርስዎ እንደሳሏቸው አምናለሁ አለቻቸው።
ሽማግሌ ፍርሃት ውስጣቸውን ሲወራቸው ተሰማቸው። በንጉሱ ፊት የዋሹት ታላቅ ውሸት አስደነገጣቸው። ቡርሽና ቀለም ተሰጣቸውና ልዕልቷን እንዲስሉ ታዘዙ።
ወትሮውንም አሳ ማስገር እንጂ ስዕል መሳል ሞክረውት የማያውቁት እኒያ መልካም ሽማግሌ ውስጣቸው በፍርሃት ራደ። ለመልካም ብለው ልጁን ማዳናቸው ከፍተኛ ቅጣት እንደሚያስጥልባቸው ተገነዘቡ። በልባቸውም ልጁን ረገሙት።
እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ስዕሉን ለመሳል ቢሞክሩም አልሆን አላቸው። ንጉሱ በዝምታ ሲመለከታቸው ከቆዬ በኋላ አንድ ትዕዛዝ አስተላለፈ። እጅኛ እግራቸው በሰንሰለት እንዲታሰር አሽከሮቹን አዘዘ። ባላወቁትና ባልጠበቁት መንገድ በሰንሰለት ለመታሰር በቁ።
ትክክለኛውን የስዕሉን ባለቤት እንዲናገሩ በአሽከሮች ብዙ ጅራፍ ተገረፉ እሳቸው ግን እውነቱን ለመናገር አልቻሉም። የልጁን ቃል አክብረው ከንጉሱ አሽከሮች ዱላ እና ከንጉሱ ፍርድ የሚመጣውን የመጨረሻውን ውሳኔ መጠባበቅ ጀመሩ።
ቀኑ መሽቶ ፀሀይ የምዕራቡን አድማስ ሀምራዊ ቀለም አልብሳ ወደቤቷ ስታሸልብ ጨረቃ በተራዋ ብቅ አለች።
የድሃይቱ ልጅ የሽማግሌው ወጥቶ መቅረት አሳስቦታል። ቀኑን ሙሉ ጠብቋቸው ስላልመጡ ውስጡ በፍርሃት እና በጭንቀት ተውጧል።
ከሽማግሌው ጎጆ ወጠጥቶ ውጭ ላይ ተቀመጠና በጨረቃዋ ውበት ተመሰጠ። በምስራቅ በኩል ብቅ ያለችው ጨረቃ ልዕልቷን መስላ ታየችው። ቡዝዝ ብሎ ተመለከታት። ከልዕልቷ ጋር ያሳለፈው ጊዜ አንድ በአንድ መጣበት ...ጨረቃዋ ለመሙላት ትንሽ ይጎድላታል። ታራራዎችን ተንተርሳ የወጣችው ጨረቃ ልቡን ወስዳዋለች። ወደ ጎጆዋ ተመልሶ ቡርሽና ቀለም ይዞ ተመለሰ ። ጠረቃዋን ተራራ ተንተርሳ ሳላት። እጅግ ውብ አድርጎ ሳላት። ስዕሉን ይዞ ወደ ጎጆዋ ተመለሰና ጋደም አለ። | 1 551 |
| 3 | ታሪኩን ለማስታወስ ያህል ትረካው የቆመበትን ሁኔታ ላስታውሳችሁ.....ልጁ እየሳለ ለአሳ አጥማጁ ወይም ለሽማግሌው የሚሰጠው ስዕል ልዕልቲቱጋ ደርሶ ነበር። ከዚያም አባቷን ይሄንን ስዕል የሳለውን ሰው አስመጣልኝ ብላው ሰዓሊው ወይም ልዕልቲቱን ከሽፍታዎች አድኖ የወሰዳት ወጣት ሽልማቱን ከባህር ያዳኑት ሽማግሌ እንዲያገኙ ስለፈለገ ወደ ንጉሱ ጥሩ ልብስ አልብሶ ልኳቸው ነበር። ልዕልቷ ደግሞ ሽማግሌውን ስታያቸው ተናዳ እርስዎ አይደሉም የሳሉት የሳለውን ሰው ይንገሩኝ እያለች እየተማፀነቻቸው ነበር ታሪኩ ልባችንን አንጠልጥሎ የቀረው።
እኔ በራሴ መንገድ ደፍሬ ቀጥዬበታለሁና ከዚህ በመቀጠል አቀርብላችኋለሁ! | 1 263 |
| 4 | "ሰበዝ" የተሰኜው የአለማየሁ ዋሴ መጽሐፍ ላይ "አልጨረስክልኝም" የተሰኜ ልብ አንጠልጥል የሚያስቀር አንድ ንዑስ ርዕስ አለ!
እስኪ ያነበባችሁት የ ❤ ምልክት አሳዩና በራሴ መንገድ የጨረስኩትን ላጋራችሁ! | 1 268 |
| 5 | አባ ታጠቅ ካሳ የቋራው አንበሳ
ይህ መጽሐፍ ከሁሉም ስለ አፄ ቴዎድሮስ ከተጻፉ የታሪክ ድርሳናት ሁሉ ልዩ የሚያደርገው፣ የንጉሡን ታሪክ በደረቅ የታሪክ መረጃዎች ብቻ ሳይሆን የነበራቸውን ሕዝባዊ መሠረት፣ ስሜት እና የነፍስ ትግል በጥልቀት በሚያሳይ ልዩ የአጻጻፍ ስልት የተከተለ መሆኑ ነው።
ሌሎች መጻሕፍት ብዙውን ጊዜ ትኩረታቸውን በጦርነቶቻቸው እና በፖለቲካዊ ውሳኔዎቻቸው ላይ ብቻ ሲያደርጉ፣ ይህ መጽሐፍ ግን የአፄ ቴዎድሮስን የኢትዮጵያዊነት ጽኑ ፍቅር፣ መላ ሕይወታቸውን የገዛውን የአንድነት ራዕይ እና ከሕዝባቸው ጋር የነበራቸውን ጥልቅ ትስስር በስሜት ቀስቃሽ ቋንቋ ይተነትናል።
በተጨማሪም፣ በመቅደላ ምሽግ ላይ የፈጸሙትን የጀግንነት መስዋዕትነት የኢትዮጵያዊነት ክብር ማኅተም አድርጎ በመሳል፣ አንባቢው የንጉሡን የታሪክ ጉዞ በቅርበት እንዲረዳና የእውነት ስሜቱ እንዲቀሰቀስ የሚያደርግ በመሆኑ ከማንኛውም ስለ ቴዎድሮስ ከተጻፈ መጽሐፍ በላይ በእውነተኛ ታሪካዊና ስነ-ጽሑፋዊ ዋጋው ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።
0991001450
@a9OaG | 1 613 |
| 6 | ይህ መጽሐፍ በታዋቂው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት የተጻፈ ሲሆን በኢትዮጵያ የመካከለኛው ዘመን ታሪክ ውስጥ በሃይማኖት (በቤተ ክርስቲያን) እና በፖለቲካዊው ሥልጣን (በመንግሥት) መካከል የነበረውን ጥልቅና ውስብስብ ግንኙነት የሚመረምር እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ የምርምር ሥራ ነው።
መጽሐፉ ትኩረት የሚያደርገው የአክሱም ሥርወ-መንግሥት ካበቃ በኋላ የሰለሞናውያን ሥርወ-መንግሥት በዓፄ ይኩኖ አምላክ አማካኝነት በ1270 ዓ.ም. ዳግም ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ፣ በግራኝ አህመድ ወረራ ምክንያት አጠቃላይ የአገሪቱ መዋቅር እስከ ተናወጠበት 1527 ዓ.ም. ባለው ወርቃማና ፈታኝ ዘመን ላይ ነው።
በዚህ ዘመን የነበሩት ነገሥታት (በተለይም እንደ ዓፄ ዓምደ ጽዮን እና ዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ያሉ ጠንካራ መሪዎች) ግዛታቸውን ወደ ደቡብና ምስራቅ ለማስፋፋት፣ ሕዝቡን አንድ ለማድረግና ማዕከላዊ ሥልጣናቸውን ለማጠናከር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ዋና የመንፈሳዊ፣ የባህልና የፖለቲካ መሣሪያ እንደተጠቀሙባት መጽሐፉ በስፋት ይተነትናል።
በተያያዥም ቤተ ክርስቲያን በአገሪቱ የትምህርት፣ የሥነ-ጽሑፍና የስምሪት ማዕከል በመሆን ያበረከተችውን አስተዋጽኦ፣ ከመንግሥት የምታገኘውን የርስት (የጉልት) መሬትና የሀብት ጥገኝነት፣ እንዲሁም አልፎ አልፎ በመንፈሳዊ መሪዎች (እንደ ደብረ ሊባኖስ ገዳማውያን) እና በነገሥታቱ መካከል በሃይማኖታዊ ሥርዓቶችና በሥነ-ምግባር ጉዳዮች ላይ ይፈጠሩ የነበሩትን መካረሮችና የሥልጣን ሽኩቻዎች በብራና ምንጮችና በነገሥታት ገድላት ተደግፎ በዝርዝር ያሳያል።
በአጠቃላይ መጽሐፉ ቤተ ክርስቲያንና መንግሥት እርስ በእርስ እየተደጋገፉና እየተሻኮቱ እንዴት የአሁኗን የኢትዮጵያን ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ማንነት እንደቀረጹ የሚያስረዳ ዋቢ የታሪክ መጽሐፍ ነው። | 1 648 |
| 7 | ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ሕይወት (1810-1881)" የተሰኘውና በደጃዝማች አበበ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ፣ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያን የታሪክ አቅጣጫ በቁርጠኝነት በለወጡት ታላቁ ወታደራዊ ስትራቴጂስትና ፖለቲከኛ ራስ ጎበና ዳጨ ላይ የተሰናዳ ድንቅ የታሪክ ሰነድ ነው።
መጽሐፉ የጀግናውን የልጅነት ዘመን፣ የአመራር ብቃት፣ የጦር ሜዳ ውሎዎች እንዲሁም ከዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ጋር በመሆን የዘመናዊቷን ኢትዮጵያ አንድነትና መልክዓ-ምድር በመቅረጽ ረገድ የተጫወቱትን ታላቅ ሚና በጥልቀትና በምርምር ይተነትናል።
መጽሐፉ፣ ተደብቀውና ተረስተው የቆዩ በርካታ የታሪክ እውነታዎችን በይፋ የሚያወጣና ለአንባቢ አዲስ እይታን የሚለግስ ውድ የሥነ-ጽሑፍ ሀብት ነው ።
በተለይም የሀገራቸውን ጥንታዊ የወታደራዊ ጥበብ፣ የዲፕሎማሲ ጥልቀትና የአንድነት ጉዞ በጥሩ ቃላትና ሚዛናዊ በሆነ የታሪክ ትረካ ማወቅ ለሚሹ ሁሉ ይህ ሥራ የማይተካ የምርምርና የንባብ ማጣቀሻ ነው።
0991001450 | 1 633 |
| 8 | "ድንግል ነኝ አትበይኝ"
እኔ አውሬ አይደለሁ ፣ ደም አፍስሼ አልረካ፣
በሴት የዋይታ እምባ ፣ ቀኔን የማፈካ፣
የአንችነት ክብርሽን ፣ በደም ዋጋ አልካም፣
ድግል ልብሽ እንጅ ፣ አካልሽ አይደለም።
ላንች እንደው ደም ማለት........
ሰርክ የምታፈሽው ፣ 1 ወር እየጠበቅሽ፣
ከሄዋን በለስ ጋር ፣ የመጣ ርግማንሽ።
እናንልሽ አለሜ..........
ለመድማት ከሆነ ፣ ድሚ ግድ የለኝም፣
አንች ያልደማሽ እንደው፣ ትውልድ አይተካም፣
ፅንስ አይፈጠርም ፣ ህይወት አይቀጥልም፣
በደም ግብር ምክነያት ፣ ከፍ ያለው ይህ ስምሽ፣
በአለም አደባባይ ሁሉም እንዲጠራሽ፣
ደምሽ ንፁህ ይሁን ፣ ቆሻሻ እጅ አይንካው፣
በንፁሀን ደም ነው ፣ ትንሳኤሽ ሚበስረው።
እናልሽ አለሜ......!
ስለንፅህናሽ ....
ፍፁም አታስቢ፣ተይው ግድ የለሽም፣
ክብርሽ ልብሽ ላይ ነው ገላሽ ላይ አይደለም።
ይድረስ ለውዷ ድንግል ሀገር፣ የት እንዳለች ለጠፋችብን የኖህ መርከብ ኢትዮጵያ!!!!
ገጣሚ ጊዜአለው ✍️ | 3 285 |
| 9 | An Introduction to the Economic History of Ethiopia
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ታሪክ መግቢያ የተሰኘው መጽሐፍ፣ ከጥንት ጀምሮ እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን ማብቂያ ድረስ የነበረውን የኢትዮጵያን ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ጉዞ በጥልቀት የሚመረምር እጅግ ጠቃሚ የታሪክ ማጣቀሻ ነው።
መጽሐፉ የአገሪቱን የግብርና ሥርዓት፣ የየብስና የባሕር የንግድ መስመሮችን፣ የገንዘብና የግብይት ዓይነቶችን፣ የከተሞች አገነባብን እንዲሁም የዕደ-ጥበብና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በሰፊው የሚያትት ሲሆን፣ የሕዝቡን የዕለት ተዕለት ኑሮና የባርነት ታሪክን ጨምሮ ሰፊ ማኅበራዊ ገጽታዎችን በታሪካዊ ሰነዶችና ማስረጃዎች አስደግፎ ያቀርባል።
ከዚህም በተጨማሪ የባህላዊ ሕይወት ሥዕል አገሪቱ የነበራትን ጥንታዊ የሥራ ባህልና የማኅበረሰብ አወቃቀር የሚያንጸባርቅ ሲሆን፣ መጽሐፉ በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ታሪክ በኢኮኖሚው መዋቅር ላይ የነበረውን ተጽዕኖ ለመረዳት ለሚፈልጉ ተመራማሪዎችና አንባቢዎች እንደ ዋነኛ መነሻ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል።
መጽሐፉን በመደብራችን ያገኙታል! | 1 |
| 10 | ይህ የታሪክ ሰነድ በምሥራቅ አፍሪካ ምድር ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድና የሰዎች ዕጣ ፈንታ የተሰናሰሉበትን ያንን ታላቅ ዘመን በጽኑ የጽሑፍ ምስክርነት ያዘክራል።
መጽሐፉ ልክ እንደ ቅዱሳን የጉዞ ታሪኮች ሁሉ፣ ሰላምን ለመፈለግና ሥርዓትን ለመመሥረት ከፍ ካለውና በተባረከው የኢትዮጵያ ደጋማ ምድር ተነስተው፣ እግራቸው እሳት ወደሚመስለውና ፈታኝ ወደሆነው የሶማሊላንድ በረሃ የተጓዙትን የእንግሊዝ መኮንኖችና የአፄ ምኒልክን ጨዋ አርበኞች የተቀደሰ የትብብር ጉዞ በስሱ ይተርካል።
ታዋቂው የታሪክ ሊቅ ሪቻርድ ፓንክረስትና ፍሬድሪክ ሻርፍ እንደ ታማኝ የቤተ-መቅደስ ጠባቂዎች ይህንን የተረሳ የዘመን ታሪክ አድሰውና ጠብቀው ያቆዩት ሲሆን፣ መጽሐፉ በምድር ላይ ስላለው የነገሥታት ዲፕሎማሲ፣ ስለ ሰብአዊ ፍጡራን መከራ፣ ጽናትና ሕብረት በጥልቀት የሚሰብክ፣ የሰው ልጅ በፈጣሪ መሬት ላይ ያሳለፈውን ፈታኝ የሕይወት ጎዳና የሚያሳይ ሕያው ምስክር ነው።
ዴርቶጋዳ መጽሐፍት መደብር! | 2 850 |
| 11 | እነዚህ ሦስት ድንቅ መጽሐፍት በአገራችን የሥነ-ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ የኢትዮጵያን አብዮት ማዕበል በጥልቅ የከሸኑ እውነተኛ የጥበብ ማማዎች ናቸው። ታላቁ ደራሲ ብርሃኑ ዘሪሁን በዚሁ ታዋቂ የረጅም ልብ-ወለድ ጥራዝ፣ የአንድን ትውልድ የለውጥ ናፍቆት፣ የትግል ወላፈን እና የሕዝብን ማኅበራዊ ስብራት በደማቅ ቀለማት ይሥላል።
ታሪኩ በለውጥ ዋዜማ ካለው ማኅበራዊ መናወጥ ተነስቶ፣ አሮጌው ሥርዓት ሲናድና አዲሱ አብዮት በደም አበራሽ ጎዳና ላይ ሲወለድ የነበረውን እውነተኛ ገጽታ በገጸ-ባህሪያቱ ሕይወት ውስጥ በሕያውነት ይተርካል።
ደራሲው የሰው ልጅን የሥልጣን ጥም፣ የነፃነት ፍለጋ፣ የክህደት ምሬት እና የጋራ ሰብአዊ መከራን በብዕሩ በመቅረጽ፣ አንባቢን በታሪክ ማኅደር ውስጥ እንዲጓዝ የሚያደርግና የዘመኑን ማኅበራዊ ውቅያኖስ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የማይደበዝዝ የሥነ-ጽሑፍ ሐውልት ነው።
መጽሐፎችን በመደብራችን ታገኟቸዋላችሁ! | 2 401 |
| 12 | ይህ መጽሐፍ ቅዱስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ጥንታዊና ታሪካዊ የቅዱሳት መጻሕፍት ሀብት በዕንግሊዝኛ ቋንቋ አጠቃሎ የያዘ ታላቅ መንፈሳዊ መዝገብ ነው።
መጽሐፉ «The Complete Orthodox Ethiopian Bible in English» በሚል ርዕስ በኮቨናንት ሴክሬድ ፕሬስ (Covenant Sacred Press) የታተመ ሲሆን፣ በውስጡም ከቀኖና መጻሕፍት በተጨማሪ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ የማይገኙ ነገር ግን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቀኖና ውስጥ በቅዱስነትና በስልጣን የተጠበቁትን እንደ መጽሐፈ ሄኖክ፣ መጽሐፈ ኢዮቤልዩ፣ የዕዝራ ሱቱኤል እና መጽሐፈ ጥበብ ያሉ እጅግ ውድ የሆኑ ጥንታውያንና አዋልድ መጻሕፍትን አካትቶ የያዘ የጥበብ ምንጭ ነው።
በሽፋኑ ላይ በግልጽ እንደሚታየው፣ በውስጡ 88 የታተሙ መጻሕፍትን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ ዲጂታል መጻሕፍት ማጣቀሻዎችን (3500 Books) የያዘ በመሆኑ፣ ለአንባቢያንና ለተመራማሪዎች ሰፊ መንፈሳዊና ታሪካዊ ዕውቀትን የሚያድል፣ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ክርስቲያናዊ ቅርስና ሥነ-ጽሑፋዊ ትውፊት ለዓለም የሚያስተዋውቅ ድንቅ የሃይማኖት ሰነድ ነው።
ኦርጅናል የሆኑ ሁለት ፍሬ መጽሐፎችን አስገብተናል። እዘዙን ያሉበት ቦታ እናደርሳለን! | 2 497 |
| 13 | "የሰው ፊት"
አንዳንድ ህመም አለ ይማርህ የማይሉት፣
ወደ ውስጥ ዘልቆ የሚገባ ካ'ንጀት።
በቃላት ሰንሰለት ሊገለጥ የማይችል፣
የጭንቅላት ህመም ክፉ የልብ ቁስል።
በዚህ ምስል መሀል....
ይታየኛል ህመም ይታየኛል ስቃይ፣
ይነበባል በደል ተጽፏል ፊቱ ላይ።
ኑ እስኪለን ድረስ....
ማግኜትና ማጣት መቼገር ቢኖርም፣
እንደ ሰው ፊት ማየት የሚያም ነገር የለም።
ገጣሚ ጊዜአለው✍️ | 2 596 |
| 14 | የሰሞኑ የአዲስአበባ ኢግዚቢሽን የመጽሐፍት አውደ ርዕይ ያልተካፈላችሁ አንባቢዎች ክፉኛ ተጎድታችኋል።
አሁንም አልረፈደም ኢግዚቢሽኑ ነገ እና እሁድም የሚቀጥል ሲሆን በተለይ እሁድ ይህ የአዳም ረታ መጽሐፍ በይፋ ለንባብ ይቀርባልና አንዳትቀሩ።
ከተወዳጅ ደራሲዎች ጋር የማይረሳ ጊዜም አሳልፉ! | 2 714 |
| 15 | የተነበቡ (ያገለገሉ) አሮጌ መጽሐፍትን እንገዛለን!
በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ የተፃፉ፦
👉 የታሪክ
👉 የሐይማኖት
👉የፍልስፍና
👉የሳይኮሎጂ እና ልቦለድ መጽሐፍትን እንገዛለን!
ከዚህም በተጨማሪ
👉ጋዜጣ
👉ወረቀት
👉የክር ካሴቶችን እንገዛለን!
ስልክ ፦0991001450
ወይም ከታች ባለው የቴሌግራም ሊንክ ገብታችሁ አናግሩኝ!
👇👇👇👇👇
@a9OaG
@a9OaG
@a9OaG | 3 211 |
| 16 | በ 1900 ማለትም ከዛሬ 118 ዓመት በፊት የታተመ የኦሮምኛ የማቴዎስ ወንጌል ማለትም አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ሲሆን አሰጅግ ታሪካዊ ሰነድ ነው።
መጽሐፉን በመደብራችን ታገኙታላችሁ።
0991001450 | 116 |
| 17 | "የሴቶች ገመና መጽሐፍ ዋና ዋና ነጥቦች"
👉የሴቷ የግል ተግባራትና ምስጢራት
👉የሴቷ አካላትና የግል ንብረቶች
👉ሴቶች በቤታቸው ደብቀው የሚያስቀምጧቸው 5 ነገሮች
👉ሴቶች ስለወሲብ ምን ያህል ያስባሉ?
👉ሴቶች እራሳቸውን በራሳቸው በወሲብ ያረካሉን?
👉ሴቶች ከወንዶች ይበልጥ ውስብስብ የሆኑበት ምክንያቶች
👉የተለያዩ የሴት ምስጢራት
👉ድንግልናዬን መቼና እንዴት አጣሁ?
👉ገመናዊ ውይይት - የሴቷ ራስን በራስ ማርካት (ሴጋ) ምስጢር
👉የምትፈልጋትን ሴት ለማግኘትና ለማማለል
👉 በመጀመሪያው ዕይታ ሴቷን የሚማርክ የወንድ ዓይነት
👉የወንዶች መልክ በሴቶች ዘንድ ያለው ዋጋ
ሴቶችን ቶሎ ወንድ እንዲቀርቡ የሚያደርጉ ነገሮች
👉አጫጭር ወንዶች ሴቶችን ለመማረክ ማሟላት የሚጠበቅባቸው ዓበይት ነጥቦች
መጽሐፉን እኛጋ ታገኙታላችሁ!
በpdf የምትሉ pdf እኔጋ የለኝም ።
ከታች ባለው የቴሌግራም user name ጠይቁት።
👇👇👇
@gmy231
@gmy231 | 3 582 |
| 18 | ይህ መጽሐፍ የ20ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያን የፖለቲካ ምስቅልቅልና ማኅበራዊ ገጽታ በጥበብ የሳለ፣ የአንድ ታማኝ የሥርዓት ሰው መታሰቢያ ነው። መጽሐፉ የነገሥታቱን የሥልጣን ኮሪደር ውስብስብ ሽኩቻና የባለሥልጣናቱን የጽናት ፈተና በጥልቅ ትንተና ያጋልጣል።
የአፄ ኃይለ ሥላሴን ዘመን ውስብስብ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ገጽታዎች ጥልቅ በሆነ እይታ የሚተርክ እውነተኛ ትዝታ እና ማሽታወሻ ሲሆን ደራሲው የነበራቸውን ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊነቶች መሠረት በማድረግ፣ የዘመኑን የቢሮክራሲ ጉዞና የሥልጣን ሽኩቻ በድፍረትና በጥልቀት ጽፈውታል! | 2 977 |
| 19 | የተከፈለበት ማስታወቂያ!
ያገለገሉ አሮጌ መጽሐፎችን እንገዛለን!
ከታች ባለው user name አናግሩን!
@gmy231
@gmy231 | 3 862 |
| 20 | ከ 73 ዓመት በፊት የተጣፈ ግጥም!
መንግስቱ ለማ✍️ | 4 259 |
