ከመፅሀፍት ዓለም 📖 📚books world 📖📚
የተለያዩ ሀገር በቀልና የባህር ማዶ መፅሀፎች የሚገኙበት ገፅ ሲሆን ገፁን ሼር በማድረግ ተደራሽነቱን ያስፉት 📚📚
Mostrar más1 781
Suscriptores
+524 horas
+447 días
+15430 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
///እናት ቀን የላትም///
ቀንሽን በሙሉ ለልጆችሽ ሰጥተሽ፣
የኔ የምትይው እናት ምን ቀን አለሽ።
ስለዚህም እኔ!
ላንች ቀን ተቆርጦ ቀኗ ነው ቢሉኝም፣
እናቴን ነው እንጅ ቀኗን አላከብርም።
ለምን ካላችሁኝ!
እድሜዋን በሙሉ ሳትሰስት ስትሰጠኝ፣
እሷ እየተራበች እኔን ስታጎርሰኝ።
የኖርኩ እኔ ልጇ!
ብዙ እልፍ ስቃዮች እንዳለፈች ባውቅም፣
ለኔ የምትለው እናት ቀን የላትም።
ገጣሚ ጊዜአለው ...✍️
❤ 13
የፍቅረኞቻችሁን ስም ክንዳችሁ ላይ መነቀስኮ በራሱ ችግር አይደለም! ከመነቀሳችሁ በፊት ግን ይችን አዳምጡኝ! ብዙ ሰው ከተነቀሳችሁ በኋላ ብትለያዩ ምናምን ይላል ... እኔ እሱ አያሳስበኝም! ችግሩ ስታረጁ ታቱው አንዳንድ የትርጉም ለውጥ ሊያመጣ ይችላል! ለምሳሌ አባባ ሳህሌ ወጣት በነበሩበት ዘመን ውጥርጥር ያለ ጡንቻቸው ላይ የራሳቸውንና የባለቤታቸውን ስም ተነቀሱ! "ሳህሌ ፣ ያርበድብዱ " እንደውም የተረፈው ቦታ ላይ ጦርና ጋሻ ጨመሩበት!
እያረጁ ጡንቻቸው ሲሟሽሽ ግን ከሚስታቸው ስም የተወሰኑ ፊደላት በቆዳቸው ሽብሽባት ውስጥ እየገቡ ተደበቁ ! እና የቀሩት ፊደሎች ሲነበቡ ትንሽ የባለጌ አይነት ሆኑ (ያው ትገምታላችሁ) ...🤔 የባሰው ነገር ደግሞ የተነቀሱት ጋሻ ቆዳቸውን ተከትሎ ወደታች ታጠፈና የተንጠለጠሉ ሁለት ፍሬዎች መሠለ ! በዛ ላይ ከላይ ጦሩ አለ..."ኧረ ወዲያ ሸፈን ያርጉት አንቱ ሰው አማረብኝ ብለው ነው? ሆሆ በስተርጅና " ይላሉ ሚስቲቱ ባዮት ቁጥር እፍረት ባንዣበበት ፊት! "ምን ሆነ "ብለው ቆዳቸውን ሳብ አድርገው ሲያዪት የተደበቁት ፊደላት ይወጡና ይስተካከላል ፤ ሲለቁት ይባልጋል! እንዲቹ ሲጨቃጨቁ ይውላሉ😂!
አሌክስ አብርሃም
😁 10😇 1
ውድ የዚህ ገፅ ተከታዮች እንደምን ሰነበታችሁ!? በእናንተ ጥያቄ መሰረት ፍቅር እስከመቃብርን በትረካ እያቀረብንላችሁ ነው። ሌላ በትረካ እንዲቀርብ የምትፈልጉት መፅሀፍ ካለ መጠዬቅ ትችላላችሁ!
👍 3
ይህ ሰው በወጣትነቱ ነው ጫካ የገባው ምናልባትም ጫካ ገብቶ በትግሉ ውጤት የሀገር መሪ መሆን የቻለ ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ጠቅላይ ሚኒስተርም ነው፡፡ መለስ ከታጋይነቱ ጎን ለጎን አሰላሳይ፣ አንባቢና ጨዋታ አዋቂ ነው፡፡ የአዳም ስሚዝ፣ ሙራይ ሮዝባርድና የሚኬል ማሽለር ስራዎችን እድሜው ሐያዎቹ መጀመሪያ ላይ እያለ ነው ያነበባቸው፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የአለም ኢኮኖሚክ ፎረም እውቀቱ የተገለጠባቸው መድረኮች ናቸው፡፡ የአክሱም ሐውልት መመለስና የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ በአዲስ አበባ መቅረቱ የዲፕሎማሲ እውቀቱ ውጤት ናቸው፡፡ የህዳሴ ግድብ ደግሞ ስሙን ከመቃብር በላይ ያስቀረው ፕሮጀክቱ ነው፡፡
መለስ ጨዋታ አዋቂም ነበር፡፡ አቶ ልደቱ አያሌው "የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር በአስደንጋጭ ሁኔታ እየጨመረ ነው ይህ ደግሞ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ አደጋ ነው" ሲሉ ላቀረቡት ጥያቄ የመለስ ዜናዊ መልስ እንዲህ የሚል ነበር
"የሀገሪቱ የድህነት ምንጭ ህዝቡ 75 ወይም 80 ሚሊየን መድረሱ ነው ብዬ አልወስድም ምክንያቱም ሰው ሲወለድ ሆድ ብቻ አይደለም ይዞ የሚወለደው እጅና እግርም ይወለዳል፤ እጅ ይሰራል እግር ይሰራል ከዛ ሆድ ይበላል ስለዚህ ዋናው ጉዳይ ሆዱ ብቻ የሚሰራን ግለሰብ እጅና እግሩ እንዲሰራ ማድረጉ ነው"
ከአንድ የፓርላማ አባል ቅርሶችን ስለመጠበቅ ቀርቦላቸው ለነበረው ጥያቄ የሰጡት ምላሽ "ቤተመንግስት የምንገለገልባቸው በሐይለስላሴ ዘመን የተገዙ መርሴዲስ መኪኖች ነበሩ፤ ቅርስ ስለሆኑ ለሀገራችን መልካም ስም ያመጣሉ ብለን ስንጠቀምባቸው ቆየን በኋላ ግን ከቦሌ የሚመጡ እንግዶችን ይዘው ወደቤተመንግስት ሲመጡ ሒልተን ሆቴል አካባቢ ዳገቱ እየከበዳቸው መቆም ጀመሩ፤ እንዳንቀይራቸው ቅርስ ናቸው እንዳንጠቀምባቸው ከሒልተን ማለፍ አቃታቸው ምን እናድርግ?" የሚል ነበር
ለማንኛውም በህይወት ቢኖሩ ዛሬ ልደታቸው ነበር፡፡ እስኪ ስለመለስ ዜናዊ ትውስታችሁን አጋሩን፡፡