fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 484 مشترک است و جایگاه 6 043 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 334 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 484 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 30 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 530 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 23 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 39.14% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.20% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 666 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 477 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 33 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 01 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 484
مشترکین
+2324 ساعت
+1447 روز
+53030 روز
آرشیو پست ها
“በውድዋ ላይ ተደግፋ ከምድረ በዳ የምትወጣ (የምታርግ) ይህች ማን ናት?” መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 8፥5 በክርስትና ስም ከሚጠሩ ቤተ እምነቶች በተለየ መልኩ፥ “ቀጥተኛ መንገድ” የሚል ትርጉም ያለው የኦርቶዶክስ እምነትን የሚከተሉ አብያተ ክርስቲያን ለተቀደሰው ሐዋርያዊ ትውፊት (Holy Tradition) ትልቅ ቦታ አላቸው። ቅዱስ ትውፊት የምንለው ከቅዱሳን ሐዋርያት አባቶቻችን ዘመን ጀምሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሸጋገር የመጣውን አስተምህሮ እና ሥርዓተ አምልኮ ሲሆን፥ መጽሐፍ ቅዱስም እኛ ዘመን የደረሰው በዚሁ የተቀደሰ የትውፊት ሰንሰለት ነው። ለዚህም ነው ኦርቶዶክሳውያን አበው፦ “መጽሐፍ ቅዱስ፥ በተቀደሰው የትውፊት ዛፍ ላይ የበቀለ መልካም ፍሬ ነው” የሚሉት። የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን፥ በምድረ ፍልስጥኤም በ5ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጨረሻ አካባቢ የወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያምን በዓለ ዕረፍት ወፍልሰት ማክበር እንደጀመረች የሚጠቁሙ ታሪካዊ መረጃዎች አሉ። በዚሁ ዘመን “The Dormition and the Assumption of the body of St. Mary into Heaven” በሚል ርእስ ዙሪያ የሚያትቱ ጽሑፎች በተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ይጻፉ እንደነበር በቅርቡ የተደረጉ ጥናቶች ያመለክታሉ። ከነዚህ ጥናቶች መካከል ዓለም አቀፋዊ እውቅናን ያተረፈው የሚከተለው መጽሐፍ ነው፦ Stephen Shoemaker, Ancient Traditions of the Virgin Mary’s Dormition and Assumption, Oxford University Press, 2006. በፍልስጥኤም (Palestine) የተጀመረው “በዓለ ዕረፍታ ወፍልሰታ ለማርያም” ቀስ በቀስ ወደ ምዕራቡ ዓለም ደርሶ፥ በ8ኛውና 9ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዓለም አቀፋዊ በዓል ለመሆን ችሏል። ይህን በዓል ኦርቶዶክሳውያን አብያተ ክርስቲያን August 15 ቀን ሲያከብሩት፥ ጥንታዊውን Julian Calendar የምትከተለው ቤተ ክርስቲያናችን ደግሞ ነሐሴ 16 (August 22) ቀን በታላቅ ድምቀት ታከብረዋለች። “በውድዋ ላይ ተደግፋ ከምድረ በዳ የምትወጣ ይህች ማን ናት?” የሚለው የንጉሥ ሰሎሞን ዝማሬ፥ ሕይወቷን በሙሉ አምላኳን ያከበረች ነፍስ ከሥጋዋ ተለይታ ወደ፡ምትወደው ጌታ ስትሄድ የሚጠቀስ ጥቅስ ነው። ከዚህ በተሻለ መልኩ ግን፥ እመቤታችን ድንግል ማርያም በልጇ ኃይል ከሞት ተነሥታ፥ ንጽሕትና ቅድስት የሆነችውን ነፍሷን ውድ ልጇ በክብር ተቀብሎ ወደ መንግሥቱ ያሳረገበትን በዓል ለመዘከር ልንጠቀምበት እንችላለን። እንዲያውም የግእዙ ንባብ፦ “መኑ ይእቲ ዛቲ እንተ ተዐርግ እም ገዳም አንተ ትትመረጐዝ በወልድ እኁሃ? - በውድዋ ላይ ተደግፋ ከምድረ በዳ የምታርግ ይህች ማን ናት?” ያላትን፥ “ሠናይት ከመ ወርኅ፥ ወብርህት ከመ ፀሐይ - እንደ ጨረቃ የተዋበች፥ እንደ ፀሐይም የምታበራ” በማለት ስለሚገልጻት፥ በፈቃድ ከሚሰራው የግል ኃጢአት ነጻ ለሆነችው ለቅድስቲቷ የእመቤታችን ነፍስ ዕርገት በእጅጉ የሚስማማ አገላለጽ ነው። ይህን መጽሐፍ ቅዱሳዊ አሳብ በሥነ-ሥዕል (iconography) ለማመልከት፥ ከስር የምትመለከቱት ኦርቶዶክሳዊ ሥዕል (icon)፥ ሐዋርያት የእመቤታችንን ሥጋ ለመገነዝ አንደተሰበሰቡና ጌታ በሕፃን ልጅ አምሳል በነጭ መጎናጸፊያ የተጠቀለለችውን የብፅዕትና ቅድስት እናቱን ነፍስ ታቅፎ ያሳያል። ጌታን በሕፃንነቱ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ታቅፈው እንደነበር፥ እርሱ ደግሞ በተራው በዕረፍቷ ቀን የእናቱን ንጽሕት ነፍስ ታቅፎ ወደ መንግሥቱ ዘላለማዊ ክብር አገባት። በሞቱ ሞትን ድል የነሣልን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ከሞት በኋላ የሚጠብቀን ትንሣኤ በኵር እንደሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ጽፎልናል (1 ቆሮ15፥20)። ይኸው ሐዋርያ ስለ ሙታን ትንሣኤ ሲጽፍ ሥጋዊ አካላችን ወደ አፈርነቱ ከተመለሰ በኋላ (በመበስበስ ከተዘራ በኋላ) መንፈሳዊ አካል ሆኖ በክብር አንደሚነሳ አስተምሮናል (1 ቆሮ 15፥ 42-50)። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ለፍርድ ሲመጣ፥ “በጌታ የሚሞቱ ሙታን ብፁዓን ናቸው” እንደተባለ (ራእይ 14፡13) በምድራዊ ኑሮአቸው ክርስቶስን ለብሰው የኖሩ የእግዚአብሔር ልጆች የክብር ትንሣኤ ይነሳሉ። ለዚህም ነው ሐዋርያው፦ “ክቡር ሥጋውን እንዲመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል” (ፊልጵ 3፥21) ሲል ስለሚጠብቀን ዘላለማዊ ክብር የነገረን። እንግዲህ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን፦ “ወላዲተ አምላክ ማርያም ሞትን ድል ባደረገው በልጇ ኃይል ከሞት ተነስታ ወደ ልጇ መንግሥት አርጋለች” ብላ ስታስተምረን፥ የአምላካችን ልጆች የሆንን ሁላችን በእግዚአብሔር መንግሥት የሚጠብቀንን ክብር እመቤታችን ቀድማ አግኝታለች ማለቷ ነው። ጌታ በትንሣኤው በኵር እነደሆነን፥ ቅድስትና ብፅዕት እናቱ ደግሞ ወደ ሰማያዊው መንግሥት በመግባት ቀዳሚት (በኵር) ሆነችን። ንጉሡ ጌታችን ኢየሱስ ከመንግሥቱ የተለየበት ጊዜ ፈጽሞ እንደሌለ እናውቃለን፤ መንግሥቱ ያለው ንጉሡ ባለበት ቦታ ነውና። ሁላችን ተስፋ የምናደርገውና “ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” (ማቴ 25፡22) የሚለው፥ በእርሱ ሕያዋን ሁነን በመንግሥቱ ለዘላለም የመኖራችን እውነታ (eschatological fulfillment) ከሁላችንም ቀድሞ ለቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ተደረገ። ከመለኮት ባህርይ ተካፋይ የሆንበትን (2 ጴጥ 1፥4) ምስጢር (theosis - ሱታፌ አምላክ) ከእግዚአብሔር በተሰጣት የተለየ ጸጋ በንጽሕና እና በቅድስና አጊጣ በሕይወቷ እውን ስላደረገችና ከቅዱሳን መካከል በንጽሕና የሚስተካከላት ስለሌለ፥ እመቤታችን ከቅዱሳኑ ሁሉ ቀድማ ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር ገባች ቢባል ጥያቄ ሊፈጥርብን አይገባም። ደግሞም አምላክን በድንግልና ወልዳ ላሳገደች እመቤት የሚገባት የክብር ሰማያዊ ፍጻሜ ከዚህ ውጪ ሊሆን አይችልም። እግዚአብሔር ወልድ ከእመቤታችን የነሳው ሥጋ የእኛ ሥጋ እነደሆነ ግልጽ ነው፤ በ318ቱ የኒቂያ ጉባኤ አባቶች ስም የተደረሰው የቤተ ክርስቲያናችን ቅዳሴ፦ “ተዘከር ሥጋ እንተ ነሣእከ እምቅድስት ድንግል እንቲአነ ሥጋ አኮ እምሰማያት ዘአውረድከ - ከቅድስት ድንግል የነሣኸው ሥጋ የእኛ ሥጋ እነደሆነ፥ ከሰማይ ያወረድኸው እንዳይደለ አስብ” እንዲል (ቊ. 121)። የመልአኩን ብስራት “ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ” ብላ ከተቀበለችበት ቅጽበት ጀምሮ እግዚአብሔር አብ በልጁ በኩል ያደርግ ዘንድ ላሰበው የማዳን ሥራ ድንግል ማርያምን መሣሪያ አድርጓታል። ልዑል ማደሪያውን ቀድሶ፥ “ቅድስተ ቅዱሳን - Holy of Holies” የተሰኘች የአንድ ልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ መረጣት። ስለዚህ የድንግል ማርያም ትንሣኤና ዕርገት በዋነኝነት የሚያመለክተው፥ እነ ቅዱስ ኤፍሬም፦ “አንቲ ውእቱ ደብተራ እንተ ተሰመይኪ ቅድስተ ቅዱሳን . . . መቅደስ ዘይኬልሉኪ ኪሩቤል” ብለው ያወደሷት የጌታ ንጽሕት መቅደስ በመንግሥቱ መክበሯን ነው። ይህ የመንግሥቱ ክብር (glorification) ደግሞ የእኛም ክብር ስለሆነ በዚህ የተቀደሰ ትውፊታው አስተምህሮ ደስ ሊለን እንጂ፥ በጭራሽ ሊከፋን አይገባም።

• ቡሔ ይባላል ፡- ቡሄ ብርሃን ማለት ነው በደብረታቦር ቧ ብሎ የተገለጠውን የጌታችንን የፊቱን ብርሃን ጸዳል፤ የልብሱንም እንደ ነጭ በረዶ ጸዓዳ መሆን ያስረዳል፡፡ አንድም፡- ቡሔ ማለት መላጣ (ገላጣ) ማለት ነው፡፡ ይኸውም በበዓሉ ዋዜማ ልጆች ‹‹ ቡሔ በሉ፤ ቡሔ መጣ ፣ ያ መላጣ፣ ቅቤ ቀቡት እንዳይነጣ›› ይላሉ እዚህ ላይ ቡሄ ያለው ዳቦውን ነው፡፡ • አንድም፡- ‹‹ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለምሌሊት›› እንደሚባል ወቅቱ በሃገራችን የጸዓተ ክረምት ዋዜማ ስለሆነ የክረምቱ አፈናው ተወግዶ /ተጋምሶ/ የብርሃን ወገግታ የሚታይበት ፤ በዶፉና በጎርፉ ተሸፍና የነበረች መሬት የምትገለጥበት በመሆኑ ነው፡፡ • አንድም፡- ቡሔ (ቡሔእየ) ተብሎ ይተረጎማል ይኸውም የደብረታቦር እለት እርሾ ሳይገባበት ተቦክቶ የሚጋገረውን ኅብስት ያሳያል፡፡ # "ችቦ የመብራቱ ፣ የሙልሙል ዳቦ የመጋገሩና የጅራፍ ማጮኽ ምክንያት፡- ችቦ የሚበራው 12 ለ13 ዋዜማ ሌሊት በ3 ሰዓት ነው ። • የጌታችን ክብሩ በተገለጠበት ጊዜ ብርሃኑ የሌሊቱን ጨለማ ገፍቶት እስከ አርሞንዔም ደርሶ ነበርና በዚያ አካባቢ የነበሩ እረኞች በሁኔታው ተገርመው ቀንም መስሎኣቸው ሌሊቱም ተዘንግቷቸው በዚያው ቆይተው ነበርና ቤተሰዎቻቸው ምን አግኝቷቸው ይሆን በማለት መብራት አብርተው (ችቦ ይዘው)፣ የሚመገቡትን ይዘው ወገኖቻቸውን ፍለጋ ወጥተዋል እረኞችም ያሉበትን ቦታ ለቤተሰዎቻቸው ጅራፍን በማጮኸ አመልክተዋቸዋልና ይህን ለማሰብ ነው፡፡ • ዋናው ምሥጢሩ ግን፡- የችቦው ብርሃን የጌታ ክብር መገለጡን፣ የጅራፋ ጩኸት ሓዋርያትን ያስደነገጣቸው የአብ የምስክርነቱ ቃል ምሳሌ ሲሆን፣ ኅብስቱ ጌታችን በመስቀል ላይ መሥዋዕት የመሆኑ (የሥጋወደሙ) ምሳሌ ነው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ደብረ_ታቦር (ነሐሴ 13) ደብር ማለት ተራራ ሲሆን ታቦር ደግሞ የተራራው ስም ነው፡፡ ደብረ ታቦር ከገሊላ ባሕር በስተምዕራብ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ በዚህ ተራራ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተአምራቱን ገልጦበታል፡፡ ይህም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነሐሴ 13 ቀን ዘጠኙን ሐዋርያት ከእግረ ደብር/ከተራራው ግርጌ/ ትቶ ሦስቱን ሐዋርያት (ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ወንድሙ ዮሐንስን) አስከትሎ ወደ ተራራው ወጣ። በዚያም ለሦስቱ አርዓያው ተለውጦ፣ ፊቱ እንደ ፀሐይ አብርቶ፣ ልብሱ እንደ በረዶ ነጽቶ፣ ሙሴና ኤልያስ በቀኝና በግራው ቁመው ታዩአቸው፡፡ ስምዖን ጴጥሮስ ‹‹እመሰ ትፈቅድ ንንበር ዝየ ወንግበር ሠልስተ ማኅደረ አሐደ ለከ፣ አሐደ ለሙሴ፣ ወአሐደ ለኤልያስ›› ትርጓሜውም ‹‹በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ፣ አንዱን ለሙሴ፣ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ›› እያለ ሲናገር ወዲያው ብሩህ ደመና መጥቶ ጋረዳቸውና ‹‹ዝንቱ ውእቱ ወልድዬ ዘአፈቅር ወሎቱ ስምዕዎ›› ትርጓሜውም ‹‹በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት›› የሚል ቃል ሰሙ፡፡ በዚህ ጊዜ ሁሉም መቆም ተሳናቸው፤ ሙሴ ‹‹ትኄይሰኒ መቃብርየ›› መቃብሬ ትሻለኛለች ብሏል፤ ኤልያስም በሠረገላው ወደየመጡበት ተመልሰዋል፡፡ ሦስቱ ሐዋርያትም ደንግጠው ወድቀው ነበርና ጌታ ዳስሶ በአስነሳቸው ጊዜ ከእርሱ በቀር ሌላ ሰውን አላዩም፡፡ ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ያዩትን ለማንም እንዳይናገሩ አዝዟቸው ከተራራው ወርደዋል፤ (ማቴ 17፥1-9)። ተራራ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ሲሆን ነብያት እና ሐዋርያት በተራራው ላይ መገኘታቸው ቤተ ክርስቲያን የነብያትንም የሐዋርያትንም ትምህርት ይዛ የመገኘቷ፡፡ ሙሴ ከሞት ተነስቶ በተራራው ላይ ተገኘ ኤልያስም ከብሔረ ሕያዋን መጣ፡፡ ይህም በሰማይ ያሉትም ይሁኑ በምድር ያሉት በአንድነት የሚያመሰግኑባት ቦታ እንደሆነች ሲያስተምረን ነው፡፡ ምሥጢረ መንግሥቱን ለምን በታቦር ተራራ ገለጸው? መድኃኔዓለም ሌሎች ተራሮች እያሉ ክብሩን ለመግለጥ ስለምን ደብረ ታቦርን መረጠ ቢሉ ትንቢቱንና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ 1/ ትንቢቱን ለመፈጸም “ታቦርና አርሞንኤም በስምህ አምነው በተደረገላቸው ነገር ደስ ይላቸዋል፣ ስምህን ያመሰግናሉ፣ ለስምህም ምስጋና ያቀርባሉ” እንዲል /መዝ. 88፡12/፡፡ 2./ ምሳሌውን ለመፈጸም ይህ ተራራ ባርቅ ሲሳራን ድል አድርጎበታል /መሳ.4፡6/፡፡ ታሪኩም እንዲህ ነው፡፡ “የእስራኤል ልጆች በእግዚአብሔር ፊት እንደገና ክፉ ሥራ ሠሩ፡፡ እግዚአብሔርም በአሶር በነገሠው በከነዓን ንጉሥ በኢያቡስ እጅ አሳልፎ ሰጣቸው፤ የሠራዊቱም አለቃ በአሕዛብ አሪሶት የተመረጠው ሲሣራ ነበር፡፡… ዘጠኝ መቶ የብረት ሰረገሎች ነበሩትና የእስራኤልንም ልጆች ሃያ ዓመት ያስጨንቃቸው ነበር” /መሳ 4.1-3/፡፡ ሁሌም ቢሆን የሰውን በደል ዐይቶ እንደወጣችሁ ግቡት፣ እንደገባችኋት ውጧት የማይልና “ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል” የተባለለት እግዚአብሔር ከዚህ ቀንበር የሚላቀቁበትን መላ ራሱ አመለከታቸው /1ቆሮ. 10-13/፡፡ እስራኤላውያን ወደ ፈጣሪያቸው በጮኹ ጊዜ የለፊዶት ሚስት የሆነችውንና እስራኤልን በነቢይነትና ዳኝነት ታገለግል የነበረችው ነቢይቱን ዲቦራን ተጠቅሞ የማሸነፊያ መላውን አመለከታቸው፡፡ ነቢይቱ ዲቦራ ትንቢት ከመናገር አልፋ የእስራኤልን ንጉሥ ባርቅ ከእኔ ጋር ወደ ጦርነቱ ውጪ ብሎ ባስጨነቃት ጊዜ በጦር አዝማችነትም ተሳተፈች፡፡ እግዚአብሔር በነቢይቱ በዲቦራ በኩል ለእስራኤል ንጉሥ “ሔደህ ወደ ታቦር ተራራ ውጡ” ብሎ አዞት ነበርና ንጉሡ ዐሥር ሺሕ ብረት ለበስ ያልሆነ እግረኛ ሠራዊት ይዞ ደብረ ታቦርን ተማምኖ በተራራው ላይ መሸገ፤ ጦርነቱም ሳይጀመር አለቀ፡፡ ምክንያቱም “እግዚአብሔርም ሲሣራን ሰረገሎቹንም ሁሉ ሠራዊቱንም ሁሉ ከባርቅ ፊት በሰይፍ ስለት አስደነገጣቸው፡፡ ሲሣራም ከሰረገላው ወርዶ በእግሩ ሸሸ” /መሳ. 4.15/፡፡ እስራኤል በእግዚአብሔር አጋዥነት በታቦር ተራራ ላይ የሃያ ዓመት የግፍና የሰቀቀን አገዛዝ ቀንበራቸውን ከትከሻቸው አሽቀንጥረው በምትኩ የድል ካባን ደረቡ፡፡ “በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ የባዕድ ጭፍሮችንም አባረሩ” ተብሎም ጀግንነታቸው ተጻፈላቸው፡፡ የታቦር ተራራ ያኔ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ባለውለታቸው ነበር /ዕብ. 11.32-34/፡፡ ጌታም በልበ ሐዋርያት ያለ ሰይጣንን ድል ያደርጎበታልና ማለትም በልባቸው ጥርጥርን እና ፍቅረ ሢመትን (የሥልጣን ፍቅር) ያሳደረ ዲያብሎስን ድል ነስቶላቸዋል ፡፡ ከዚህም በመነሣት ነው “በዓለ ደብረታቦር የደቀመዛሙርት ተማሪዎች በዓል ነው” የሚባለው ፡፡ ኤልያስና ሙሴን ለምን አመጣቸው? 1/. በአንድ ወቅት ሙሴ እግዚአብሔርን ፡- “በአንተ ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘቴ እውነት ከሆነስ ፊት ለፊት ተገልጸህልኝ ልይህና በአንተ ዘንድ ባለሟልነትን ማግኘቴን ልወቀው” ሲል ጠይቆት ነበር፡፡ እግዚአብሔርም “ጀርባዬን ታያለህ ፊቴን ግን አታይም” ብሎት ነበር /ዘጸ. 33.13፣23/፡፡ የዚህ ኃይለ ቃል ትርጓሜና ሐተታ በደብረ ታቦር ተፈጽሟል፡፡ እንዲህ ማለቱ “አምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም ሰው ሆኜ ሥጋ ለብሼ ኋላ በደብረ ታቦር እስክገለጽልህ ድረስ አንተ በመቃብር ተወስነህ ትኖራለህ” ማለቱ ነበርና፡፡ ይህን ማለቱ እንደሆነ የታወቀው ግን በደብረ ታቦር ሙሴን ከብሔረ ሙታን አምጥቶ ባቆመው ጊዜ ነበር፡፡ 2/ ልዑል እግዚአብሔር ነቢዩ ኤልያስን፡- “አንተ በኋለኛው ዘመን ምስክር ትሆነኛለህ” ብሎት ነበር፡፡ ይኸውም ኃይለ ቃል ኤልያስ ከብሔረ ሕያዋን መጥቶ “የእኔን የኤልያስን ጌታ ማን ኤልያስ ነው ይልሃል? እግዚአ ኤልያስ፤ አምላከ ኤልያስ ይበሉህ እንጂ” ሲል በደብረ ታቦር ተፈጸመ፡፡ ታያለህ የተባለው ሙሴም አየ፣ ትመሰክራለህ የተባለው ኤልያስም መሰከረ፡፡ 3/ በፊልጶስ ቂሳርያ ጌታ ሐዋርያትን “ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደሆነ ይሉታል?” ብሎ በጠየቃቸው ጥያቄ ሲመልሱ “ሙሴ ነው ይሉሃል ፤ እንዲሁም የኃይል ሥራህን ተመልክተው ኤልያስ ነው ይሉሃል” ብለው ነበርና ሙሴን ከመቃብር ፤ ኤልያስን ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ እግዚአ ሙሴ ፤ አምላከ ሙሴ ፤ እግዚአ ኤልያስ ፤ አምላከ ኤልያስ መሆኑን ለማስመስከር፡፡ 4/ አይሁድ ፈሪሳውያን ጌታን እንደ ሕግ ተላላፊና የእግዚአብሔርን ክብር ለራሱ የሚወስድ አድርገው ያስቡት ስለነበረ /ዮሐ.9፡16፣ 10፡33/ ሕግን የሰጣቸው ሙሴንና ለሕገ እግዚአብሔር ቀናተኛ የነበረው ኤልያስን አምጥቶ ሕግ አፍራሽ አለመሆኑን የእግዚአብሔር ተቃዋሚም አለመሆኑን ለማስረገጥ፡፡ 5/ ጌታችን በሙታንና በሕያዋን ላይ ሥልጣን ያለው እንደሆነ ይታወቅ ዘንድ ሞተው ከተቀበሩት ሙሴን ከብሔረ ሕያዋንም ደግሞ አልያስን አምጥቶ ሲነጋገር ታየ፡፡ 6/ የሐዋርያቱን የወደፊት አገልግሎት ሲነግራቸው፡፡ ይኸውም ሙሴ እና ኤልያስ ለሕዝበ እስራኤል በጣም ታማኝ እንደነበሩ ሁሉ እነርሱም ለሚያገለግሉት ሕዝብ ታማኝ እረኞች እንዲሆኑ፡፡ ሆኖም ግን አገልግሎታቸው ከሙሴና ከኤልያስ ይልቅ ጠንከር እንደሚልም አሳይቶአቸዋል፡፡ ምክንያቱም ውጊያቸው እንደ ሙሴ ከፎርዖን እንደ ኤልያስም ከአክዓብ ጋር ሳይሆን ከክፋት መናፍስት ጋር ነውና፡፡ # የበዓሉ መጠሪያ ስሞች (ደብረ ታቦር / ቡሄ/ ቡሔ መባሉ ስለምንድ ነው ? • ደብረ ታቦር የተባለው ጌታ ክብሩን የገለጠበት ስፍራ ደብረ ታቦር ስለሆነ በዚሁ በዓሉ ስያሜውን አግኝቷል፡፡

🗝 የግል ሱባዔ/ዝግ ሱባዔ/ የግል ሱባዔ አንድ ሰው ብቻውን ሆኖ በቤትና በአመቺ ቦታ የሚይዘው ማንም ሰው ሳያየው በግሉ የጸሎት በኣቱን ዘግቶ በሰቂለ ኅሊና ሆኖ ፈጣሪው ብቻ እንዲያየው እንዲሰማው በኅቡዕ የሚፈጽመው ሱባዔ ነው፡፡ ማቴ.6፡5-13፡፡ በዚህ ዓይነት መልክ አንድ ሰው ሱባዔ ሲገባ ዘጋ ይባላል፡፡ ዝግ ሱባዔ የያዘ ሰው የሚያስፈልገውን ነገር ይዞ ወደ በኣቱ ከተከተተ በኋላ ሱባዔው እስኪፈጸም ድረስ ከሰው አይገናኝም፡፡ መዝ. 101-6-7፡፡ 🗝 የማኅበር ሱባዔ የማኅበር ሱባዔ የሚባለው ካህናት፣ ምእመናን ወንዶችና ሴቶች፣ ሽማግሌዎችና ወጣቶች በአንድ ሆነው በቤተ ክርስቲያንና አመቺ በሆኑ ቦታዎች ሁሉ ተሰብስበው የሚገቡት ሱባዔ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን የነበሩ ምእመናን ወደ እግዚአብሔር በመሄድ ይጸልዩ ነበር፡፡ 1ኛ ሳሙ.1፡9፤ መዝ.121፡1፤ ሉቃ.18፡10-14፡፡ በሐዲስ ኪዳንም የሐዋርያት ተከታዮች የኾኑ መነኮሳት፣ ካህናትና ምእመናን በገዳማት፣ በአድባራት፣ የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች፣ የጽዋ ማኅበርተኞች ስለ ማኅበራቸው ጥንካሬና ከማኅበርተኞቹ መካከል አንዱ ችግር ሲገጥመው የማኅበር ሱባኤ ይያዛል፡፡. 🗝 የዐዋጅ ሱባዔ የዐዋጅ ሱባዔ በአገር ላይ ድንገተኛ አደጋ፣ አባር ቸነፈርና ጦርነት ሲከሰት እንዲሁም ለማኅበረ ምእመናን አስጊ የሆነ መቅሰፍት ሲከሰት፣ እግዚአብሔር መዓቱን በምሕረት ቁጣውን በትዕግሥት እንዲመልስ የሚያዝ የሱባዔ ዓይነት ነው፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ሱባዔ የነነዌ ሰዎችና በፋርስ በስደት ይኖር የነበረ እስራኤላውያን ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የነነዌ ሰዎች የዮናስን ስብከት ሰምተው ከሊቅ እስከ ደቂቅ ለሦስት ቀን ከመብል ከመጠጥ ተከልክለው በመጾም በመጸለይ እግዚአብሔር መዓቱን በምሕረት ቁጣውን በትዕግሥት እንዲመልስ አድርገዋል፡፡ ሌላው በፋርስ በስደት ይኖር የነበረ አይሁድ በአስቴር ትእዛዝ የያዙት ሱባዔ ተጠቃሽ ነው፡፡ በዚያን ዘመን አርጤክስስ አይሁድ በያሉበት እንዲገደሉ በማዘዙ ከዚህ የጅምላ ጭፍጨፋ ለመዳን አይሁድ በዐዋጅ ሱባዔ ገብተዋል፡፡ አስቴር ገብታ ንጉሡን ስታናግረው ሌላው ሕዝብ በውጭ ዐዋጅ ዐውጀው ሱባዔ ገብተው ፈጣሪያቸውን ተማፅነዋል፡፡ አስቴር 4፡16 - 28፡፡

👉 ሱባዔ ምንድን ነው? ሱባዔ በሰዋስው ትርጉሙ ሰባት ማለት ነው፡፡ ሱባዔ በመንፈሳዊ አተረጓጎም አንድ ሰው ከዚህ ቀን እስከዚህ ቀን በጸሎት ከፈጣሪዬ እገናኛለሁ ብሎ የሚያቅደው መንፈሳዊ ዕቅድ ነው፡፡ ሰባት ቁጥር በእስራኤላውያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ለምሳሌ፡- ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረትን ከመፍጠር ማረፉ፣ ለጸሎት የሚተጉ ምእመናን በቀን ለሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥርን ፍጹምነት ያመለክታል፡፡ ዘፍ.2፥2፤ መዝ.118፥64፡፡ ከዚህ አንጻር አንድ ሰው ለሰባት ቀናት ቢጾም አንድ ሱባዔ ጾመ ይባላል፡፡ ለዐሥራ አራት ቀን ቢጾም ሁለት ሱባዔ ጾመ እያለ እየጨመረ ይሄዳል፡፡ 👉 መቼ ተጀመረ? ሱባዔ የተጀመረው ከውድቀት በኋላ በመጀመሪያው ሰው በአዳም ነው፡፡ ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት መጸለይን እንዳስተማሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይናገራሉ፡፡መላእክት ለአዳም ጊዜያትን አስተምረውት ነበር፡፡ ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ፡፡ አዳም ጥፋቱን አምኖ ከባሕር ውስጥ ሱባዔ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔር በማይታበል ቃሉ ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንኀለሁ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶለታል /መጽሐፈ ቀሌምጦስ አንቀጽ አራት/፡፡ 👉 ሱባዔ ለምን? የሰው ልጅ ኃጢአት በሚስማማው የሥጋ ሰውነቱ ዘወትር ፈጣሪውን ይበድላል፡፡ በፈጸመው በደል ኅሊናው ይወቅሰዋል፡፡ ይጸጸታል፡፡ በመጀመሪያ ደፍሮ በሠራው ኃጢአት በኋላ ይደነግጣል፡፡ ይህ በማንኛውም ሰብአዊ ፍጥረት ኅሊና ውስጥ የሚፈራረቅ ክስተት ነው፡፡ በዚህ ጊዜ የፈጣሪውን ይቅርታ ለማግኘት ያስባል፤ ይተክዛል፡፡ በውስጡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛል. ነገር ግን በብልቶቼ ባለ በኃጢአት ሕግ የሚማርከኝ ሌላ ሕግ አያለሁ፡፡ እኔ ምንኛ ጐስቋላ ሰው ነኝ ለዚህ ሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ያድነኛል? እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ፡፡ ሮሜ.7.22-25፡፡ ሰው በደፋርነቱ የኃያሉን አምላክ ትእዛዝ ተላልፎ ትካዜ ሽክም ሲያስጨንቀው ሸክሙን የሚያቃልልበትና የሚያስወግድበት መንፈሳዊ ጥበብ ከቸሩ ፈጣሪ ተሰጥቶታል፡፡ ይኸውም በጥቂት ድካመ ሥጋ ጸጋ እግዚአብሔር የሚያገኝበት ሥርዓት ሱባዔ ነው፡፡ ከጥንት እስከ ዛሬ አንድ ሰው በትካዜ ሽክም መንፈሱ ሲታወክ የነፍስና የሥጋ ጸጥታውን ለመመለስና ለማስከበር መጾምና መጸለይ ግድ ይሆንበታል፡፡ በዚህ ጊዜ አመክሮ /ሱባዔ/ ይገባል፡፡ 🗝 እግዚአብሔርን ለመማፀን ሰው ሱባዔ ከሚገባባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች አንዱ እግዚአብሔርን ለመማፀን ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ሱባዔ ሲገባ በቁርጥ ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማኅፅኖ ሊኖረው ይገባል፡፡ ምንም የምንጠይቀው /የምንማፀነው/ ነገር ሳይኖር ሱባዔ ብንገባ የምናገኘው መልስ አይኖርም፡፡ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታና ዝግጅት ሱባዔ የሚገቡ ሰዎች ከሱባዔ በኋላ ምን እንደ ተመለሰላቸው የሚያውቁት ነገር ስለማይኖር ሱባዔ በመግባታቸው የሚያገኙት ነገር የለም፡፡ ስለዚህ ሱባዔ ከመግባታችን በፊት፡- ሱባዔ የምገባው ለምንድን ነው? በማለት ራሳችንን መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ ለምሳሌ አንድ ክርስቲያን በግል ሕይወቱ ዙሪያ ስለ ሀገር ሰላም፣ ስለ ጓደኛው ጤና ወዘተ ጉዳዮች ላይ ፈጣሪውን ይማፀናል፡፡ በዚህ ጊዜ በግል ሕይወቱም ሆነ በሀገር ጉዳይ ለገባው ሱባዔ ወዲያውኑ መልስ ሊያገኝ ይችላል፤ እንዲሁም መልሱ ሊዘገይ ይችላል፡፡ በዚህ ጊዜ ከተሐራሚው ትዕግሥት /መታገሥ/ ይጠበቅበታል፤ «ለምን ላቀረብኩት ጥያቄ ቶሎ መልስ አልተሰጠኝ?» በማለት ማማረርና እግዚአብሔርን መፈታተን ተገቢ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ሥራውን የሚሠራበትና ለሚማፀነውም መልስ የሚሰጥበት የራሱ ጊዜ አለው፡፡ 🗝 የቅዱሳንን በረከት ለመሳተፍ ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶች የተጋደሉትን ተጋድሎ በማዘከር ቃል ኪዳን በተሰጣቸው ገዳማትና አድባራት የሚገባ ሱባዔ የቅዱሳኑን በረከት ተካፋይ ያደርጋል፡፡ ቅዱሳን በሚጋደሉበት ቦታ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋ የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ /ኢሳ.56.6/ በማለት እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ስለ ገባላቸው ሱባዔ በመግባት በረከታቸውን መሳተፍ ይቻላል፡፡ በጾመ ነቢያት የነቢያትን በረከት ለመሳተፍ፣ በጾመ ሐዋርያት የሐዋርያትን በረከት ለመሳተፍ፣ በጾመ ፍልሰታ የእመቤታችንን በረከት ለመሳተፍ ሱባዔ መግባት የነበረና ወደ ፊትም የሚኖር የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ነው፡፡ ዛሬ ይህን ሥርዓት በመከተል የተለያዩ ቅዱሳንን በረከት ለመቀበል /ለመሳተፍ/ የቅዱሳን አፅም ካረፈበት ገዳም በጾም፣ በጸሎት፣ በጉልበትም ገዳማትን በማገልገል የቅዱሳንን በረከት ደጅ የሚጠኑ ምእመናንና መናንያን በየገዳማቱ እጅግ በርካታ ናቸው፡፡ ይኸውም በመጽሐፈ ነገሥት ካልዕ በምዕራፍ 2.9 እንደ ተመለከተው ነቢዩ ኤልሳዕ መምህሩን ኤልያስን በማገልገል የኤልያስ በረከት በእጥፉ በኤልሳዕ ላይ አድሮበታል፡፡ ይህን አብነት በማድረግ በየገዳማቱ በትህርምት የሚኖሩ መናንያንን ያገለገሉበትን ገዳም አባት በረከት በእጥፍ እየተቀበሉ ለሌሎችም የሚያቀብሉ አባቶች በየገዳማቱ አሉ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሆኖ በስመ ገዳማዊ የምእመናንን ገንዘብ የሚዘርፉና የእውነተኛ መነኮሳትንና መናንያንን የተቀደሰ ሕይወት የሚያጐድፉ መኖራቸውን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ 🗝 የተሰወረ ምሥጢር እንዲገለጥልን በዘመነ ብሉይ እግዚአብሔር ለአንዳንድ ነገሥታት ራእይ በማሳየት ምሥጢርን ይሰውርባቸው ነበር፡፡ ለምሳሌ የግብፁን ፈርዖን፣ የባቢሎኑን ናቡከደነፆርንና ብልጣሶርን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ዘፍ.41.14-36፡፡ ዳን.4.9፤ ዳን.5.4፡፡ እነዚህ ነገሥታት በግል ሕይወታቸውም ሆነ በመላው ሽክም ወደ ፊት ሊፈጸም የሚችል ራእይ ቢያዩም ቅሉ ራእዩን በትክክል ተረድተው እንዲህ ይሆናል የማለት ብቃት አልነበራቸውም፡፡ ስለዚህ በዘመናቸው ይኖር የነበሩትን ነቢያት ሱባዔ ገብተው የሕልማቸውን ትርጉም እንዲነግሩአቸው ይማፀኑ ነበር፡፡ ነቢያትም ሱባዔ በመግባት ነገሥታቱ ያዩትን የምሥጢረ ሥጋዌ ነገርና የመንግሥታቸውን አወዳዳቅ ገልጸው ይናገሩ ነበር፡፡ ዳን.5.28፡፡ 👉 ሱባዔ በዘመነ ሐዲስ በዘመነ ሐዲስ በሰፊው የሚወሳው ቅዱሳን ሐዋርያት ከነሐሴ 1-14 የገቡት ሱባዔ ነው፡፡ ይህ ሱባዔ ተሰውሮ የነበረውን የቅድስት ድንግል ማርያምን ትንሣኤ ተረድተው በረከቷን ለመሳተፍ አብቅቷቸዋል፡፡እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሦስት ዓመት በእናት በአባቷ ቤት፣ ዐሥራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከጌታችን ጋር አሥራ አምስት ዓመት በወንጌላዊው በዮሐንስ ቤት ከኖረች በኋላ በ64 ዓመቷ ጥር 21 ቀን ዐርፋለች፡፡ ለሐዋርያት የእመቤታችን የዕረፍትና የዕርገት ምሥጢር የተገለጠላቸው በሱባዔ ነው፡፡ ይህን መሠረት በማድረግ በየዓመቱ ጾመ ፍልሰታ ወይም የሐዋርያት ሱባዔ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ይታሰባል፣የቻሉ ርቀው ስባዔ ገብተው፣ያልቻሉ በአጥቢያቸው የውዳሴዋና የቅዳሴዋን ትርጉም ይሰማሉ፣በሰዓታቱና በቅዳሴው መርሀ ግብራት ይሳተፋሉ፡፡በእመቤታችን አማላጅነት በልጇ ቸርነት በምድር ሳሉ በሃይማኖት ጸንተው ለመኖር ኋላም ለመንግሰቱ እንዲያበቃቸው ድጅ ይጠናሉ፡፡ 👉 የሱባዔ ዓይነቶች

+ጾመ ፍልሰታ+ ጾመ ፍልሰታ ሐዋርያት የእመቤታችንን ሥጋ ለመቀበል እና በክብር ለማሳረፍ /ለመቅበር/ እንዲሁም ትንሣኤዋን ለማየት ይበቁ ዘንድ ሱባኤ ገብተው የጾሙት ጾም ሲሆን ምንምጊዜም ነሐሴ አንድ ቀን ገብቶ ከሁለት ሱባኤ በኋላ የእመቤታችን ትንሣኤና ዕርገት ይከበራል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው..."ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ የሆነው ሐዋርያው ቶማስ ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ከሕንድ በደመና ተጭኖ ሲመለስ የአምላክ እናት የሆነችውን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ተነስታ ስታርግ በመንገድ አገኛት። አስቀድሞ የልጇንም ትንሣኤ ከውንድሞቹ ከሐዋርያት ጋራ መጀመሪያ ላይ ባማለማየቱ የሚቆጨው ሐዋርያው ቶማስ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምም እሱ ሳያያት ለሌሎች ደቀመዛሙርት ተገልጣ ያረገች መስሎት ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ፤ ዛሬ ደግሞ ያንቺን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁን ብሎ አምርሮ እያለቅሰ ከደመናው ሊእርድቅ ሲል የሩህሩህ የሆነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም አይዞህ አትዘን እነሱ ትንሣኤየን ዕርገቴን አላዩም አንተ አይተሃልና ተነሣች፣ ዐረገች ብለህ ንገራቸው ብላ ሰበኗን /የመግነዟን ጨርቅ/ ሰጥታው አረገች። ሐዋርያው ቶማስም ወደ ሐዋርያት ዘንድ በመሄድ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ አላቸው። እነርሱም መላኩ አምጥቶ ሥጋዋን እንደሰጣቸው እና እንደቀበሯት ነገሩት፡፡ ቶማስም ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር ተው ይህ ነገር አይመስለኝም አላቸው። ጴጥሮስም መልሶ፦ አንተስ ልማድህ ነው፤ ነገር ግን አንተ ብቻ ተጠራጥረህ ሳትቀር እየተጠራጠርክህ ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራለህ አለው፡፡ ይዞትም ወደ መቃብሩ ሄደና መቃብሩን ቢከፍተው ሥጋዋ በመቃር ውስጥ የለም፡፡ ሥግጋዋንም ባጣ ጊዜ ደንግጦ ቆመ፡፡ ሌሎችም ደቀ መዛሙርት ሁሉ ደነገጡ፡፡ ቶማስም ሁኔታቸውን በተመለከተ ጊዜ አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችንስ ተነስታ ዐርጋለች አላቸው።የያዘውንም ሰበን ቀራርጠው ተከፋፈሉት፡፡ ዛሬም ካህናት በመስቀላቸው ሥር ይህንን መሰል ጨርቅ መያዛቸው የዚሁ ምሳሌ ነው፡፡ ከዚህ በኋላም ሐዋርያት በዓመቱ ቶማስ ትንሣኤሽን ዕርገትሽን አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ጾመ ፍልሰታን እንደገና መጾም ጀመሩ። በዚህን ጊዜ ጌታችን ከእናቱ ጋራ ተገልጦ መነሳቷን እና ማረጓን አረጋገጠላቸው፡፡ ዛሬ ቤተክርስቲያን የሐዋርያትን አሰረ ፍኖት ተከትላ እኛ ልጆቿን የፍልሰታ ጾም እንድንጾም ታዘናለች። እኛም ሐዋርያት ያዩትን የእመቤታችንን ትንሣኤ እናይ ዘንድ ከእጇ በረከትን እንቀበል ዘንድ የበረታን በገዳማት ሱባኤ ይዘን ሎቻችን ደሞ በቅዳሴው በሰዓታቱ እየተሳተፍን እመቤታችንን ንዒ በማለት እንማፀናታለን። + ጸሎታ ወበረከታ ወምሕረተ ፍቁር ወልዳ የሃሉ ምስለ ኩልነ ሕዝብ ክርስቲያን ለዓለመ ዓለም+ ✍️ቤተልሔም

✝በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት ሲሰጥ የነበረው ለአንድ ወር ተከታታይ ቀናት የተተኪ መምህራን ስልጠና ማጠናቀቂያ መርሐ ግብር በታላቅነት ድምቀት ተካሄደ። ➡️
+4
✝በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት ሲሰጥ የነበረው ለአንድ ወር ተከታታይ ቀናት የተተኪ መምህራን ስልጠና ማጠናቀቂያ መርሐ ግብር በታላቅነት ድምቀት ተካሄደ። ➡️ ከሐምሌ 1 እስከ ሐምሌ 30 በሀገረ ስብከት ደረጃ ለአንድ ወር ያክል በተከታታይነት ከተለያዩ ሰ/ት/ቤቶች የተውጣጡ ወጣቶችን የሰባክያነ ወንጌል ስልጠና የወሰዱ ሰልጣኞች ዛሬ እለተ እሑድ በ30/11/2014 ዓ.ም የሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ ፣ የመምሪያ ኃላፊዎች እና በርካታ የሰ/ት/ቤት አባላት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት የምርቃን መርሐ ግብር ያከናወነ ሲሆን በዕለቱም በመ/ር ፍሬ ሕይወት አራጌ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን ✅በሥልጠና ውስጥም ሲሳተፉ የነበሩ ሰልጣኞችን ሰርተፍኬት በመስጠት በሀገረ ስብከቱ ስራ አስኪያጅ ቃለ ምዕዳንና ጸሎት ተደርጎ ፍጻሜውን አግኝቷል:: ✅ይህም ሰ/ት/ቤቶች ለትምህርት ታላቅ ትኩረት እንዲሰጡ እና የተማሩትንም በሕይወት ተርጉሞ የቤተ ክርስትያንን ልጅነት ማጽናት እንደሚገባ በአንክሮ ተነግሯል:: 🌐የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ለዚህ አበቃችሁ። በእውነት ትልቅ ተስፋ ሰጭ ተግባር ነው። የቸርነት አምላክ ያበርታልን። ✍️
+1
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ለዚህ አበቃችሁ። በእውነት ትልቅ ተስፋ ሰጭ ተግባር ነው። የቸርነት አምላክ ያበርታልን። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ●••••✥••••✥••••✥✞ ✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ● የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤት
+5
✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ●••••✥••••✥••••✥✞ ✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ● የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤት ማደራጃ ክፍል ጋር በጋራ በመሆን በአዲስ አበባ ውስጥ ካሉ የደብራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣ የሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቃነ መናብርት እንዲሁም የስብከተ ወንጌል ኃላፊዎች ጋር በቀጣዩ ዓመት የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙሪያ ዛሬ ሐምሌ 22/2014 ዓ.ም የጋራ ምክክር አደረገ ። የምክክር መድረኩ የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤት ማደራጃ ዋና ክፍል ኃላፊ መምህር ደምስ አየለ የተመራ ሲሆን :: ስለ ስርዓተ ትምህርቱ ገለጻ እና ውይይት በመምህር በላይነህ መኮንን እና ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው ቀርቧል :: በምክክር ጉባዔው ማጠናቀቂያ ላይም ከየአጥቢያው የመጡ ባለድርሻ አካላት በየአጥቢያችን ላይ ሥርዓተ ትምህርቱን ለማስተግበር ኃላፊነት እንወስዳለን በማለት አጋርነታቸውን ገልጸዋል ። #የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት ✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ●••••✥••••✥••••✥✞ ✥••••✥••••✥••••●✞ ● ✞ ●✞ ●

ሐምሌ 19..... እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!! "ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል" በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ከሚከበሩ በዓላት መካከል ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል ነው። ይህ ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት እየሉጣንና ልጇን ቅዱስ ቂርቆስን ከፈላ ውሃ ከሞት እንዳዳነ የሚታሰብበት ዕለት ነው። ይህንንም በሐምሌ 19 መጽሐፈ ስንክሳር እና በመልአኩ በሐምሌ ድርሳን እንዲህ በሆነ መልኩ ተገልጦ እናገኘዋለን። እኛም ከብዙ ጥቂቱን ለአንባብያን በሚሆን መልክ እንደሚከተለው አሰናድተናል፦ እንሆ በዘመነ ሰማዕታት ከሐዲያን ነገሥታትና መኳንንት በክርስቲያኖች ላይ መከራ አጽንተውባቸው ነበር በዚህ ምክንያት ብዙዎች ሰማዕትነት ሲቀበሉ የተቀሩት አገር ጥለው ተሰደዱ ኢየሉጣም የሦስት ዓመት ህጻን የነበረውን ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ሸሸች በዚያም መኮንኑን አገኘችው ሰዎችም ነገር አሴሩባት ወደእርሱ አቀረቧት መኮንኑም ስለአምልኮዋ ጠየቃት እርሷም "መኮንን ሆይ ዕድሜው የሦስት ዓመት ህጻን ልጅ አለኝ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እሱን ጠይቅ" አለችው። ህጻኑም ወዳለበት ጭፍራውን ልኮ ወደ እርሱ አስመጣው ህጻኑም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና "አንተ ደስተኛ ህጻን ሆይ እንዴት ነህ?" አለው ህጻኑም መልሶ "አዎ ለኔ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ሐዘንና ለቅሶ ጥርስ ሟፏጨትም ነው። መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏል እና " አለው፤ እግዚአብሔር ኃይልንና ንግግርን ሰጥቶታልና በዚያ ተናገረ፡፡ በዚያም ያሉት እስኪደነግጡ ድረስ ንጉሡን መኳንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ መኮንኑም በአፈረ ጊዜ እጅግ ብዙ ስቃይን አሰቃየው እናቱንም ከእርሱ ጋር አሰቃያት እግዚአብሔርም ካለምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር። በዙዎች አህዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት የክብር አክሊል ተቀናጁ። በህጻኑም ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችም አዳናቸው። መስፍኑም በውስጡ ስም፤ ጨው፤ ባሩር፤ ሙጫ፤ የዶሮ ማር፤ እርሳስ፤ ብረት፤ ቅንጭብ፤ ቁልቋል ጨምራችሁ ታላቅ የብረት ጋን አምጡልኝ ብሎ ጭፍሮቹን አዘዛቸው ጭፍሮቹም እንዳዘዘአቸው ካደረጉ በኋላ ያዘዝከንን ሁሉ ፈጽመን እሳቱ ነዶ ፈልቷል እንግዲህ በውስጡ የሚጣሉትን እዘዝ አሉት። በዚህ ጊዜ ህጻን ቂርቆስና እናቱ እየሉጣ በክርስቶስ ስም ስለሚያምኑ አስረዋቸው ነበርና ከፍላቱ ሊጨምሯቸው ከእስር ቤት አወጣቸው። በዚህም ፍላቱ ወደላይ በሚዘል ብረት ጋን ውስጥ ለመጨመር ሲወስዷቸው የነዚህን ቅዱሳን አሟሟት ያዩ ዘንድ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲሰበሰቡ አዘዟቸው። በዚህ ጊዜ ቅድስት ኢየሉጣ የፍላቱን ጩኸት በሰማችና ባየች ጊዜ ተሸበረች ተዘጋጅቶላት ከነበረው ክብር ልታፈገፍግ ሞከረች። ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን "እናቴ ሆይ ከዚህ የብረት ጋን ግርማ የተነሳ አትፍሪ ድንጋጤም አይደርብሽ አናንያን፤ አዛርያን እና ሚሳኤልን እግዚአብሔር ከእቶን እሳት እንዳወጣቸው ሁሉ እኛንም ከዚህ ብረት ጋን ሊያወጣ ችሎታ እንዳለው አትጠራጠሪ" አላት ነገር ግን እናቱ በዚህ ምክር ልትጽናና ባለመቿሏ ቅዱስ ቂርቆስ ዐይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ "አቤቱ አምላክ ሆይ ይቺን ባሪያህን ከርስትህ የምትለይ ከሆነ ከባለሟልነትህ መጽሐፍ ፋቀኝ፤ ዲያብሎስ ከባለስልጣኑ ይልቅ እኔ በረታሁ ቅዱሳኖችህንም ድል ነሰኋቸው ብሎ እንዳይመካ ከመንጋውም አንድ ባጣ ቀማሁ በማለት እንዳይገፋ ለእናቴ ጽኑ መንፈስ ቅዱስን ስጣት" ብሎ በጸለየ ጊዜ ዲያብሎስ ከኢየሉጣ አጠገብ ብን ብሎ ጠፋ ከዚህ በኋላ ቅድስት እናቱ "በሰማያዊ መንግስት አባት የሆንከኝ ልጄ ሆይ ጌታህ ኀይልን ሰጥቶኛልና የሚጠብቀንን ገድላችንን ፈጽመን ድል እናድርግ እነሆ በብረት ጋን ውስጥ የሚነደውን እሳት በማይበት ጊዜ ለምለም (ምንጭ) ላይ እንደሚወርድ ጠል ሆኖ አይቼዋለሁና አለችው" እነዛም ከሀዲያን በሚፍለቀለቀው ጋን ውሰጥ ጨመሯቸው ቂርቆስና እየሉጣም የክብርን አክሊል በዚች ቀን ተቀበሉ። በረከታቸው ይደረብን

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠 📣📣📣 የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የማጠናቀቂያ ምዘና በሁሉም ክፍለ ከተሞች በተሳካ መልኩ ተከናወነ።🌷🌷🌷 በዘንድሮው ዓመት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ እና ትምህርታቸውን ሲካተታሉ የነበሩ ከሁሉም ክፍለ ከተማ #የ4ኛ#የ6ኛ እና #የ10 ክፍል አራት ሺህ ሰማንያ ሰባት {4087} ሰንበት ተማሪዎች #ሐምሌ_17_2014_ዓ_ም ከቀኑ 4:00 -7:00 ሰዓት ድረስ የትምህርት ዓመቱ ማጠናቀቂያ ምዘና የተደረገ ሲሆን በሁሉም ክፍለ ከተማ በእግዚአብሄር ፍቃድ በተሳካ መልኩ ምዘናው ተጠናቋል። በነበረው የምዘና (የፈተና) አገልግሎት በማስተባበር ፥ በመፈተንና በማስፈተን ለተሳተፋችሁ ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ ዋጋችሁን ይክፈልልን ሲል የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መደበኛ አገልግሎት ማስተባበሪያ ክፍል ምስጋናውን አቅርቧል። 🌷🌷🌷የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስተባበሪያ ክፍል !!🌷🌷🌷 💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

👉በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት በሀገረ ስብከቱ ሥር በሚገኙ ሥርዓተ ትምህርቱን ተግባራዊ ባደረጉ ሰንበት ት/ቤቶች ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተመሳሳይ ቀንና ሰ
+7
👉በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት በሀገረ ስብከቱ ሥር በሚገኙ ሥርዓተ ትምህርቱን ተግባራዊ ባደረጉ ሰንበት ት/ቤቶች ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ሲካሄድ የነበረው የ፳፻፲፬ ዓ.ም ማጠቃለያ ፈተና በዛሬው ዕለት ሐምሌ ፫ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። 👉በሀገረ ስብከት ደረጃ የፈተናው ሰነ ሥርዓት በደመቀ ሁኔታ በደ/ብርሃን ቅ/ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት ጊዜያዊ አዳራሽ፤ የደ/ብርሃን ቅ/ሥላሴ ቤ/ክ አስተዳዳሪ ንቡረ ዕድ ቆሞስ አባ መዘምር አሰግደው እና የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤት ማ/መ ክፍል ኃላፊ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ አብርሃም ሙሉጌታ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ሊቀ አዕላፍ ቀሲስ ዮርዳኖስ አቢ በተገኙበት ተካሂዷል። 👉በቀጣይ በሀገረ ስብከት ደረጃ የሚካሄደውን የተማሪዎች የምረቃ ስነ ሥርዓት በቅርቡ የምናሳውቃችሁ ይሆናል። ደ/ብርሃን፤ ሐምሌ ፫ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም +++++++++++++++++++++++++++++++++++++ መንፈሳዊ ትምህርቶችንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት👇 👉YouTube https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg 👉Facebook https://www.facebook.com/EOTC.DSSUDB 👉Telegram https://t.me/EOTCDSSUDB 👉Website https://eotc-gssu.org/a