Nejashi TV // ነጃሺ ቲቪ
የነጃሺ ቲቪ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን ። የተለያዩ መረጃዎችና እውቀቶች ይገበያሉ ። ተቀላቀሉን ! Facebook: https:// Jeilumedia.com Telegram: https://t.me/nejashitvofficial E-mail: nejashitvaddis@gmail.com https://youtube.com/@nejashitva?si=O8pqOoIDjDmMBX74
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام Nejashi TV // ነጃሺ ቲቪ
کانال Nejashi TV // ነጃሺ ቲቪ (@nejashitvofficial) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 12 581 مشترک است و جایگاه 15 985 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 2 675 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 12 581 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 26 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -5 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 12.08% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.10% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 1 520 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 019 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 8 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የነጃሺ ቲቪ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን ። የተለያዩ መረጃዎችና እውቀቶች ይገበያሉ ። ተቀላቀሉን ! Facebook: https:// Jeilumedia.com
Telegram: https://t.me/nejashitvofficial
E-mail: nejashitvaddis@gmail.com
https://youtube.com/@nejashitva?si=O8pqOoIDjDmMBX74”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 26 ژوئیه | +2 | |||
| 25 ژوئیه | +17 | |||
| 24 ژوئیه | 0 | |||
| 23 ژوئیه | 0 | |||
| 22 ژوئیه | +3 | |||
| 21 ژوئیه | +2 | |||
| 20 ژوئیه | +9 | |||
| 19 ژوئیه | +2 | |||
| 18 ژوئیه | 0 | |||
| 17 ژوئیه | +6 | |||
| 16 ژوئیه | 0 | |||
| 15 ژوئیه | 0 | |||
| 14 ژوئیه | +2 | |||
| 13 ژوئیه | 0 | |||
| 12 ژوئیه | +3 | |||
| 11 ژوئیه | +1 | |||
| 10 ژوئیه | +4 | |||
| 09 ژوئیه | +5 | |||
| 08 ژوئیه | +6 | |||
| 07 ژوئیه | +1 | |||
| 06 ژوئیه | +1 | |||
| 05 ژوئیه | +9 | |||
| 04 ژوئیه | +2 | |||
| 03 ژوئیه | +15 | |||
| 02 ژوئیه | +5 | |||
| 01 ژوئیه | 0 |
| 2 | በኢራን በጥንታዊው ፓሳርጋዴ አካባቢ ታሪካዊ ሚህራብ ተገኘ
በደቡባዊ ኢራን በሚገኘውና የአካሜኒድ ግዛት የመጀመሪያ መዲና በሆነው በፓሳርጋዴ ታሪካዊ ፍርስራሽ አቅራቢያ በሚገኝ ካራንሰር ውስጥ የሶላት አቅጣጫ ጠቋሚ ጥንታዊ ሚህራብ ተገኝቷል። ይህ ግኝት በጥንታዊው የንጉሣዊ ቅርስ ላይ በኢስላማዊው ዘመን የተደረጉ አዳዲስ የዕድሳትና የአጠቃቀም ታሪኮችን ለማጥናት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የፓሳርጋዴ ዓለም አቀፍ ቅርስ ማዕከል ኃላፊ ሰይድ አብዱልማጂድ አቤዲ ገልጸዋል። ሚህራቡ የተገኘው ከታላቁ ቂሮስ መቃብር በስተሰሜን 100 ሜትር ገደማ ርቀት ላይ በሚገኘው የሙዛፋሪ ካራንሰር ላይ ጥበቃና ዕድሳት እየተደረገ ባለበት ወቅት ነው።
በ14ኛው ክፍለ ዘመን በሙዛፋሪ ተከታታይ ሥርወ መንግሥት እንደተገነባ የሚታመነው ይህ ካራንሰር፣ ከጥንታዊው የአካሜኒድ ቅርሶች በተወሰዱ ድንጋዮች የተሠራ መሆኑ ተመላክቷል። የቅርስ ጥናት ባለሙያዎች ሕንፃው በወቅቱ መስጅድ፣ የሶላት መስገጃ ስፍራ ሳይሆን እንደማይቀር ግምታቸውን ሰጥተዋል።
በ2004 በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበው የፓሳርጋዴ አርኪኦሎጂያዊ መልክዓ ምድር፣ አሁን በዚህ አዲስ ታሪካዊ ግኝት ተጨማሪ የጥናት አውድ አግኝቷል። የዚህ ግኝት ትክክለኛ ዘመንና ታሪካዊ ይዘት በሂደት ላይ ባሉት የጥበቃና የምርምር ሥራዎች ማጠናቀቂያ ላይ ሙሉ በሙሉ ይፋ እንደሚሆን ይጠበቃል። | 1 278 |
| 3 | ቻይና በቅርቡ በተፈጠረው ውጥረት የኢራንን ሉዓላዊነት እና ደህንነት እንደምትደግፍ አስታወቀች
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 18/2018
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግዪ፤ ቤጂንግ የኢራንን ሉዓላዊነት፣ ደህንነት እና ብሄራዊ ክብር ለማስጠበቅ ከጎኗ እንደምትቆም አረጋግጠዋል ። ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት በኪርጊስታን በተካሄደው የሻንጋይ የትብብር ድርጅት ስብሰባ ከኢራኑ አቻቸው አባስ አራግቺ ጋር ባደረጉት ውይይት መሆኑ ተገልጿል ።
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ በመጣው ውጥረት ላይ ቻይና ጥልቅ ስጋት እንዳላት የገለጹት ዋንግ ዪ፤ ሁሉም ወገኖች ግጭቱን ለማስቆምና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ወደ 'ኢስላማባዱ የመግባቢያ ስምምነት' ዳግም ሊመለሱ እንደሚገባ አሳስበዋል። ቤጂንግ የፓኪስታንን እና የሌሎች ሀገራትን የሽምግልና ጥረት እንደምትደግፍም አክለዋል።
የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ፤ ቴህራን ግጭት እንዲቀጥል እንደማትፈልግና ለድርድር ያላት አቋም አለመቀየሩን ገልጸዋል። በመሆኑም ቻይና ውጥረቱን በማርገብ ረገድ ወሳኝ ሚናዋን እንድትጫወት ጠይቀዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢስላማባዱ የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈጻሚ አለመሆኑን መናገራቸውን ተከትሎ፤ ባለፉት ሳምንታት አሜሪካ እና ኢራን እርስበርስ ወታደራዊ ጥቃቶችን እየተለዋወጡ መሆናቸው ይታወቃል።
በ ቃለላህ ሳዲቅ | 1 296 |
| 4 | በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ላይ ወንድ ልጅ የተገላገለችው ሀዲያ አልመህዲ የልጇን ስም "ኮሚሽን" በማለት ሰየመች
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 17 / 2018
ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኡራ ወረዳ ተወክላ በሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች የምትገኘው ወ/ሮ ሀዳ አልማህዲ፣ የመውለጃ ጊዜዋ የደረሰ ቢሆንም ለኢትዮጵያውያን አብሮነትና ለሀገር ዘላቂ ሰላም ቅድሚያ በመስጠት በጉባዔው ላይ ተገኝታለች። በቆይታዋም በጉባኤው አጀንዳዎች ላይ ለሀገር ይበጃል የምትለውን ሐሳብ በመስጠት ንቁ ተሳትፎ ስታደርግ ቆይታለች።
በጉባኤው ማዕቀፍ ውስጥ በሰላም ወንድ ልጅ የተገላገለችው እናት፣ ለሀገራዊ ሰላም እና መግባባት መሠረት ለሆነው በዚህ ታሪካዊ ክስተት ማስታወሻ ይሆን ዘንድ የልጇን ስም "ኮሚሽን" ብላ ሰይማለች፤ በጉባኤው ወቅት ልጇን በመገላገሏም ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማት ገልጻለች።
ይህ ክስተት ከዚህ ቀደም ባሳለፈው ሳምንት በሀገራዊ ምክክሩ ላይ በመሳተፍ ላይ ከነበረችው የጋምቤላ ክልል ተወካይ ወ/ሮ ክርኑዶ ኡጁሉ ጋር ተመሳሳይነት ያለው ሲሆን፣ እርሷም በጉባኤው ወቅት ወንድ ልጅ ተገላግላ "ምክክር" የሚል ስም መስጠቷ ይታወሳል። | 1 531 |
| 5 | ስፔን በማድሪድ የተከሰተውን ሰደድ እሳት ተከትሎ ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀች
ስፔን ከባድ የሙቀት መጠንንና ድርቅን ተከትሎ በማድሪድ እና በአቪላ ግዛቶች የተከሰተውን ከባድ የደን ቃጠሎ ለመቆጣጠር ብሔራዊ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጇን የሀገር ውስጥ ሚኒስትር ፈርናንዶ ግራንዴ-ማርላስካ አስታወቁ። በቪላ ዴል ፕራዶ፣ በሳን ማርቲን ዴ ቫልዴግሌሲያስ እና በሌሎች አካባቢዎች እየተቀጣጠሉ የሚገኙት ሰደድ እሳቶች በአስቸጋሪ የአየር ንብረት ሁኔታዎች ሳቢያ እየተስፋፉ በመምጣታቸው የሰራዊቱ አስቸኳይ ጊዜ ክፍል ለአደጋው ምላሽ እንዲሰጥ ሀገሪቱ ትዕዛዝ ማስተላለፏን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ሁኔታው እጅግ አሳሳቢ በመሆኑ ከ10,000 በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎች ከቀያቸው በአስቸኳይ እንዲለቁ የተደረገ ሲሆን፣ በክልሉ የሚገኙ ሦስት ዋና ዋና የደን እሳቶች አሁንም ከቁጥጥር ውጭ መሆናቸውን እና በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፉ እንደሚገኙ ተገልጿል። የስፔን ባለስልጣናት አያይዘውም ሀገሪቱ ከባድ የሙቀት ማዕበል እና ጠንካራ ነፋስን ያካተተ አስቸኳይ የጫካ ቃጠሎ እያስተናገደች መሆኑን ገልጸዋል። | 1 380 |
| 6 | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን እና የሚዲያ ባለድርሻ አካላት "ተስፋን እንትከል " በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ አካሄዱ
ነጃሺ ቲቪ:- ሐምሌ 16 ቀን 2018
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን እና የሚዲያ አመራሮች በቀበና መናፈሻ አካባቢ 8ኛውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አካሄደዋል።
የመገኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሀይማኖት ዘለቀ ለመጪው ትውልድ አሻራ ለመጣል ከብዕርና ማይክ ባለፈ አፈር ዝቀው ችግኝ ለመትከል መምጣታቸውን አድንቀው ሚዲያዎች የችግኝ ተከላና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳዮችን አጀንዳችፕው አድእገው ሊሰሩበትና ሰፊ ግንዛቤ መፍጠር እንዳለባቸው አሳስበዋል። | 1 655 |
| 7 | የኢትዮጵያ እና የሳዑዲ ዓረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መከሩ
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 16 / 2018
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ከሳዑዲ ዓረቢያ አቻቸው ልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሃን ቢን አብደላህ ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በስልክ ተወያይተዋል። የሳዑዲ ፕሬስ ኤጀንሲ እንደዘገበው፤ ሁለቱ ባለሥልጣናት ሐምሌ 14 ቀን 2018 ባደረጉት በዚህ ውይይት፣ በሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና በጋራ ጥቅሞች ላይ በሚያተኩሩ በርካታ ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። ምንም እንኳ ኤጀንሲው የተወያዩባቸውን ልዩ ልዩ ቀጣናዊ ጉዳዮች ዝርዝርም ሆነ የተደረሱ ስምምነቶችን ይፋ ባያደርግም፣ ውይይቱ በአፍሪካ ቀንድ እና በመካከለኛው ምስራቅ ውጥረቶች ባሉበት ወቅት መካሄዱ ትኩረት ስቧል።
ይህ ዲፕሎማሲያዊ ውይይት የተካሄደው የቀይ ባሕር ቀጣና የጸጥታ ችግሮች እየተባባሱና የየመኑ ሁቲ ንቅናቄ በሳዑዲ ዓረቢያ ላይ የባሕር ላይ ማዕቀብ መጣሉን ባስታወቀበት ማዕቀፍ ውስጥ ነው። በተመሳሳይ ወቅት ሳዑዲ ዓረቢያ በሶማሊያ ጋልሙዱግ ግዛት እስከ 5 ሺሕ የሚጠጉ ወታደሮችን ሥልጠና በመደገፍ የደኅንነት ትብብሯን ማጠናከሯ ተዘግቧል። በአንጻሩ በኢትዮጵያ በኩል፣ በሳዑዲ የሞት ፍርድ የተበየነባቸውን በርካታ ኢትዮጵያውያን ዜጎች እጣ ፈንታ ለመታደግና ቅጣቱን ለማስቆም ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንዲደረግ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች እና የሀገር ውስጥ አካላት ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ። | 1 443 |
| 8 | የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የ2018 የክረምት በጎ ፈቃድ ንቅናቄ መርሃ ግብር ይፋ አደረገ
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 15 / 2018
የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል “ንቁ ወጣት ለተሻለ ነገ!” በሚል መሪ ቃል በከተማ አቀፍ ደረጃ የሚካሄደውን የ2018 የክረምት በጎ ፈቃድ ንቅናቄ መርሃ ግብር በይፋ አስጀመረ። ካውንስሉ ወጣቶች የዕረፍት ጊዜያቸውን በማህበራዊ አገልግሎት፣ በአካባቢ ጥበቃና በሰብዓዊ ድጋፎች እንዲያሳልፉ ለማስቻል ባዘጋጀው በዚህ አጠቃላይ ንቅናቄ አማካኝነት የወጣቶችን በጎ ፈቃደኝነት፣ አንድነትና የመረዳዳት ባህል ለማጠናከር እንደሚረዳ ገልጿል።
በዘንድሮው የክረምት ንቅናቄ ከሚከናወኑ ዋና ዋና ተግበራት መካከል በህክምና ላይ የሚገኙ ወገኖችን ሕይወት ለማዳን የታለመ የደም ልገሳ ዘመቻ፣ የአረንጓዴ አሻራና የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እንዲሁም አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች የሚደረግ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ይገኙበታል። በተጨማሪም ወጣቶችን ከአሉታዊ ተጽዕኖዎች ለመጠበቅ የሚረዱ የስፖርት እና የወንድማማችነት ውድድሮች ከመካሄዳቸውም በላይ፣ ለአቅመ ደካማ አረጋውያንና ወገኖች የመኖሪያ ቤት ጣሪያና የግድግዳ እድሳት ጥገናዎች እንደሚከናወኑ ተገልጿል።
እነዚህን ማህበራዊ የበጎ አድራጎት ተግባራት እውን ለማድረግ የመንግስት ተቋማት፣ የግል ድርጅቶች፣ ባለሃብቶች፣ የሃይማኖት ተቋማት እና ማንኛውም በጎ አሳቢ ዜጋ ከካውንስሉ ጎን በመቆም የንቅናቄው አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል። ካውንስሉ በሁሉም ክፍለ ከተሞች በሚከናወኑት እነዚህ ሁለገብ ስራዎች ማህበረሰቡን የሚበጅ ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ሙሉ እምነት እንዳለው ገልጿል።
በመሐመድ ሚፍታህ | 1 684 |
| 9 | የካይሮው ታሪካዊ የሱልጣን ቁጥብይ መስጂድ ተከፈተ
በግብፅ ካይሮ የሚገኘው ታሪካዊው የሱልጣን አል አሽረፍ ቁጥብይ መስጂድ ከረጅም ዓመታት እድሳት በኋላ በይፋ ተከፍቷል። መስጅዱ የግብፅ ቱሪዝም እና ጥንታዊ ቅርሶች ሚኒስትር ሼሪፍ ፋቲ እና በርካታ አለም አቀፍ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በይፋ ለጎብኚዎች ክፍት ሆኗል።
ይህ ከጥንታዊው የ1474 ከተሰራው ታሪካዊ ሕንፃ ጋር የተያያዘው ማዕከል ክፍት የሆነው በውጫዊ የድንጋይ ንጣፎች እና በጉልላቱ ላይ ጥገናዎች ከተደረጉለት በኋላ ነው።
ለዚህ አጠቃላይ የጥገናና የዕድሳት ፕሮጀክት ስኬት የአሜሪካ አምባሳደሮች የባህል ጥበቃ ፈንድ ለካይሮው "አርቺኖስ አርክቴክቸር" ድርጅት የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል። የታደሰው ይህ ታሪካዊ ቅርሶች መገኛ ስፍራ የቱሪስቶችን ቀልብ በመሳብ የሀገሪቱን ታሪካዊና ቱሪዝም ዘርፍ ይበልጥ ያጠናክራል ተብሎ ይጠበቃል። | 1 535 |
| 10 | በሞሪታንያ የባህር ጠረፍ 144 ስደተኞች ሞቱ
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 15 / 2018
በሞሪታንያ የባህር ጠረፍ አቅራቢያ ለ25 ቀናት በባህር ላይ ቆይቶ የነበረ ጀልባ ላይ በደረሰ አሳዛኝ አደጋ ቢያንስ 144 ስደተኞች መሞታቸው ተዘግቧል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ (UNHCR) ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት፤ ከሐምሌ 14 እስከ 18 በተደረጉ ሶስት የነፍስ አድን ስራዎች ከተለያዩ ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት የመጡ 387 ሰዎች በኑአድሂቡ ከተማ ወደ ሀገር መግባታቸው ተነግሯል።
ከእነዚህ መርከቦች መካከል ከጋምቢያ ቡፋሎ ተነስቶ ወደ ስፔን እያመራ ሳለ በባህር ላይ ለረጅም ቀናት የቆየው አንዱ ጀልባ ከፍተኛ ሰብአዊ ጉዳት ያስተናገደ ሲሆን፤ በዚህ መርከብ ላይ ተሳፍረው የነበሩ 143 ሰዎች ደብዛቸው መጥፋቱን ነው ተመድ ያስታወቀው። ከዚህ አሳዛኝ አደጋ የተረፉት 38 ሰዎች ብቻ ሲሆኑ፣ በጉዞው ወቅት ቤተሰቦቻቸውን ያጡ ሁለት የሴኔጋል ህፃናት በሕይወት ከተረፉት መካከል እንደሚገኙበት ተመላክቷል።
ተመድ ፣ ምንምኳን በ2026 ወደ ካናሪ ደሴቶች የሚደረጉ የስደተኞች ቁጥር ከቀድሞው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ61 በመቶ ቀንሶ 4,400 መድረሱ ቢገለፅም፣ የአትላንቲክ የባህር መስመር ግን አሁንም ለአደጋ የተጋለጠ እና ለስደተኞች ሞት ምክንያት መሆኑን ጠቅሷል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ (UNHCR) ቃል አቀባይ ማቲው ሳልትማርሽ፤ ይህ አሳዛኝ ክስተት እንዲቆም ስደተኞችን ለከፍተኛ አደጋ የሚዳርጉ ዋና ዋና ምክንያቶች ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል። | 1 381 |
| 11 | ኢጋድ ለሱዳኑ ጦርነት አፍሪካዊ መፍትሔ እንደሚያስፈልግ አስታወቀ
ኢጋድ በሱዳን ለተከሰተው ጦርነት አፍሪካዊ መፍትሔ ለማፈላለግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ በሱዳን ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሦስተኛ ዙር የልዩ መልዕክተኞች ስብሰባ በኬንያ ናይሮቢ ያካሄደ ሲሆን፤ በሀገሪቱ ያለውን ቀውስ በዘላቂነት ለመፍታት ከሚደረጉ ጥረቶችና የቀጣናዊ ትብብር አቅጣጫዎች ላይ መክሯል።
በውይይቱ የቀጣናዊና የዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላትን ትብብር ማጠናከር እንደሚገባ የተገለጸ ሲሆን፤ ኢጋድ ከአባል ሀገራት፣ ከአፍሪካ ኅብረት፣ ከአውሮፓ ኅብረት እና ከሌሎች ሰላም ፈላጊ ተቋማት ጋር በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጧል፡፡ | 1 194 |
| 12 | ኔታንያሁ አሜሪካ ከገቡ ሊታሰሩ ይገባል ሲሉ የኒውዮርክ ከተማ ከንቲባ አሳሰቡ
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 15/ 2018
የኒውዮርክ ከተማ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁን “የጦር ወንጀለኛ ናቸው” ሲሉ በማውገዝ፤ ግለሰቡ ወደ አሜሪካ ከገቡ የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ያወጣው የእስር ማዘዣ እንዲተገበርባቸው የሀገሪቱን የፌዴራል መንግስት መጠየቃቸው ተገልጿል ።
ከንቲባው በኤክስ (X) ገጻቸው ባስተላለፉት የቪዲዮ መልእክት፤ ኔታንያሁ በፍልስጤም ህዝብ ላይ ለተፈጸመው ዘግናኝ የዘር ማጥፋት ወንጀል፣ ከ73 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ንጹሃን ግድያ፣ ለሆስፒታሎች ውድመት እና ሰብዓዊ እርዳታን በመከልከል በዋነኛነት ተጠያቂ ናቸው ብለዋል። አክለውም "የዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ማዘዣ ያወጣበት በቂ ምክንያት አለው፤ ኔታንያሁም ሆነ ሌላ የጦር ወንጀለኛ በኒውዮርክ ከተማ ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም" ሲሉ አቋማቸውን በግልፅ ተናግረዋል።
ማምዳኒ የፌዴራል መንግስቱ የፍርድ ቤቱን ማዘዣ ተቀብሎ እንዲያስፈጽም ጥሪ ቢያቀርቡም፤ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን ኔታንያሁ በአሜሪካ ቆይታቸው በምንም ዓይነት ሁኔታ እንደማይታሰሩ አስታውቀዋል። ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በጋዛ ለተፈጸመው የጦር ወንጀል በኔታንያሁ እና በቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ላይ የእስር ማዘዣ ማውጣቱ ይታወሳል።
በ ቃለላህ ሳዲቅ | 1 351 |
| 13 | بدون متن... | 1 241 |
| 14 | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የንዑሳን ቡድኖች ውይይት በጥሩ ሁኔታ መቀጠሉን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 14 / 2018
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የተሳተፉ ተመካካሪዎች ትናንት ከሰዓት ጀምሮ በበለጠ ዝርዝር ሁኔታ በየንዑስ ቡድኖቻቸው በመሆን የምክክር ሂደቱን አጠናክረው መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል። ኮሚሽኑ 50 ተመካካሪዎችን የያዙ እና በ80 ቡድኖች የተዋቀሩት ንዑሳን ቡድኖች፣ እያንዳንዳቸው አስር አስር አባላትን ይዘው በሚያደርጉት በዚህ ውይይት ላይ በአጀንዳ ሃሳቦች ላይ ሰፊና ጥልቅ ምልከታዎችን በማንጸባረቅ ላይ ይገኛሉ ብሏል። እስከ ነገ በሚቀጥለው በዚህ የውይይት ሂደት፣ ተመካካሪዎች ላለመግባባት መንስኤ በሆኑ እጅግ መሰረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን አመለካከትና ምክንያቶች ከመሠረቱ እንዲረዱ ሰፊ መደላድል እንደሚፈጥር ተጠቁሟል።
ይህንን አጠቃላይ የምክክር ሂደት በብቃት ለመደገፍ እና ሊፈጠሩ የሚችሉ ብዥታዎችን ለመፍታት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከልዩ ልዩ ተቋማት የተውጣጡ 80 የሚጠጉ የባለሙያዎች ስብስብ አሰባስቦ እያሳተፈ ይገኛል። በሙያቸው፣ በትምህርት ዝግጅታቸው እና ለአጀንዳ ሃሳቦቹ ባላቸው ቅርበት ብቁ እንደሆኑ የታመነባቸው እነዚህ ባለሙያዎች፣ ተመካካሪዎች በሚያነሷቸው ሀሳቦች ላይ አስፈላጊውን ሙያዊ ማብራሪያና ድጋፍ በመስጠት ሂደቱ ይበልጥ ግልጽና ውጤታማ እንዲሆን እየረዱ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል የምክክር ሂደቱን ግልጽነትና ታማኝነት ለማረጋገጥ የተለያዩ የሀገር ውስጥ ተቋማት ታዛቢዎች በቦታው ተገኝተዋል። | 1 559 |
| 15 | "የሐማስ አዲስ መሪ መመረጥ የ‘ሐማስ’ መጠናከር ማሳያ ነው" - የኢራን ወታደራዊ አዛዥ
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 14 / 2018
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ቁድስ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል እስማኤል ቃኒ ኸሊል አል ሃያ በኢራን ድጋፍ የሚደረግለት የሐማስ የፖለቲካ ቢሮ አዲስ መሪ ሆኖ መመረጡን አስመልክቶ የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል። አዛዡ በመልዕክታቸው፣ የእስራኤል ኃይሎች የፍልስጤምን እስላማዊ ቡድንን ሰብረው ለመውጣት ያደረጉት ጥረት ከሽፏል ሲሉ ገልጸዋል።
ብርጋዴል ጄኔራል እስማኤል ቃኒ አክለውም የሐማስ አመራር ሆነው የተመረጡት አል ሃያ የትግል ተምሳሌት መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ይህ ምርጫ ቡድኑ የሐማስን ትግል ለማስቀጠል ያላቸውን ጽኑ አቋም በድጋሚ ያረጋገጠ መሆኑን አንስተዋል። እስራኤል በፈጸመችባቸው ስፍር ቁጥር የሌላቸው ወንጀሎችና ጥቃቶች የተቃውሞውን እንቅስቃሴ ማስቆም እንደማትችል የተናገሩት ጄኔራሉ፣ ዛሬ ላይ የእስልምና ተቃውሞ ኃይል ከየትኛውም ጊዜ በበለጠ ጠንካራ ሆኖ የክብር ጉዞውን እንደሚቀጥል አስገንዝበዋል።
ይህ የኢራን ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣን መግለጫ መካከለኛው ምስራቅ ውስጥ ያለውን ወቅታዊ የፖለቲካና የጸጥታ መዋቅር ፍጥጫ የሚያሳይ ሲሆን፣ የኢራን መንግስት ለፍልስጤም ታጣቂ ቡድኖች እያደረገ ያለው ድጋፍና ቁርጠኝነት ወደፊትም የማይለወጥ መሆኑን በግልጽ ያሳያል። በሁለቱ አካላት መካከል ያለው ጥብቅ ቁርኝት በቀጣይ ክልላዊ ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊያሳድር የሚችል መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች ይገልጻሉ። | 1 441 |
| 16 | ኢራን በቴክኖሎጂ ለማደግ የማንንም ፍቃድ እንደማትጠይቅ እና በ'AI' ከዓለም ቀዳሚ ለመሆን እየሰራች መሆኑን አስታወቀች
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 14/11/2018
የኢራን ምክትል ፕሬዝዳንት መሐመድ ሬዛ አሬፍ፤ ሀገራቸው በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ ከዓለም አስር ምርጥ ሀገራት ተርታ ለመሰለፍ እየሰራች መሆኑን አስታወቁ። ምክትል ፕሬዝዳንቱ የሀገሪቱ የቴክኖሎጂ ዕድገት የማንንም ሀገር ፍቃድ እንደማይጠይቅ አጽንዖት ሰጥተው፣ ነገር ግን ኢራን ያገኘችውን የቴክኖሎጂ እውቀት እና ስኬት ለወዳጅ ሀገራት እንደምታካፍል ገልጸዋል።
የኢራን የመከላከያ እና የደህንነት አቅም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ መሆኑን ያነሱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሀገሪቱ የሳይንስ ሊቃውንት በአጭር ጊዜ ውስጥ ብሔራዊ ፍላጎትን ያሟሉ ፈጣን ውጤቶችን ማስመዝገባቸውን አድንቀዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞም፣ የቀጠናው ሀገራት ግዛቶቻቸውን በኢራን ላይ ለሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት መነሻ እንዳያደርጉ ጠንከር ያለ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
መንግስት የቴክኖሎጂ እና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እቅዶችን በተለይም በነዳጅ እና ኢነርጂ ዘርፍ ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑ ተገልጿል። ቴክኖሎጂውን ከማልማት ባለፈ በተግባር ላይ ለማዋል ተጨባጭ እርምጃዎች መወሰድ እንዳለባቸው ያሳሰቡት አሬፍ፤ የተለያዩ ተቋማት እቅዶቻቸውን እንዴት እያሳኩ እንደሆነ በቀጣይነት ክትትል ሊደረግበት እንደሚገባ አቅጣጫ ማስቀመጣቸው ተዘግቧል ።
በ ቃለላህ ሳዲቅ | 1 431 |
| 17 | بدون متن... | 1 183 |
| 18 | የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት በሚቀጥሉት 10 ቀናት ከመካከለኛ እስከ ከባድ የዝናብ መጠን እንደሚኖር አስታወቀ
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 13 / 2018
የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት እ.ኤ.አ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24/2018 ይፋ ባደረገው የክረምት ወቅት የአየር ሁኔታ ትንበያ መሰረት፤ በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ እና በሰሜን የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከባድ እንዲሁም በአንዳንድ አካባቢዎች በ24 ሰዓት ውስጥ ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራል። በተጨማሪም በመካከለኛው፣ በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ እና በደቡብ የሀገሪቱ ከባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የዝናብ ሥርጭትና የአፈር እርጥበት ሊጨምር የሚችል የአየር ሁኔታ እንደሚጠበቅ ተመላክቷል።
ይህ የተሻሻለ የክረምት ዝናብ ለግብርና ሥራዎች ሰፊ መልካም አጋጣሚዎችን የሚፈጥር በመሆኑ፣ አርሶ አደሮች እና የሚመለከታቸው አካላት ሊከሰቱ የሚችሉ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመቀነስና የሚጠበቁ ጥቅሞችን ሙሉ በሙሉ ለመጠቀም ቦታ ተኮር የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክረ ሀሳቦችን ከወዲሁ ተግባራዊ እንዲያደርጉ ተቋሙ አሳስቧል። | 1 444 |
| 19 | ራህማ እስላማዊ ድርጅት የ2019 የስራ ዘመን በጀቱን 32 ሚሊዮን ብር አድርጎ አጸደቀ
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 13/2018
ራህማ እስላማዊ ድርጅት ትናንት ጦር ኃይሎች በሚገኘው የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዋና መስሪያ ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ባካሄደው የፓናል ውይይት፣ ባለፉት ሶስት ዓመታት ያከናወናቸውን ተግባራት ሪፖርት አቅርቧል። ድርጅቱ ባቀረበው ሪፖርት መሰረት፣ በሶስት ዓመታት ውስጥ በጎዳና ላይ ዳዕዋ ውጤታማ ስራዎችን ማከናወኑን አስታውቋል። በውይይቱም የድርጅቱ የ2019 የስራ ዘመን አጠቃላይ በጀት 32 ሚሊዮን ብር ሆኖ መጽደቁን ይፋ አድርጓል።
በመድረኩ ላይ የመጅሊስ አመራሮች፣ ኡስታዞች እና በርካታ ተጋባዥ እንግዶች የተገኙ ሲሆን፤ ተሳታፊዎቹ ለራህማ እስላማዊ ድርጅት ያላቸውን አጋርነት አረጋግጠዋል። በመድረኩ ንግግር ያደረጉ የመጅሊስ አመራሮች እና ታላላቅ ዱዓቶች፣ የድርጅቱ ዋነኛ ተግባር የሆነው የጎዳና ላይ ዳዕዋ የነብያት መንገድ መሆኑን ገልጸው፤ ህዝበ ሙስሊሙ ከድርጅቱ ጎን ሊቆም እንደሚገባ አሳስበዋል።
ራህማ እስላማዊ ድርጅት በ2019 የስራ ዘመን በሚሊዮን ለሚቆጠሩ የሌላ እምነት ተከታዮች እስላማዊ አስተምሮዎችን በተገቢው ደረጃ ለማዳረስ እቅድ ይዟል። የዳዕዋ ስራውን ለማሳለጥም ከ3 ሚሊዮን በላይ በራሪ ወረቀቶች እና ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ መጽሐፎች እንደሚያስፈልጉት አስታውቋል። ይህንን ተከትሎ ኡስታዝ አዩብ ደርባቸው ለድርጅቱ 1,000 መጽሐፍትን ለማቅረብ ቃል የገቡ ሲሆን፣ ሌሎች ግለሰቦች እና ድርጅቶችም መሰል ድጋፎችን አበርክተዋል።
በመጨረሻም፣ በዕለቱ የተገኙ በርካታ ተሳታፊዎች እና የመጅሊስ አመራሮች ህዝበ ሙስሊሙ ለራህማ እስላማዊ ድርጅት የተጠናከረ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። | 1 627 |
| 20 | በዱባይ የሚዘጋጀው ታላቁ የኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የንግድ ፎረም የሁለትዮሽ ትብብርን ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግር ተገለጸ
ነጃሺ ቲቪ || ሐምሌ 13 / 2018
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ከዱባይ ንግድ ምክር ቤት እና በዩኤኢ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር በመቀናጀት መስከረም 2 ቀን 2026 በዱባይ ታላቅ የሁለትዮሽ የንግድ ፎረም ሊያካሂድ ነው። ይህ ስትራቴጂካዊ መድረክ በሁለቱ ሀገራት መካከል እያደገ የመጣውን የኢኮኖሚ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር እና ቀጣይ የገበያ ትስስሮችን በፅኑ መሰረት ላይ ለመገንባት ያለመ ነው ተብሏል።
በዚህ አውደ ጥናት ከ40 በላይ የሚሆኑ የአዲስ ቻምበር አባል ኩባንያዎች እና የግል ባለሀብቶች በቀጥተኛ የንግድ ለንግድ (B2B) ውይይቶች ላይ እንደሚሳተፉ ተመላክቷል። የኢትዮጵያ አምራቾች፣ ላኪዎች እና አገልግሎት ሰጪዎች ከዱባይ አቻዎቻቸውና ከኢንዱስትሪ መሪዎች ጋር በመገናኘት አዳዲስ የንግድ አጋርነት ዕድሎችን የሚፈጥሩበት ሰፊ አጋጣሚ እንደሚፈጠር ተገልጿል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የሁለትዮሽ ንግድ ከ6 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሻገሩን የሚያሳዩ መረጃዎች እየወጡ ባሉበት በአሁኑ ወቅት፣ ይህ ፎረም የሀገር ውስጥ ኩባንያዎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ከፍ ለማድረግ ወሳኝ ምዕራፍ ነው ተብሏል። | 1 569 |
