fa
Feedback
ሪፖርተር ET

ሪፖርተር ET

رفتن به کانال در Telegram

🔖 ይህ የሪፖርተር ET የቴሌግራም ገፅ ነው ®️ ☆ በቻናሉ 📌 ፈጣን 📌 ትኩስ 📌 ወቅታዊ እና 📌 ወሳኝ መረጃዎችን እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል ! 🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ሪፖርተር ET

کانال ሪፖርተር ET (@reportereth) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 20 075 مشترک است و جایگاه 11 616 را در دسته اخبار و رسانه‌ها و رتبه 1 677 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 20 075 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 09 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -409 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -16 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 21.37% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً N/A% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 0 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 0 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
🔖 ይህ የሪፖርተር ET የቴሌግራም ገፅ ነው ®️ ☆ በቻናሉ 📌 ፈጣን 📌 ትኩስ 📌 ወቅታዊ እና 📌 ወሳኝ መረጃዎችን እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል ! 🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 10 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانه‌ها تبدیل کرده‌اند.

20 075
مشترکین
-1624 ساعت
-737 روز
-40930 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰርን በተመለከተ ይህን ብሏል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ያላስተሳሰሩ ደን
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰርን በተመለከተ ይህን ብሏል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ያላስተሳሰሩ ደንበኞች የባንክ አገልግሎት ማግኘት አይችሉም። በመሆኑም ባንካችን ያዘጋጀውን የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) በመጠቀም ወይም ወደሚቀርባችሁ የባንካችን ቅርንጫፍ በመሄድ  ሂሳባችሁን እንድታስተሳስሩ እንገልፃለን ብሏል። @seledadotio @seledadotio

1447ኛው የዒድ አልአድሃ በዓል ረቡዕ ይውላል። ​ዛሬ በሳዑዲ አረቢያ ጨረቃ በመታየቷ የዙል-ሂጃ ወር መግባቱ ተገልጿል። ​ይህን ተከትሎ 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (የዓረፋ) በዓል ዕሮብ ረቡዕ ግ
1447ኛው የዒድ አልአድሃ በዓል ረቡዕ ይውላል። ​ዛሬ በሳዑዲ አረቢያ ጨረቃ በመታየቷ የዙል-ሂጃ ወር መግባቱ ተገልጿል። ​ይህን ተከትሎ 1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (የዓረፋ) በዓል ዕሮብ ረቡዕ ግንቦት 19 ተከብሮ ይውላል። #Haramain @tikvahethiopia

የዒድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል የሚውልበትን ቀን ለመወሰን የዙል ሂጃህ ወር ጨረቃ ዛሬ ማታ ትጠበቃለች! የታላቁን የዒድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል የሚውልበትን ትክክለኛ ቀን ለመወሰን፣ የዙል ሂ
የዒድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል የሚውልበትን ቀን ለመወሰን የዙል ሂጃህ ወር ጨረቃ ዛሬ ማታ ትጠበቃለች! የታላቁን የዒድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል የሚውልበትን ትክክለኛ ቀን ለመወሰን፣ የዙል ሂጃህን ወር መግቢያ ጨረቃ ዛሬ ማታ ይከታተላሉ። እንደ ዘገባዎች መግለጫ፡ * የጨረቃዋ መታየት ዛሬ ማታ ከተረጋገጠ፣ ታላቁ የዒድ በዓል ረቡዕ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም (May 27, 2026) ይጀምራል። * ጨረቃዋ ዛሬ ማታ ካልታየች ደግሞ፣ በዓሉ ሐሙስ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም (May 28, 2026) ላይ የሚውል ይሆናል። በዓሉ የሚውልበት ቀን በይፋ እስኪታወቅ ድረስ፣ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዙል ሂጃህ ወር እና ለታላቁ የዒድ አል-አድሃ (የአረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ይህ በዓል የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የደግነት በዓል እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን። ዒድ ሙባረክ! Kul 'am wa antum bi-khair!

ዛሬ የእናቶች ቀን እየተከበረ ይገኛል ለሁሉም እናቶች እንኳን ለእናቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ። ፈጣሪ ለእናቶቻችን ረጅም እድሜ ከ ጤና ጋር ይስጠልን።🙏 🙏ክብር ለነዛ የሰው ፊት እየገረፋቸው በመ
ዛሬ የእናቶች ቀን እየተከበረ ይገኛል ለሁሉም  እናቶች እንኳን ለእናቶች ቀን በሰላም አደረሳችሁ። ፈጣሪ ለእናቶቻችን ረጅም እድሜ ከ ጤና ጋር ይስጠልን።🙏 🙏ክብር ለነዛ የሰው ፊት እየገረፋቸው በመከራ መሀል ሰው ላደረጉን እናቶች🥰 እስቲ ለእናቶቻችን ❤️ SHARE | @ETHIO_ARSENAL

ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ሊመጡ ነው የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑ ተዘግቧል የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ና
ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ሊመጡ ነው የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ መሆኑ ተዘግቧል የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኬንያ ናይሮቢ የሚካሄደውን "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ ካጠናቀቁ በኋላ፣ በመጪው ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለአጭር የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ታውቋል። ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡት በጥንቃቄ የተመረጡ የፈረንሳይ ግዙፍ ኩባንያዎች መሪዎችን በማስከተል ሲሆን፣ ጉብኝቱም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው ይላል የካፒታል ዘገባ። በፕሬዝዳንቱ የታጀበው ልዑክ እንደ ካርፉር ያሉ ታዋቂ የችርቻሮ ንግድ ተቋማትን እና ሜሪዲያም የተሰኘውን የኢንቨስትመንት ድርጅት አመራሮችን ያካተተ ሲሆን፣ በተለይም ካርፉር ከኢትዮጵያው ሚድሮክ ጋር በፈጠረው የፍራንቻይዝ ስምምነት አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት ማቀዱ የጉብኝቱ አንዱ ዋነኛ ትኩረት መሆኑ ተጠቁሟል።

በአዲስአበባ የሚገኘዉ የፋኖ ክንፍ ቅሬታ አነሳ ለተሃድሶ እየተሰጠ ያለው ስልጠና አጥጋቢ አይደለም ሲል “በአማራ ክልል ትጥቅ ትግል” ላይ የነበረው እና አሁን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር እየተወያየ
በአዲስአበባ የሚገኘዉ የፋኖ ክንፍ ቅሬታ አነሳ ለተሃድሶ እየተሰጠ ያለው ስልጠና አጥጋቢ አይደለም ሲል “በአማራ ክልል ትጥቅ ትግል” ላይ የነበረው እና አሁን ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር እየተወያየ ያለው ‛የፋኖ ክንፍ’ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በበኩሉ በጫካ ካሉ ከታጣቂዎች ጋር እያካሄደ ያለውን ግንኙነትን በተመለከተ አንዳንድ ጉዳዮች በግልጽ አይነገሩም ብሏል። ‛የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት’ ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ሀላፊ እያሱ አባተ እንደገለጹት “ለተሃድሶ በትንሹ ዘጠና ቀናት መስጠት ነበረበት” ያሉ ሲሆን አሁን ላይ ግን እየተሰጠ ያለው ለሰባት ቀናት ብቻ መሆኑን ገልጸዋል። Via Ankuar Merja

በፌደራል ፖሊስ እና በባለሀብቷ በረከት ወርቁ መካከል ያለው ውጥረት አይሏል! ባለሀብት በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ) በወንጀል መፈለጓን ተከትሎ ከባድ ውንጀላዎችን የሰነዘረችበት ምላሽ ሰጥታለች።
በፌደራል ፖሊስ እና በባለሀብቷ በረከት ወርቁ መካከል ያለው ውጥረት አይሏል! ባለሀብት በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ) በወንጀል መፈለጓን ተከትሎ ከባድ ውንጀላዎችን የሰነዘረችበት ምላሽ ሰጥታለች። ባለሀብቷ ከእርሻ ስራዋ ወጥታ ወደ ወርቅ ማዕድን ዘርፍ መግባቷን እንደምትቆጭ ገልጻ፣ ስምንት ሚሊዮን ብር ሀገር አሳጣሽ መባሏን በማጣጣል "እናንተ ራሳችሁ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወስዳችሁብኛል" ስትል ስማቸውን ያልጠቀሰቻቸውን አካላት ወንጅላለች። በተጨማሪም የተፈቀደላትን ነዳጅ እንዳልወሰደችና ሌሎች አካላት ሸጠው እንደበሉት በመጥቀስ፣ ድርጊቱ እሷን ከመንገድ ለማስወገድ የተጠነሰሰ ሴራ እንደሆነ ገልጻለች። ባለሀብቷ አብሮት ስሙ የተጠቀሰው አቡሽ አየለ 28 የሚደርሱ የወርቅ ማውጫዎች ያሉትና ለብሔራዊ ባንክ በኩንታል ወርቅ የሚያስገባ መሆኑን በመጥቀስ፣ በወርቅና ነዳጅ ዘርፍ ያሉ ጥቂት ቡድኖች ሌሎች ተወዳዳሪዎች እንዲወገዱ እያደረጉ ነው ስትል ተናግራለች። "መጨረሻውን አብረን እናያለን" በሚል መልእክት ምላሽዋን የደመደመችው በረከት ወርቁ፣ ከዚህ ድርጊት ጀርባ ያሉ ግለሰቦች እጃቸውን እንዲሰበስቡ አሳስባለች። በአሁኑ ወቅት ጉዳዩ በፖሊስ የክትትል ሂደት እና በባለሀብቷ የመከላከል ምላሽ መካከል ሆኖ ከፍተኛ ህዝባዊ ትኩረትን ስቧል።#ጉርሻ

ወ/ሮ በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ)ን ጨምሮ 4 ሰዎችን በወንጀል እንደሚፈልጋቸው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል እንደሚፈልጋቸው ነው ያስታወቀው። ግለሰቦቹ፥ የኢ
ወ/ሮ በረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ)ን ጨምሮ 4 ሰዎችን በወንጀል እንደሚፈልጋቸው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። ፖሊስ በከባድ የሙስና ወንጀል እንደሚፈልጋቸው ነው ያስታወቀው። ግለሰቦቹ፥ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል ተብለው ክስ ከተመሰረተባቸው 13 ግለሰቦች መካከል ናቸው። ቴሌግራም ቻናላችንን JOIN በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በትኩሱ ይከታተሉ 👇   ■➥   http://T.ME/REPORTERETH   ■➥   http://T.ME/REPORTERETH

በዛሬው ዕለት በአለማችን የአህዮች ቀን እየተከበረ ይገኛል ! ለአህያ ጓደያቹ ላኩለት 😁
በዛሬው ዕለት በአለማችን የአህዮች ቀን እየተከበረ ይገኛል ! ለአህያ ጓደያቹ ላኩለት 😁

ሌ/ጀ ታደሰ ወረደ ማስጠንቀቂያ ሰጡ #FastMereja I በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ውስጥ ያለው የውስጥ የሥልጣን ሽኩቻ ወደ ከረረ ደረጃ መሸጋገሩን ተከትሎ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ሌተናል
ሌ/ጀ ታደሰ ወረደ ማስጠንቀቂያ ሰጡ #FastMereja I በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ውስጥ ያለው የውስጥ የሥልጣን ሽኩቻ ወደ ከረረ ደረጃ መሸጋገሩን ተከትሎ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ የተቃውሞ መግለጫ አወጡ። ዛሬ ሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም "ተመርጠናል" የሚሉ አካላት በጸጥታ ኃይሎች ታጅበው በጊዜያዊ አስተዳደሩ የካቢኔ አዳራሽ ስብሰባ መጀመራቸውን ገልጸዋል። ድርጊቱ "የሥልጣን ወረራ" መሆኑን የጠቀሱት ጄነራሉ፣ ለሚከተለው ማንኛውም ዓይነት ቀውስ ተጠያቂው ይህ በጉልበት ሥልጣን ለመያዝ የሚንቀሳቀሰው አካል መሆኑን አስታውቀዋል።

ሰበር ዜና መቀሌ የተዋጊ ጄት ቅኝት እየተደረገ ነው! በመቀሌ ከተማ ከአንድ ሳምንት ልዩነት ለሁለተኛ ጊዜ የተዋጊ ጄት ቅኝት መደረጉ ወጋህታ የአይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡ የጄት ቅኝቱ 5
ሰበር ዜና መቀሌ የተዋጊ ጄት ቅኝት እየተደረገ ነው! በመቀሌ ከተማ ከአንድ ሳምንት ልዩነት ለሁለተኛ ጊዜ የተዋጊ ጄት ቅኝት መደረጉ ወጋህታ የአይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡ የጄት ቅኝቱ 5 ሰአት 37 ደቂቃ ጀምሮ በስፋት ታይቷል፡፡ ከፕሪቶሪያ ስምምነት መፈረም በኋላ የጄት ቅኝት ሲደረግ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡

ሰበር_መፈንቅለ መንግስት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መፈንቅለ መንግስት በማድረግ ዛሬ በይፋ ወደ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ገብተዋል። ​ዶ/ር ደብረፅዮን የካቢኔ አባላትን የጠሩ ሲሆን፤ በግልበጣ ስለ
ሰበር_መፈንቅለ መንግስት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መፈንቅለ መንግስት በማድረግ ዛሬ በይፋ ወደ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ገብተዋል። ​ዶ/ር ደብረፅዮን የካቢኔ አባላትን የጠሩ ሲሆን፤ በግልበጣ ስለመጣው አዲስ አስተዳደር ማብራሪያ ለመስጠትና ወቅታዊ ሁኔታዎችን አስመልክቶ ለመወያየት ለጋዜጠኞች ጥሪ አቅርበዋል። #Desye

ልዩ መረጃ! ‹‹ተዘጋጅተናል..›› ጀነራል አበባው ታደሰ በጦር ግንባር ታዩ! የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ በሰሜን ምእራብ ዕዝ ጉብኝት እያደረጉ መሆኑ ታውቋል፡፡
ልዩ መረጃ! ‹‹ተዘጋጅተናል..›› ጀነራል አበባው ታደሰ በጦር ግንባር ታዩ! የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ በሰሜን ምእራብ ዕዝ ጉብኝት እያደረጉ መሆኑ ታውቋል፡፡ ፊልድ ማርሻል ብርሓኑ ጁላ የላኩትን መልዕክትም ለሰራዊቱ ማድረሳቸውን አንዳፍታ ሚዲያ ከሰራዊቱ ድህረገጽ ተመልክቷል፡፡ በፌዴራል መንግስቱ እና በሕውሓት ኃይሎች መካከል ያለው ውጥረት ባየለበት በዚህን ወቅት፤ ጀነራሉ የሰራዊቱን የግዳጅ ዝግጁነት ለመመልከት በሰሜን ምእራብ ዕዝ ተገኝተዋል፡፡ ጀነራሉ በግንባር የሚገኙ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ የጦር ክፍሎችን ወታደራዊ ፣አካላዊና ስነ-ልቦናዊ ዝግጁነት ተዘዋውረው ተመልክተዋል የተባለ ሲሆን፤ እንዲህ የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል፡- ‹‹ዕዙ ከታሪካዊ ጠላቶቻችንም ይሁን ከባንዳዎች ሊሰነዘር የሚችል ጥቃትን መመከትና መደምሰስ በሚያስችለው የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል›› የሚል። ጀነራል አበባው ‹ባንዳ› ሲሉ የጠሯቸውን አካላት በስም ባይጠሩም፤ ከዚህ ቀደም በመከላከያ አመራሮች ‹ባንዳ› በሚል የሚጠራው በአካባቢው ያለው ኃይል ግን የፋኖ አማጺ ቡድን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ቀጥለውም ‹‹የህወሃትን አገር የማፍረስ ተከታታይ ወረራ በመመከትና ሀገርን በማፅናት ትልቅ ሚና የነበረው ጠንካራ ዕዝ›› በማለት አሞካሽተውታል፡፡ ‹‹ሰሜን ምዕራብ ዕዝ በአማራ ክልል ግጭትና ሁከት ለመፍጠር በተንቀሳቀሰው የሀገር ውስጥ ባንዳ በሆነው ፅንፈኛው ቡድን ላይ ጠንካራ ምት በማሳረፍ ያሰበውን ኢትዮጵያን የማጥፋት ሴራ በማክሸፍ ፅንፈኛው ቅስሙ እንዲሰበር እና እጅ እንዲሰጥ በማድረግ ወገን የኮራበት፤ ጠላት ያፈረበትን ከፍተኛ ስራ የሰራ ዕዝ ነው›› ሲሉም አክለዋል፡፡ ጄኔራል አበባው ታደሠ ከሠራዊቱ ጋር በነበራቸው ቆይታ ‹‹ኢትዮጵያና ተቋሙ ይኮሩባችኋል›› ሲሉም ተናግረዋል።

አርሰናል ከ20 ዓመት በኋላ በሻምፒዮንስሊግ ለፍጻሜ ደረሰ አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ግማሽፍጻሜ የመልስ ጨዋታ አርሰናል አትሌቲኮ ማድሪድን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለፍጻሜ ደርሷል፡፡ በኤምሬትስ በተደረገው ጨ
አርሰናል ከ20 ዓመት በኋላ በሻምፒዮንስሊግ ለፍጻሜ ደረሰ አውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ግማሽፍጻሜ የመልስ ጨዋታ አርሰናል አትሌቲኮ ማድሪድን 1 ለ 0 በማሸነፍ ለፍጻሜ ደርሷል፡፡ በኤምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ቡካዮ ሳካየማሸነፊያዋን ግብ አስቆጥሯል፡፡ በመጀመሪያው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታበስፔን አንድ አቻ ተለያይቶ የተመለሰው አርሰናል በድምር ውጤት 2 ለ 1 በማሸነፍ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል፡፡ በዚህ ዓመት በሻምፒዮንስ ሊግአንድም ጨዋታ ያልተሸነፈው የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በአውሮፓ ትልቁ የክለቦች ውድድር ከ20 ዓመት በኋላ የደረሰበትም ምሽት ሆኗል፡፡ አርሰናል በቡዳፔስት በሚደረገውየፍጻሜ ጨዋታ ከባየር ሙኒክ እና ፒኤስጂ አሸናፊ የሚገናኝም ይሆናል፡፡

ሰበር‼️ ኢራን በዛሬው ዕለት በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ በፉጃሪህ የነዳጅ ማከማቻ እና የኢንደስትሪ ማዕከል ላይ የድሮን ጥቃት የፈፀመች ሲሆን ከጥቃቱ በኋላ ከፍተኛ እሳት እንደተነሳ የተባበሩት አረብ
+2
ሰበር‼️ ኢራን በዛሬው ዕለት በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ በፉጃሪህ የነዳጅ ማከማቻ እና የኢንደስትሪ ማዕከል ላይ የድሮን ጥቃት የፈፀመች ሲሆን ከጥቃቱ በኋላ ከፍተኛ እሳት እንደተነሳ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ገልፃለች። ይህንን ጥቃት ተከትሎ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከፍተኛ ባለስልጣን ለሲኤንኤን (CNN) እንደገለጹት፤ አሜሪካ እና እስራኤል በሚቀጥሉት 24 ሰዓታት ውስጥ በኢራን ላይ የአጸፋ ጥቃት ያደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል ስሉ ገልጸዋል። @seledadotio @seledadotio

🚨 BREAKING NEWS❗ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ላይ ተጥሎ የነበረው እገዳ ሊነሳ ይችላል! ​ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግሥት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ የጣ
🚨 BREAKING NEWS❗ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ላይ ተጥሎ የነበረው እገዳ ሊነሳ ይችላል! ​ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ መንግሥት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ የጣለውን እገዳ ዳግም ሊመለከተው እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል። ይህ ውሳኔ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) አባል ለመሆን ለምታደርገው ጥረት አንዱ አካል ነው። ​ዋና ዋና ነጥቦች፦ ​ 🔹 የዓለም የንግድ ድርጅት መስፈርት፦ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ድርጅቱን ለመቀላቀል ማንኛውንም የንግድ ምርት እንዳይገባ መከልከል (Ban ማድረግ) አይቻልም። ስለዚህ እገዳውን ማንሳት የድርጅቱ አባል ለመሆን የግድ አስፈላጊ ነው። 🔹 ከእገዳ ወደ ታክስ፦ እገዳው ተነሳ ማለት ግን ቀድሞ ወደነበረው ሁኔታ ይመለሳል ማለት አይደለም። መንግሥት የነዳጅ መኪናዎች እንዳይበዙ ለማድረግ ከፍተኛ የኤክሳይዝ ታክስ እና የአካባቢ ጥበቃ ክፍያዎችን (Environmental taxation) ሊጥል ይችላል። 🔹 የትኩረት አቅጣጫ፦ መንግሥት አሁንም ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) ቅድሚያ መስጠቱን ይቀጥላል። የነዳጅ መኪናዎች እገዳ ቢነሳም፣ በከፍተኛ ታክስ ምክንያት ዋጋቸው ሊጨምር ስለሚችል የኤሌክትሪክ መኪናዎች አሁንም የተሻለ አማራጭ ሆነው ይቆያሉ። 🔹 ቀጣይ እርምጃዎች፦ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የሚመለከታቸው አካላት በነዳጅ መኪናዎች ላይ የሚጣለውን የታክስ መጠን እና ሌሎች መስፈርቶችን በዝርዝር ተወያይተው ይወስናሉ። ​ ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ ለ23 ዓመታት የዓለም የንግድ ድርጅትን ለመቀላቀል ለምታደርገው ጥረት ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ተገልጿል። ​አዩዘሀበሻ ===================== 💎⬇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇 https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ሰበር ዜና 100 ቢሊዮን ብር መዘረፉ ከተጋለጠ በኋላ ሚዲያዎች በፓርላማ እንዳይዘግቡ ተከለከለ! ሪፖርተር ጋዜጣ በትናንት እትሙ ባለስልጣናት እና አርቲስቶች 98 ቢሊዮን ብር መመዝበራቸውን መዘገቡ መ
ሰበር ዜና 100 ቢሊዮን ብር መዘረፉ ከተጋለጠ በኋላ ሚዲያዎች በፓርላማ እንዳይዘግቡ ተከለከለ! ሪፖርተር ጋዜጣ በትናንት እትሙ ባለስልጣናት እና አርቲስቶች 98 ቢሊዮን ብር መመዝበራቸውን መዘገቡ መነጋገሪያ ሆኖ ውሏል፡፡ 98 ቢሊዮን ብር ማለት የኢትዮጵያ አመታዊ በጀት አምስት በመቶ እንደማለት ነው፡፡ ይህ መረጃ መጋለጡን ተከትሎ ሚዲያዎች ላይ ክልከላ ተጥሏል፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያቀርበው የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ ላይ አዲስ ማለዳን ጨምሮ መንግስታዊ ያልሆኑ የግል መገናኛ ብዙኃን ተገኝተው እንዳይዘግቡ ከልክሏል፡፡ የአዲስ ማለዳን ጨምሮ የግል መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች የመግቢያ በር ላይ መግባት አትችሉም ተብለው ሲከለከሉ እንደ ብሔራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ እና ኦ.ቤ.ኤን. ያሉት ግን ተፈቅዶላቸው መግባታቸውን የአዲስ ማለዳ ሪፖርተር ተመልክቷል፡፡ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ጋር የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በፊት ለፊት መድረክ ለመገምገም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በምክር ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ፕሮግራም የያዘው መርሐ ግብር ባለፈው ዓርብ እንዲዘገብለት ለአዲስ ማለዳ ጥሪ አቅርቦ ነበር፡፡ ነገር ግን ዛሬ ሰኞ ክልከላ ጥሏል፡፡ ይህ ውሳኔ የቋሚ ኮሚቴው ስለመሆኑም ለጋዜጠኞቹ ተነግሯቸዋል፡፡ በተመሳሳይ ዛሬ ከሰዓት ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀው የጤና ሚኒስቴር የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገም ለግል ሚዲያዎች ክፍት ይደረጋል ወይስ እንደ ገንዘብ ሚኒስቴር ክልከላ ይጣልበታል በሚል በስፍራው ከነበሩ ዘጋቢዎች በኩል ለምክር ቤቱ ጥያቄ ቢቀርብም እናሳውቃለን የሚል ምላሽ ከማግኘት ባለፈ ይሁንታ አልተገኘም፡፡ @Ankuar_mereja @Ankuar_mereja

የመውጫ ፈተና ምዝገባ! የቅድመ-ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ምዝገባ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም የሚከናወን መሆኑን አገልግሎቱ አሳውቋል። ተፈታኞች በተሰጠው የምዝገባ ጊዜ ገደብ ው
የመውጫ ፈተና ምዝገባ! የቅድመ-ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ምዝገባ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም የሚከናወን መሆኑን አገልግሎቱ አሳውቋል። ተፈታኞች በተሰጠው የምዝገባ ጊዜ ገደብ ውስጥ ብቻ እንድትመዘገቡ አገልግሎቱ አሳስቧል። ያልተመዘገበ አይፈተንም ተብሏል።

አሜሪካ ጥቃት ከፈፀመችብኝ ረዥም እና ህመም የሚያስከትል የአፀፋ ምላሽ እሰጣለሁ ስትል ኢራን ዛተች ኢራን ዋሽንግተን ጥቃቱን ከፈፀመችብኝ በገልፍ አካባቢ ባሉ የአሜሪካ ቦታዎች ላይ ረዥም እና የሚያሰ
አሜሪካ ጥቃት ከፈፀመችብኝ ረዥም እና ህመም የሚያስከትል የአፀፋ ምላሽ እሰጣለሁ ስትል ኢራን ዛተች ኢራን ዋሽንግተን ጥቃቱን ከፈፀመችብኝ በገልፍ አካባቢ ባሉ የአሜሪካ ቦታዎች ላይ ረዥም እና የሚያሰቃዩ የአፀፋ ምላሽ እንደምትሰጥ ገልጻለች። በሆርሙዝ የባህር ዳርቻ ላይ ያላትን ይዞታ ኢራን በድጋሚ በመግለጽ የዩናይትድ ስቴትስ ጥምረት የውሃ መስመሩን ለመክፈት የያዘውን እቅድ አወሳስቦታል። ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በኢራን ላይ ጦርነት ከከፈቱ ከሁለት ወራት በላይ ሲያስቆጥር የውሃ መስመሩ ተዘግቷል። 20 በመቶውን የዓለም የነዳጅ እና የጋዝ አቅርቦት እንቅስቃሴን በማስተጓጎክ የአለም የኢነርጂ ዋጋ እንዲጨምር እና የኤኮኖሚ ውድቀት ስጋትን ከፍ አድርጓል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኢል ባጋይ የሆርሙዝ ባህርን መዘጋቱን በተመለከተ እንደተናገሩት በጦርነቱ ለራሳችን ጥበቃ በሚል መብታችን ነው ብለዋል።  በአለም አቀፍ ህግ መሰረት ህጋዊ እና ተቀባይነት ያለው ነው ሲሉ አክለዋል። በሌላ በኩል የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ዜጎቿ ወደ ኢራን፣ ሊባኖስ እና ኢራቅ እንዳይጓዙ  ያሳሰበች ሲሆን በአሁኑ ወቅት በነዚያ ሀገራት ያሉት በአስቸኳይ ለቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ጥሪ አቅርባለች። @seledadotio @seledadotio

ፖለቲከኛው ጃዋር መሀመድ በዛሬዉ ዕለት በከፈተዉ የቲክቶክ አካዉንት ፡ በሰአታት ዉስጥ ብቻ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ማግኘቱ አነጋገር ሆኖ ዉሏል። @seledadotio @seledadotio
ፖለቲከኛው ጃዋር መሀመድ በዛሬዉ ዕለት በከፈተዉ የቲክቶክ አካዉንት ፡ በሰአታት ዉስጥ ብቻ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ማግኘቱ አነጋገር ሆኖ ዉሏል። @seledadotio @seledadotio