fa
Feedback
FM 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ

FM 94.7 የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ

رفتن به کانال در Telegram

የትምህርት ሬዲዮ ጣቢያ

نمایش بیشتر
2 769
مشترکین
+124 ساعت
-117 روز
-2730 روز
آرشیو پست ها
በት/ቤት ይዞታ ማረጋገጫና ግንባታ ዙሪያ ልዩ የሬድዮ ዝግጅት

6461 ጎልማሶች የብርሃን ምዘና እየወሰዱ እንደሚገኝ ተገለጸ። (ሰኔ 23/2018 ዓ.ም) በበጋ ወቅት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 6461 ጎልማሶች የብርሃን ምዘና በመውሰድ ላይ ይገኛሉ፡፡ የአዲስ
+5
6461 ጎልማሶች የብርሃን ምዘና እየወሰዱ እንደሚገኝ ተገለጸ።     (ሰኔ 23/2018 ዓ.ም) በበጋ ወቅት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 6461 ጎልማሶች የብርሃን ምዘና በመውሰድ ላይ ይገኛሉ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴ ቢሮው በ2018 የትምህርት ዘመን በበጋ ወቅት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ጎልማሶች የብርሀን ምዘና በመስጠት እንደፍላጎታቸው 3ኛ ክፍል ገብተው መደበኛ ትምህርት የሚማሩበት ወይም በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ገብተው በሚመርጡት ሙያ የአጭር ጊዜ ስልጠና ወስደው ህይወታቸውን የሚመሩበት አማራጭ አዘጋጅቶ ተግባራዊ እያደረገ መቆየቱን ገልጸው፤ በዘንድሮው መርሀግብርም በክረምት ወቅት የ90 ቀን የንቅናቄ እቅድ አዘጋጅቶ እያከናወናቸው ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ ጎልማሶች በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች የትምህርት አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም ቢሮው ትምህርቱ በወጣለት መርሀግብር መሰረት በአግባቡ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን በየጣቢያዎቹ በሚያደርገው ድጋፍና ክትትል ማረጋገጡን በመጥቀስ ትምህርቱን እየሰጡ ለሚገኙ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ምስጋና አቅርበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የልዩ ፍላጎትና የጎልማሶች መሰረተ ትምህርት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገመቺስ ፍቃዱ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ 6462 ጎልማሶች በበጋ  ትምህርታቸውን ሲከታተሉ መቆየታቸውን አስታውሰው አሁን ላይ የብርሀን ምዘና እየወሰዱ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የ8ኛ ክፍል ውጤት መለቀቅን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ ሰኔ 23 ይጀምራል። (ሰኔ 22/ 2018 ዓ.ም )የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ
የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ነገ ሰኔ 23 ይጀምራል። (ሰኔ 22/ 2018 ዓ.ም )የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በ607 የፈተና ማዕከላት በስድስት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል። ለፈተናው በድምሩ 563,501 ተፈታኞች የተመዘገቡ ሲሆን፣ 306,456 የተፈጥሮ ሳይንስ እና 257,045 የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ናቸው። አገልግሎቱ ለፈተናው የሚያስፈልጉ ሁሉንም ዝግጅቶች ማጠናቀቁንና የፈተና አስፈጻሚዎችን ወደ ፈተና ማዕከላት ማሰማራቱን ገልጿል። ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከላት ሲቀርቡ የመፈተኛ መግቢያ ካርዳቸውን (Admission Card)፣ የተማሪ ወይም ህጋዊ መታወቂያ፣ በፈተና አስተዳደሩ የተፈቀደ እስክሪብቶ እና ባዶ ወረቀት ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል። ሞባይል ስልክ፣ ስማርት ሰዓት፣ ብሉቱዝ፣ ጆሮ ማዳመጫ፣ ፍላሽ ዲስክ፣ ሜሞሪ ካርድ፣ የግል ላፕቶፕ ወይም ታብሌት እና ሌሎች ያልተፈቀዱ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት አይፈቀድም። ፈተናው በበይነ መረብ በ6 ዙር የሚሰጥ ሲሆን፣ በወረቀት የሚፈተኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሐምሌ 1 እስከ 3፣ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ደግሞ ከሐምሌ 6 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚፈተኑ ተገልጿል። የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም ተፈታኞች መልካም እድል እየተመኘ፣ ፈተናውን በመረጋጋት፣ በሥነ ምግባር እና በራስ መተማመን እንዲወስዱ ጥሪ አቅርቧል።

አያይዘውም የዘንድሮው ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ ያስችላል ብለው ለተማሪዎች ፣ ወላጆች ፣ ለትምህርት ቤቶችና መምህራን እንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል:: ተማሪዎች ውጤታችሁን የማስፈንጠሪያዉን በመጫን መመልከት ትችላላችሁ https://aa.ministry.et/#/result

በ2018 የትምህርት ዘመን በ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና 95.85% ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት አስመዘገቡ፡፡ (ሰኔ 22/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት
+4
በ2018 የትምህርት ዘመን በ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና 95.85% ተማሪዎች 50 እና ከዛ በላይ ውጤት አስመዘገቡ፡፡ (ሰኔ 22/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤትን ይፋ አድርጓል:: የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ውጤቱ ይፋ በተደረገበት ወቅት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የከተማ አስተዳደሩ የትምህርት ጥራትን በሚፈለገው ደረጃ ለማድረስ በልዩ ሁኔታ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ የሚገኝና ከዚህ አኳያ ባለፉት አመታት በከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ላይ የታየውን ውጤት በመመልከት ዘንድሮ በ2018 የትምህርት ዘመን የተመዘገበዉን የላቀ ውጤት በማነጻጸር የትምህርት ማህበረሰቡ በትምህርት ልማት ስራዉ ላይ የተከናወኑ ተግባራት ያስመዘገቡትን ውጤት እንዲያውቅና ለቀጣይ ጉልበት በመሆንና የፉክክር መንፈስን በመፍጠር ሀገር የሚገነባ ትውልድ የመፍጠሩ ስራ ግቡን እንዲመታ ቢሮው በትኩረት እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል:: የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ አንዱ አመላካች የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ውጤት መሆኑን የገለፁት ዶክተር ዘላለም 95.85% ወደ ቀጣዩ የትምህርት ደረጃ 50 እና ከዛ በላይ ውጤት በማምጣት ማለፋቸውን ተናግረው ለውጤቱ መመዝገብ የከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ስራዉ ልዩ ትኩረት መስጠቱ ፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሀ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉ ፣ የሂሳብና እንግሊዘኛ ትምህርት ስትራቴጂ ተደንፎ በትኩረት መሰራት መቻሉ ፣ የመማሪያና የማስተማሪያ ግብዓቶች መቅረባቸው እንዲሁም ከትምህርት ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መሰራቱ ተጠቃሽ መሆናቸውን አብራርተዋል::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን በዛሬው እለት ወስነዋል። (ሰኔ 22/
+3
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን በዛሬው እለት ወስነዋል። (ሰኔ 22/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በ2018 የትምህርት ዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ ከፍተኛ ዉጤት መመዝገቡን ጠቅሰው የተመዘገበው ውጤት አበራታች መሆኑን ተናግረዋል። ዶክተር ዘላለም አያይዘውም በ2018 ዓ.ም የሒሳብና እንግሊዘኛ ትምህርትን ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረገው ስትራቴጂ በተማሪዎች ውጤት መረጋገጡን በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ዘርፉ ላይ ባደረገው ትኩረት ውጤቱ መመዝገቡን ተናግረው ፈተናውን በአጭር ጊዜ በማረም ውጤቱ ይፋ እንዲሆን ቀን ከሌት ሲሰሩ ለቆዩ የፈተና ክፍል ባለሙያዎችና ሂደቱን ሲደግፉ ለነበሩ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም 85,737 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አበራ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ የቅድመ አንደኛ ትምህርትን ውጤታማ ለማድረግ መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ ለተቋማ
+3
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ አበራ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ የቅድመ አንደኛ ትምህርትን ውጤታማ ለማድረግ መንግስት ከፍተኛ በጀት በመመደብ ለተቋማቱን ግብዓት ከማቅረብ ጀምሮ ለመምህራን ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰው ፤ በደብረ ብርሀን አሰላ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ተምረው በዛሬው እለት የተመረቁ መምህራንም የዚሁ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን በመግለጽ ለተመራቂዎች መልካም እድል ተመኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ከትምህርት ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑን የማህበሩ ፕሬዘዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ ገልጸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከሁለቱ ኮሌጆች ጋር በጋራ በመሆን መምህራኑን አሰልጥኖ በማስመረቁ በማህበራቸውና በተመራቂ መምህራን ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በደብረብርሀንና አሰላ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ያሰለጠናቸውን 2,349 የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራንን አስመረቀ። (ሰኔ 20/2018 ዓ.ም) በአድዋ
+7
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በደብረብርሀንና አሰላ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጆች ያሰለጠናቸውን 2,349 የቅድመ አንደኛ ደረጃ መምህራንን አስመረቀ። (ሰኔ 20/2018 ዓ.ም)  በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው የምርቃት መርሀ ግብር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ስትራቴጂክ ካውንስል አባላትን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት አመራሮች፣የሁለቱ ኮሌጆች ዲኖችና መምህራን  እንዲሁም የተመራቂ ቤተሰቦችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊና የመርሀግብሩ የክብር እንግዳ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ባስተላለፉት መልዕክት በከተማ አስተዳደሩ የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምን ተግባራዊ በማድረግ አዲስ አበባ ህጻናትን ለማሳደግ ምቹና ተመራጭ አፍሪካዊት ከተማ ለማድረግ እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ በጨዋታ የማስተማር ስነ ዘዴን ተግባራዊ በማድረግ በተማሪዎቹ ሁለንተናዊ እድገት ላይ መስራት መሆኑን አመላክተዋል። ኃላፊው  አያይዘውም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ህጻናቱ ለቀጣዩ የትምህርት ደረጃዎች መሰረት የሚጥሉበት የትምህርት እርከን እንደመሆኑ በዛሬው እለት የተመረቁ መምህራን በኮሌጆቹ በነበራቸው ቆይታ ባገኙት ዕውቀትና ክህሎት መሰረት በጨዋታ የማስተማር ስነዘዴን በአግባቡ በመተግበር ተማሪዎችን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባቸው ገልፀው ኮሌጆችን ጨምሮ ለመርሀግብሩ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። (ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገ
+1
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። (ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል። ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል።

የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። (ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገ
የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጋል። (ሰኔ 13/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሠረት በኦንላይን (Computer-based Testing (CBT) የሚፈተኑ ተፈታኞ በስድስት ዙር የሚፈተኑ ሲሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ይፈተናሉ። ከአራተኛ እስከ ስድስተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች የሚፈተኑ ይሆናል። ፈተናውን በወረቀት የሚፈተኑ ተፈታኞች የተፈጥሮ ሳይንስ በሶስተኛ ዙር ላይ የሚፈተኑ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ በአራተኛ ዙር በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚፈተኑ ይሆናል።

QOPHI QORMAATAA 9.10.MB.ABEEBOOCH FIREE.mp336.30 MB

በቴክኖሎጂ የታገዘና ወቅቱን የጠበቀ እቅድ አዘገጃጀት ስልጠና