2 766
Suscriptores
Sin datos24 horas
-67 días
-1530 días
Archivo de publicaciones
የመምህርነት የስራ ቅጥር ምዝገባ ማስታወቂያ!
ሀምሌ 13/2018 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ10/11/2018 ዓ.ም ያወጣው የመምህርነት የስራ ቅጥር ማስታወቂያ ምዝገባ ከዛሬ ማለትም ከ13/11/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት የሚከናወን ይሆናል፡፡
የመምህርነት የስራ ቅጥር መመዝገቢያ ሊንክ
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfszWEujUr29knX3mhUsQJfzvosKBGCg7Jw2WznB0EsBMybGQ/viewform?usp=publish-editor
እንኳን ደስ አለን! አላችሁ!
(ሀምሌ 12/2018 ዓ.ም) በ2018 በጀት ዓመት በትምህርት ዘርፍ የህዝባችንን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎችን በመስራት የላቀ ውጤት ካስመዘገቡ የካቢኔ አባል ከሆኑ ቢሮዎች መካከል በበጀት አመቱ ላስመዘገበው የላቀ ውጤት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ እውቅናና ሽልማት ከክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተበርክቶለታል።
ቢሮ ላለፍት ተከታታይ ሶስት አመታት ላስመዘገበው ስኬት የመኪና ተሸላሚ የሆነ ሲሆን ዘንድሮም የመኪና ተሸላሚ ለመሆን በቅቷል።
እውቅናና ሽልማቱ ለመላው የትምህርት ዘርፍ አመራሮች ፣ ለትምህርት ባለድርሻ አካላት ፣ በየደረጃው ለሚገኙ የትምህርት ባለሙያዎች ፣ ለመምህራን እና አብራችሁን ለሰራችሁ በሙሉ ለጋራ የቅንጅት ስራ የተሰጠ ሲሆን ይህም ይበልጥ ሰርተን የህዝባችንን የትምህርት ፍላጎት የምናሳካበት ፣ የውድድር መንፈስን የምንፈጥርበት ነው።
በመሆኑም እውቅናው በቀጣይ በጀት ዓመት አልቀን በመስራት የህዝባችንን ተጠቃሚነት እንድናረጋግጥ፣ የትምህርት የአገልግሎትን ፣ ጥራትንና ተደራሽነትን አልቀን እንድንሰራ የሚያነሳሳ ነው ።
በድጋሜ እንኳን ደሰ አለን! ደስ አላችሁ!
ስምምነቱ በከተማ አስተዳደሩ የሚሰጠውን ትምህርት ጥራት ለማረገገጥ እና የተማሪዎችን ውጤትና ስነ ምግባር ለማጎልበት ትልቅ ሚና እንዳለው የጠቀሱት ሀላፊው ስልጠናው ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ በሚያወጣው የስልጠና መስጫ መርሀ ግብር መሰረት ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
ቢሮ ያመቻቸዉን ይህንን የ PGDT ስልጠና እድል መምህራን በመጠቀም ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ የሚናቸዉን ሊወጡ ይገባል ያሉት ሀላፊው ስምምነቱ በ2019 የትምህርት ዘመን በከተማ አስተዳደሩ ለሚሰጠው ትምህርት የቅድመ ዝግጅት ስራ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ ትምህርትና ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ዲን ዶ/ር የቆየሰው ደሴ በበኩላቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በከተማ አስተዳደሩ የሚሰጠዉን ትምህርት ስኬታማና ጥራቱ የተረጋገጠ እንዲሆን እየሰራቸዉ የሚገኙ ስራዎች አስደሳች መሆናቸውን ጠቅሰው በክረምት መርሀ ግብር ላይ የሚሰጠው የ PGDT ስልጠና ስኬታማ እንዲሆን በትኩረት የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
+5
ቢሮ ለ1884 መምህራን የማስተማር ስነ-ዘዴ /PGDT/ ስልጠና በክረምት መርሀ ግብር ለመስጠት የሚያስችል የጋራ ስራ ውል ስምምነት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ ትምህርት ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ጋር ተፈራረመ፡፡
(ሀምሌ 10/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ለ1884 መምህራን የPGDT/የማስተማር ስነ-ዘዴ/ ስልጠና በክረምት መርሀ ግብር ለመስጠት የሚያስችል የጋራ ስራ ውል ስምምነት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ ትምህርት ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ጋር ተፈራርሟል፡፡
በፊርማ መርሀ ግብር ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ክቡር ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ ትምህርት ቋንቋዎች ጥናት ኮሌጅ ጋር ያደረገው የጋራ ስራ ውል ስምምነት ለ1884 መምህራን በክረምት በርሀ ግብር የPGDT ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዘንድሮ ለተመዘገበው ውጤት ከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ስራዉ ልዩ ትኩረት በመስጠት መንቀሳቀሱ ፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሀ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉ ፣ የሂሳብና እንግሊዘኛ ትምህርት ስትራቴጂ ተነድፎ በትኩረት መስራት መቻሉ ፣ የመማሪያና የማስተማሪያ ግብዓቶች መቅረባቸው እንዲሁም ከትምህርት ባለድርሻ አካላት ጋር በተለይም ከወላጆች ጋር በቅንጅት መሰራቱ ተጠቃሽ መሆናቸውን ኃላፊው አብራርተዋል::
በከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ስርአቱ የብዝሀ ቋንቋ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞ እንደሁለተኛ ቋንቋ የተማሩ ተማሪዎች በትምህርት አይነቶቹ ፈተና መውሰዳቸውን ዶክተር ዘላለም አስታውሰው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናን ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከል 543 ያህሉ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸውን አስታውቀዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁሟል።
https://aa6.ministry.et/#/result
+2
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2018 የትምህርት ዘመን 97.48% የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ ተዘዋወሩ፡፡
(ሰኔ 28/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 97.48 % የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ አስታወቁ።
ኃላፊው የ2018 የትምህርት ዓመት የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑን በማስመልከት ለተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በጋዜጣዊ መግለጫቸው በከተማ አስተዳደሩ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 84,257 ተማሪዎች መካከል 82,137 የሚሆኑ ተማሪዎች 50 በመቶ እና በላይ በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ የትምህርት እርከን መሸጋገራቸውን አስታውቀዋል።
ኃላፊው አያይዘውም ዘንድሮ 97.48% የሚሆኑ ተማሪዎች 50 እና በላይ በማምጣት ወደ ዘጠነኛ ክፍል ያልፉበት ውጤት በ2017 ዓ.ም ከነበረው 95% አንጻር እድገት ማሳየቱን ገልጸው ውጤቱ እንዲመዘገብ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ መምህራን ፣ የትምህርት አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም ለወላጆችና ለሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
+5
6461 ጎልማሶች የብርሃን ምዘና እየወሰዱ እንደሚገኝ ተገለጸ።
(ሰኔ 23/2018 ዓ.ም) በበጋ ወቅት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 6461 ጎልማሶች የብርሃን ምዘና በመውሰድ ላይ ይገኛሉ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥላዬ ዘውዴ ቢሮው በ2018 የትምህርት ዘመን በበጋ ወቅት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ጎልማሶች የብርሀን ምዘና በመስጠት እንደፍላጎታቸው 3ኛ ክፍል ገብተው መደበኛ ትምህርት የሚማሩበት ወይም በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ገብተው በሚመርጡት ሙያ የአጭር ጊዜ ስልጠና ወስደው ህይወታቸውን የሚመሩበት አማራጭ አዘጋጅቶ ተግባራዊ እያደረገ መቆየቱን ገልጸው፤ በዘንድሮው መርሀግብርም በክረምት ወቅት የ90 ቀን የንቅናቄ እቅድ አዘጋጅቶ እያከናወናቸው ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ ጎልማሶች በበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች የትምህርት አገልግሎት እንዲያገኙ ማስቻል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አያይዘውም ቢሮው ትምህርቱ በወጣለት መርሀግብር መሰረት በአግባቡ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን በየጣቢያዎቹ በሚያደርገው ድጋፍና ክትትል ማረጋገጡን በመጥቀስ ትምህርቱን እየሰጡ ለሚገኙ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ምስጋና አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የልዩ ፍላጎትና የጎልማሶች መሰረተ ትምህርት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ገመቺስ ፍቃዱ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ 6462 ጎልማሶች በበጋ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ መቆየታቸውን አስታውሰው አሁን ላይ የብርሀን ምዘና እየወሰዱ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
