fa
Feedback
Fuad Muna (Fuya)

Fuad Muna (Fuya)

رفتن به کانال در Telegram

የኛ እዉነታ የሌሎችን ስጋ ለብሶ ሲቀርብ! በፅሁፍ ያስነበብኳችሁን በድምፄ ስትሰሙት! ዩቲዩብ ቻናል http://Www.YouTube.com/c/FuadMuna የፌስቡክ አካውንቴን ለማግኘት www.facebook.com/fuadmuna14 ለፒዲኤፍ ብሎግ www.fuadmuna.wordpress.com

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Fuad Muna (Fuya)

کانال Fuad Muna (Fuya) (@fuadmu) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 15 624 مشترک است و جایگاه 2 456 را در دسته وبلاگ‌ها و رتبه 2 168 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 15 624 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 29 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 625 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 31 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 24.86% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 13.63% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 3 882 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 128 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 87 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
የኛ እዉነታ የሌሎችን ስጋ ለብሶ ሲቀርብ! በፅሁፍ ያስነበብኳችሁን በድምፄ ስትሰሙት! ዩቲዩብ ቻናል http://Www.YouTube.com/c/FuadMuna የፌስቡክ አካውንቴን ለማግኘት www.facebook.com/fuadmuna14 ለፒዲኤፍ ብሎግ www.fuadmuna.wordpress.com

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 30 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته وبلاگ‌ها تبدیل کرده‌اند.

15 624
مشترکین
+3124 ساعت
+1547 روز
+62530 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
ژوئیه '26
ژوئیه '26
+663
در 4 کانال‌ها
ژوئن '26
+37
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+32
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+38
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+45
در 4 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+61
در 3 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+34
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+24
در 3 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+39
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+63
در 3 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+96
در 3 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+44
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+42
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+50
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+231
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+114
در 16 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+66
در 3 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+179
در 2 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+281
در 2 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+123
در 2 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+100
در 5 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+79
در 4 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+120
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+112
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+315
در 3 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+149
در 8 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+241
در 4 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+248
در 2 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+658
در 3 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+946
در 2 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+238
در 2 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+101
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+112
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+85
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+131
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+237
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+243
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+380
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+256
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+278
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+222
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+344
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+241
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+166
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+168
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+197
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+153
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+175
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+156
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+105
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+160
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+110
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+63
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+117
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+61
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+54
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+67
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+122
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+134
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+106
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+166
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+194
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+209
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+162
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+164
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+191
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '20
+19 616
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
30 ژوئیه+9
29 ژوئیه+31
28 ژوئیه0
27 ژوئیه+16
26 ژوئیه+18
25 ژوئیه+28
24 ژوئیه+50
23 ژوئیه+18
22 ژوئیه+35
21 ژوئیه+19
20 ژوئیه+26
19 ژوئیه+25
18 ژوئیه+42
17 ژوئیه+16
16 ژوئیه+30
15 ژوئیه+51
14 ژوئیه+10
13 ژوئیه+40
12 ژوئیه+3
11 ژوئیه+6
10 ژوئیه+15
09 ژوئیه+5
08 ژوئیه+15
07 ژوئیه+11
06 ژوئیه+54
05 ژوئیه+4
04 ژوئیه+31
03 ژوئیه+6
02 ژوئیه+49
01 ژوئیه0
پست‌های کانال
እነሆ ነገ ምሽት 1:30 ሲል ሰርፕራይዙ ይፋ ይደረጋል። ብዙ ግምቶ ተሰጥተዋል። እርስዎ የቱ ትክክል ይመስልዎታል?
Anonymous voting

2
2 ቀናት ብቻ! ሁላችሁም ፕሮፋይል፣ ስቶሪ፣ ፖስት በማድረግ ማስታወቂያው ላይ አግዙኝ! ዛሬና ነገ ብቻ ቀርተዋል። . @Fuadmu
2 ቀናት ብቻ! ሁላችሁም ፕሮፋይል፣ ስቶሪ፣ ፖስት በማድረግ ማስታወቂያው ላይ አግዙኝ! ዛሬና ነገ ብቻ ቀርተዋል። . @Fuadmu
834
3
እጥፋት አጭር ልብወለድ በፉአድ ሙና . @Fuadmu
1 866
4
ሰው አልባው ቤት በሰው ተሞላ፡፡ በህይወት ሳለ ሰው የራበው ሰው በድን ሆኖ በሰው ተከበበ፡፡ ልጆች በለሊት ተነስተው ጠዋቱን ወደ አባታቸው ቤት ደረሱ፡፡ ለአረፋ አርዶ ‹‹የተንቢ … ባፈር ንተን!›› ይላቸው የነበረው አባታቸው በብቸኝነት ብርድ ተቆራምዶ ወደ ቀጣዩ አለም ተሻገረ፡፡ እዚያ ናፍቆቱን ሳትሰለች የምትሰማው ሚስቱ አለች … አይበርደውም ይሆናል፡፡ የሰው ልጅ ወደ አፈር መከተቱ የተፈጥሮ ግዴታ ነውና … መዲናን የናፈቁት ሰው ወደ አፈር ተከተቱ፡፡ ልጆቹ ልክ እናታቸው ስታመልጣቸው እንዳሉት … ‹‹አመለጠን! … አመንጠንደም!›› እያሉ ተንሰቀሰቁ፡፡ ለእናታቸውም እንዲሁ ተንሰቅስቀው ነበር፡፡ ግን ከተማ ሲመለሱ ተረሳቸው፡፡ ገንዘብ ሲቆጥሩ አባታቸውም እንደ እናታቸው ሊያመልጣቸው እንደሚችል ዘነጉት! ሰደቃ እንዲሆንላቸው … የጥፋተኝነት ስሜታቸውን ለመሻርም ሊሆን ይችላል … ሰንጋ ወደ ቤቱ ነዱ፡፡ መንደርተኛ ሁሉ ሰደቃ ተጠራ፡፡ በየቀኑ ይታረዳል … ለከብት ብቻ ከግማሽ ሚሊየን በላይ አውጥተዋል፡፡ አሄሄ … ይኼ ገንዘብ በህይወት እያለ የአባታቸውን ናፍቆት አይቆርጠውም ነበር? ይቆርጠዋል፡፡ ግን ልብ ጠፋ … ወላጆቹን የሚያስታውስ ደህና ልብ! አጥተውስ ቢሆን ይሁን … ገንዘብ ተርፏቸው … እንዲህ ባይተዋር ሲያደርጓቸው! ለቀስተኛው ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ እነሱም ቀስ በቀስ ወደ ከተማ መመለስ ጀመሩ፡፡ ታላቅ ወንድማቸው ብቻ ቀረ፡፡ ቤቱን ወደ መስጂድ ስለመለወጥ አስበዋል፡፡ ለማፅዳት ሲሞክር የአባቱን ቴፕ አገኘ፡፡ ካሴት እንደጎረሰች ናት፡፡ አጫወታት፡፡ ካቆመችበት ቀጠለች፡፡ ‹‹ሰላም ዘይኔ ለእናት እጅሁ፣ ሰው አንዴም ላልመታው፣ ጭነት ለከበደው ፈረስ፣ ለሚወርደው መንታው፣ ባለሟሉን የአላህ ደጌ፣ እንዴት ረሳህ አንተው፣ አስተዋዩ ይቅርና፣ እህ ግንዱም አይስተው፡፡ እያለፈ በጎዳናው፣ የቲም ‘ሚዳብሰው፣ ቢታወሰኝ የሱ ታሪክ፣ ሙች ውስጤን አመሰው፡፡ ድኩም አጽኚ ድሀ ወዳጅ፣ ለዑመት ‘ሚያለቅሰው፣ አልማዝ ሉል ሆኖ አከበረን፣ እንባው የሚፈሰው፡፡›› ከዓይኖቹ የእንባ ዘለላዎች ተሸቀዳደሙ፡፡ ድንገት የአባቱ ናፍቆት ታወሰው፡፡ ለመዲና መንሰፍሰፉ … መንገብገቡ ዓይኑ ላይ መጣበት፡፡ ልቡን ምን እንዲህ እንዳስረሳት እያሰበ እንደ አዲስ መንሰቅሰቅ ጀመረ፡፡ ምንም ሳይጎድለው ለአባቱ አለመድረሱ ውስጡን ፈጀው፡፡ ከዘገየ ነቃ! ካመለጡት በኋላ! እንደው ሄዶ ዑምራም … ሀጅም ያደርግላቸው ይሆናል፡፡ ግን እሳቸውን ወስዶ ቢያስደርጋቸው የሚያገኘውን ቅንጣት ታክል እርካታ አያገኝም፡፡ ከምንም ይሻላልና በስማቸው ሀጅና ዑምራ ለማድረግ ወሰነ፡፡ ካመለጡት በኋላ ባነነ … ናፍቆታቸውን ሳይቆርጥላቸው ከአባቱ ተለያየ፡፡ ሳያመልጡት ቢነቃ ይመኛል … ሳያጣቸው ቢደርስላቸው! ግን አምልጠውታል፡፡ ከቴፓቸው አጠገብ ተቀምጦ ያዳምጡት የነበረውን እንጉርጉሮ እየሰማ እየተነፋረቀ ‹‹አባኖ … አባኖ … እዮ እዮ … አባዎ አባኖ!›› ይላል፡፡ ለቅሶ ግን የሄደን አይመልስም! ተፈፀመ፡፡ ===== የእንጉርጉሮው ግጥም የቀደምት መሻዒኮች ስራ ነው። በድምፅ የተያያዘው እንጉርጉሮ ደግሞ ከቲክቶክ መንደር ከወንድም አይመን ዙልፊቃር ገፅ የተወሰደ ነው። . @Fuadmu
1 835
5
እጥፋት! (ፉአድ ሙና) . ‹‹አንተ ጦይባ ያለህ፣ ኧረ ወስፍም የለህ፣ ወዳጅ ትገድላህ፣ ከሩቅ ሰፍረህ ጦይባ፣ አህመደል ሙስጠፋ፣ ሸራቢ ሶፋ! አለቀሰች ዓይኔ፣ አይታ ሲሳፈሩ፣ የረውዳው መንደሩ፣ አሳሳኝ ብላ፣ አህመደል ሙስጠፋ፣ ሸራቢ ሶፋ! ጌታዬ እኔም ልየው፣ የጦይባን ሰፈር፣ ልቃም ያን አፈር፣ ልኽተም በሱ ስፍራ፡፡ አህመደል ሙስጠፋ፣ ሸራቢ ሶፋ! አላሁመሰሊ አላሙሀመዴ፣ አላሁመሰሊ አላሙሀመዴ፣ አህመደል ሙስጠፋ፣ ሸራቢ ሶፋ! ›› አንጀት የሚበላ የናፋቂ ድምፅ ከቴፑ ይስረቀረቃል፡፡ ፂማቸው በንጣት የተወረሰ … ከቴፓቸው ወዲያ አጫዋች የሌላቸው አባት የቤታቸውን በር ተደግፈው ያነባሉ፡፡ ይህ እንባ … የናፍቆት እንባ ነው … ከተማ ሄደው የጠፉባቸው ልጆቻቸው ናፍቆት አይደለም … ሳያዩ የናፈቋቸው ውዱ ነብይ ﷺ ናፍቆት እንጂ! ቢያዩት ይመኙ ነበር … የወደዷቸውን ነብይ ﷺ ሀገር … ሊረግጡት ይንሰፈሰፉ ነበር፡፡ ግን አልሆነላቸውም፡፡ ያለቻቸው ቴፓቸው ናት … ከደቡብ እስከ ሰሜን … ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ለውዱ ነብይ የተነቡ እንባዎችን እያስፈለጉ ቴፓቸውን ያጎርሳሉ፡፡ ቁስላቸውን ያኩላቸዋል መሰል … ለቅሷቸውን ያደምጣሉ፡፡ በርካታ ልጆች አሏቸው፡፡ ለአረፋ ተግተልትለው የሚመጡ … አመቱን ሙሉ ግን ባይተዋር ያደረጓቸው ቀልብ አልባ ልጆች! በዚህ የማረፊያ ዕድሜያቸው ወደ ጓሮ ወርደው ከአትክልቱ ጋር ይታገላሉ፡፡ ይጎለጉላሉ … ይኮተኩታሉ … የደረሰውን ያወጣሉ! ሰፊ የጫት እርሻም አላቸው፡፡ ሲደርስ እሱን ሽጠው … ልጆቻቸው ላይ ጥገኛ ላለመሆን ይታገላሉ፡፡  የተወሰኑ ከብቶች አሏቸው፡፡ እነሱን ለእረኛ እየከፈሉ ያሰማሩላቸዋል፡፡ ውሀ አቀባይ የሌለው ጎሮሯቸውን በወተት ጥሙን ይቆርጣሉ፡፡ ልጆቻቸው የገንዘብ ችግር የለባቸውም፡፡ እንኳን ዑምራ … ሀጅም ሊያስደርጓቸው ቢፈልጉ ገንዘብ አላጠራቸውም፡፡ ገንዘቡ ሳያጥር … ልብ አጠረ! ከዱንያ ኮተት ተፋቶ ለአፍታ የውዱን ነብይ ﷺ ሀገር የሚያስታውስ ልብ አነሳቸው፡፡ አባታቸውን እንኳን የሳር ቤቱን አፍርሰው በጭቃ ቤት ከመተካት ውጪ በሌላ አላስታወሱም፡፡እሱም የታወሳቸው ለአረፋ ገጠር ሲገቡ አልመች ብሏቸው ነው፡፡ ለራሳቸው ምቾት! ገንዘብ እንኳን ነበር … ልብ ጠፋ፡፡ ቴፑ የጎረሰውን የሲቃ ድምፅ ይተፋል፡፡ ሽማግሌው ሰው አብረውት በናፍቆት ይነፋረቃሉ፡፡ የማይቆረጥ ጥም ሆኖባቸው ይብሰለሰላሉ! ‹‹አቤት ባየውህ ማሳዘኔ፣ ይህ ጎጆ ሲል ወና፣ ይፅናናብኛል ታማሚ፣ ህመሜን ያይና፡፡ ውዴ የቀልቤ ጀምበሩ፣ ፋኖስም ሻማዬ፣ ሳስብ ለዑመት መቅለጥሁን፣ ጠናኝ በሽታዬ፡፡ ባልመልስም ውለታሁን፣ እኔም በተራዬ፣ ከጥልቁ ቀልቤ ምንጩ ስር፣ ያንቱ ነው እንባዬ፡፡ ሰላቱሏህ ሰላሙሏህ፣ አላ ኑሪል ቁሉብ፣ ሙሀመዲን ወአሊሂ፣ ሃባኢቢል መህቡብ!›› ያኔ ሚስታቸው በህይወት ሳለች … ናፍቆታቸውን ያወጓት ነበር፡፡ ደጉን ሰው መናፈቃቸውን ይተርኩላት ነበር፡፡ እሷም አትሰለችም፡፡ አፏን ከፍታ ታደምጣቸዋለች፡፡ ጠዋት ቁርስ እየበሉ ድንገት ተነስተው ወደ በሩ ይኼዱና ‹‹ሀቢቢ ናፈኬም … ምሽራና!›› ይላሉ፡፡ ‹‹አይዞዎት ቢትወደድ … ጎይታ የስደኸ፡፡›› ታፅናናቸዋለች፡፡ ‹‹ምሩ አቴርኸም … ቀብራቸውን ሳልዘይር መሞቴ ሆነ እኮ!›› ‹‹ጎይታ የፈዘዘ ቃር አሰበንኸምታ ይኽርሸ፡፡›› ልታረጋጋቸው ትሞክራለች፡፡ አሁን አፅናኛቸውም አፈር ከተንተራሰች ቆየች፡፡ ጠዋት ተነስተው ‹‹ሀቢቢ ናፈቁኝ … ምሽራና!›› የሚሉት እንኳን ሰው የላቸውም፡፡ በራቸው ስር ተቀምጠው ለቅሷቸውን የሚያለቅስላቸውን ድምፅ ከቴፑ ያደምጣሉ፡፡ ቴፓቸው ባትሪ ድንጋይ ሲያልቀው ወለላዬን የተቋረጡ ይመስላቸዋል፡፡ ሳይውል ሳያድር ከተማ ሰው ይልካሉ … ሰውም ከጠፋ ራሳቸው በደከመ ጉልበታቸው ተጉዘው የቴፓቸውን ቀለብ ይገዛሉ፡፡ ዛሬ ከጠዋት ጀምሮ ለየት ያለ ስሜት እየተሰማቸው ነው፡፡ ደሞ እንደመቁረጥም ያደርጋቸዋል፡፡ በጠዋቱ ምግብ ስላልቀመሱ ከሆነ ብለው አሰቡ፡፡ እሳት አቀጣጥለው ከምድጃቸው ላይ ቆጯቸውን መጥበስ ጀመሩ፡፡ የታለበ ወተት ስላላቸው … ቆጮው ከተጠበሰ … በወተት ከበሉ ይበቃቸዋል፡፡ ምግብ እንደ ድሮ አይደሉም፡፡ ሚስታቸው እያለች ደህና እየተከታተለች ታበላቸው ነበር፡፡ ቴፑ ሲቃውን ቀጥሏል፡፡ ከውጋታቸው ጋር እየታገሉ … ቆጯቸውን እየጠበሱ … ልባቸው ግን ቴፓቸው ላይ ነው፡፡ ‹‹ነፍርቄ እንጂ አልፃፍኩልሆም፣ አንዷንም ደብዳቤ፣ እያቃሰትኩ በጤናዬ፣ እየመታ ልቤ፡፡ ምነው ግርዶ ቢገልጡልኝ፣ ሲብስ መንገብገቤ፣ ብንደፋደፍ እግርሁ ስር፣ ሀይባሁን ተስቤ፡፡ ንገስበት በዓለሜ፣ ባሻህ ተዘናፈል፣ ለቅሶ የሰራውን ባህሬን፣ በበትርህ ክፈል፡፡ ሙሳዬ ነህ አንተው ዒሳ፣ ካንተ እንዴት ይገፈል፣ መሻሪያም ነህ መታመምያ፣ ምን ባታውቅም በደል፡፡ ሰላቱሏህ ሰላሙሏህ፣ አላ ኑሪል ቁሉብ፣ ሙሀመዲን ወአሊሂ፣ ሃባኢቢል መህቡብ!›› ወጣት ሳሉ ልጆቻቸውን አቀማጥለው አሳድገዋል፡፡ የአካባቢው ማህበረሰብ ከሚያሳድግበት መንገድ የተሻለ አድርገው እንጂ አጉድለው አላሳደጉም፡፡ ስለ ውዱ ነብይ ﷺ ፍቅርም ነግረዋቸዋል … ከንግግርም በላይ በተግባር ልጆቻቸው መንሰፍሰፍን ከአባታቸው ላይ አይተዋል፡፡ ግን ከተማ ከገቡ ወዲያ ገንዘብ እንጂ ሙሀባ ጠፋቸው፡፡ ሳንቲም ከእጃቸው ሳይጠፋ የአባታቸውን ናፍቆት መቁረጥ ተረሳቸው፡፡ ቆጯቸውን ለመንከስ ሲሞክሩ አምልጣ ከእጃቸው ወደቀች፡፡ እርሳቸውም  ጉልበት ከድቷቸው ወደ ጎን ተፈነገሉ፡፡ ምናልባት ይህች ቆጮ ከርዝቃቸው ላይ አልተከተበችም ይሆናል፡፡ የተፃፈላቸውን ርዝቅ በልተው ስለጨረሱም ሊሆን ይችላል፡፡ የልብ ምታቸው ፈጠነባቸው፡፡ አተነፋፈስ ጠፋቸው፡፡ ይህችን ምድር እንዳሰቡት የውዱን ነብይ ﷺ ሀገር ሳይዘይሩ እየለቀቋት መሆኑ ገባቸው፡፡ በልጆቻቸው የማዘን ስሜት ውስጣቸውን በላው፡፡ ሩሀቸው ጎሮሯቸው ላይ ደረሰች፡፡ ጆሯቸው እየሞቱም ቴፑ ላይ ተቀስሯል፡፡ ‹‹የአሚነቱ ያሲን ጠሀ፣ የናፍቆቴ ውሀ፣ ትውስታሁ የአህባብ ቀለብ፣ የሩህ ጅስሙ ረሀ፡፡ ያዕቁቡህ ነኝ ሆነው ዩሱፍ፣ የጀማሉ ዱሀ፣ ግንስ ያንቱ ውበትሁ፣ ያለፈው ሙንተሀ፡፡ ሰላም ላይኑህ ዐይነ ኩሌ፣ ለተጠማው ዓይኔ፣ ሙሂቡህ ሚስባህ ይልኋል፣ ጌጤ መኮንኔ፡፡ ትዝ ሲለኝ በድሬ ወጅሁ፣ አልተኛም በጎኔ፣ እንደነኚህ ባልሆንሁም፣ ላንብብሎ እኔ፡፡ ሰላቱሏህ ሰላሙሏህ፣ አላ ኑሪል ቁሉብ፣ ሙሀመዲን ወአሊሂ፣ ሃባኢቢል መህቡብ!›› አመሻሹን እረኛቸው ከብቶቹን ለመመለስ ወደ ቤታቸው ጎራ አለ፡፡ ‹‹ቢትወደድ …›› መልስ የለም፡፡ ‹‹ቢትወደድ …›› ዝም … ጭጭ! ነገሩ አላማረውም፡፡ ወደ ጎጇቸው ዘለቀ፡፡ እኒያን የውዱን ነብይ ﷺ አፍቃሪ መሬት ላይ ተከንብለው አገኛቸው፡፡ ቴፓቸው ብቻዋን ትስረቀረቃለች፡፡ ጮኸ፡፡ ‹‹እዮ እዮ … አባኖ አባኖ … እዮ እዮ እዮ … አባዎ …›› ቀርቦ ትንፋሻቸውን አረጋገጠ፡፡ ሲነካቸው ቀዝቅዘዋል፡፡ ጩኸቱን ካቋረጠበት ቀጠለ፡፡ ‹‹ቢትወደድ ሞተም … ባሪቀንዳ ሞተም … አትሻካቸንዳ ሞተም … የጎይታ ሰብ ሞተም!›› ጩኸቱን እያቀለጠ ከቤት ወጣ፡፡ የቀዬው ሰው ‹‹እዮ እዮ … አባኖ አባኖ …›› እያለ ተሰበሰበ፡፡ ብቻቸውን መሆናቸው የሁሉንም አንጀት ይበላቸው ነበር፡፡ በተወሰነ ጊዜ ልዩነት ቡና እየያዙ ወደ ቤታቸው ጎራ እያሉ ያጫውቷቸዋል፡፡ የብቸኝነታቸውን ዳገት ሊያዋጧቸው ሞክረዋል፡፡ እንደፈሩት … ውሀ እንኳን የሚያቀብላቸው ሰው ከጎናቸው ሳይኖር ተፈነገሉ፡፡ ከዱንያ ተቆራረጡ፡፡
1 732
6
የዛሬውን ልብወለድ የምለቀው በፅሁፍና በድምፅ ነው። ድምፁን እየሰማችሁ ፅሁፉ ላይ ብትከታተሉት የተሻለ የሚሆን ይመስለኛል። እንደዚያ ሞክሩት! እንጉርጉሮ ስላለው በፅሁፍ ብቻ ካነበባችሁት ስሜቱን እንዳታጡት ብዬ ነው። ሁለቱንም 12:00 ሲል እለቃለሁ። 🥰 . @Fuadmu
1 691
7
ዛሬ በተለመደው ሰዓት ባለ አንድ ክፍል ልብወለድ አለኝ 🥰 12:00 ላይ 🥰 . @Fuadmu
2 005
8
ገደልሽኝ... ጨረስሽኝ! ግጥም በፉአድ ሙና 🥰 . @Fuadmu
2 173
9
3 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! የሀምሌ ሰርፕራይዛችን ይፋ ሊደረግ ቀርቧል። በደንብ እናስተዋውቀው ወገን 🥰 . @Fuadmu
3 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! የሀምሌ ሰርፕራይዛችን ይፋ ሊደረግ ቀርቧል። በደንብ እናስተዋውቀው ወገን 🥰 . @Fuadmu
2 297
10
ማለት ነው፡፡ደራሲው በዚህ ውስጥ መጠቀም ያለበትን በአግባቡ ሳይጠቀም በቀጣይ መፅሀፍ የማሳተም ሞራሉ ይሞታል፡፡ የህትመት ወጪ ጎሮሮውን እየረገጠው ስንት ደራሲ ያሳተመውን መፅሀፍ መሸጥ አቅቶት በኪሳራ ከጨዋታ ውጪ ሆኗል፡፡ በርካቶች መፅሀፋቸውን አቅፈው ተቀምጠዋል፡፡ በዚህ መሀል መፅሀፉ በፒዲዔፍ ተሰራጨ ማለት ጨዋታው አለቀ … ኪሳራ ማለት ነው፡፡ ያለ ደራሲው ፈቃድ የተለቀቀ ፒዲኤፍ በምታነቡበት ሰዓት የተሰረቀ ምግብ እየበላችሁ መሆኑን እወቁ፡፡ ክብራችሁን አይመጥንም፡፡ በቻላችሁት መጠን በገንዘባችሁ ግዙ፡፡ ደራሲው ይበረታታል፡፡ በተለይ አሁን ደግሞ የህትመት ዋጋ ቢቀርስ በሚያስብል ደረጃ ጣራ ስለነካ መፅሀፍ በመግዛት ደራሲዎችን አበረታቱ፡፡ ደግማችሁ ፒዲኤፍ እንዳትጠይቁኝ አደራ! በጥቅሉ የተጠየቁትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክሬያለሁ፡፡ በቀጣይ ደግሞ ሀሳቦቻችሁን እንደ ግብዓት ወስጄ አሻሽዬ ለመምጣት እሞክራለሁ፡፡ እወዳችኋለሁ! ከጥልቅ መውደድ ጋር! ፉአድ ሙና የማይነበብ ፊርማ . @Fuadmu
2 605
11
የጥያቄዎቻችሁ ምላሾች (ፉአድ ሙና) . ማለፊያ ልብወለድን በተመለከተ ከቀረቡት ጥያቄዎች ውስጥ በቀጥታ ከልብወለዱ ጋር የሚገናኙትን እንዲሁም ቢመለሱ መልካም ነው ያልኳቸውን ጥያቄዎች እንደሚከተለው መልስ ሰጥቼባቸዋለሁ፡፡ 1. ልብወለዱ ላይቭ ፊክሽን እንደመሆኑ ኮመንት ላይ የሚፃፉ ነገሮችን እንደ ግብዓት ተጠቅመህ ታውቃለህ ወይስ ሆን ብለህ ኮመንት ላይ አድርግ ከተባልከው በተቃራኒው ታደርጋለህ? አስተያየት መስጫው ላይ በአንባቢዎች የሚሰጡ አስተያየቶች አንባቢዎቼ ፅሁፌን እንዴት እየተረዱት እንደሆነ ስለሚያሳዩኝ ለፅሁፉ በጣም ጠቅመውኛል፡፡ ለምሳሌ ብንወስድ ስለ አብደላ ሁለተኛ ሚስት ማግባት በተፃፈበት ጊዜ አብዛኛዎቹ ሴት አንባቢዎቼ ከውሰር አብደላን እንድትገድለው የሚደግፍ ወይም እነሱ ቢሆኑ እንደሚገሉት የሚያሳይ አዝማሚያ ያላቸው አስተያየቶችን ሲሰጡ ተመለከትኩ፡፡ ይህ ከመጀመሪያ የያዝኩት አላማ ባይሆንም እነሱ እንደሚሉት ከውሰር ልትገድለው ብትሞክር ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማሳየትና ህይወታቸው ላይ ይህን ውሳኔ እንዲከልሱት ማድረግ እንዳለብኝ ተሰማኝ፡፡ የከውሰር መታሰርም ሆነ ባሏን ለመግደል መሞከር የአንባቢዎቼን አስተያየት ተመልክቼ ለማስተማር ያካተትኩት እና የታሪኩን ፍሰት የቀየርኩበት እንጂ መነሻ ሀሳቤ ሙሉ ለሙሉ ቤተሰብን አልፈን ስንሄድ ሊፈጠር የሚችለውን መጥፎ ነገር ሲሀምን በመጉዳት ማሳየት ላይ ያተኮረ ነበር፡፡ 2. ማለፊያ ለምን አልከው? ልብወለዱ አንድ ሀሳብ ላይ ብቻ ከማተኮር ይልቅ በተለያዩ ሀሳቦች ውስጥ እንዲያልፍ በማሰብ የተጠናቀረ ስለነበር ነው፡፡ የሆነውም እንደዛው ነው፡፡ በማለፊያ በርካታ ሀሳቦች ውስጥ አልፈናል፡፡ 3. አጨራረሱ ላይ ከውሰር ላይ ለምን በረታህ? አምረላህንስ አልተለሳለስክለትም ወይ? በተቻለኝ መጠን የታሪኩ ድምዳሜ ላይ ማሳየት የፈለግኩት በእውነታው ዓለም ላይ ሊሆን የሚችለውን ነው፡፡ እንደ አምረላ አይነት ሰዎች ይጎዳሉ እንጂ እነሱ በቀላሉ አይጎዱም፡፡ ያጠፋሉ እንጂ አይጠፉም፡፡ እንደ ከውሰርና ሲሀም ያሉ ሴቶች ግን የመከራን ገፈት ይቀምሳሉ፡፡ በተለይ አሁን ባለንበት ተጨባጭ ወንድ ሆነው ደረታቸውን ነፍተው ሚስት እንዳላቸው አሳውቀው ከሚያገቡ ጨዋ ወንዶች ይልቅ እንደ አምረላና አብደላ አይነቶቹ በርካታ ሴቶች ላይ ጉዳት እያደረሱና የገፈቱ ቀማሾች ደግሞ በታሪኩ ላይ እንደተመለከትነው ሴቶቹ እየሆኑ በመሆኑ ያንን ለማሳየት ያደረግኩት ነው፡፡ ከውሰርን ከእስር አስፈትቶ ድጋሚ ከአብደላ ጋር አብሮ ማኖር በጣም ቀላሉ ነገር ነበር፡፡ ግን ከእውነታው ዓለም ጋር በጣም ይጣረሳል፡፡ እንደ አምረላ ያለ ሰው የእጁን አኼራ ላይ ማግኘቱ አይቀርም፡፡ 4. ምክንያትና ውጤትን በተመለከተ ይኼ ብዙ ተመሳሳይ ጥያቄዎች በታሪክ መዋቅሩ ውስጥ የተጠየቁትን አንድ ላይ ለመመለስ የፈጠርኩት አርዕስት ነው፡፡ በታሪኩ ውስጥ ያሉት ድርጊቶች በእውነታው ዓለም እንዳሉ እርግጠኛ የሆንኩባቸው ናቸው፡፡ ለምሳሌ የሲሀምን ከዚያ ሁሉ ነገር በኋላ ወደ አብደላ መመለስ … የከውሰር መበደል … መቆጣት … የአምረላ ተፅዕኖ … ሳይናገሩ ማግባት … ሲታወቅባቸው መፍታት ስራቸው ሁሉ ሳይቀር … በእውነታው ዓለም በደንብ ገጦ የሚታይ ነው፡፡ አንዳንዶቹ ስም ተቀየረላቸው እንጂ የእኔ ታሪክ የሚሏቸው ሰዎች አሏቸው፡፡ 5. የሴቶችን ህይወት ሁሌ ለምን ታከብዳለህ? የሴት ልጅ ህይወት ትንሽ መንሻፈፍ ሲገጥመው ብዙ ይጎዳል፡፡ የማከብደው በትንሹ ህይወታችሁ ችግር ውስጥ ሊገባ ስለሚችል አረማመዳችሁን እንድታስተካክሉ ለማጠንቀቅ እንጂ ለሌላ አይደለም፡፡ 6. ስልጤ ገፀ-ባህሪ የልብ-ነገርና እዚህ ላይ በመጥፎ ወክለሀል ለምንድነው? የልብነገር ላይ በመጥፎ አልወከልኩም፡፡ አንድ አፍቅራ የተሳሳተች ቆንጅዬ ሴት መጥፎ መባል የለባትም፡፡ ሲጀመር የአዲስ አበባ ልጅ ናት … ኢክራም ቤብ! በጥቅሉ ግን ስልጤ ሙሉ ለሙሉ ሙስሊም ማህበረሰብ እንደመሆኑ ውክልና ከማካተት አንፃር ነው፡፡ እኔ በልብወለድ ብቻ ሳይሆን በግጥምም በርካታ ቋንቋዎችን እጠቀማለሁ፡፡ ከዚህ ቀደም ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ ሱማልኛ፣ አረብኛ፣ እንግሊዘኛ ቋንቋዎችን ተጠቅሜያለሁ፡፡ የሁለተኛ ሚስትን ጉዳይ ደግሞ በስልጤ ማህበረሰብ ቢወከል ሙሉ ለሙሉ ሙስሊም እንደመሆኑ ከሌላው የተሻለ ተዓማኒነት ይኖረዋል ብዬ አስባለሁ፡፡ ሁለተኛ በማግባት የተሻለ ልምምድ ያለው ይመስለኛል፡፡ ስልጤ አንባቢዎቼ … እናንተ የኢስላም ባንዲራ ያዦች … እወዳችኋለሁ፡፡ ይኼ አቀሳሳሪ ጥያቄ ነው፡፡ በጥቅሉ ሙስሊም እንደመሆኔ በዲኔ እስካልመጣ ድረስ አንድን ብሔርን ነጥዬ ልጠላ አልችልም፡፡ ስልጤ ደሞ በዲን ጉዳይ ቤብ ነው፡፡ 7.  አብደላን ለምን መልዓክ አደረግከው? የሰው ልጅ ብዙ ጎኖች እንዳሉት ማሳየት ፈልጌያለሁ፡፡ ይህንን አፃፃፍ ከዚህ ቀደምም የልብ-ነገር ላይ ተጠቅሜዋለሁ፡፡ አብደላ አንድ ጥፋት ሰራ ማለት ሙሉ ለሙሉ መጥፎ ነው ማለት ላይሆን ይችላል፡፡ በሂደት ተፀፅቶ ለሚስቱም ጥሩ ባል ሆኗል፡፡ ህይወት ላይም አንዳንድ ሁለተኛ ዕድሎች መልካም ሰውን ይሰራሉ፡፡ 8. በነፃ ለማስነበብ ይህን ያክል ረዥም ልብወለድ ቁጭ ብሎ ለመፃፍ ሰብር ከየት ታገኛለህ? ከዛሬ ዘጠኝ አስር ዓመት ገደማ ጀምሮ በርካታ ልብወለዶችን አስነብቤያለሁ፡፡ በሰዎች ህይወት ላይ የሚፈጥሩት መልካም ነገር ሲኖር ከክፍያም በላይ ነው፡፡ አንዳንዴ መጥፎ አሻራ ካላቸውም ከባድ ነው፡፡ ውስጤ ያለ ነገር ስለሆነ ማስነበቡ ደስ ይላል፡፡ ግን በጣም ያስቀምጣል፡፡ ረዥም ሰዓት መቀመጥንና ማሰብን ይፈልጋል፡፡ የአንባቢዎችን ቀልብ ለመጠበቅ በሰዓቱ በቋሚነት ለማድረስ ኃላፊነት መውሰድን ይጠይቃል፡፡ ላያስችል አይሰጥም አይደል የሚባለው? ለዚያ ይመስለኛል፡፡ 9. ታሪኩን ለምን አሳጠርከው? ታሪኩ ማስተላለፍ የፈለገውን መልዕክት ከጨረሰ በኋላ ለታሪክ ፍሰት ብዬ ማስረዘምን አልፈለግኩም፡፡ ከምታስቡት በላይ ብዙ ገፅ አንብባችኋል፡፡ በየቀኑ ሲለቀቅ ትንሽ ቢመስልም ብዙ ነበር፡፡ ስለዚህ ዋናውን ግብ ከመታ እዚህ ላይ ማቆም የተሻለ እንደሆነ ስላሰብኩ ነው፡፡ 10. አንዳንድ ገፀ-ባህሪያት ለምን መጨረሻቸው አልተነገረም?  እንደ ሰላሀዲን፣ ምህረትና ቤቲ አይነቶቹ መሀል ላይ ለምን ተረሱ? ሰላሀዲን ያስፈለገበትን ድርጊት ፈፅሞ ከሲሀም ጋ ስለተለያየ ለታሪኩ አስፈላጊ አልነበረም፡፡ መመረቁ ስለተነገረ ከዚህ በኋላ ለአንባቢ የሚያስፈልግ ታሪክ የለውም፡፡ ቤቲና ምህረትን መጥፎ ነገር ላይ ወድቀው እንዳሳይ የጠበቃችሁ ነበራችሁ፡፡ ግን እሱን በሰፊው የሂባዋ ናርዶስ ላይ ስለሰራነው እዚህ ላይ ዋና ገፀ ባህሪ ባልሆኑ ሰዎች ማሳየት አልፈለግኩም፡፡ ሁሌም ያረግዛሉ፣ በሽታ ይሸምታሉ ላይሆንም ይችላል፡፡ በተለይ ዶክተር ከመሆናቸው ጋር ያሉበት ውርደት ከቅጣት በኩል በቂ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ 11. ኢፋዳን ለምን በፒዲዔፍ አትለቅልንም? ይህ ጥያቄ በተደጋጋሚ አስተያየት መስጫ ላይ የታዘብኩት ስለነበር ለምን በዚሁ አልመልስም ብዬ አስቤ ነው፡፡ በጣም ብሽቅ የሚያደርገኝ ጥያቄ ነው፡፡ ምናልባት ካለማወቅ ከሆነ እስኪ ላብራራው! አንድ ደራሲ መፅሀፍ ለመፃፍ በተለይ ልብወለድ ከሆነ ከፍተኛ የአዕምሮ ድካም አለው፡፡ ለበርካታ ወራት መቀመጥ አለበት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ ገንዘብ ያወጣል፡፡ ምናልባት ለረዥም ወራት ገና ለማሳተም ያወጣውን ገንዘብ ለማካካስ ይሆናል የሚሸጠው፡፡ ኢፋዳ ተፅፋ ተስተካክላ እስክትታተም ብቻ ከሶስት በላይ ዓመታት ፈጅታለች፡፡  የታተመውን መፅሀፍ 2000 ኮፒ ለመሸጥ ደግሞ ተጨማሪ ሁለት ዓመታት ወስዷል፡፡ በድምሩ አምስት ዓመታት
2 571
12
ደረሰ! ደረሰ! ደረሰ! ሀምሌ 24 4 ቀናት ብቻ ቀርቶታል ወገን! ማስታወቂያው ላይ እንበርታ! 🥰 . @Fuadmu
ደረሰ! ደረሰ! ደረሰ! ሀምሌ 24 4 ቀናት ብቻ ቀርቶታል ወገን! ማስታወቂያው ላይ እንበርታ! 🥰 . @Fuadmu
2 508
13
ወገን ማስታወቂያው ላይ እንበርታ! ቀናቶቹ እያለቁ ነው። 🥰 . @Fuadmu
2 658
14
ማለፊያ 🥰 ዛሬ የጥያቄ ቀን ነው። ኮመንት ላይ ጥያቄዎቻችሁን አስፍሩልኝ። ነገ ጠቅለል አድርጌ ምላሽ እሰጣለሁ። 🥰 . @Fuadmu
2 872
15
ሀምሌ 24 5 ቀናት ብቻ ቀርቶታል ወገን! ማስታወቂያው ላይ እንበርታ! 🥰 . @Fuadmu
ሀምሌ 24 5 ቀናት ብቻ ቀርቶታል ወገን! ማስታወቂያው ላይ እንበርታ! 🥰 . @Fuadmu
2 998
16
ማለፊያ 🥰 ማለፊያ ለተከታታይ 20 ቀናት ያስነበብኳችሁ ‹ላይቭ ፊክሽን› ነበር። ይህም ማለት መጀመሪያ ተፅፎ አልቆ ሳይሆን እየተፃፈ የሚለቀቅ ነበር። ወደ ኋላ ተመልሶ ማስተካከል አለመቻሉ ትንሽ ከበድ ቢያደርገውም እንደ ‹የልብ ነገር› ሁሉ ለኔ ጥሩ ‹ቻሌንጅ› ነበር። ፅሁፉን በአንድ ክፍል ከሌሎች ልብወለዶች ረዘም ባለ መልኩ ሳደርሳችሁ ቆይቻለሁ። እናንተ እያረፋችሁ ስላነበባችሁ ትንሽ ቢመስላችሁም በ1.5 Spacing በA4 ወረቀት 109 ገፆችን አንብባችኋል። በA5 ወረቀት (በመፅሀፍ መጠን) 218 ገፆች ማለት ነው። በጥቅሉ 23 ሺህ 178 ቃላት አንብባችኋል። በፊደል ሲሆን ደግሞ ወደ 96 ሺህ 62 ፊደላት አንብባችኋል። በማለፊያ ብዙ ሀሳቦች ውስጥ ለማለፍ ሞክሬያለሁ። እኔ በቀጥታ ከምናገረው ይልቅ ታሪክ ይናገረው ዘንድ የደራሲውን ጣልቃ ገብነት በተቻለ መልኩ ገድቤያለሁ። ብዙ ትምህርቶችን እንደወሰድንበት ተስፋ አደርጋለሁ። በታሪኩ ውስጥ ከህይወት ጋር በቀጥታ የማይጣረሱ ውክልናዎችንና ዕጣፈንታዎችን ለማሳየት ሞክሬያለሁ። በሁሉም በኩል ትምህርት ብንወስድበት መልካም እንደሚሆን ተስፋ አለኝ። በዚህ ልብወለድ በኮመንትም በላይክም እንዲሁም ወዳጆቻችሁን በመጋበዝ የተሳተፋችሁትን ከልብ አመሰግናለሁ። ዛሬ የአስተያየት ቀናችን ነው። ስለ ልብወለዱ ያላችሁን አስተያየት ለቀጣይ ስራ ግብዓት ይሆነኝ ዘንድ ኮመንት ላይ አስቀምጡልኝ። የሁላችሁንም አነባለሁ። ነገ ሰኞ ደግሞ ጥያቄዎቻችሁን እቀበላለሁ። ማክሰኞ ምላሽ ለሚያስፈልገው ጠቅለል አድርጌ ምላሽ እሰጣለሁ። አስተያየታችሁን የዚህ ፖስት ኮመንት ላይ አስፍሩልኝ! 🥰 ከጥልቅ መውደድ ጋር! ፉአድ ሙና የማይነበብ ፊርማ . @Fuadmu
3 583
17
ሀምሌ 24 6 ቀናት ብቻ ቀርቶታል ወገን! ማስታወቂያው ላይ እንበርታ! 🥰 . @Fuadmu
ሀምሌ 24 6 ቀናት ብቻ ቀርቶታል ወገን! ማስታወቂያው ላይ እንበርታ! 🥰 . @Fuadmu
3 441
18
የሀምሌ 24 ‹ሰርፕራይዛችን› ምን ይመስላችኋል? ምን ጠረጠራችሁ? እስኪ ኮመንት ላይ አሳውቁኝ! . @Fuadmu
3 923
19
‹‹እልልልልልልልልለልልልል›› ሴቶቹ አደመቁት፡፡ አብደላ ሚስቱን በድጋሚ አገባ፡፡ ከቀለበት ስነ-ስርዓቱ በኋላ ሁሉም ስጦታውን እያመጣ ፊቷ ሲደረድር አብደላ አንድ ፖስታ አውጥቶ የሲሀም እጅ ላይ አስቀመጠ፡፡   ‹‹ለምወዳት ሴት!›› ‹‹ምንድነው? መጀመሪያ የባሌን ነው የምከፍተው!›› ሁሉም ሳቁ፡፡ ‹‹ምን ይመስልሻል?›› ‹‹ምን አውቄልህ? እስኪ ጉድህን ልየው!›› ፖስታውን ከፈተችው፡፡ ውስጡ ወረቀት ነበረው፡፡ ወረቀቱን ተመለከተችው፡፡ ከአይኗ የእንባ ዘለላዎች ወረዱ፡፡ ዱንያ ላይ ስትኖር ልቧ ላይ ሽው ያላለ ነገር ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ ግቢ ከገባችበት ቀን ጀምሮ በነበረችበት ውጥረት ምክንያት ታውሷት አያውቅም፡፡ ‹‹አብዱዬ ...›› እያለቀሰች አቀፈችው፡፡ ‹‹ምንድነው ይነገረን እንጂ!›› ጀማል አላስቻለውም፡፡ ‹‹እንዴ ይነበብ እንጂ!›› ከሪማም ባሏን ደገፈች፡፡ ‹‹ዑምራ …›› መንሰቅሰቋን ቀጠለች፡፡ ጀማልና ከሪማም እንዲህ ውጪ ለውጪ እየሄዱ ሲዝናኑ ዑምራ ትዝ ብሏቸው አያውቅም፡፡ ደነገጡ፡፡ ዑምራ የመጠራት እንጂ የገንዘብ ጉዳይ አለመሆኑን እነሱን በማየት መመስከር ይቻላል፡፡ ‹‹መች ልትሄዱ ነው?›› አባቷ በደስታ ተውጠው ጠየቁ፡፡ ሰው እንዲህ ሃይማኖቱ ትዝ ሲለው ይወዳሉ፡፡ ‹‹አላህ ካለ ከሳምንት በኋላ ብለናል ጋሼ!›› ‹‹አላህ በሰላም ወስዶ ይመልሳችሁ፡፡ አኩርተኸናል … እንዲህ ነው ባል ማለት!›› ሲሀም በደስታ አብደላ ላይ ተጠመጠመች፡፡ ወደ ጌታዋ ቤት ለመሄድ ምክንያቷ ሊሆን ስለሆነ ይበልጡኑ ወደደችው፡፡ ‹‹ሌላ ደግሞ ሰርፕራይዝ አለኝ!›› ‹‹ምንድነው?›› ሲሀም ከእቅፉ ወጥታ አይን አይኑን ማየት ጀመረች፡፡ ‹‹እስካሁን እኔና ሲሀም የምንኖርበት ቤት በኪራይ ነበር፡፡ ኢንሻ አላህ ከዑምራ ስንመለስ ወደ አዲሱ ቤታችን እንገባለን፡፡›› ደረቱ ላይ ልጥፍ አለች፡፡ እቅፍ ጭምቅ አደረገችው፡፡ ምርቃቷ … ዳግም ጋብቻዋ … ድምቅ ብሎ አለፈ፡፡ *** አላህ የጊዜ ጌታ … የጊዜ አምላክ ምስጋና የተገባው ይሁን! እነዚያ የሰቀቀን ጊዜያት አለፉ፡፡ እስረኛዋ ሴት ከውሰር ወደ ተከበረው ቤቷ ተመለሰች፡፡ ምንም ቤቷ የቀድሞ ባሏ ቢሆንም እንድትወጣለት አልጠየቀም፡፡ ልጆቹን በቤቱ እንድታሳድግ ፈቅዷል፡፡ ዛሬ ደግሞ ቤቱ ውስጥ ለየት ያለ ነገር ያለ ይመስላል፡፡ አባቷ ቤቱ ውስጥ ሰንጋ ጥለዋል፡፡ ዘመድ አዝማድ ተሰብስቦ ድግሱ ተጧጡፏል፡፡ ከውሰር በመፈታቷ ደስታ ቤተሰቡ እንዲህ ለሰደቃ መሰብሰቡ ደስ ብሏታል፡፡ ምናልባት ሰደቃው ላይ አብደላ ከመጣ አይኑን ማየቱንም ናፍቃለች፡፡ ገድላው ህይወት የሰጣት አብደላ ናፍቋታል፡፡ እስር ቤት ብዙ እንዳትማቅቅ የለፋላትን … በልፋቱ ፍርዷ ተቀንሶ በጊዜ ከእስር እንድትወጣ ያደረጋትን ሰው የእውነትም ልቧ ናፍቋል፡፡ ከታሰረች በኋላ ባየችው የአብደላ ማንነት ከድሮ ባሏ ጋር እንደ አዲስ በፍቅር ወድቃለች፡፡ ብዙ ፀጋዎች የሚታወቁት ከታጡ በኋላ መሆኑ ያማል እንጂ … የባሏን የሰው ልክነት ባለፉት ጊዜያት በደንብ ተገንዝባለች፡፡ የድግሱ ስራ ተጧጡፎ ምሳ ሰዓት ሲደርስ አብደላ ከጓደኞቹ ጋ መጣ፡፡ ከውሰር መምጣቱን አልሰማችም፡፡ ሳሎን ገብተው ተቀመጡ፡፡ ከመኝታ ክፍል ስትወጣ የአብደላን ድምፅ ሰማች፡፡ በሩ ላይ ተለጥፋ ድምፁን መስማቷን ቀጠለች፡፡ ልክ እንደዚህ በር ላይ ተለጥፋ ድምፁን የሰማችው ኒካህ ያሰሩ ጊዜ ነበር፡፡ አይኗ ላይ ትዝታው መጣባት፡፡ ‹‹ዘወጅቱከ ኢብነቲ … በሉ፡፡›› ‹‹ዘወጅቱከ ኢብነቲ …›› ‹‹ከውሰር ኢብኑ …›› ዛሬም ይህን ንግግር በሰማችው ትመኛለች፡፡ አብደላ መልሶ ቢያገባት ደስ ይላታል፡፡ እንደምንም ራሷን ካረጋጋች በኋላ ወደ ሳሎን ገባች፡፡ ዘመዶቿን አቅፋ ሰላም ካለች በኋላ አብደላ ጋ መጣች፡፡ አሁን በመካከላቸው ያለው የፈቃድ ድልድይ ተሰብሯል፡፡ እንደ ሌላ ጊዜው ልታቅፈው አትችልም፡፡ ሚስቱ ሆና ቢሆን እንዴት ሊሆኑ እንደሚችሉ አሰበች፡፡ ወደ ውስጧ አነባች፡፡ ‹‹አብደላ!›› ‹‹ከውሰር›› ፈገግ ለማለት ሞከረ፡፡ ‹‹በጣም አመሰግናለሁ … ያደረግክልኝ ሁሉ አይገባኝም ነበር፡፡ ብቻ አላህ ይክፈልህ፡፡›› ከአይኖቿ የእንባ ዘለላዎች ተሸቀዳደሙ፡፡ ‹‹አይዞሽ በቃ … ዛሬ የደስታ ቀን ነው የምን ለቅሶ ነው፡፡›› ሊያረጋጋት ሞከረ፡፡ አባቷም በስስት ያዩዋቸዋል፡፡ ልባቸው እርብሽ ብሏል፡፡ ዳግም ተጋብተው ቢኖሩላቸው ምኞታቸው ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ደግነቱን ካዩ በኋላ ሲመጣ እንደ ታናሽ ይሽቆጠቆጡለታል፡፡ ከውሰር እንደው በሆነ ተዓምር ቢሆንላትና … ላግባሽ ቢላት ደስ ይላታል፡፡ አብረው አምስት ልጆቻቸውን ቢያሳድጉ ትመኛለች፡፡ እሱም ለሷ ጥላቻ የለውም፡፡ ግን እምነት ከተሰበረ መልሶ መጠገኑ ከባድ ነው፡፡ በምግብ መርዝ የሰጠችውን ሴት መልሶ ቢያገባ እንዴት የምታቀርብለት ምግብ እሺ ብሎ ጎሮሮውን ያልፍለታል? እንዴት ከእቅፉ ሆና በደህንነት መንፈስ እንቅልፍ ያሸልባል? ለልጆቹ ሲል ቢያደርገው ደስ ይለው ነበር፡፡ ግን ውስጡ እሺ ሊለው አልቻለም፡፡ በመልካም መለያየት … ጥሩ ግንኙነት ያላቸው ወላጆች ብቻ ሆነው ልጆቻቸውን በመግባባት ማሳደግን መርጧል፡፡ ሰዓቱ ሲገፋ ሰው እየመጣ ምሳውን መብላት ጀመረ፡፡ ቤተሰቦቿ ሰደቃው እኛ ቤት ካልሆነ አላሉም፡፡ ለነሱ ሁለቱም የራሳቸው ቤት ሆኗል፡፡ የዛሬን አያድርገውና ከውሰርም ሚስቱ የነበረች ሴት ናት፡፡ አይ ስህተት! የቀድሞ ሚስት ተባለች፡፡ ‹‹አብደላላላላ!›› ‹‹እንዴ!›› ‹‹እንዴት ነህ?›› ‹‹አለሁልህ!›› ‹‹የድሮ ሚስትህ ተፈታችልሀ!›› ‹‹አንተ ፍታ ባክህ!›› ከውሰር እንደማትወደው ስላሰበ ወደ ሰደቃው አምረላን አልጠራውም ነበር፡፡ ሆኖም ሰምቶ መጣ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ደግሞ ብትተዋቸውም አይተዋችሁም፡፡ አምረላ ከሆስፒታል ከወጣ በኋላ ትንሽ አደብ ይዞ ነበር፡፡ ምሳውን ከበላ በኋላ ተጠግቶ ከአብደላ ጋ ማውራት ጀመረ፡፡ ‹‹ደስ ብሎኛል!›› ‹‹ምኑ?›› ‹‹መፈታቷ?›› ‹‹አታስመስል ባክህ!›› ‹‹እውነት የምሬን ነው!›› ‹‹ከዚህ በኋላ ከውሰር አጠገብ ባይህ ጓደኝነታችን ይቋረጣል እወቅ!›› ‹‹ኧረ ምን አገናኝቶን … ረሳታለሁ ከዚህ በኋላ! ባይሆን ሳልነግርህ?›› ‹‹ምን?›› ‹‹ላገባ ነው!›› ‹‹ደሞ እንደገና?›› ‹‹አዎ!›› ሳቀ፡፡ አንዳንድ ሰው ደግሞ ከስህተቱ አይማርም! እንዲህ ያለ ኃላፊነት የማይሰማው ሰው እስካለ ድረስ የሚስኪን ሴት ህይወት መበላሸቱ ይቀጥላል፡፡ ተፈፀመ፡፡
4 305
20
ማለፊያ (ፉአድ ሙና) ክፍል ሀያ *** አንዳንዱ ስሜት እንጂ አዕምሮ አልታደለም፡፡ ለራሱ ደስታ እንጂ ለሌሎች ሀዘን ግድ የለውም፡፡ ጥፋቱም በራሱ አይገደብም፡፡ እሱ የጀመረው ጥፋት በራሱ እንዲቆም አይፈልግም፡፡ የሚያውቃቸውን ሁሉ ወደ ጥፋቱ ያሰማራል፡፡ የአምረላም ጉዳይ ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ ‹‹በዲኑ ተፈቅዷል … መብቴ ነው፡፡›› ‹‹ምንድነው በዲኑ የተፈቀደው? ደስ እንዳለህ መፍታት?›› ‹‹አዎ ለመፋታት ምክንያት አቅርብ አልባልም … ከደበረችኝ መፍታት እችላለሁ፡፡›› ‹‹የተፈቀደ ነገር ሁሉ ይተገበራል እንዴ?›› አብደላ ይራከረዋል፡፡ ‹‹ከተፈቀደ ተፈቀደ ነው፡፡›› ‹‹አሁን ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኋላ ፈተሀት … የሷ ህይወት ምን ሊሆን እንደሚችል ግን ለአፍታ አስበኸዋል?›› ‹‹ይፈቀዳል በቃ አትጨቅጭቀኝ!›› ‹‹የፈረስ ስጋ ትበላለህ? የጅብ ስጋስ? ባመጣልህ ትበላለህ?›› ‹‹አዑዙቢላህ ለምንድነው የምበላው?›› ‹‹ይፈቀዳል በዲኑ!›› ‹‹ምኑ?›› ‹‹መብላቱ ነዋ!›› ‹‹ኧረ የማይባል አትበል!›› ‹‹አንተም ስለምትችል ብቻ ማድረግ የለብህም፡፡ ኃላፊነት ሊሰማህ ይገባል፡፡ አንተ የምታደርገው ነገር እህትህ ላይ ቢደረግ የማያስቆጣህ መሆን አለበት፡፡ ራስህን ካልገደብክ ስሜት አይገደብም፡፡ ወንድነትህ ሺህ ሴትም ብታቀርብለት ጨምርልኝ ከማለት አይቆጠብም፡፡ ስለዚህ ራስህም ሰክነህ … ለልጆችህ ነገ የሚበጅ ነገር ማመቻቸቱ ላይ ብትበረታ ይሻላል፡፡›› ‹‹ተው ባክህ ያላገባህ አታመስል!›› ‹‹ማግባት ችግር የለውም፡፡ በአግባቡ ኃላፊነቱን ለሚወጣና ለስሜቱ መወጣጫ ብቻ ለማያደርገው ሰው ችግር የለውም፡፡ አንተ ግን ሀቃቸውን እንኳን በአግባቡ አልጠበቅክ፡፡ አግብተህ አስወልደህ ትፈታታለህ? ከሞቀ ቤቷ አውጥተህ … ድንግልናዋን ወስደህ ልጅ አስወልደህ ምንም ሳታደርግህ መፍታት ምን የሚሉት ድንቁርና ነው?›› ‹‹ባክህ የሚመጣው ሳምንት ሽምግልና አለኝ ተዘጋጅ ባይሆን!›› ‹‹ለምኑ?›› ‹‹በሷ ቦታ አንዲት ቆንጅዬ ልጅ አግኝቻለሁ … ላገባ ነው፡፡›› ‹‹የለሁበትም!›› ‹‹ምኑን?›› ‹‹እኔ ለቀጣይዋ ህይወቷን ለምታበላሻት ሴት ሽማግሌ ሆኜ አልሄድም፡፡›› ‹‹አብደላ ግን እየተቀየርክ ነው፡፡›› ‹‹አዎ ተቀይሬያለሁ፡፡ ሲጀመር የኔን ህይወት ራሱ እንደዚህ ችግር ውስጥ የከተተው ያንተ ምክር ነው፡፡›› ተጨቃጭቀው ተለያዩ፡፡ አብደላ አምረላ በሴቶቹ ላይ በሃይማኖት ሽፋን የሚያደርሰው ጥቃት ሰላም ነስቶታል፡፡ ህይወቱን አብሮ ሊዘልቅ ሳይሆን የተወሰነ አብሯቸው ቆይቶ ለመለያየት የሚያገባ ይመስላል፡፡ እህት ያለው ሰው እንዴት ይህን በሌላ ሰው እህት ላይ ያደርጋል? ከራሱ የደቂቃዎች ደስታ አሻግሮ ትንሽ እንኳን የሌሎችን ህመም ማየት እንዴት ይሳነዋል? አምረላ ግን ልቡ ሳይታወር አልቀረም፡፡ የሴት ልጅ ለቅሶ ጌታው ፊት እንደሚያስጠይቀው የዘነጋ ይመስላል፡፡ ‹‹ባክህ ፈታኋት የምን መከራ ነው!›› አንዱ ጓደኛው አብደላ ጋ መጥቶ እያወጋው ነው፡፡ ‹‹የቷን ፈታህ?›› ‹‹ሁለተኛዋን ነዋ!›› ‹‹ለምን?›› ‹‹መደባበቁ ሰላም ነሳኝ፡፡ ትኩረቴም እሷ ላይ ሆኖ ስራ እየተበላሸ ነው፡፡ አርፌ ከሚስቴ ጋ በሰላም ልኑርበት!›››› ‹‹እና አሁን ያገባሀት ልጅ ምን ትሆናለች?›› ‹‹ልጅ አልወለደችም … ምን ትሆናለች!›› ‹‹አግብታ የፈታች አላደረግካትም? ድንግልናዋንስ አልወሰድክም?›› ‹‹መህር የከፈልኩት ለሱ አይደል?›› ‹‹መህሩ ይጠግናት ይመስልሀል?›› ‹‹ካልሆነ ደህና ስራ አስጀምራታለሁ እንጂ እንደዚህ አልቀጥልም ባክህ!›› ‹‹ባይተካላትም ቢያንስ እንደሱ አድርግ! ለሚወርድ ዱላ … የስንቱን ህይወት አወረድን?›› ‹‹እኔም ከጅምሩ ባልገባንበት ነው ያስባለኝ! በአግባቡ ወንድ ሆነን ተጋፍጠን እኩል ላናስተዳድር የሴቶቹን ህይወት አበላሸነው፡፡ በተለይ አምረላ ሴቱን ፈጅቶ አስፈጀን!›› ከጥቂት ቀናት በኋላ አብደላ ሱቅ ሆኖ ስልክ ተደወለለት፡፡ ጓደኛው ነበር፡፡ ‹‹ሀጂ …›› ‹‹አብደላ ባክህ ጉድ ሆነናል!›› ‹‹ምን ተፈጠረ?›› ‹‹አምረላ!›› ‹‹አምረላ ምን ሆነ?›› ‹‹ባለፈው የፈታትን ልጅ አወቅካት?›› ‹‹አዎ!›› ‹‹ወንድሟ ትንሽ ዱርዬ ነገር ነው፡፡›› ‹‹እና?›› ‹‹እናማ …›› ‹‹እናማ ምን ቶሎ ተናገር እንጂ!›› ‹‹ማታ ወደ ቤት ሲገባ ጠብቆ በሩ ላይ አስወጋው!›› ‹‹ኧረ በአላህ? እና እንዴት ነው አሁን?›› ‹‹ሆስፒታል ተኝቷል፡፡ አንተ የታከምክበት ሆስፒታል፡፡›› ‹‹እና ልጁ ተያዘ?›› ‹‹አልተያዘም … እሱ አይደለም የወጋው … ልጆቹም አምልጠዋል፡፡›› ‹‹እሱ መሆኑን እንዴት አወቃችሁ?›› ‹‹ነግሮት ነበር … የእህቴ እንባ እንደፈሰሰ ያንተ ደም ይፈሳል ብሎ ዝቶበት ነበር፡፡›› ‹‹መጣሁ በቃ!›› አብደላ መኪናውን አስነስቶ ወደ ሆስፒታሉ አቀና፡፡ ተኝቶ ወደታመበት ሀኪም ቤት ሰው ሊጠይቅ እየነዳ ሄደ፡፡ አላህ ምን ይሳነዋል! *** ቀናት መቁጠራቸው አይቆምም፡፡ የማይደርሱ የሚመስሉት ቀናት ይደርሳሉ፡፡ በትዕግስት ብዙ እሾሀማ መንገዶች ይታለፋሉ፡፡ ለዚህ ቀን ለመድረስ በመከራ ውስጥ አልፋለች፡፡ ከከውሰር መታሰር በኋላ የአብደላ ልጆች በከውሰር እህቶች ጠባቂነት ቤታቸው ናቸው፡፡ አብደላ እየተመላለሰ ያያቸዋል፡፡ ቤቱ የአብደላ ስለሆነ የሚያስጨንቃቸው ነገር አልነበረም፡፡ አስፈላጊ ወጪዎችንም እንደ አባትነቱ ከሚያስፈልገው በላይ ስለሚያደርግ ችግር አይተው አያውቁም፡፡ ግን የእናት ናፍቆት … እናትን በፍርግርግ መሀል አይቶ መመለስ … እሱ ለልጆችም ህመም አለው፡፡ ‹‹ኮርቼብሻለሁ፡፡›› ‹‹ምን ያህል?›› ‹‹በጣም እጅግ በጣም!›› ‹‹አንተ ባታበረታኝ … ባታግዘኝ … አይሳካም ነበር፡፡›› ‹‹እኔማ እንደውም መከራ ሆንኩብሽ! ያንቺ ብርታት ነው፡፡›› ‹‹እወድሀለሁ፡፡›› ‹‹እኔም በጣም እወድሻለሁ፡፡›› እቅፉ ውስጥ ተመሸገች፡፡ የምርቃት ኮፍያዋን ጭንቅላቱ ላይ አደረገችው፡፡ አዲስ ሙሽራ ይመስላሉ፡፡ እሱም ለዶክተሯ ሚስቱ ምርቃት ሙሽራ መስሎ ተገኝቷል፡፡ ለሷ ያለውን ቦታ የሚያሳይ ነው፡፡ ሲሀም አብደላ የሰጣትን አበባ አቅፋ ወደ መኪናው ሄዱ፡፡ አዳራሽ ውስጥ መግባት የሚችለው አንድ አስመራቂ ብቻ ስለነበር ሌሎቹ ቤቷ እየጠበቋት ነው፡፡ መኪናው ውስጥ ገብተው ወደ ቤታቸው ነዱ፡፡ ቤት ውስጥ ሲገቡ የሁለቱም ቤተሰብ ተሰብስቦ እየጠበቃቸው ነበር፡፡ የተደኮነው ድንኳን ለምርቃት ነው ቢባል ለማመን ይከብዳል፡፡ አብደላ ሰርጓን ያዘለለበትን ቀዷ እያወጣ ይመስላል፡፡ የመኪናው ብዛት ሲታይ ምርቃት ነው ብሎ ለማን ይጠናል፡፡ ምግቡ የተዘጋጀው ‹በኬተሪንግ› ድርጅት ነው፡፡ ያልቀረበ የምግብ አይነት የለም፡፡ በዚህ ሁሉ ችግር ውስጥ ጠንክራ እዚህ የደረሰችውን ሚስቱን ለማስደሰት አብደላ የቻለውን ያህል ተግቷል፡፡ ምግቡ ተበልቶ አስር እንዳለፈ የኬክ መቁረስ ስነ-ስርዓት ተካሄደ፡፡ ልክ ኬኩ ሊቆረስ ሲል አብደላህ ከጃኬት ኪሱ ውስጥ የቀለበት ማስቀመጫ አውጥቶ ከፈተ፡፡ ‹‹እንደምታውቁት ከሚስቴ ጋር እንዲህ እናንተ በተሰበሰባችሁበት በደመቀ መልኩ ሰርግ አላደረግንም፡፡ ይህ ደግሞ ለሲሀም የምርቃት ቀን ብቻ ሳይሆን ለኛም የሰርጋችን ቀን ነው፡፡ እና ለውዷ ሚስቴ ቀለበት እንዳጠልቅ ፍቀዱልኝ፡፡››
3 372