2 745
Suscriptores
-224 horas
-57 días
-2530 días
Archivo de publicaciones
+1
የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤታቸውን ዛሬ ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው ማየት ይችላሉ - የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸውን ማስፈንጠሪያዎች የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጓል፡፡
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ
https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ማቅረብና ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et፣ ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram፣ አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡
https://result.eaes.et/sms መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መረጃ ያመላክታል፡፡
ማስታወቂያ!
(ሀምሌ 27/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2019 የትምህርት ዘመን በእቴጌ መነን የልጅ አገረዶች እና በገላን የወንዶች መካከለኛና ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በሚኒሊክ ሳይንስ ሼርድ ካንፓስ የ7ኛ እና የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት በኦን ላይን/online/ ምዝገባ ያከናወናችሁና የመግቢያ ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች በሙሉ ;-
ውጤታችሁን https://bs.ministry.et ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
Beeksisa!
Biiroon Barnootaa Bulchiinsa Magaalaa Finfinnee bara barnootaa 2019tti Mana Barnootaa Bultii addaa Sadarkaa Giddu-galeessaa fi Waliigalaa Sadarkaa 2ffaa Shamarranii Itegee Manan, Mana Barnootaa Bultii addaa Dhiiraa Galaan fi Kaampaasii Saayinsii Sheerdiitti barattoota kutaa 7ffaa fi 9ffaa simatee barsiisuuf beeksisa baase irratti hundaa'uun: Barattoonni onlaayiniidhaan (online) galmooftanii fi qormaata seensaa fudhattan hundi;-
Bu'aa keessan marsariitii https://bs.ministry.et irratti ilaaluu kan dandeessan ta'uu ni beeksifna.
