fa
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

کانال የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 838 مشترک است و جایگاه 5 321 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 2 154 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 838 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 02 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 562 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 10 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 37.65% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.49% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 962 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 661 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 44 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 03 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

15 838
مشترکین
+1024 ساعت
+657 روز
+56230 روز
آرشیو پست ها
የመተከል ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጋር በመተባበር   በቀን 14/06/2018 ዓ.ም. ለአድባራት አለቆች ለመምህራን እና ለሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ሐላፊዎች ስልጠና ሰጠ። በእለቱ ከየወረዳ ቤተ ክህነቱ የሰንበት ትምህርት ቤት ክፍል ሐላፊ ከ39 አቢያተ ክርስቲያናት የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ እና መምህራን በተገኙበት ስለ ኢ/ኦ/ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ሁኔታ ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አደረጃጀት እና አወቃቀር  እንድሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህት ምንነት እና ትግበራ ዙሪያ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 11:00 ድረስ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተላከው መምህር ያሬድ ዮናስ አማካኝነት ሥልጠናው ከተሰጠ በኋላ በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይትምተደርጓል። በዕለቱ የመተከል ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መ/ም/ኅሩይ ብሩ እና የሰንበት ክፍል ሐላፊ ቀሲስ ንብረት እጅጉ የውይይት መርሐ ግብር ያደረጉ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይ ጥያቄ እና መልስ ከተደረገበት በኋላ ለሥልጠና መርሐ ግብሩ  መሳካት አስተዋፅዖአቸው ለላቀ አካላት እና ለሥልጠናው ተሳታፊዎች  የእውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል። በመጨረሻም ሠልጣኞች ወደ አጥቢያቸው እንደተመለሱ ሰንበት ትምህርት ቤትን በማጠናከር ሥርዓተ ትምህርቱን እንዲያስቀጥሉ በወረዳ ደረጃ የሰንበት ትምህርት ቤትን በማቋቋም ደረጃ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ አፅዕኖት በመስጠት አባታዊ መመሪያ ሰጥተው የዕለቱ መርሐ ግብር በጸሎት ተጠናቋል። መረጃው የመተከል ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

#አስተርዕዮ_ማርያም "ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።" ራዕ 12፡1 እንኳን
#አስተርዕዮ_ማርያም "ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።" ራዕ 12፡1 እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት በዓል (አስተርዕዮ ማርያም) በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

#ጥምቀት "ክርስቶስ ተወለደ፤ ክርስቶስ ተጠመቀ፤ እኛንም ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ዳግመኛ ወለደን።" ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበ
#ጥምቀት "ክርስቶስ ተወለደ፤ ክርስቶስ ተጠመቀ፤ እኛንም ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ዳግመኛ ወለደን።" ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

#ከተራ "ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።" ማቴ 3:13 እንኳን ለከተራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁ
#ከተራ "ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።" ማቴ 3:13 እንኳን ለከተራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

"የባሕርይ ገዥ ክርስቶስ ከዕለት ከሰዓት አስቀድሞ የነበረ ሲሆን የሰዎችን ልደት ዛሬ ተወለደ።" ሃይማኖተ አበው የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ የሐዋርያት ደቀ መዝሙር የነበረ አጢፎስ በሃይማኖተ አበው ላይ የልደትን ነገር በተናገረበት ድርሳኑ ይህን መሰከረ። ክርስቶስን የባሕርይ ገዥ ጌታ አለው። ሌሎች ገዥ ቢባሉ በጸጋ በስጦታ፤ ሌሎች ጌታ ቢባሉ የምድር፤ ሌሎች ገዥ ቢባሉ በጊዜ የሚገደብ፤ በዘመን የሚወሰን ነው። ለእርሱ ግን ጌትነትን የሚሰጠው ሰጪ አልያም የሚወስድበት ወሳጅ የሌለበት የባሕርይ ገንዘቡ ነውና የባሕርይ ገዢ አለው። ዮሐ 13:13 ከዕለትና ከሰዓት አስቀድሞ ነበርም አለው። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመናት የማያረጅ እንዲሁም በጊዜ የማይወሰን ከ ብሎ መጀመርያ እስከ ብሎ መጨረሻ የሌለው ቀዳማዊ ድኃራዊ ነውና ከዕለት ከሰዓት አስቀድሞ የነበረ ብሎ መሰከረ። ዮሐ 1:1 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በመልእክቱ ቀዳማዊነቱን ሲናገር "በሰማይና በምድር ያለው ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ከፍጥረት አስቀድሞ #በኩር ነው። ሁሉ በእርሱ ለእርሱ ተፈጥረዋል።" ብሎ የዘመናት ፈጣሪ ከዘመን አስቀድሞ የነበረ አምላክ መሆኑን መሰከረ። ቆላ 1:15 ጌታ በወንጌል ዓለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር የነበረ መሆኑን ሲናገር እንዲህ አለ። "አባት ሆይ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ።" አለ። ዮሐ 17:5 ይህ የባሕርይ ገዥ ከዕለት ከዓመት ከዘመናት አስቀድሞ የነበረ አምላክ ልዑል እግዚአብሔር የሰዎችን ልደት ዛሬ ተወለደ ተባለ። እንዴት የሚደንቅ እንዴትስ የሚረቅ ምሥጢር ነው??? ሥጋ ያልነበረ በመለኮቱ ጥንት ያልነበረው እርሱ ጥንት ያለውን ሥጋ ስለምን ተዋሐደ? አይታይ የነበረው አምላክ የሚታይ ሥጋን ተዋሕዶ ስለምን ታየ? ስለምንስ ተዳሰሰ? በባሕርይው የማይወሰንና ሰማይ ዙፋኑ ምድር የእግሩ መረገጫ የሆነ አምላክ ስለምን በድንግል ማኅጸን አደረ? የማይሰጡት ቸር የማያበድሩት ባለጠጋ ሲሆን ስለምን በከብቶች በረት ተጣለ? ሰማይን በደመና የሚሸፍን በከዋክብት የሚያስጌጥ እርሱ ስለምን በጨርቅ ተጠቀለለ? ለዚህ ሁሉ መልሱ ሰው ወዳጅ የሆነ እግዚአብሔር የሰው ልጅን ፍጹም ቢያፈቅረው አይደለምን? ሰው ሰውን ቢወድ ነቅ ፈልጎ ምክንያት አበጅቶ ነው። እግዚአብሔር ግን ሰውን የወደደው እንዴት ነው ቢሉ እንዲሁ ያለምክንያት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ነው። እንደውም መወደድ የሚገባን ሆነን ሳለን እንኳን አይደለም። ስንጠላው ወደደን ስናምጽና ስንርቀው ቀረበን ስንበተን ሰበሰን ጠላቶቹ ሳለን ነፍሱን ስለኛ ቤዛ ሰጥቶ ታረቀን። ዮሐ 3:16 ሮሜ 5:10 የነገሥታት ንጉስ በትሕትና ከሰማይ ከመንበሩ ወርዶ ፍቅሩን ከገለጸልን እኛማ ምን ያህል ልንዋረድ ምን ያህልስ ልንዋደድ ይገባል? ይቆየን። መልካም የልደት በዓል ይሁንልን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube https://www.youtube.com/@eotc-gssu 👉 Facebook https://www.facebook.com/gssu.eotc 👉 Telegram https://t.me/eotcgssu21 👉 Tiktok https://www.tiktok.com/@eotc_gssu 👉  Website https://eotc-gssu.org/a/

እንኳን ለእመቤታችን ወደ መቅደስ የገባችበ በዓል (በዓታ ለማርያም) በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት
እንኳን ለእመቤታችን ወደ መቅደስ የገባችበ በዓል (በዓታ ለማርያም) በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ጽዮን ማርያም እንኳን አደረሳችሁ! “እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ፦ ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ።” መዝ 13
ጽዮን ማርያም እንኳን አደረሳችሁ! “እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ፦ ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ።” መዝ 131፡13-14 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

ቅዱስ ሚካኤል ሚዛን ይዞ መሣሉ፥ በፍርድ ቀን ሱታፌ እንዳለው ያስገነዝበናል። ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ እንደ ዘገበው፥ ጌታችን ዳግመኛ የሚመጣው ከቅዱሳን መላእክት ጋር ነው፦ ማቴ ፲፮፥፳፯ “የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና፤ ያን ጊዜም ለሁሉ እንደ ሥራው ያስረክበዋል።” እንዲል፡፡ በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት አተረጓጐም መሠረት “መጽሐፍ ስም ካልጠራ ማብዛት ልማዱ ነው” እናም እዚህ ጋር እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደ ምድር አሸዋ የበዙትን ቅዱሳን መላእክትን ብቻ ለመጥቀስ ብቻ ሳይሆን አለቃቸውን ቅዱስ ሚካኤልን ለማውሳትም ጭምር ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ይህን የሚደግፍ ነገር ጽፎልናል፦ ፩ኛ ተሰ ፬፥፲፮ “ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክት አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና” በእርግጥም አለቃውን ትቶ ስለ ጭፍራው ብቻ መናገር ግር የሚያሰኝ ነገር ነው። በዘመን ፍጻሜ ስለሚከሰተው ነገር ራእይ የተመለከተው ነቢዩ ዳንኤልም ቅዱስ ሚካኤል በዚህ ወቅት ስለሚያደርገው ተግባር ፍንጭ ሰጥቶናል፡ “በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል” (ዳን ፲፪፥፩) እነዚህን ሁሉ ማስረጃዎች ግልጽ በሆነ ቋንቋ የሚያረጋግጥ ቃል በድርሳነ ሚካኤል ውስጥ ተጽፎ የምናገኝ ሲሆን ቃሉም፦ “ወለጻድቃንሰ ውሉደ ጥምቀት እለ የአምኑ ፍጹመ ትንሣኤ ሙታን ያበውኦሙ ውስተ ገነት ወኀበ ክርስቶስ ወያዓርጎሙ ኀበ አብ ወይትፌሣሕ በእንቲአሆሙ ወበእንተ ዘወሀቦ ሢመተ ለሚካኤል ሊቀ መላእክት ከመ ይፍርድ ላዕለ ሕያዋን ወሙታን” (ትንሣኤ ሙታንን የሚያምኑ በጥምቀት የተወለዱ ጻድቃንን ግን ወደ ገነት ያስገባቸዋል፤ አብም ልጁ ክርስቶስ ወዳለበት ያሳርጋቸዋል፤ ስለ እነርሱ እና ለቅዱስ ሚካኤል በሕያዋን እና በሙታን ላይ ይፈርድ ዘንድ ስለሰጠው ሹመት ደስ ይለዋል፡፡) ይህም የቅዱስ ሚካኤልን ፈራጀነት የሚገልጽ ነው፡፡ #2. “ሰላም ለመልክዕከ ዘኢይጤየቅ ለዓይንነ ኆኅያቲሁ ርብዓ በከመ ርኢነ” (በአራቱ መዓርገ ኆኅት እንደተመለከትነው በዓይን ታይቶ ለማይመረመር መልክህ ሰላም እላለሁ።) አራቱ መዓርገ ኆኅት የት ነው? መች ነው የተመለከትነው? አራቱ ኆኅያት የተባሉት <መልክዕ> የሚለው ቃል ፊደሎች ብዛት ናቸው። ኆኅያት ማለት የፊደል ደጅ ማለት ነውና። ከዚህ አተረጓጐም ጋር የሚመሳሰል መልክዕ በማኅሌተ ጽጌ ላይ ተጽፎ ይገኛል። “ዝንቱ መስቀል መንበረ ነበልባል ዘኪሩቤል ቢጽ፤ አምሳለ ስምኪ ድንግል ርቡዐ ኆኅያት ወገጽ” (ድንግል ሆይ፥ የኪሩቤል ቢጤ፣ የነበልባል ዙፋን የሆነው ይህ መስቀል እንደ ስምሽ አራት ፊደል እና ገጽ ነው) [ማለትም <ማርያም> እና <መስቀል> የሚሉት ስሞች አራት ፊደል ናቸው] “እንደ ተመለከትነው” ማለት ደግሞ እንደምናነበው፣ እንደምናየው ማለት ነው። ይህንን መልክዕ በተለየ ሁኔታ ስንገልጸው “እንደምናየው ኆኅያቱ (ፊደሎቹ) አራት ለሆኑ፣ በዓይንናችን ለማይመረመረው መልክዕህ ሰላም እላለሁ” ይሆናል። #3. ቅዱስ ሚካኤል ለምን ክነፈ ርግብ ይባላል? ይህንን የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤልን ተራዳኢነት ለመግለጽ ቤተክርስቲያን ‹‹ክነፈ ርግብ›› ብላ ትጠራዋለች፡፡ የድርሳኑ ፀሐፊ በተራዳኢነቱ ነፍሳትን በክንፎቹ ከሲዖል እሳት ዲን እንዲያወጣ፦ “ወውእቱ ሚካኤል ይጸውሮ በክነፊሁ ብሩሃት ወያዐድዎ ባሕረ እሳት ወያበውኦ ውስተ መንግሥተ ሰማያት ወኀበ ኩሉ መዝገበ ብርሃን” (እሱ ቅዱስ ሚካኤል በብርሃን ክንፎቹ ተሸክሞ ባሕረ እሳትን አሻግሮ ወደ መንግሥተ ሰማያትና የብርሃን ድንኳን ወዳለበት ያገባዋል) በማለት ይናገራል፡፡ መልአኩ በ<ክንፉ ይበራል> ሲባልም ለዓለም መዳን የሚፋጠን መሆኑን ያሳያል። “ይሠርር ለመድኃኒተ ኵሉ ዓለም በክልኤ ክንፍ” (ለዓለም ሁሉ መዳን በሁለት ክንፍ ይበራል) እንዲል፡፡ #4. “....ቀዊመከ አንተ በምሥዋዓ ሰማይ ሳብዕ...” (....በሰባተኛው ሰማይ የመሠዊያ አዳራሽ ቆመህ...) የተባለው ምንድን ነው? የትኛው ነው? እዚህ ጋር መሠዊያ የተባለው ሰባተኛው ሰማይ ጽርሓ አርያም ነው። ቅዱስ ሚካኤል በኅዳር ፲፪ ቀን ወደዚህ ሰማይ ገብቶ ለኃጢአተኞች ምሕረትን እየለመነ ይሰግዳል። ‹‹ወእምዝ ይበውእ ኀበ መንጦላዕቱ ለአብ ማር ሚካኤል ሊቀ መላእክት ወይሰግድ ታሕተ መንበሩ ለአብ በይእቲ ዕለት በእንተ ምሕረቱ ሰማያዊት ወምድራዊት›› (ከዚህ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል ወደ አብ መጋረጃ ውስጥ ይገባል በዚች ዕለት ምድራዊትና ሰማያዊት ስለሆነች ምሕረቱም ከመንበሩ በታች ይሰግዳል) እንዲል። ስግደቱም የሚቀርበው ኃጢአተኞች ሥርየትን እስኪያገኙ ድረስ ነው። “ይሰግድ በብረኪሁ እስከ ይመጽእ ሥርየት ለኃጥአን” (ለኃጢአተኞች ሥርየት እስከሚመጣ ድረስ በጉልበቱ ይሰግዳል) እንዲል፡፡ እነዚህ የመልአኩ ክንፎች ባለ መልክኡ ‹‹ሰላም እብል ለአክናፊከ ስፉሐት ምስካቤ ኵሉ ፍጥረት …..›› (ሚካኤል ሆይ የፍጥረታት ሁሉ መጠለያ ለሆኑ አክናፎችህ ሰላም እላለሁ፡፡) እንዳለው የፍጥረታት መጠለያ ብቻ ሳይሆኑ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የክብሩ መገለጫዎችም ጭምር ናቸው፡፡ ይህንንም በአባታችን ፍስሐ ፅዮን( አቡነ ተክለ ሃይማኖት) ታሪክ ውስጥ የምናየው ነው፡፡አባታችን ገና ሕፃን ሳሉ ዲቁናን ተቀብለው በፍቅርና በንጽሕና በማገልገል ጎለመሱ፡፡ ባደጉም ጊዜ ለአደን ወደ ዱር ሲሄዱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጎልማሳ ሰው አምሳል ሆኖ በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ክንፍ ላይ ተገልጦ አራዊትን ሳይሆን የኃጢአተኞችን ነፍስ ወደ ሕይወት የሚያጠምድ እንደሚሆን ነግሮታል፡፡ ‹‹ወበ ጊዜ ቀትር አስተርአዮ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት በዲበ ክንፉ ለቅዱስ ሚካኤል በአምሳለ ወሬዛ ዘሠናይ ላህዩ›› እንዲል፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር! መልካም በዓል! የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! #1. ቅዱስ ሚካኤል ሥዕሉ ላይ ሚዛን ይዞ የሚታየው ለምንድን ነው? ከዚህ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ የመልአኩ ሥዕላት ላይ መልአኩ ሚዛን ይዞ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! #1. ቅዱስ ሚካኤል ሥዕሉ ላይ ሚዛን ይዞ የሚታየው ለምንድን ነው? ከዚህ ጋር በተያያዘ በአንዳንድ የመልአኩ ሥዕላት ላይ መልአኩ ሚዛን ይዞ ተስሎ እናገኛለን፡፡ ይህም የመልአኩን ፈራጀነት የሚገልፅ ነው፡፡ ሚዛን በቅዱሳን መጻሕፍት የፍትህ ወይም የፍርድ ምልክት ነው፡፡ ምንም እንኳን የቴክኖሎጂ አብዮቱ፥ የዘመኑን የክብደት መለኪያ መሣሪያዎችን ይዞልን ቢመጣም፤ በግብይት ሥርዓት የሚገኙ ነጋዴዎችና ደንበኞች የተለያዩ ቁሶችን በሚዛን ግራና ቀኝ ላይ በማስቀመጥ የትኛው በክብደት እንደሚበልጥ ለመለየት ሲጠቀሙበት እናስተውላለን። የፍርድ ጉዳይም በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በዚህ ምሳሌነት ቀርቦ እንመለከታለን። ለምሳሌ ያህል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተሰጣት ቃልኪዳን የዳነው የ<በላዔ ሰብእ> ወይም ስምዖን ታሪክ ማሳያ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስም ጥበበኛው ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ፍርድ በሚዛን ምሳሌነት ይናገራል፦ ምሳ ፲፮፥፲፩ “እውነተኛ ሚዛንና መመዘኛ የእግዚአብሔር ናቸው፤ የከረጢት መመዘኛዎች ሁሉ የእርሱ ሥራ ናቸው።” እንዲል።