2 753
Suscriptores
+1424 horas
+167 días
-930 días
Archivo de publicaciones
የትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ ምደባን ይፋ አደረገ።
የትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ወደ ዩኒቨርሲቲዎች የመመደብ ሂደቱን ፍትሐዊነት፣ ግልጽነትና እኩል ዕድልን ባረጋገጠ መልኩ ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።
ምደባው የተማሪዎችን ውጤት፣ ምርጫ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ቅበላ አቅም፣ የፆታ ሚዛን እንዲሁም የህብረ ብሔራዊነት ስርጭትን ታሳቢ ያደረገ ነው ተብሏል።
በዚህም 500 እና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎች በመጀመሪያ ምርጫቸው የተመደቡ ሲሆን፣ ማየትና መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች ደግሞ አስፈላጊው ድጋፍ በሚደረግላቸው ዩኒቨርሲቲዎች መመደባቸውን
ተማሪዎችም የተመደቡበትን ዩኒቨርስቲ ለመመልከት በዚህ ሊንክ https://student.ethernet.edu.et/view-placementመመልከት እንደሚችሉ የትምህርት የሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል።
በምደባው ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች ደግሞ ቅሬታቸውን ለዚሁ ሲባል በተዘጋጀው የኦንላይን ሥርዓት ብቻ https://student.ethernet.edu.et/complaints ይህ ምደባ ይፋ ከሆነበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ አስፈላጊውን መረጃና ማስረጃ በማያያዝ እንዲያቀርቡ ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡
በአካል ወደ ተቋሙ በመምጣት የሚቀርብ የምደባ ቅሬታ የማይስተናገድ መሆኑን የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ በተጨማሪም የተሳሳተ ማስረጃ ወይም የተጭበረበረ ሰነድ ማቅረብ በፍጹም የተከለከለ መሆኑን ተማሪዎችና ወላጆች እንዲገነዘቡ አሳስቧል፡፡
በመላው ሀገራችን ለሚገኙ ተማሪዎቻችን አዲሱ የትምህርት ዘመን ስኬታማ እንዲሆን እንመኛለን!
ወጣቱ ትውልድ ለኢትዮጵያ ትልቁ ሀብቷ በመሆኑ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጅማሮን ተከትሎ፤ እያንዳንዱ ተማሪ ለላቀ እውቀት በትጋትና ጉጉት ትምህርቱን እንዲከታተል፣ ለጥሩ ውጤት በጽናት እንዲተጋ፣ እንዲሁም የሀገራችንን የወደፊት ዕድል መቅረጽ በሚያስችሉ ክህሎቶች እንዲገነባ አበረታታለሁ።
ዛሬ እየተገበርነው ያለው በርካታ የልማት ሥራዎች የነገን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ በመሆናቸው፣ የዚህ ቀጣይ ዕድል ተጠቃሚ እና ባለአደራ እንደመሆናችሁ መጠን፣ የኢትዮጵያን ታላቅ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የእናንተ ቁርጠኝነት መሠረት እንደሆነ ሙሉ እምነቴ ነው።
ብቁ እና በራሱ የሚተማመን ትውልድ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመምህራኖቻችን ትጋትና መሰጠት መሰረታዊ ምሰሶ ነው። ተማሪዎቻችንን ማነቃቃት፣ አቅማቸውን ማውጣት፣ እንዲሁም ነገ ተፎካካሪ ሆነው እንዲወጡ የሚያስችሏቸውን ዕውቀት፣ ክህሎትና እሴቶችን የማስታጠቅ አደራን ቀጥሉበት ስል በትህትና አሳስባለው።
በትምህርት ዘርፉ ውስጥ ለምትገኙ ባለድርሻ አካላት በሙሉ፤ ስኬታማ እና ፍሬያማ የትምህርት ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
የስራ ክፍሉ ባለሙያዎች ስልጠናው መደበኛ ስራቸውን በማከናወን ሂደት ሊከተሏቸው የሚገቡ ጉዳዮችን በማንሳት ተጨማሪ እውቀት እንዳገኙበት ገልጸው ስልጠናው ወቅቱን የጠበቀና ሚዲያን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችል ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡
ስልጠናው በዋናነት የዲጂታል ሚዲያና የሶሻል ሚዲያ ምንነት እና ባህሪያት ፤የዲጂታል ሚዲያ ጠቀሜታና ሊያስከትላቸው የሚችሉ ጉዳቶች እንዲሁም የሶሻል ሚዲያ ይዘት መረጣ በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ትምህርት ክፍል የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ረዳት ፕሮፊሰርና የእቅድና ጥናት ክፍል ኃላፊ በሆኑት ዶ/ር ፈይሳ ግርማ አማካኝነት ተሰጥቷል፡፡
+5
በሶሻል ሚዲያ እና ዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀምና ይዘት መረጣ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
(ጷግሜ 3/2018 ዓ.ም) የሚዲያ ይዘት ማበልፀግና ስርጭት ዳይሬክቶሬት በስራክፍሉ ለሚገኙ ባለሙያዎች በሶሻል ሚዲያ እና ዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀምና ይዘት መረጣ ላይ ትኩረት ያደረገ አቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጠ፡፡
የሚዲያ ይዘት ማበልፀግና ስርጭት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ የውብዳር አያሌው በሶሻል ሚዲያ እና ዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀምና ይዘት መረጣ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ትክክለኛ መረጃ ለማሰራጭት ያለው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ መሆኑን ገልጸው ፤ የሚዲያ ይዘት ዳይሬክቶሬት የቢሮውን የስራ ተልእኮ ከግብ ለማድረስና በቴክኖሎጂ የታገዘና ጥራት ያለው ትምህርት ለማህበረሰቡ ማስተላለፍ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑንና ስልጠናው መዘጋጀቱ የስራ ክፍሉ ባለሙያዎች በሶሻልና ዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ ያላቸውን አቅም እንደሚያሳድግ ተናግረዋል፡፡
ዳይሬክተሯ አያይዘውም ሰልጣኞች ጥራቱን የጠበቀና ተአማኒነት ያለው፤ የሚዲያ ስነምግባርን የጠበቀ መረጃ በማስተላለፍ ሂደት ሊተገብራቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦችን ከስልጠናው በመውሰድ በዘወትር ስራቸው ሊተገብሩት እንደሚገባ ተናግረው፤ ዳይሬክቶሬቱ የባለሙያዎችን ክህሎት ለማሳደግ በየጊዜው ወቅቱን የጠበቀ ሙያዊ ስልጠና ለመስጠት እቅድ መያዙን አብራርተዋል፡፡
+6
Miidhagina Simannaafi Hawwii Bara Haaraa Goobeefi Shinooyyee Magaalaa Finfinneetti
