fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 296 مشترک است و جایگاه 6 167 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 365 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 296 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 20 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 492 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 16 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 52.64% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.12% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 7 523 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 875 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 29 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 21 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 296
مشترکین
+1624 ساعت
+1157 روز
+49230 روز
آرشیو پست ها
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የደረጃ ሁለት የአሠልጣኞች ሥልጠና የወሰዱ መምህራንን አስመረቀ። በምርቃት መርሐ ግብሩ የሀገረ ስብከቱ ም/ሥራ አስኪያጅ ክቡር ቀሲስ ጌቱ ሞቲ : ክቡር ሊቀ ካህናት ሻውል ታዬ የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ኃላፊ: ክቡር መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ ጳውሎስ ምንዳ የአዳማ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ገዳምና ካቴድራል አስተዳዳሪ የአንድነቱ አመራሮች እንዲሁ ሠልጣኝ ተመራቂዎች በተገኙበት በትላንትናው ዕለት በአዳማ ደ/መ/መ/ካቴድራል የሰንበት ት/ቤት አዳራሽ ተካሒዷል። በመርሐ ግብሩም የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ የሆኑት ሊቀ ካህናት ቀሲስ ሻውል ታዬ የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት ለተተኪ መምህራኑ ያስተላለፉ ሲሆን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተ/ም/ሰብሳቢ የሆኑት ኢንጂነር አለምዓንተ አበጀ የሥልጠናውን ዓላማና ጠቀሜታ በአጭሩ ለታዳሚዎች ገለጻ አድርገዋል። በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱ ም/ሥራ አስኪያጅ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ጢሞቴዎስ ሆይ፥ በውሸት እውቀት ከተባለ ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍና መከራከር እየራቅህ፥ የተሰጠህን አደራ ጠብቅ" ያለውን ቃለ እግዚአብሔር መነሻ በማድረግ ትምህርት ተሰጥተዋል። በትምህርታቸውም ቤተ ክርስቲያን ከናንተ ብዙ ትጠብቃለች በሔዳቹበት ሁሉ አገልግሎታችሁ በትዕግስትና በፍቅር ይሁን" በማለት መመሪያ ለተመራቂ ተማሪዎች አስተላልፈው ለተማሪዎች የምሥክር ወረቀት ሰጥተዋል። ተመራቂ ተማረዎች በነበራቸው ቆይታ ምክረ አበው:የሥራ አመራር አቅም ማሳደጊያ :የአገልግሎት ምንነት :ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር : የቤተ ክርስቲያን ታሪክ: የሕጻናት የማስተማር ዘዴ:የሰንበት ት/ቤት መዋቅር: የቅድመ መደበኛ ት/ት ተሞክሮና የልምድ ልውውጥ :የምዘና እና ግምገማ አዘገጃጀቶች:የንባብ ሕይወት :መሠረተ ሃይማኖት ፣ የአስተዳደር ክህሎትን በሚመለከቱ 16 ኮርሶችን በተከታታይ ለ9 ቀናት በቀንና በማታ መርሐ ግብር የወሰዱ ናቸው። ሠልጣኞቹ በሀገረ ስብከቱ ሥር ከሚገኙ ስድስት ወረዳ ቤተ ክህነቶች የተወጣጡ ናቸው። መረጃውን ያደረሰን የሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተመሰረተ። በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ከሁሉም የወረዳ ቤተክህነት የተውጣጡ የሰንበት ት/ቤት አባላት ለተከታታይ አምስት ቀን ይሰጥ የነበረው ሥልጠና ተጠናቅቋል። በሥልጠናው ማጠናቀቂያ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ዓባል ብፁዕ አቡነ ገሪማ ፣የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ሐላፊዎች ፣የመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተክህነት ዋና ሥራአስኪያጅ ሊቀ ጠበብት መሠረት ይልማ ፣የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ለአምስት ቀን ሥልጠና ይከታተሉ የነበሩ ወጣቶች ተገኝተዋል። በመርሐ ግብሩ ማጠቃለያ የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤት አንድነት የተመሰረተ ሲሆን የሚመሩትም ሥራ አስፈጻሚዎች ተመርጧል።ሠልጠኞች በቆይታቸው የተማሩትን አመርቂ የማለፊያ ውጤት ላመጡ ሰርተፍኬት ተሰጥቷል። ሰርተፍኬት  ለሁሉም ወረዳ ቤተክህነት ፣ ለአድባራት፣ ለአሰልጣኝ መምህራን፣ ለጠቅላይ ቤተክህነት ለሰንበት ት/ቤት ማደራጃ መምሪያና ለዓለም አቀፍ ሰንበት ት/ቤት ለአስተባባሪዎች ተሰጥቷል። በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ ቃለ ምዕዳን ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸው  ወጣቶች የሚያገለግሉባት ቤተክርስቲያን መሆኗል ገልጸው፤ የተዛባ የሰንበት ት/ቤት አገልግሎት መስተካከል አለበት ፤ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶችም የቤተክርስቲያን የጀርባ አጥንት ናቸው ብለዋል።ለቤተክርስቲያን ከፍተኛ የክህነት የማዕረግ ምንጩ ሰንበት ት/ቤት መሆን አለበት። ከሰንበት ት/ቤት የቤተክርስቲያን አገልጋይ የሚወጣበት ነው። በአግባቡ ትምህርት መስጠት አለበት። ሰንበት ት/ቤት ህጻናት በምግባር በቃለ እግዚአብሔር የሚኮተኩቱበት መሆን አለበት አሁን እየሆነ ባለመሆኑ በቀጣይ መሥራት አለብን በማለት አባታዊ መልእክት ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ አስተላልፈው   የሥልጠናው መርሐ ግብሩ ተፈጽሟል ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! መልካም በዓል! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! መልካም በዓል! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የመጽሐፍ ሥርጭትና ሽያጭ ወር እንኳን ለ2018ዓ.ም የትምህርት መርሐ አደረሳችሁ የትምህርት መርሐ ግብሩን ጅማሮ ምክንያት በማድረግ የሰ/ት/ቤቶይ ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የመማርያ መጻ
የመጽሐፍ ሥርጭትና ሽያጭ ወር እንኳን ለ2018ዓ.ም የትምህርት መርሐ አደረሳችሁ የትምህርት መርሐ ግብሩን ጅማሮ ምክንያት በማድረግ የሰ/ት/ቤቶይ ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የመማርያ መጻሕፍት ሥርጭትና ሽያጭ መጀመሩ ያበስራል። መጻሕፍቱን ባለድርሻ አካላት 👉 የሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤት አንድነት 👉 የአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች 👉 መምህራነ ቤተክርስቲያን 👉 ወላጆችና 👉ተማሪዎች መጻሕፍቱን በመውሰድ ወደ ትግበራ ትገቡ ዘንድ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን። ለሽያጭ የቀረቡ መጻሕፍት ✍️ ከ1-7ኛ ክፍል በአማርኛ ✍️ ከ1-4ኛ ክፍል በኦሮምኛ አድራሻ ጠቅላይ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለበለጠ መረጃ 0913969785 0920741461 (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! መልካም በዓል! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Face
እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! መልካም በዓል! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

ሲሰጥ የነበረው የሰንበት ትምህርት ቤት ሥልጠና ተጠናቀቀ! የኢሉ አባ ቦር ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ላለፉት 10 ቀናት ሲሰጥ የነበረውን ሥልጠና አጠናቆ በዛሬው ዕለት ሠ
+4
ሲሰጥ የነበረው የሰንበት ትምህርት ቤት ሥልጠና ተጠናቀቀ! የኢሉ አባ ቦር ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ላለፉት 10 ቀናት ሲሰጥ የነበረውን ሥልጠና አጠናቆ በዛሬው ዕለት ሠልጣኞችን አስመርቋል። የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ያዘጋጀው አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት ለመተግበር በሀገረ ሰብከቱ ለሰንበት ትምህርት ቤት መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና ተሰጥቷል። ሥልጠናው ላለፉት 10 ቀናት ሲሰጥ የነበረ ሲሆን ከመላው የሀገረ ስብከቱ ወረዳዎች እና ከመቱ ከተማ 66 ሰልጣኞች ትምህርቱን ተካታትለው ዛሬ በታላቅ ድምቀት ተመርቀዋል። በምረቃው መርሀ ግብር ላይ የተገኙት የሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ስዩማን ቀሲስ ታከለ ዳዲ ባስተላለፉት መልእክት እንዳመለከቱት ሰንበት ትምህርት ቤት የቤተክርስቲያናችን መሠረት ነው ብለው ይህንን መሠረት በእውቀት እና በሥነ ምግባር ኮትኩቶ የነጌይቷን ቤተክርስቲያን ተረካቢ እንዲሆኑ እየሠራን ነው ብለዋል። ምክትል ሥራአስኪያጁ አያይዘው እንደተናገሩት ይህንን መሠረታዊ ሥልጠና ለመስጠት ድጋፍ ያደረጉትን ማኅበረ ቅዱሳን እና አድባራትን አመስግነው ሀገረ ስብከቱ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች በሰጠው ልዩ ትኩረት የሰው ኃይል እና ፋይናንስ መድቦ እየሠራ ነው ብለዋል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ጽንሰት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮው
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ጽንሰት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: ጾሙን የፍሬ የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ! ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን ልበዎውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: ጾሙን የፍሬ የትሩፋትና የበረከት ያድርግልን! (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

#ቃለ_በረከት_ዘብፁዕ_ወቅዱስ_አቡነ_ማትያስ_ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ.ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የ2017 ዓ/ም የጾመ ፍልሰታ መግባትን አስመልክተው ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል። መግለጫው የሚከተለው ነው።        መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ፡- በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን!!!        በሀገራችን በኢትዮጵያና በመላው ዓለም የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ፡- የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓ.ም የቅድስት ድንግል ማርያም ጾመ ፍልሰታ በሰላም ኣደረሳችሁ!   ‹‹ታዓብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር፣ ነፍሴ እግዚአብሔርን እጅግ ታከብረዋለች›› (ሉቃ.፩÷፵፮) ይህንን ዐረፍተ ነገር የተናገረችው ማኅደረ መንፈስ ቅዱስ የሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፤ ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር ዓለምን ለማዳን በሰራው ስራ ሰውነታችንን ለመዋሓድ የመረጣት ምርጥ የፍጥረት ወገን ናት፤ፍጥረት ሁሉ በእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር ተፈጥሮኣል፤የእግዚአብሔርም ነው፤ የቅድስት ድንግል ማርያም መመረጥም በእግዚአብሔር ለሰው የተደረገ ምርጫ ነው፤ የሰው መዳን ከጥንቱ ከጠዋቱ በእግዚአብሔር ልዩ ኣሰራር እንደሚከናወን በነቢያት የተገለጸ ነበረ፣‹‹ኣኮ በተንባል ወኣኮ በመልኣክ ኣላ ለሊሁ እግዚእ ይመጽእ ወያድኅነነ፤ በኣማላጅም ኣይደለም፤ በመልኣክም ኣይደለም እሱ ራሱ ጌታ መጥቶ ያድነናል እንጂ›› የሚለው የነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ ትንቢትም ይህንን ያስረዳል፤ ቃለ ትንቢቱ ድኅነታችን በጌታ ቤዛነት እንደሚከናወን ያረጋግጣል፤ይህም ሊሆን የቻለው ከፍጡራን ወገን በደሙ ቤዛነት ፍጡራንን የሚያድን ስለሌለ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር የሰው መዳን በእግዚአብሔር ኣሰራር በደም ቤዛነት ከሆነ፣ በደሙ ቤዛነትም ዓለምን ማዳን የሚችል ከፍጡር ወገን ከሌለ፣ መዳናችን በእግዚአብሔርና በእግዚአብሔር እጅ ብቻ የተንጠለጠለ ነበረ፤ እግዚአብሔር በደሙ ቤዛ ሆኖ ዓለምን ለማዳን ደግሞ ደም ሊኖረው ይገባ ነበር፤ በመሆኑም እግዚአብሔር በክዋኔው ደም የሌለው ስለሆነ ለቤዛ ዓለም የሚፈስ ደምን ገንዘብ ማድረግ ነበረበት፤ይህንን ደም ለመዋሓድ ቅድስት ድንግል ማርያምን መረጠ፤ ለዚህ ብቁ እንድትሆንም በእስዋ ላይ ስራውን ሰራ፤በምርጫውም መሠረት ከቅድስት ድንግል ማርያም ደማዊ ሥጋንና ነፍስን ተዋሕዶ ለቤዛዊ መሥዋዕት መንገዱን ኣመቻቸ፤ ቅድስት ድንግል ማርያም በነገረ ድኅነት መሰላል ለመሆን በእግዚአብሔር የተመረጠች በመሆኗ ኣንቀጸ ኣድኅኖ ወይም የድኅነት በር ትባላለች ፤ ቅድስት ድንግል ማርያም ለዚህ ታላቅ ነገረ ድኅነት መመረጥዋ እጅግ ታላቅ ዕድል መሆኑን ስለተገነዘበች ‹‹ታላላቅ ስራዎችን ሰርቶልኛልና›› በማለት እግዚአብሔርን በመዝሙር ኣመስግናለች ኣክብራለችም፤         የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! የቅድስት ድንግል ማርያም የምስጋና እና የኣምልኮ መዝሙር የኛም መዝሙር ነው፤ እግዚአብሔር ለቅድስት ድንግል ማርያም ታላላቅ ስራዎችን እንደሰራ ለኛም ብዙ ታላላቅ ስራዎችን ሰርቶልናል፤ እየሰራልንም ነው፤ ለሰራልን ኣምላክም እንደ ቅድስት ድንግል ማርያም ታላቅ ክብርን መስጠት ይገባናል፤ ለእግዚአብሔር የምንሰጠው ክብርም በቃል ብቻ የሚገለጽ ሳይሆን በተግባር የሚታይ ሊሆን ይገባል፤ የድንግል ማርያም መንፈሳዊ ሕይወት በማስተዋል በትሕትና፣ በትዕግሥት በርኅራኄ በመታዘዝ በንጽህና በቅድስና በክብርና በበረከት የተሞላ እንደሆነ በቅዱስ መጽሓፍ ከተጻፈው ሥነ-ሕይወቷ መረዳት እንችላለን፤ ታድያ በእርሷ ክብርና ተማሕፅኖ የምንተማመን ልጆቿም የእሷን ያህል እንኳ ባንችል ወደእርስዋ የሚጠጋጋ መንፈሳዊ ሕይወት ሊኖረን ይገባል፤ ይህም የምናደርገው ለእግዚአብሔር ክብርና ለእኛ መዳን ሲባል ነው፤ እኛ እግዚአብሔርን ስናከብር እንከብራለን እንድንማለን፤ ለእግዚአብሔር ክብር የማንሰጥ ከሆነ ግን ውጤቱ መክበር ሳይሆን ሌላ ነው የሚሆነው፤   የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! እኛ በየጊዜው ጾምን እንድንጾም ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት ፈቃደ ሥጋችንን በመግራት ለእግዚአብሔር ታዛዦች እንድንሆን ነው፤ ጾም የኃጢኣት መግቻ መሳሪያ በመሆኑ ‹‹ልጓመ ኃጢኣት›› ተብሎ ይታወቃል፤ በዚህም ሰውነታችንን ለግብረ ኃጢኣት ከሚያጋግሉ ምግቦች ኣርቀን በሰከነ መንፈስ እግዚአብሔርን እያሰብን ኃጢኣታችንንም እያስታወስን በንስሓ ወደ እርሱ ለመቅረብና ለሱ ለመታዘዝ እንጾማለን፤ የጾም ጥቅም ከጥንት ጀምሮ የታወቀ በእግዚአብሔርና በሰውም ተቀባይነት ያለው ነው፤ እግዚአብሔር ከመሥዋዕት ይልቅ መታዘዝን ይወዳልና በጾምና በጸሎት ለሱ ልንታዘዝ ይገባል፤ እግዚአብሔር በቅድስት ድንግል ማርያም ማሕፀን ሊያድር የቻለው ‹‹እንዳልኸኝ ይሁንልኝ›› ብላ ታዛዥነትዋን በገለጸች ጊዜ ነው፤ እኛም እንዳልከን ይሁንልን እያልን እንደእስዋ ታዛዥ መሆን አለብን፤ ዛሬ በዓለማችን ያለው መተረማመስ ለእግዚአብሔር ያለመታዘዝ ያመጣው ጣጣ እንደሆነ ማንም ኣይስተውም፤ መታዘዙ ቢኖር ኖሮ የሰው ልጅ ሰውን የሚያድን ብቻ እንጂ ሰውን የሚገድል መሳሪያ ኣያመርትም ነበር፤ ምክንያቱም እግዚአብሔር ወንድምህን እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ ኣለ እንጂ ግደል ብሎ ኣላዘዘምና ነው፤ኣሁንም በዚህ ባለንበት ዓለም በጣም ተባብሶ የሚገኘው የመጠፋፋት ዝንባሌ ለእግዚአብሔር በመታዘዝ በሰላምና በሰጥቶ መቀበል ካልተቋጨ ዳፋው ኣስከፊ መሆኑ ኣይቀርም ፤ ከዚህ አንጻር ዛሬም ለሰው ልጆች ሁሉ የምናስተላልፈው መልእክት ‹‹በፍቅር ከሆነ ትንሹም ለሁሉ ይበቃልና ያለውን በጋራ በመጠቀም በፍቅርና በሰላም እንኑር›› የሚል ነው፤ ‹‹ፍትሕና ርትዕም ለሰው ልጅ መነፈግ የበለትም፤ ሰው በምድር ላይ ሰርቶ የመኖር መብቱ ሊከበርለት ይገባል፤ይህንን ማድረግ ማለት ለእግዚአብሔር መታዘዝ ማለት ነው፤ስለሆነም ለእግዚአብሔር ክብርና ለራሳችን መዳን ስንል ለእርሱ በመታዘዝ በሕይወትና በሰላም እንኑር፡፡                           በመጨረሻም፡- በጾመ ማርያም ሱባዔ ስለሀገር ሰላምና ስለሕዝብ ደኅንነት በመጸለይ፣ በልዩ ልዩ ምክንያት በመከራ ላይ ወድቀው የሚገኙ ወገኖቻችንን በሚያስፈልጋቸው ሁሉ በመርዳት ሱባዔውን እንድናሳልፍ ኣባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን እናስተላልፋለን።    መልካም የሱባዔ ወቅት ያድርግልን    እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!    ወስብሐት ለእግዚአብሔር ኣሜን!!     አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት          ነሐሴ 1 ቀን 2017 ዓ.ም             ዋሽንግተን ዲሲ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ሰ/ት/ቤት ማ/መ/ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ስለ ሥርዓተ ትምህርት ምንነት እና አስፈላጊነት በሚገባ ግንዛቤ ለመፍጠር እና ንቃተ ኅሊና ከአጥቢያ ሰበካ ጉባኤ ፣ ሰንበት ትምህርት
+8
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ሰ/ት/ቤት ማ/መ/ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ስለ ሥርዓተ ትምህርት ምንነት እና አስፈላጊነት በሚገባ ግንዛቤ ለመፍጠር እና ንቃተ ኅሊና ከአጥቢያ ሰበካ ጉባኤ ፣ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እስከ ወረዳ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራር ድረስ ከ26/11/2017 ዓ/ም - 27/11/2017 ዓ/ም ድረስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ቀርሳ ማልማ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ተካሂዷል። ሥልጠናውን ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የኦሮሚኛ ቋንቋ ሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት አስተባባሪ የሆኑት ዲያቆን አዲሱ እና ዲያቆን ጉታ የሰጡ ሲሆን የሥርዓተ ትምህርት ምንነት ፣ ኦርቶዶክሳዊ ማያ ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዋቅር ፣ እቅበተ እምነት፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ጉዞ እና ሐዋሪያዊ አገልግሎት ለቤተክርስትያን መስፋፋት የተጫወተው ሚና በሥልጠናው ላይ የተዳሰሱ ጉዳዮች ነበሩ። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉 Website

በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሲሰጥ የነበረው የመምህራን ሥልጠና መርሐ ግብር ተጠናቀቀ። የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሐምሌ 29/2017ዓ.ም (ጭሮ) በምዕራብ ሐረርጌ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አዘጋጅነት ከሐምሌ 25 እስከ 29 ሲሰጥ የነበረው የተተኪ የመምህራን ሥልጠና መርሐ ግብር የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ የሐሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን አባ ፍቅረ ዮሐንስ እንዲሁም  የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ሓላፊ መጋቤ ሥርዓት ቀሲስ ዘነበ ብርሃኑ በተገኙበት ተከናውኗል። ሥልጠናው በሀገረ ስብከቱ መንበረ ጵጵስና ጭሮ/አሰበ ተፈሪ መንበረ ጵጵስና ደብረ ጽዮን ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን የተከናወነ ሲሆን ሠልጣኞችም በሀገረ ስብከቱ ከሚገኙ ዘጠኝ ወረዳ ቤተ ክህነት የተውጣጡ ከ160 የሚበልጡ  መምህራን፣ የሰ/ት/ቤት አንድነት አመራሮች፣ የሰ/ት/ቤት ሥራ አስፈጻሚዎች እንደተሳተፉ በጉባኤው ሪፖርት ያቀረቡት የሰ/ት/ቤት ክፍል ሓላፊው መጋቤ ሥርዓት ቀሲስ ዘነበ ብርሃኑ ገልጸዋል። በቆዩባቸው ቀናት በቀንና በማታ በሦስት የትምህርት ክፍለ ጊዜ ከመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመጡ ሁለት መምህራን በቋንቋ ጭምር በ12 ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና እንደተሰጠ ተናግረዋል። ሀገረ ስብከቱ ለሰ/ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራና የመምህራን ችግር ለመቅረፍ ሰፊ ሥራ እየሠራ እንደሆነ፤ በክረምት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚዘጋጀውን የመምህራን ሥልጠና ለሁለተኛ ግዜ ልዑካንን አዲስ አበባ ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ በመላክ አሠልጥኖ በየወረዳው ሥልጠና እንዲሰጡ እያደረገ መሆኑን ተናግሯል። ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ በመልዕክታቸው "ጎበዞች ሁኑ በተማራችሁት ኑሩ፣ ወርዳችሁ ያላወቁትን አሳውቁ አስተምሩ፣ ነፋሱ ቢነፍስ ጎርፉ ቢበረታም ዓለት በተባለች በሃይማኖት ላይ ራሳችሁን አጽኑ፣ በፍቅር አገልግሉ።" የሚል አባታዊ መልዕክትና ቃለ ምዕዳን በማስተላለፍ ለሠልጣኞች የምስክር ወረቀት ሰጥተው የጉባኤው ፍጻሜ ሆኗል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website