fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 200 مشترک است و جایگاه 6 236 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 378 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 200 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 14 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 485 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 20 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 41.07% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً N/A% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 830 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 0 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 28 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 15 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

14 200
مشترکین
+2024 ساعت
+1457 روز
+48530 روز
آرشیو پست ها
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትቤቶች አንድነት ጥቅምት 30/2018ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ የሚያካሂደውን የምርቃት እና የጉባኤ መርሐግብር ዝግጅት ማጠናዘቀቁን የአንድነቱ የመረሐ ግብር አዘጋጅ አብይ ኮሚቴ አስታወቀ። በእለቱ ከ164ገዳማት እና አድባራት የተውጣጡ የሀገረ ስብከቱን ምዘና ወስደው ወደ ቀጣይ ክፍል የተዘዋወሩ ከ11,800 በላይ የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በብጹእ ወቅዱስ ፖትሪያሪኩ እና ብጹአን አባቶች ቡራኬ እንደሚመረቁ ኮሚቴው አሳውቋል። መርሐግብሩ በሁለት ክፍል የተከፈለ ሲሆን የመጀመርያው ክፍል ጉባኤ ሲሆን ከቀኑ 6:00እስከ9:00  በዝማሬ፣በኪነጥበብ እና በቃለእግዚአብሔር  የሚከናወን ሲሆን ፣ ሁለተኛው ክፍል የምርቃት መርሐግብር ሲሆን በመርሐግብሩም ተመራቂዎች ከብጹአን አባቶችቡራኬ  ይቀበላሉ በውጤታቸው ከፍተኛ ነጥብ ያመጡ  ተማሪዎች እና ሰንበት ት/ቤቶች ከአባቶች እጅ ሽልማት ይቀበላሉ በሁለተኛውም ምእራፍ በተመራቂዎች ዝማሬ እና በብጹአን አባቶች ትምህርት እና ቃለ ምእዳን እንደሚሰጥ የተገለጸ ሲሆን በእለቱ ሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ተመራቂ ተማሪዎች ነጭ ልብሳቸውን ለብሰው  ከጠዋቱ 5:00 ሚሊኒየም አዳራሽ  እንዲደርሱ  ያሳሰበ ሲሆን ካለው የቦታ ጥበት አኳያ ተማሪዎች አመቺ ቦታ ለማግኘት  በቅድሚያ ተገኝተው ቦታቸውን እንዲይዙ አሳስቧል  ፣ ወላጆች ምእመናን የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች የሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቃነመናብርት፣ የሰንበት ት/ቤት አመራሮች  መዘምራን ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ከ5:30ጀምሮ ወደ አዳራሹ መግባት እንደሚችሉ እና ጉባኤው ከቀኑ6:00 በጸሎተ ወንጌል እንደሚጀመር  ኮሚቴው አብራርቷል። በመጨረሻም በዚህ ጉባኤ ምእመናን በነጻ መሳተፍ እንደሚችሉ ያሳወቀ ሲሆን ለጉባኤው የሚያስፈልጉ ቅድመዝግጅት መጠናቀቁን እና መርሐግብሩን ለማከናወን እለቱን በጉጉት እየጠበቅን ነው ሲል  አብይ ኮሚቴው በመግለጫው አብራርቷል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የምርቃት አብይ ኮሚቴ።

#አስቸኳይ_መልዕክት የመጻሕፍት ሥርጭትን በተመለከተ ለሁሉም ሀገረ ስብከት እንደሚታወቀው ከ1-7ኛ ክፍል በአማርኛ እንዲሁ ከ1-4ኛ ክፍል በአፋን ኦሮሞ መማርያ መጻሕፍት ታትመው ለየሀገረ ስብከቱ ስና
#አስቸኳይ_መልዕክት የመጻሕፍት ሥርጭትን በተመለከተ ለሁሉም ሀገረ ስብከት እንደሚታወቀው ከ1-7ኛ ክፍል በአማርኛ እንዲሁ ከ1-4ኛ ክፍል በአፋን ኦሮሞ መማርያ መጻሕፍት ታትመው ለየሀገረ ስብከቱ ስናሰራጭ መቆየታችን ይታወቃል። ከእነዚህ መጻሕፍት መካከል ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል የአማርኛ መጻሕፍት በአሁኑ ሰዓት ሙሉ ለሙሉ ተሽጠው ያለቁ መሆኑን እየገለጽን ከ1-4ኛ ክፍል መጻሕፍት ለኹለተኛ ሕትመት ፍላጎታችሁን ከአሁኑ እንድታሳውቁ፤ እንዲሁ ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል እና ከ1-4 የኦሮምኛ መጻሕፍት በሥርጭት ላይ ሲሆኑ ነገር ግን ያለው ብዛት ጥቂት በመሆኑ ሀገረ ስብከቶች በመጻሕፍት ግዥ ያላችሁን ፍላጎት አስቀድማችሁ በመላክ ቅድሚያ እንድታገኙ ስንል እናሳስባለን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የአንድነት ገዳማት ኅብረቱ መተዳደሪያ ደንብ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ታይቶና ተመርምሮ እንዲቀርብ፣ በአጠቃላይ በአንድነት ገዳማት ኅብረት የቀረበው የገዳማውያንና ገዳማውያት ማረፊያ እና የገቢ ማስገኛ ሁለገብ ሕንጻ ግንባታ የትግበራ ዕቅድ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል በዘርፉ ባለሙያዎች ታይቶና ተገምግሞ ከባለሙያ አስተያየቶችና የውሳኔ ሐሳብ ጋር ተጠንቶ ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡ 9.በበዓላት አከባበር፣ በመንፈሳዊ አገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ የሚታዩ ግድፈቶች፣ ያልተገቡ እንቅስቃሴዎችና ከሥርዓት የወጡ የአገልግሎት አፈጻጸሞች መታረም ስላለባቸው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሚሰየሙ ሊቃውንትና ባለሙያዎች ለመመሪያና ለማስተማሪያ የሚሆን ሰነድ ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተገቢውን ውሳኔ ያስተላለፈ መሆኑን እየገለጽን ያለጠባሳ የሚያድኑ ሐኪሞች፣ ያለቅሬታ የሚያስታርቁ ሽማግሌዎች በነበሩባትና ባሉባት ሀገር ተመካክሮ ችግርን አለመፍታት ተገቢ አይደለምና ሀገራችንን እንወዳለን፣ ሕዝባችንን እናከብራለን የምትሉ፣ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ያለባችሁ ሁሉ ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ እንዳይጠፋ፣ አካሉ እንዳይጐድል የሀገር ልማትና መልካም ገጽታ እንዳይበላሽ ጠላት መባባሉ ቀርቶ፣ የጦር መሣሪያ ትግል ተወግዶ፣ በእኩልነትና በመስማማት ሰላማዊ የችግር አፈታት መንገድን ተከትላችሁ በውይይትና በጥበብ ልዩነቶችን በመፍታት የተሟላ ሀገራዊ ሰላም እንዲሰፍን ታደርጉ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ከአደራ ጭምር ሐዋርያዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ በመጨረሻም የሀገራችን ኢትዮጵያና የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ሕልውና ስለማይነጣጠሉ፣ ሀገራችን በሉአላዊነቷ እንድትቀጥል የቤተ ክርስቲያናችን የአንድነት መዋቅሯ የበለጠ ተጠናክሮ፣ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮዋ ሰፍቶ፣ ለትውልድ እንድትሻገር፣ ሕዝባችን ደኅንነቱና ሰላሙ ተጠብቆ እንዲኖር ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ ሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን መምህራን፣ ካህናትና ሕዝባውያን፣ መነኰሳትና መነኰሳይያት በሙሉ በፍቅርና በአንድነት ዘወትር በመጸለይ ዘመኑ ከደረሰበት አሠራርና ጥበብ በላቀ ሁኔታ ከፍ ብለን ትውልዱን ለመዋጀት እንድንችል የበኩላችሁን እንድትወጡ በማሳሰብ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባውን አጠናቋል፡፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ አሜን! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ ምንጭ ኢኦተቤክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

1.ሁለንተናዊ ሰላምና መረጋጋት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖታዊ መሠረቷ፥ የሥርዓተ ቅዳሴዋና የምሥጢራት አገልግሎቷ አካል፣ የመንፈሳዊና ማኅበራዊ ሥምሪቷ ማእከላዊ ዐምድ በመሆኑ በግንቦት 2017 ዓ.ም. ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሠየመው የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፤ የደረሰበትንም ውጤት ለግንቦት 2018 ዓ.ም ምልዓተ ጉባኤ እንዲያቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፏል 2.በትግራይ አህጉረ ስብከት የሚገኘው ሕዝበ ክርስቲያን ሕዝባችንና ወገናችን ስለሆነ አብያተ ክርስቲያናቱና ገዳማቱም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሀብቶች በመሆናቸው፣ አህጉረ ስብከቱም የተደራጁት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በመሆኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ቀኖና ተጠብቆ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ተከብሮ፣ የመዋቅር ግንኙነቱን ወደ ቀደመ ቦታው እንዲመለስ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሰላም፣ የአንድነትና የይቅርታ በር ክፍት መሆኑን ከመግለጽ ጋር ቅዱስ ሲኖዶስ በክልሉ ለሚገኙት አባቶች፣ ካህናትና ምእመናን ያልተቋረጠ የሰላም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ የቀድሞዎቹ ቅዱሳን አባቶቻችን ዋጋ ከፍለው፣ ቀኖናዊ ሥርዓቷንና ክብሯን ጠብቀውና አስጠብቀው ፣ አንድነቷን አጽንተው ያወረሱንን አሐቲ ቤተ ክርስቲያን የቀደመ ሉዓላዊ ክብሯ እንደተጠበቀ ለመጭው ትውልድ ማስተላለፍ የበለጠ ዋጋ ያሰጣልና ቀደም ሲል ለዚሁ ጉዳይ የተሠየመው ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ሊቃውንቱ፣ ካህናቱና መላው ሕዝባችንም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ሁሉ የበኩላችሁን እንድትወጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በአጽንኦት ያሳስባል፡፡ 3.ቅዱስ ሲኖዶስ አባት እንዲመደብላቸው ጥያቄ ባቀረቡ አህጉረ ስብከት ዙሪያ የውሳኔ ሐሳብ የሚያቀርቡ ብፁዓን አባቶችን በመሰየምና ተገቢውን ውይይት በማድረግ፡ ሀ) ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የኢሉ አባቦራ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣ ለ) ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የምሥራቅ ጎጃምን ሀገረ ስብከት ደርበው እንዲመሩ፣ ሐ) ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ፣ መ) ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ የምሥራቅ ወለጋና ሆሮ-ጉድሩ ወለጋ አህጉረ ስብከትን ደርበው እንዲመሩ ሠ) በተጨማሪም የሸካ ዞን ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ተብሎ ራሱን ችሎ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋም፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ሀገረ ስብከቱን እንዲያደራጁና እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 4.ነባሩና ጥንታዊው የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገድል እንደተጠበቀ ሆኖ ገድለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሚል ያለአግባብ በአንድ ግለሰብ ተዘጋጅቶ እየተሠራጨ ያለው መጽሐፍ በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ ያለበት ግድፈትና የስሕተት ትምህርት በሙሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሰ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ የማይወክል ሆኖ በመገኘቱ ተወግዟል፤ በውስጡ የያዛቸውም የተሳሳቱ ትምህርቶች በሙሉ ተቀባይነት ስለሌላቸው መጽሐፉ ለጥናትና ምርምርም ሆነ ለማጣቀሻ አገልግሎት እንዳይውል፣ በሥርጭት ላይ የዋለው መጽሐፍ እንዲታገድና በድጋሚም እንዳይታተም፣ ለየአህጉረ ስብከቱ ሠርኩላር እንዲተላለፍ፣ የአፈጻጸም ክትትል እንዲደረግና አጠቃላይ ሁኔታው በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚዲያ እንዲገለጽ፣ የአስተምህሮ ስሕተትን በማካተት አሳትመው ያሰራጩት ግለሰብ በቋሚ ሲኖዶስ ተጠርተው እንዲጠየቁና የፈጸሙትን ስሕተት ዐውቀው ወደፊት ተመሳሳይ ስሕተት እንዳይፈጽሙ ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጣቸው፣ መጽሐፉ እንዲመረመር ያደረገው የደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳምና የገዳሙ የቅኔ መምህር መጋቤ ምሥጢር አባ ክንፈሚካኤል ወልደ ገብርኤል የምስጋና ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 5.በሰሜን ካሊፎርኒያ ኔቫዳና አሪዞና ሀገረ ስብከት የኆኅተ ሰማይ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም መንፈሳዊ ኮሌጅና የአብነት ምስክር ጉባኤ ቤት ለማቋቋም በጠየቀው መሠረት እንዲፈቀድ ሆኖ የትምህርት አሰጣጥ ፖሊሲውና ሥርዓተ ትምህርቱ፣ የሰው ኃይል አደረጃጀቱና መዋቅራዊ ተጠሪነቱ ተዘጋጅቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተጠንቶ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለግንቦት 2018 ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ 6.በምዕራብና በመካከለኛው ካናዳ የሚገኙት ሁለቱ አህጉረ ስብከት ከአሁን በፊት በ2017 ዓ.ም. በተሰጠው ውሳኔ መሠረት ያለ ጣልቃ ገብነት በየራሳቸው እንዲተዳደሩና የኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የመካከለኛው ካናዳ ኤድመንተንና አካባቢው ሀገረ ስብከት በሚል ሥያሜ እንዲስተካከል ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡ 7.በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓል ለማክበር ሄደው አዲሱን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን በመጐብኘት ላይ እያሉ አደጋ በደረሰባቸው ምዕመናን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ እግዚአብሔር አምላካች ላረፉት ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስ እንዲሰጥልን ከመጸለይ ጋር አካላዊ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች ለማሳከምና የተጎጂ ቤተሰቦችን ለመርዳት የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ ለወደፊቱም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ በሚገነቡ ሕንጻ ግንባታዎች አደጋ ከመድረሱ በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጽንዖት ያሳስባል፤ 8.በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ገዳማት ያሉት መነኰሳትና መነኰሳይያት ለአገልግሎትና ጉዳይ ለማስፈጸም ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ክብራቸውና ገዳማዊ ሕይወታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸውን እስከሚፈጽሙ ድረስ የገዳማት ኅብረቱ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል ማረፊያ የሚሆን ቦታ እንዲዘጋጅላቸው፣

የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ምልዓተ ጉባኤ መጠናቀቁን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ ጥቅምት ፲፯/፳፻፲፰ ዓ.ም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክር
የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ምልዓተ ጉባኤ መጠናቀቁን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ ጥቅምት ፲፯/፳፻፲፰ ዓ.ም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የሚመራው፣ የሐዋርያት መንበር ወራሽ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ “ወይኩን ጉባኤ ሊቃነ ኤጴስ ቆጶሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ክልዔተ ጊዜ በበዓመት ወይትናገሩ በእንተ ግብረ አብያተ ክርስቲያናቲሆሙ ወያሰስሉ ዕቅፍታተ … የሊቃነ ጳጳሳትና የጳጳሳት ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ ይሁን ስለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን ሁሉ ይነጋገሩ የሐዋርያዊ ተልእኮ መሰናክሎችንም ሁሉ ያስወግዱ” ተብሎ በመጀመሪያው የሐዋርያት ቀኖና፣ በሁለተኛው ቀሌምንጦስ በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 - ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋት ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት ሰፊ ውይይት አድርጓል፡፡ ወቅቱን ያማከሉና ዘላቂ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማዊ ሕልውና የሚያረጋግጡ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናንን የሚያስጠብቁ፣ ለምእመናን ደኅንነትና ለአገልጋዮች ሕይወት በሚጠቅሙ፣ መንሳፈዊ አስተዳደርንና ማኅበራዊ ጉዳዮችን መሠረት ባደረጉ አጀንዳዎች ላይ በመንፈስ ቅዱስ አንድነት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ በዚሁ መሠረት፡-

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የመጀመሪያ ቀን ውሎው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ ሰጠ። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በሰጠው ዕለታዊ መግለጫ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከናወነው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የጥቅምት ወር ምልዓተ ጉባዔውን ጥቅምት 11 ቀን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በመክፈቻ ጸሎት መጀመሩን አስታውሷል። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን በመወከል መግለጫውን የሰጡት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ምልዓተ ጉባዔው ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን የመጀመሪያ ቀን ጉባዔውን ያከናወነ ሲሆን 16 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቁን ገልጸዋል። በጠዋቱ ውሎ 7 ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን አጀንዳ እንዲቀርጹ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን እነዚህም ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ፣ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል እና ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ናቸው ፡፡ ኮሚቴው በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በሰብሳቢነት በብፁዕ አቡነ ዲዎስቆሮስ በአስረጂነት ተሰብስቧል። ምልዓተ ጉባኤው በከሰዓቱ ውሎም ከ16ቱ አጀንዳዎች በ4ቱ ላይ ውሳኔ የሰጠ መስጠቱን ያስታወቀ ሲሆን እነዚህም ውሳኔዎች፦ 1 ቅዱስነታቸው በጠዋቱ የመክፈቻ ጸሎት ያስተላለፉት መልዕክት በቀጣይ የሥራ መመሪያ አድርጎ ምልዓተ ጉባዔው አጽድቋል፡፡ 2 ከጥቅምት 4-10 በነበረው የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ የነበሩ የቡድን ውይይቶች በቃለ ጉባኤ ቀርቦ ቃለ ጉባዔውን ምልዓተ ጉባዔው የ2018 ዓ.ም የሥራ መመሪያ አድርጎ አፅድቋል፡፡ 3 ሀገራዊ ሰላምን አስመልክቶ ምልዓተ ጉባዔው በግንቦት ወር ተወያይቶ ሊቃነ ጳጳሳትን የያዘ ኮሚቴ ያዋቀረ ሲሆን ኮሚቴው የተሰጠውን ኃላፊነት አጠንክሮ እንዲቀጥል ተወያይቶ አጽድቋል፡፡ 4 በትግራይ የተፈጠረው ወቅታዊ ክፍፍልን አስመልክቶ የተወያየ ሲሆን በውይይቱም ሕዝቡ ሕዝባችን አብያተ ክርስቲያናቱም የቤተክርስቲያን ሀብት እንደመሆናቸው ቀደም ብሎ የተዋቀረው የሰላም ኮሚቴ ሥራውን አጠንክሮ እንዲቀጥል በምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡ ጉባዔው በነገው ዕለትም ቀጥሎ በቀሪዎቹ 12 አጀንዳዎች ላይ ውይይት ያደርጋል፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የመጀመሪያ ቀን ውሎው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ ሰጠ። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በሰጠው ዕለታዊ መግለጫ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከናወነው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የጥቅምት ወር ምልዓተ ጉባዔውን ጥቅምት 11 ቀን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በመክፈቻ ጸሎት መጀመሩን አስታውሷል። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን በመወከል መግለጫውን የሰጡት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ምልዓተ ጉባዔው ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን የመጀመሪያ ቀን ጉባዔውን ያከናወነ ሲሆን 16 አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቁን ገልጸዋል። በጠዋቱ ውሎ 7 ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን አጀንዳ እንዲቀርጹ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን እነዚህም ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ፣ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል እና ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ናቸው ፡፡ ኮሚቴው በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በሰብሳቢነት በብፁዕ አቡነ ዲዎስቆሮስ በአስረጂነት ተሰብስቧል። ምልዓተ ጉባኤው በከሰዓቱ ውሎም ከ16ቱ አጀንዳዎች በ4ቱ ላይ ውሳኔ የሰጠ መስጠቱን ያስታወቀ ሲሆን እነዚህም ውሳኔዎች፦ 1 ቅዱስነታቸው በጠዋቱ የመክፈቻ ጸሎት ያስተላለፉት መልዕክት በቀጣይ የሥራ መመሪያ አድርጎ ምልዓተ ጉባዔው አጽድቋል፡፡ 2 ከጥቅምት 4-10 በነበረው የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ የነበሩ የቡድን ውይይቶች በቃለ ጉባኤ ቀርቦ ቃለ ጉባዔውን ምልዓተ ጉባዔው የ2018 ዓ.ም የሥራ መመሪያ አድርጎ አፅድቋል፡፡ 3 ሀገራዊ ሰላምን አስመልክቶ ምልዓተ ጉባዔው በግንቦት ወር ተወያይቶ ሊቃነ ጳጳሳትን የያዘ ኮሚቴ ያዋቀረ ሲሆን ኮሚቴው የተሰጠውን ኃላፊነት አጠንክሮ እንዲቀጥል ተወያይቶ አጽድቋል፡፡ 4 በትግራይ የተፈጠረው ወቅታዊ ክፍፍልን አስመልክቶ የተወያየ ሲሆን በውይይቱም ሕዝቡ ሕዝባችን አብያተ ክርስቲያናቱም የቤተክርስቲያን ሀብት እንደመሆናቸው ቀደም ብሎ የተዋቀረው የሰላም ኮሚቴ ሥራውን አጠንክሮ እንዲቀጥል በምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡ ጉባዔው በነገው ዕለትም ቀጥሎ በቀሪዎቹ 12 አጀንዳዎች ላይ ውይይት ያደርጋል፡፡

• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት! በጐዶሎው ዓለም የምትኖር ቤተ ክርስቲያን ጉድለቷን ለመሙላት ብዙ መሥዋዕትነት ከፍላለች፤ ቤተ ክርስቲያን ለቀጣዩ ትውልድ መሸጋገርና የጐደለባትን ለመሙላት ስትል ከቅዱሳን ሐዋርያት አንሥቶ እስካለንበት ዘመን ድረስ ብዙና የብዙ ብዙ አበው ካህናትን፣ ሊቃውንትንና ምእመናንን ከደም ጠብታ፣ እስከ ቁስ ስጦታ ገብራለች፡፡ አሁን በምድር ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያን የዚህ ሁሉ ውጤት ናት፤ ቤተ ክርስቲያን እንደ ሌላው ጊዜ ሁሉ ዛሬም የጐደለባት ብዙ ነገር አለ፤ በተቻለ መጠን እርሱን ለሟሟላት መጣርና በተሻለ ሁኔታ ወደፊት ማሻገር ደግሞ የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ በዚህ ረገድ ይህ ጉባኤ ብቻው አይደለም፤ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቈጠሩ የእግዚአብሔር ልጆች ድምፁን ለመስማት ከዙሪያው ሆነው በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡ እነኝህ የእግዚአብሔር ልጆች ለመስማት ብቻ ሳይሆን ድምፁን ሰምተው ለመታዘዝም የተዘጋጁ ናቸው፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ “ሁለትም ሦስትም ሆናችሁ በስሜ በተሰበሰባችሁበት እኔ በመካከላችሁ እገኛለሁ” በማለት ጉባኤውን የመሠረተው አምላክ ከዚህ ጉባኤ መካከል አለ፡፡ በመሆኑም ይህ ጉባኤ የተወሰን አባቶች ብቻ ሳንሆን ብዙ ሰማውያንና ምድራውያን ባለድርሻ ያሉበት፣ መንፈስ ቅዱስም በመንፈስ የሚመራው እንደሆነ የማይታበል ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ጉባኤው በምድር ያለችውን የእግዚአብሔር መንግሥት በበላይነት የሚመራ ነውና፣ ያለበት ኃላፊነት ከባድና እጅግ የላቀ ነው፡፡ ጉባኤው ኃላፊነቱን በአግባቡ ሲወጣ የሚሰጠው ሽልማት ታላቅ እንደሆነ ሁሉ፣ ኃላፊነቱን በትክክል ካልተወጣ ደግሞ ተጠያቂነቱ በዚያው ልክ ከባድ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለጋል ተብሎአልና፡፡ • ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት! እኛ በአገልግሎትና በመሪነት በምንገኝበት በዚህ ዘመን ቤተ ክርስቲያን የጐደሉባት ነገሮች ብዙ ናቸው፤ ከሁሉ በላይ በውስጣችን የአንድነት ጐድለት በስፋት ይታያል፤ ለተሰየምንለት መለኮታዊ ተልእኮ አንድ ሐሳብ፣ አንድ ቃል፣ አንድ ልብ ሆነን መሰለፍ ያለመቻል ክፍተት እየተንጸባረቀ ነው፡፡ የዘመኑን ጥበብና ስልት ያልተከተለ ሐዋርያዊ ተልእኮአችንና አስተዳደራችንም ምእመናንን አላረካም፤ ክፍተቱ የሚድያ ቀለብ ከመሆንም አልፎ በጎቻችን በሌሎች እንዲዘረፉ ትልቅ በር እየከፈተ ነው፡፡ በእነዚህ ዓበይት ጉዳዮች እና በመሳሰሉት ጉድለቶቻች ላይ ፈጣን፣ ቈራጥና አዋጭ የሆነ ሥራ ካልሰራን ለወደፊት የቤተ ክርስቲያንን ህልውና ጥያቄ ውስጥ መክተቱ አይቀሬ ነው፡፡ • ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት! ቤተ ክርስቲያናችን በተጠቀሱት ችግሮች ተከባ ባለችበት ሁኔታ የሀገራችን ሰላም መቀዛቀዝ ደግሞ ሌላው ተጨማሪ ጉድለትን እያስከተለብን ነው፡፡ አማንያን የመንፈስና የሥነ ልቡና ሰላም ከማጣታቸውም በላይ አካላቸው ለሞትና ለጉዳት፤ ሃብታቸው ለዝርፊያና ለውድመት እየተዳረገ ነው፡፡ ይኽም ሁሉ ሆኖ ፍትሕን እያገኙ አይደለም፤ አብያተ ክርስቲያናትም በምእመናን ፍልሰት እየተዘጉም እየተቃጠሉም ነው፡፡ ከዚህም ሌላ የሌለን ነገር እንዳለ አስመስሎ ከየአቅጣጫው የሚወረወረው የባዕዳን ስም የማጥፋት ዘመቻ፣ የቤተ ክርስቲያኗን እምነት ከመንቀፍና ከማብጠልጠል በላይ አልፎ የቅዱሳንን ቅዱስ ሥዕል በአደባባይ እስከ መቅደድ ተደርሶአል፤ በቤተ ክርስቲያናችን ህልውና ላይ በዓላማ የተነሡ አካላት የላኳቸው እንዳሉ በሚመስል መልኩ በስመ ተሐድሶ የሚደረገው እንቅስቃሴ የኛው መለያ የሆነውን ንዋየ ቅድሳትና ልብሰ ተክህኖ፣ መዝሙርና ሥርዓተ አምልኮ በመጠቀም ቤተ ክርስቲያናችንን በአደባባይ እየተዳፈረ ይገኛል፡፡ ይህ አላስፈላጊ ተግባር የሀገሪቱን ዜጎች በእኩልነት የሚያስተዳድረውን ሕገ መንግሥት በቀጥታ የሚፃረር ድርጊት ነው፤ ሆኖም በሕግ የሚጠይቅና የሚያስቆም አካል አልተገኘም፤ እኛም ዝምታን የመረጥን መስለናል፡፡ ነገር ግን መፍትሔው ዝምታ ሳይሆን በሕግ አግባብ ነገሩን ለመፍታት መንቀሳቀስ እንደሆነ ሁሉም ሊገነዘበው ይገባል፡፡ • ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት! በዘመናችን እየተከሠተ ያለው ችግር ስንዘረዝር ውለን ብናድር መናገሩ በራሱ መፍትሔ ሊያመጣልን አይችልም፤ ጉባኤው ከዚህ በላይ መናገር እንደሚችልም እንገነዘባለን፤ ነገር ግን ለዚህ ሁሉ ችግር ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ የሚችል መደላድል ይህ ጉባኤ በዚህ ስብሰባ ሊተልም ይገባል ብለን ከአደራ ጋር ማሳሰብ እንወዳለን፡፡ በሌላ በኩል በሀገራችን ያለው ያለመረጋጋት በሕዝባችን አጠቃላይ ሥነ ልቡና በሀገሪቱ አንድነትና ዕድገት የሚያስከትለውን ጫና በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፤ የሕዝቡ ሥነ ልቡና ከተጐዳ የነገው ዕድል ጤናማ ይሆናል ተብሎ አይታሰብም፡፡ ችግሩ እየታየ ያለው በዋናነት በሀገራችን ፖለቲከኞች በመሆኑ ነገሩ የተወሳሰበና የተራዘመ እንዲሆን አድርጎታል፤ በመሆኑም ይህ የርስ በርስ ግጭት ቆሞ ችግሮች በውይይትና በድርድር በመፍታት የወንድማማች እልቂት የሚያስቆም የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል፡፡ የነገው ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን ሊሆን የሚችለው ሰላምና አንድነት ሲኖር ነውና መንግሥት፣ ተፎካካሪ ፖለቲከኞችና ነፍጥ ያነሡ ወገኖች ሁሉ ለሰላም መስፈንና ለልማት ዕድገት መረጋገጥ ሲባል ወደ መግባባት እንዲመጡ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ በመጨረሻም ዓመታዊውና ቀኖናዊው የቅዱስ ሲኖዶስ ዓቢይ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጸሎት የተከፈተ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ በእግዚአብሔር ስም እናበስራለን፡፡ እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን፤ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን፡፡ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲8 ዓመተ ምሕረት አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ • ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የ
+1
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ • ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ • ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ በአጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ ቅዱስ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፤ የጎደለብንን እየሞላ አገልግሎታችንን እያቃና ከዚህ ላደረሰን፣ ይህንን ዓመታዊና ሐዋርያዊ ጉባኤያችንን ለማካሄድም ለሰበሰበን ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ምስጋና እናቀርባለን፡፡ “ወእፌጽም ታሕጻጸ ሕማሙ ለክርስቶስ በሥጋየ በእንተ ሥጋሁ እንተ ይእቲ ቤተ ክርስቲያኑ፡- ስለ አካሉ ማለትም ስለ ቤተክርስቲያኑ ስል በሥጋዬ በክርስቶስ መከራ የጎደለውን እፈጽማለሁ” (ቈላ.፩÷፳፬) ያለንበት ዓለም በሁሉም ነገር በጉድለቱ የሚታወቅ ነው፤ ጉድለት ባይኖርና ሁሉም የሞላለት ቢሆን ኖሮ ፍጥረት እርስ በርስ የሚተረማመስበት ሁኔታ አይኖርም ነበር ወይም አሁን ባለበት ደረጃ የከፋ አይሆንም ነበር፡፡ እግዚአብሔር ሁሉንም አሟልቶ መፍጠር ወይም መስጠት የሚችል ከሃሊ አምላክ ቢሆንም፣ እሱ ባወቀ ፍጥረትን ሁሉ ጉድለት ያለበት አድርጎ ፈጥሮታል፤ በዚህም ምክንያት እያንዳንዱ ጉድለቱን ለመሙላት በሚያደርገው ፍትጊያ እየተጋጨ እርስ በርስ ሲተረማመስ ማየቱ የተለመደ ነው፡፡ ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያንም በጐዶሎው ዓለም እስካለች ድረስ ከሚመጣው ፈተና አታመልጥም፤ ይህም በመሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ ለቈላስይስ ሰዎች “የጎደለውን እፈጽማለሁ” በማለት ሲጽፍ እናስተውላለን፡፡

የ፵፬ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ታዳሚዎች ፮ ምድብ በመፍጠር የጋራ ውይይት አደረገ። በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የታደመው ዓለም አቀፍ መንፈሳዊ ሰበካ ጉባኤ ሰሞኑን የመላው አህጉረ ስብከት ሪፖርትን ሲያደምጥ ቆይቶ በዛሬው ዕለት በቅዱሳን ፓትርያርኮች በተሰየመ በቡድን አማካኝነት በሚከተሉት አጀንዳዎች ላይ ውይይት አድርጓል። ለዐርባ ዐራተኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ ጉባኤ ስብሰባ ለውይይት የቀረቡ የውይይት እና የትኩረት ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው: 1. በሀገራዊ ሰላምና መረጋጋት፣ ለቤተ ከርስቲያን ጠንካራ አንድነት፣ ለሕዝብ ትሥሥርና ማኅበራዊ መስተጋብር ሐዋርያዊ ተልእኮን መሠረት ያደረገ የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ ሚና እንዴት ይገለጻል? 2. ሐዋርያዊ ተልእኮ ያለ ምንም ገደብ ተደራሽ እንዲሆን፥ የቤተ ክርስቲያንን ተቋማት (አጥቢያ፥ ገዳም፥ የቅርስ ማእከል፥ ጉባኤ ቤቶች፥ የልማት ተቋማት) ህልውና እንዴት ይጠበቅ፥ የዘመኑን ተግዳሮት ተቋቁሞና አጣጥሞ ለማሻገር ምን ይደረግ? 3. ቅዱሳት መጻሕፍትን፣ ከብረ ከህነትን፣ ንዋያተ ቅድሳትን፣ አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያንን ሀብትና ክብር ከመጠበቅ አንጻር ምን መደረግ አለበት? 4. የቤተ ከርስቲያን አስተዳደር አሠራር እጅግ ዘመናዊና ዘመን ተሻጋሪ ቢሆን ፥ መዋቅራዊ ትስስር እንዲጠናከር፣ የሀብት ብከነት፥ የመልካም አስተዳደር እጦት ማረም እንዲቻል ያለው ጠቀሜታ እንዴት ተግባራዊ ይሁን? 5. የቅድስት ቤተ ከርስቲያን ማኅበራዊ ዘርፎቿን ለማጠናከርና የራስ አገዝ የልማት አውታሮችን ለማሳደግ ያሉት ተግዳሮቶችና ስኬቶች ምንድን ናቸው? ችግሮቹን ለማስተካከል ምን ይደረግ? 6. የዘመናዊ ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ከወቅቱና ከቤተ ክርስቲያን ህልውና፥ ሐዋርያዊ ተልእኮ፥ አስተዳደራዊ መዋቅር አንጻር ምን ያስፈልጋል፥ ምን ይደረግ? በውይይቱ ከእያንዳንዱ ምድብ ዘርፈ ብዙ ጭብጦችና ጠቃሚ ሐሳቦች የተነሱ ሲሆን እነዚሁኑ ሐሳቦች የምድብ መሪዎች በየተራ እየተነሱ በተብራራና በተረዳ መልኩ ለጉባኤው ገለጻ አድርገው ጉባኤው በቀረበው ሐሳብ ላይ መስማማቱን የሚገልጽ ድጋፍ ሰቷቸዋል። በመቀጠልም ጉባኤው በቆይታው የተወያየባቸውን ሐሳቦች በመመርኮዝ የጋራ አቋም መግለጫ አውጥቶ የእለቱ መርሐግብር የተጠናቀቀ ሲሆን በነገው እለት መልካም አፈጻጸም ላስመዘገቡ አህጉረ ስብከት የሽልማት መርሐግብር ተካሂዶ የ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም. ፵፬ኛው ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በነገው ዕለት ይጠናቀቃል። ምንጭ EOTCPR የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤውን ጥቅምት 02/2018 ዓ.ም በም/ሸዋ ሀ/ስብከት አዳራሽ
+5
የምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት  የሰንበት ትምህርት ቤቶች  አንድነት  የ2017ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤውን ጥቅምት 02/2018 ዓ.ም በም/ሸዋ ሀ/ስብከት አዳራሽ አካሔደ። በጠቅላላ  ጉባኤውም  የአንድነቱ የ2017 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፓርት ; የሰንበት ት/ቤት አገለግሎት ለቤተክርስቲያን እና ለሀገረ ያለው ጉልህ ሚና እና አሁናዊ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ተግዳሮቶች  በሚል ርዕስ በመ/ር ቃል ኪዳን ንጉሴ ሥልጠና  ተሰጥቷል። እንዲሁም የ2018 ዓ.ም  ዕቅድ  ቀርቦ ውይይት ተደርጎበት በጠቅላላ ጉባኤ ጸድቋል። በጠቅላላ ጉባኤውም  ክቡር መጋቤ ሐዲስ መምህር ዮሐንስ ኃየሎም የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ትምህርት ክፍል ሐላፊ ፣ ክቡር መልአከ ፀሐይ ቀሲስ እንዳለ ሐረገ ወይን የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ ክቡር ሊቀ ካህናት ቀሲስ ሻውል ታዬ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤ/ማ/ክፍል  የበላይ ሐላፊ ፣  የማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማዕከል ተወካዮች፣ የማኅበራት ተወካዮች፣ የሀገረ ስብከቱ አንድነት ጽሕፈት ቤት ተጠሪዎች ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት  ሥራ አመራር አባላት  ፣ ከየሰንበት ትምህርት ቤቶች   የተወከሉ የጠቅላላ  ጉባኤ ተሳታፊ ዓባላት እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተካሂዷል። በመጨረሻም የጠቅላላ ጉባኤ የጋራ ውሳኔዎች ቀረቦ በጉባኤው በሙሉ ድምጽ የጸደቀ ስሆን፣  የሰ/ት/ቤቶች  አንድነት  መልእክት  ተነቦ  መርሐ ግብሩ ተጠናቋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በ በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት አዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ማስጀመርያ መርሐ ግብር ተደረገ!! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የተዘጋጀው በሁሉም አህጉረ ስብከት የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች የዕድሜያቸውና በትምህርት ደረጃቸው መሠረት ተዘጋጅቶላቸው የተሰራጨው ሥርዓተ ትምህርት በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ባሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማስጀመርያ መርሐ ግብር ተካሄደ። የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶችና የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል ሐላፊ መልአከ ብርሃን ዳንኤል ነቢዩ በሀገረ ስብከቱ ስር ለሚገኙ የወረዳ ቤተ ክህነት ሠራተኞች፣ ለአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ለሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አባላት፣ ለሰብከተ ወንጌል ሐላፊዎች እና ለሰንበት ትምህርት ቤት ሥራ አመራሮች የሥርዓተ ትምህርት ምንነትን በተመለከተ እንዲሁም ዓላማውን፣ ቅዱሳት መጻሕፍትንና ትምህርተ ሃይማኖትን እንዲሁም የተማሪዎችን አካላዊ አእምሯዊ ሥነ ልቡናዊ ዕድገት መሠረት ከትምህርት ፍልስፍና መርሕ (Educational philosophy) ጋር የተገናዘበ ሆኖ መሠራቱን፣ ተፈጻሚ እንዲሆን ድርሻ ያላቸው ባለድርሻ አካላት እነማን እንደሆኑ እንዲሁም የሥርዓተ ትምህርቱ የአተገባበር አቅጣጫ ዘርዝረው በቂ ግንዛቤ ፈጥረዋል። በመቀጠል የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ምክትል ሰብሳቢ ዲያቆን አሳሳኸኝ በሥርዓተ ትምህርቱ ዙርያ የነበረውን በመንበረ ጵጵስናና ወናጎ ወረዳ ቤተ ክህነት ስር ባሉ አድባራት የነበረውን እንቅስቃሴ አጭር ዳሰሳ ያቀረቡ ሲሆን የዝግጅት ሂደቱ ምን ይመስል እንደነበር፣ የምዝገባ ሂደት፣ አኃዛዊ መረጃ (የምዝገባ)፣ ለሥርዓተ ትምህርቱ የተፈጠሩ መልካም አጋጣሚዎችን እንዲሁም የነበሩትን ተግዳሮቶች እና ወደፊት ምን ምን ሥራዎች መሠራት እንዳለባቸው አቅርበዋል። ብፁዕ አቡነ ገሪማ የሀገረ ስብከቱ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ዓባል ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን በመዝጊያ ንግግራቸው የሰንበት ትምህርት ቤቶችን እንዴት ማጠናከር እንደሚቻል በሰፊው አስረድተው የሰንበት ትምህርት ቤት ዓባል መሆን የሚያስገኘውን መልካም ነገር እንዲሁም ሰንበት ትምህርት ቤት በሚጠበቀው ልክ እንዳያድግ ማነቆ የሆኑትን ነገሮች በመጥቀስ እንዲስተካከል መመሪያ አስተላልፈው በጸሎት ተፈጽሟል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ማኅሌተ ጽጌ "አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ። የዜማ ጊዜም ደረሰ።" መኃ 2:12 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Yo
ማኅሌተ ጽጌ "አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ። የዜማ ጊዜም ደረሰ።" መኃ 2:12 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

የጥናት ግብዓት መረጃ ስለመጠየቅ በሰንት ት/ቤቶች አንድነት ሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሥራ እና በኑሮ ምክንያት በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ተገኝተው መማር ለማይችሉ እና ቤተ ክርስቲያን ባልተ
የጥናት ግብዓት መረጃ ስለመጠየቅ በሰንት ት/ቤቶች አንድነት ሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሥራ እና በኑሮ ምክንያት በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ተገኝተው መማር ለማይችሉ እና ቤተ ክርስቲያን ባልተመሠረተችባቸው ሀገሮች ለሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ትምህርቱን ተደራሽ ለማድረግ የቨርችዋል እና የርቀት ትምህርት ሥርዓት በማዘጋጀት ላይ በመሆኑ ለዝግጅቱ ተጨማሪ ግብዓቶችን ለመሰብሰብ ይረዳ ዘንድ ይኽን መጠይቅ ማዘጋጀት አስፈላጊ ኾኖ ተገኝቷል። ስለዚኽ በግል፣ በቤተሰብና እና በጽዋ ማኅበር በኩል የትምህርቱን አገልግሎት ማግኘት የምትፈልጉ ኹሉ ቀጥሎ በቀረበው ሊንክ ላይ በምታገኙት ቅጽ መሠረት መረጃችሁን እንድትልኩ በአክብሮት እንገልጻለን፡፡ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የጥናት-ግብዓት-መረጃ-ስለመጠየቅ/ 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

የጥናት ግብዓት መረጃ ስለመጠየቅ በሰንት ት/ቤቶች አንድነት ሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሥራ እና በኑሮ ምክንያት በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ተገኝተው መማር ለማይችሉ እና ቤተ ክርስቲያን ባልተ
የጥናት ግብዓት መረጃ ስለመጠየቅ በሰንት ት/ቤቶች አንድነት ሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር በሥራ እና በኑሮ ምክንያት በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ተገኝተው መማር ለማይችሉ እና ቤተ ክርስቲያን ባልተመሠረተችባቸው ሀገሮች ለሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን ትምህርቱን ተደራሽ ለማድረግ የቨርችዋል እና የርቀት ትምህርት ሥርዓት በማዘጋጀት ላይ በመሆኑ ለዝግጅቱ ተጨማሪ ግብዓቶችን ለመሰብሰብ ይረዳ ዘንድ ይኽን መጠይቅ ማዘጋጀት አስፈላጊ ኾኖ ተገኝቷል። ስለዚኽ በግል፣ በቤተሰብና እና በጽዋ ማኅበር በኩል የትምህርቱን አገልግሎት ማግኘት የምትፈልጉ ኹሉ ቀጥሎ በቀረበው ሊንክ ላይ በምታገኙት ቅጽ መሠረት መረጃችሁን እንድትልኩ በአክብሮት እንገልጻለን፡፡ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የጥናት-ግብዓት-መረጃ-ስለመጠየቅ/ 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆

የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ4ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈቸናቸው አባላት አስመርቋል። የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በ2017
+4
የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት  የ4ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈቸናቸው  አባላት አስመርቋል። የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በ2017 ዓ.ም በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የ4ኛ ክፍል ተማሪዎችን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ፣ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ሥልጣናት አባ ዮሴፍ ደስታ ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ መ/ር ንጋቱ እንዲሁም የሰ/ት/ቤት ክፍል ሐላፊ ሊቀ አዕላፍ ብርሃኑ በተገኙበት ባሳለፍነው ሳምንት መስከረም 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል። በዚህ መርሐ ግብርም በተማራቂዎች ልዩ ልዩ መርሐ ግብር ሲቀርብ: ከ1-10 ለወጡት አባላት ልዩ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ክቡር ዋና ሥራ አስኪያጁ መልክት ካስተላለፉም በኋላ በብጹዕ አቡነ ዮሐንስ ቃለ ምዕዳን እና አባታዊ ምክር የሥራ መመሪያ ተሰጥቶ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website