fa
Feedback
Dire Dawa Government Communication Affairs Office

Dire Dawa Government Communication Affairs Office

رفتن به کانال در Telegram

government organization

نمایش بیشتر
1 773
مشترکین
+224 ساعت
+57 روز
+3530 روز
آرشیو پست ها
#ዜና /ቅርሶችን የመጠበቅ እና የመንከባከብ ሚና የሁሉም ሀላፊነት ሊሆን እንደሚገባ ተገለፀ #DGC ሰኔ 25/2018 የኢትዮጲያ ቅርስ ባለስልጣን የድሬዳዋ ምድር ባቡር እና የቀፊራ የገበያ ስፍራን የ
+4
#ዜና /ቅርሶችን የመጠበቅ እና የመንከባከብ ሚና የሁሉም ሀላፊነት ሊሆን እንደሚገባ ተገለፀ #DGC ሰኔ 25/2018 የኢትዮጲያ ቅርስ ባለስልጣን የድሬዳዋ ምድር ባቡር እና የቀፊራ የገበያ ስፍራን የዲዛይን ጥናት ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት በዛሬው እለት ከዳሎል ሆልዲንግስ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ጋር አድርጓል ። በድሬዳዋ አስተዳደር በርካታ ቅርሶች እና ታሪካዊ ስፍራዎች መኖራቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንሸስትመንት ቢሮ ምክትል ሀላፊና አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኤጀንሲ ሀላፊ የሆኑት አቶ ኡስማን አህመድ ተናግረው በተለይም ደግሞ የቱሪዝም መዳረሻ የሆኑትን የድሬዳዋ ምድር ባቡር እና የቀፊራ የገበያ ስፍራ የዲዛይን ጥናት መደረጉ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል ። የኢትዮጲያ ቅርሶች ባለስልጣን ቅርሶችን ከመመዝገብ አንስቶ ቅርሶችን የመጠገን ስራዎችን ሲረራ መቆየቱን የኢትዮጲያ ቅርስ ባለስልጣን የቅርስ ዘርፍ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ወ\ሮ ህይወት ሀይሉ ተናግረው የምድር ባቡር እንዲሁም ደግሞ የቀፊራ ገበያ ስፍራን የዲዛይን ጥናት በማድረግ ለአስተዳደሩ እንደሚያስረክቡም ነው ወ\ሮ ህይወት ያስታወቁት ። የኢትዮጲያ ቅርስ ባለስልጣን ከዚህ ቀደም የለገኦዳ ሼልተር እና የድሬዳዋ አስተዳደር ምድር ባቡር ተርሚናልን የጥገና ስራ መስራታቸውን የድሬዳዋ አስተዳደር ባህል እና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ወንደሰን አባይ ተናግረው የቀፊራ የገበያ ስፍራ እና የምድር ባቡርን የዲዛይን ጥናት ለማድረግ በመምጣታቸው ምስጋናቸውን በእለቱ አቅርበዋል ። በአለማየሁ አበበ ፎቶ :- በአገኘሁ ሸዋረጋ

የአርሶ አደሩን ክብርና ምቾት ያረጋገጠው ዘመናዊው የሀማሳ ሞዴል መንደር ተመረቀ ******* ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ79.4 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውንና የገጠር ኮሪደር ልማት አ
+9
የአርሶ አደሩን ክብርና ምቾት ያረጋገጠው ዘመናዊው የሀማሳ ሞዴል መንደር ተመረቀ ******* ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ79.4 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውንና የገጠር ኮሪደር ልማት አካል የሆነውን ዘመናዊውን የሀማሳ ሞዴል መንደር ዛሬ በይፋ መርቀዋል። ይህ አዲስ የሞዴል መንደር ግንባታ የአርሶ አደሩን ኑሮ ይበልጥ ለማዘመንና ምርታማነቱን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ታስቦ የተገነባ ነው። መንደሩ አርሶ አደሩን ከተለመደው አኗኗር በማላቀቅ፤ ዘመናዊ የመታጠቢያ ክፍሎች፣ የእንስሳት ማደሪያዎች፣ የጓሮ አትክልት ስፍራዎች፣ የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ እና ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለነዋሪዎቹ ሁለንተናዊ ብልጽግናን እንደሚያረጋግጥ ተገልጿል። "ይህ ሞዴል መንደር የገጠሩን ማኅበረሰብ ክብር፣ ምቾት እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ የሪፎርማችን ሕያው ፍሬ ነው" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፕሮጀክቱን ሀገራዊ ትርጉምና ፋይዳ ገልጸዋል።

የአረንጓዴ ዐሻራ ሳይንሳዊ እውነታዎች፦ 6ቱ የውኃ ጸጋዎቻችን ***** የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ ዛፎችን ከመትከል ባለፈ፣ የሀገራችንን የውኃ ሀብት ዘላቂነት የሚያረጋግጡ ሳይንሳዊ ጠቀሜታዎችን ይዟል።
የአረንጓዴ ዐሻራ ሳይንሳዊ እውነታዎች፦ 6ቱ የውኃ ጸጋዎቻችን ***** የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ ዛፎችን ከመትከል ባለፈ፣ የሀገራችንን የውኃ ሀብት ዘላቂነት የሚያረጋግጡ ሳይንሳዊ ጠቀሜታዎችን ይዟል። ጥቅሞቹም፦ የከርሰ-ምድር ውኃን በመሙላት የውኃ እጥረትን የሚቀርፍ ሲሆን፣ አርሶ አደሮች በዓመት ከ2 እስከ 3 ጊዜ በስፋት እንዲያመርቱ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። አስከፊ የጎርፍ አደጋዎችን ከመከላከል ባለፈ፣ ወደ ግድቦች የሚገባውን ደለል በመቀነስ የግድቦቻችንን ዕድሜ ያራዝማል። በተጨማሪም እንደ ተፈጥሯዊ የውኃ ማጣሪያ ሆኖ በማገልገል የንጹህ ውኃ አቅርቦትን ያሻሽላል፤ እንዲሁም የዝናብ ዑደትን በማፋጠን የአየር ንብረት መዛባትን ይቋቋማል። ይህ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ የውኃ ዋስትናችንን እና የተፈጥሮ ሚዛናችንን ለመጠበቅ የምናደርገው የህልውና ጉዞ ነው። #GreenLegacy #Ethiopia #WaterResources #ClimateResilience

ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው፡- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት *** ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስ፣ አካታችና ስልታዊ የምክክር ምዕራፍ ላይ ት
ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው፡- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት *** ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስ፣ አካታችና ስልታዊ የምክክር ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ይህ ምዕራፍ ለዘመናት የዘለቁ መዋቅራዊና ፖለቲካዊ ልዩነቶችን በሕዝቦች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለመፍታት፣ በሰለጠነ የውይይት መድረክ ላይ የጋራ ብሔራዊ መግባባትን ለመገንባት የሚያስችል ታሪካዊ ዕድል ነው። ለረጅም ጊዜ በውስጥ ሽኩቻዎችና በቅሬታዎች የተተበተበውን የፖለቲካ ባህል በመቀየር፣ አካታችነትንና ብሔራዊ መግባባትን የሉዓላዊነትና የብልጽግና ዋነኛ መሠረት የሚያደርግ ራዕይ ዛሬ በተጨባጭ እየተተገበረ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ሀገራዊ ምክክር ለኢትዮጵያ የምርጫ ጉዳይ ሳይሆን፣ ጠንካራ፣ ሉዓላዊና የተረጋጋ ሀገርን መገንባት የሚጠይቅ ታሪካዊ ግዴታ ነው። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ብዝኃነት፣ የተለያዩ ባህሎችና የፖለቲካ አመለካከቶች ባሉባቸው ሀገራት ውስጥ፣ የአንድ ወገንን ሐሳብ ብቻ በመጫን መጓዝ ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ አይችልም። ስለዚህ የሀገራዊ ምክክሩ አስፈላጊነት ከመቼውም ጊዜ በላይ ጎልቶ ይታያል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ይፋ ያደረጋቸው ስምንቱ ዋና ዋና የምክክር አጀንዳዎች፣ ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎችና ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተሰበሰቡ የኢትዮጵያውያን ድምፆች፣ ተስፋዎችና የወደፊት ራዕዮች ማንጸባረቂያ ናቸው። የእነዚህ አጀንዳዎች ስኬታማነት ወደ ተግባር የመቀየር ሂደት የአንድ ወገን ብቻ ኃላፊነት ሳይሆን፤ የሁሉንም ኢትዮጵያውያን በጎና ንቁ ተሳትፎ የሚጠይቅ ነው። ሰኔ 25፣ 2018፣ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ኢትዮጵያ ***** ደቡብ ኢትዮጵያ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን በውብ የባህል ቀለም እና እሴት ደምቃ ተቀብላቸዋለች!
+9
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ኢትዮጵያ ***** ደቡብ ኢትዮጵያ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን በውብ የባህል ቀለም እና እሴት ደምቃ ተቀብላቸዋለች!

በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ
+9
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል። ● ‌‎ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 7ኛው አጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትውልድ ስፍራቸው በሻሻ ወረዳ በመገኘት ድምጻቸውን የሰጡ ሲሆን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክትም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ እና ለሀገር ፍቅር ላሳየው ቁርጠኝነትና ለከፈለው መስዋዕትነት ታላቅ አድናቆታቸውን ገልጸዋል። ይህንኑ አስመልክቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም የምርጫ ውጤቱን በይፋ ያወጀ ሲሆን በተመዘገበው ስኬት የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት እንዲሁም የሀገራት መሪዎች የደስታ መግለጫና የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክቶችን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አድርሰዋል። ● አረንጓዴ ዐሻራ የ2018ዓ.ም አረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ማስጀመሪያ በሰኔ ወር የተከናወነ ሲሆን ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ በዚሁ ኩነት ላይ ተገኝተው ዐሻራቸውን በማሳረፍ የዚህን ዓመት ሀገር አቅፍ ንቅናቄ በይፋ አስጀምረዋል። በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን መርሃ-ግብሩ ቀደም ሲል ከታለመለት 48 ቢሊዮን ችግኞች ግብ ወደ 65 ቢሊዮን ችግኞች ከፍ ብሏል። ለዚህም ትልም መሳካት ‘’ተስፋን እንትከል’’ በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ሀገር አቀፍ ኩነቶች ላይ ዜጎችና መሪዎች በጽናት ዐሻራቸውን በማሳረፍ ላይ ይገኛሉ። #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ፤ የአፍሪካ ትልቁ የሉዓላዊ ሀብት ፈንድ እና የመደመር መንግሥት ስትራቴጂያዊ የኢንቨስትመንት ክንፍ የኢትዮጵያን የወደፊት ዕድል የሚቀርፁ ልማቶች እያንቀሳቀሰ ይገኛ
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ፤ የአፍሪካ ትልቁ የሉዓላዊ ሀብት ፈንድ እና የመደመር መንግሥት ስትራቴጂያዊ የኢንቨስትመንት ክንፍ የኢትዮጵያን የወደፊት ዕድል የሚቀርፁ ልማቶች እያንቀሳቀሰ ይገኛል። #PMOEthiopia #EthiopiaDelivers

#ሾዴኬሎ - የተፈጥሮ ሀብት ዘብ ካፋ ምድር ለአያሌ ዘመናት ከነክብሯ ተጠብቃ የኖረችው ድንቅ ተፈጥሮ ያላት በማራኪ ውበቷና በምትመግበው ንጹህ አየሯ የሰውን ልጅ ስሜትን እንደተቆጣጠረች ዛሬም አለች።
+3
#ሾዴኬሎ - የተፈጥሮ ሀብት ዘብ ካፋ ምድር ለአያሌ ዘመናት ከነክብሯ ተጠብቃ የኖረችው ድንቅ ተፈጥሮ ያላት በማራኪ ውበቷና በምትመግበው ንጹህ አየሯ የሰውን ልጅ ስሜትን እንደተቆጣጠረች ዛሬም አለች። አረንጓዴ ምድር፣ ጉምና የማለዳ የአዕዋፋት ዝማሬ የማይለየው ጫካ፣ የሚፍለቀለቁ ምንጮች፣ ተፈጥሮ ያበጀቻቸው ድልድዮች፣ ቡና እና ቅመማ ቅመምን የካፋ ጥብቅ ደን ድንቅ የተፈጥሮ በረከቶች ናቸው። በልምላሜዋና በውብ ተፈጥሮዋ ዓለም የሚያውቃት ካፋ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ተቋም (ዩኔስኮ) የካፋ ባዮስፌር ሪዘርቭን አስመዝግባለች። ከ760 ሄክታር በላይ የሚሸፍነው የካፋ ባዮስፌር ሪዘርቭ በዓለም በብዝሃ ሕይወት ከሚታወቁ ጥቂት ስፍራዎች አንዱ ሲሆን፤ በውስጡ ከ250 በላይ የእፅዋት ዝርያዎችን፣ 300 አጥቢ እንስሳትንና ከ300 በላይ አዕዋፋትን፣ እድሜ ጠገብ እናት የጫካ ቡና፣ የአፍሪካ ቀይ እንጨት፣ ቀርከሃና ሌሎች ሀገር በቀል ዛፎችን ይዟል። ይህ የካፋ ድንቅ ተፈጥሮ ለዘመናት ተጠብቆ ዛሬ ላይ የደረሰው ስለሚመጣው ትውልድ ያሰቡ የካፊቾ ማህበረሰብ ተፈጥሮን በመጠበቅ፣ ጠብቆ ለትውልድ በማቆየት አንዱ የህይወታቸው አካላቸው አድርገው በመኖራቸው ነው። የካፊቾዎች ህይወት ከጥንት እስከ ዛሬ ከደን ጋር በጥብቅ የተቆራኘ መሆኑን የሚገልጹት የብሔረሰቡ ባህል አዋቂ አቶ ወርቁ ወልደማሪያም፤ ለካፊቾዎች ደን የሁለንተናዊ ማንነታቸው መገለጫ በመሆኑ በልዩ ክብር ይጠብቁታል። ህይወትን ከተፈጥሮ ደን ጋር ያቆራኙት ካፊቾዎች ደንን ጠብቀው ያቆዩበት ሀገር በቀል ዕውቀትና ባህል በአረንጓዴ ዐሻራ አማካኝነት አረንጓዴ እየለበሰች ለምትገኘው ኢትዮጵያ ድንቅ ተሞክሮ ይሆናል። ምንጭ: FBC

#ዜና | የመደመር እሳቤ የተገለጠበት የወንጪ-ደንዲ ኢኮ-ቱሪዝም የወንጪ-ደንዲ ኢኮ-ቱሪዝም ፕሮጀክት ዋነኛ የቱሪዝም መስህብ ከመሆን ባለፈ የዜጎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን አረጋግጧል፡፡ #DGC | ሰኔ
+5
#ዜና | የመደመር እሳቤ የተገለጠበት የወንጪ-ደንዲ ኢኮ-ቱሪዝም የወንጪ-ደንዲ ኢኮ-ቱሪዝም ፕሮጀክት ዋነኛ የቱሪዝም መስህብ ከመሆን ባለፈ የዜጎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን አረጋግጧል፡፡ #DGC | ሰኔ 23/2018 ከአዲስ አበባ በ150 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ወንጪ ከባህር ጠለል በላይ 3 ሺህ 380 ሜትር ከፍታ ላይ ሲገኝ ሐይቅና ፍል ውሃን ጨምሮ እጅግ ማራኪ የሆኑ የተፈጥሮ ሀብቶችን የያዘ ድንቅ የቱሪስት መዳረሻ ነው። በአካባቢው የሚገኘው ደንና በውስጡ ያሉት ብርቅዬ አዕዋፋት ዝማሬ የጎብኚዎችን ቀልብ የሚስቡና አዕምሮን ዘና የሚያደርጉ ናቸው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ተጀምረው እውን ከተደረጉ የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው የወንጪ ፕሮጀክት ቱሪስቶችን በስፋት እየሳበ ይገኛል። የአካባቢው ማህበረሰብም የቱሪስቶችን ቆይታ ለማራዘም የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ተግባራትን ያከናውናሉ። በዚህም በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ከመሆን ባለፈ ባህልና እሴትን ለማስተዋወቅ እየተጠቀሙበት ነው። ከወሊሶ አምቦ፤ ከወንጪ ደንዲ፤ ከደንዲ አስጎሪ ሰፊ የሆነ ቦታ ላይ በምዕራፍ ተከፋፍሎ እንዲገነባ የተቀረጸ ሰፊ ራዕይ ያለው ትልቅ ሀገራዊ የልማት ዐሻራ የሆነው ፕሮጀክቱ፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥር 4 ቀን 2016 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል። የፕሮጀክቱ የግንባታ ሂደት ብቻ ከ10 ሺህ ለሚበልጡ የአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፤ ከቱሪስት መዳረሻነት ባሻገር ለአካባቢው የማያቋረጥ የሥራ ዕድልና ልማት እያስገኘ ነው። ለአብነትም በ22 ማኅበራት ለተደራጁ ከ560 የሚበልጡ ወጣቶች በተለያዩ ዘርፎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተሰርቷል። ምንጭ: FBC

የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን የማዕድን ዘርፍ አቅም የከፈተ ሲሆን፣ የብሔራዊ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ እያደረገው ይገኛል!
የመደመር መንግሥት የኢትዮጵያን የማዕድን ዘርፍ አቅም የከፈተ ሲሆን፣ የብሔራዊ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ እያደረገው ይገኛል!

#ዜና | በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አሰራር በመዘርጋት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በፍጥነት ለመመለስ በርብርብ እና በቅንጅት እንደሚሰራ ተገለፀ #DGC | ሰኔ 23/2018 የድሬዳዋ አስ
+9
#ዜና | በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ አሰራር በመዘርጋት የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በፍጥነት ለመመለስ በርብርብ እና በቅንጅት እንደሚሰራ ተገለፀ #DGC | ሰኔ 23/2018 የድሬዳዋ አስተዳደር የመልካም አስተዳደር የህዝብ ቅሬታና አቤቱታ ጽሕፈት ቤት የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የተቋማትና ወረዳዎች የመልካም አስተዳደር ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሂዷል። በዚህ የግምገማ መድረክ ላይ ከተገልጋዩ ማህበረሰብ የሚነሱ የመሰረተ ልማት እና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት አሰራሮችን ፈጣን እና ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ በትኩረት እንደሚሰራ ተመላክቷል። የድሬዳዋ አስተዳደር የመልካም አስተዳደር እና የህዝብ ቅሬታ አቤቱታ ጽ/ቤት የመልካም አስተዳደር ችግሮች ጥናት፣ ክትትል እና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግርማ ዘለቀ እንደገረጹት፤ በበጀት ዓመቱ የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ዕቅዶችን በየጊዜው በመገምገም እና በማጽደቅ የሕዝብ ቅሬታዎች እልባት እንዲያገኙ ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል። ዳይሬክተሩ አያይዘውም በ2019 ዓ.ም ማህበረሰቡ የሚያነሳቸውን የመሰረተ ልማት እና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በግልጽ በመለየት፣ አሰራሮችን ዘመናዊና ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው አብራርተዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በየተሰማሩበት የሴክተር ተቋማት እና ወረዳዎች ከማህበረሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን እና የሕዝብ ቅሬታዎችን በፍጥነት ለመመለስ በቅንጅት እና በርብርብ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም በቀጣዩ በጀት ዓመት የውስጥና የውጪ የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶችን በቴክኖሎጂ በመደገፍ የሕዝቡን እርካታ ለማምጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አመላክተዋል። በኤደን ሳሙኤል ፎቶ፦ ሰላም አበበ

የኢትዮጵያን የግብርና አብዮት እውን ያደረገው ምን እንደሆነ ይረዱ። #PMOEthiopia #EthiopiaDeliver
የኢትዮጵያን የግብርና አብዮት እውን ያደረገው ምን እንደሆነ ይረዱ። #PMOEthiopia #EthiopiaDeliver

#ዜና | "የተጠበቁ ህጻናት ለበለጸገ ትውልድ" በሚል መሪ ሀሳብ የአፍሪካ የህጻናት ቀን በአስተዳደሩ በድምቀት ተከበረ #DGC | ሰኔ 23/2018 በድሬዳዋ አስተዳደር ሴቶች፣ህጻናት እና ማህበረዊ ጉ
+9
#ዜና | "የተጠበቁ ህጻናት ለበለጸገ ትውልድ" በሚል መሪ ሀሳብ የአፍሪካ የህጻናት ቀን በአስተዳደሩ በድምቀት ተከበረ #DGC | ሰኔ 23/2018 በድሬዳዋ አስተዳደር ሴቶች፣ህጻናት እና ማህበረዊ ጉዳይ ቢሮ አዘጋጅነት በአፍሪካ ለ36ኛ በኢትዮጵያ ለ35 ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው የአፍሪካ የህጻናት ቀን የማጠቃለያ መርሃግብር በድምቀት ተካሂዷል። በእለቱም ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ሴቶች፣ህጻናት እና ማህበረዊ ጉዳይ ቢሮ ተወካይና የሴቶች ማሳተፍ ማብቃትና ስርዓተ-ጾታ ስርጸት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍሪ ጥበቡ በዓለም አቀፍ እና በአፍሪካ ደረጃ የሚከበረው የህፃናት ቀንን ከመዘከር ባለፈ ህፃናት ላይ የሚደርሱ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች፣ የመብት ጥሰቶችና ጥቃቶችን ለማስወገድ፣ ሰብዓዊ መብቶቻቸውንና ደህንነታቸውን ለማስጥበቅ ሀገራት ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ለማድረግም ጭምር እለቱ እንደሚከበር ተናግረዋል። እንደ አስተዳደርም የለውጥ አመራሩ ለህጻናት ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶት የመብት ማስከበርና ደህንነትቸውን ለማስጠበቅ፣ የአማራጭ የድጋፍና እንክብካቤ ፕሮግራሞችን በማስፋፋት በኩል በርካታ ስራዎችን እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የህፃናት ፓርላማ አፈ ጉባኤ ህጻን ብሌን ድልአድርጋቸውም በአፍሪካም ሆነ በኢትዮጵያ በተለያዩ ሰው ሰራሽና በተፈጥሮ ምክንያት ትምህርታቸውን እንዲያቋርጡ የተገደዱ ህፃናት ዛሬም ደረስ መኖራቸው ጠቅሳ እነዚህን ህፃናት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱና እንዲማሩ ማህበረሰቡና መንግስት ትኩረት ሰጥቶ አንዲሰራበት አበክሬ በኢትዮጵያ ህፃናት ስም እጠይቃለሁ፡፡ ሰላም ለማ ምስል:- አገኘው ሸዋረጋ

#ዜና | በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድ እና ኢንዱሰትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአስተዳደሩን ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮን የእቅድ አፈጻጸም ገመገመ ። #DGC | ሰኔ 22/2018
+9
#ዜና | በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድ እና ኢንዱሰትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአስተዳደሩን ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮን የእቅድ አፈጻጸም ገመገመ ። #DGC | ሰኔ 22/2018 ​የድሬዳዋ አስተዳደር የፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት ያከናወናቸውን አበይት የልማትና የፋይናንስ ተግባራትን የሚያሳይ ዓመታዊ ሪፖርት አቅርቧል። ቢሮው ባቀረበው ዕቅድና ሪፖርት መሠረት በሥሩ የሚገኙ አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶችንና የድጋፍ ሰጪ የሥራ ሂደቶችን በማስተባበር ውጤታማ ሥራዎችን ማከናወኑን አስታውቋል። የአስተዳደሩን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የመንግሥት ታክስ፣ የውስጥ ገቢና ከማዘጋጃቤታዊ የገቢ ምንጮች ሰፊ የገቢ ማሰባሰብ ሥራ እንዳከናወነ እና ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ዘመናዊ የፋይናንስ አስተዳደር ሥርዓትን ለመዘርጋትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ለማሳደግ በርካታ ተግባራት በትኩረት መሰራታቸው ተገልጿል ። የሕዝብና የመንግሥት ሀብት በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል ለማድረግ የውስጥ ኦዲት አሰራርን የማጠናከርና የተገኘ ጉድለትን ወደ መንግሥት ካዝና ተመላሽ የማድረግ ሥራዎች መከናወናቸወን በሪፓርቱ ተመላክቷል ። በተጨማሪም ከምክር ቤት የተሰጡ ግብረ መልሶችን መሠረት በማድረግ፣ በግዥና ንብረት አስተዳደር፣ በዲጂታል አሰራር እንዲሁም በበጀት ዝግጅት ዙሪያ ለብዙ ባለሙያዎች ሰፊ የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎችውን እና በአስተዳደሩ ሥር ከሚገኙ የልማት አጋሮችና ለጋሽ ድርጅቶች የሚገኙ የውጭ ሀብቶችን በማስተባበርና ፕሮጀክቶችን በክትትልና ድጋፍ በመምራት ረገድ በርካታ የካፒታል ፕሮጀክቶች የተጠናቀቁ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ወደ ቀጣዩ በጀት ዓመት እንዲሸጋገሩ መደረጋቸው ተነስቷል ። በፉአድ አሊ ምስል ያብስራ ተክሌ

#ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የ12 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ተገመገመ #DGC | ሰኔ 22/2018 የድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት የከተማ ልማት ኮንስትራክሽን እና ማዘጋጃ
+7
#ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የ12 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ተገመገመ #DGC | ሰኔ 22/2018 የድሬዳዋ አስተዳደር ምክርቤት የከተማ ልማት ኮንስትራክሽን እና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮን የ2018 በጀት አመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፓርት ቀርቦለት ገምግሟል። ​ቢሮው በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን፣ የተመዘገቡ ስኬቶችንና ያጋጠሙ ማነቆዎችን በመለየት በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርጓል። ​በግምገማው ላይ እንደተገለጸው፣ ቢሮው በጀት ዓመቱ የመሬት አቅርቦትን ማሳደግ፣ የመሬት ወረራን መከላከልና መቆጣጠር፣ ካሳ ክፍያና ይዞታ ማረጋገጥ እንዲሁም የከተማዋን የመሬት መረጃ ሥርዓት ዘመናዊ ማድረግ ላይ ትኩረት አድርጎ ሰርቷል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የከተማ ልማት ኮንስትራክሽን እና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ቤዛ ዳምጠው ተቋሙ ከዚህ በፊት በተሰጠው ግምገማ እና አቅጣጫን በማሻሻል የሰራቸውን ስራዎች አድንቀዋል። የቢሮውን የአሰራር ስርዓት ዘመናዊ፣ ፈጣንና ግልፅ ለማድረግ ተቋሙን በቴክኖሎጂ የመገንባት ስራዎች በልዩ ትኩረት የተከናወነ ሲሆን ይህም የህዝብን የእርካታ ደረጃ ለማሳደግና መረጃዎችን በአግባቡ ለመያዝ ያግዛል ተብሏል። የድሬዳዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ካከናወናቸው ተቋማዊ ስራዎች መካከል በህንፃው ላይ የህፃናት ማቆያ ማዘጋጀቱ እጅግ አበረታች ተግባር መሆኑን በመግለፅ በተቋሙ ውስጥ የሚሰሩ እናቶች ስራቸውን በሰላምና በሙሉ ትኩረት እንዲያከናውኑ ትልቅ እገዛ አድርጓል። በተለይም የከተማዋን ገቢ ሊያሳድጉ የሚችሉ ስራዎች ላይ እና የህዝብን እርካታ የሚያረጋግጥ የአገልግሎት አሰጣጥ መዘርጋት የቀጣይ ጊዜ ዋነኛ ትኩረት እንደሚሆን ተጠቅሷል። የድሬዳዋ አ

የ8ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን ተወሰነ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 5
+3
የ8ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን ተወሰነ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን ተወሰነ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ(ዶ/ር) በ2018 የትምህርት ዘመን ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ፣ በዘርፉ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ጠቅሰዋል፡፡ የሒሳብና የእንግሊዘኛ ትምህርትን ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረገው ስትራቴጂ በተማሪዎች ውጤት መረጋገጡ ተነስቷል፡፡ በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ በትምህርት ዘርፉ ላይ ባደረገው ትኩረት ውጤቱ መመዝገቡን የሮው ኃላፊ ገልጸዋል፡፡ ፈተናውን በአጭር ጊዜ በማረም ውጤቱ ይፋ እንዲሆን ቀን ከሌት ሲሰሩ ለቆዩ የፈተና ክፍል ባለሙያዎችና ሂደቱን ሲደግፉ ለነበሩ አመራሮች ምስጋና መቅረቡን ቢሮው ለፋና ዲጂታል አሳውቋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም 85,737 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡ ምንጭ: FBC

"ባሰብነው ልክ ሰርተናል ብዬ አልገምትም፤ ብዙ ማየት ስላልቻልን፣ ብዙም ገንዘብ ስለሚቸግር፣ ሰዎቻችንም ገብቷቸው ማገዝ ገና ስለሆነ በታየው ልክ አይደለም። ከዚህ በላይ ውብ መሆን ይቻላል።" ጠቅላይ
"ባሰብነው ልክ ሰርተናል ብዬ አልገምትም፤ ብዙ ማየት ስላልቻልን፣ ብዙም ገንዘብ ስለሚቸግር፣ ሰዎቻችንም ገብቷቸው ማገዝ ገና ስለሆነ በታየው ልክ አይደለም። ከዚህ በላይ ውብ መሆን ይቻላል።" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

‎#ኢትዮጵያ አንድ ቪዛ፣ ዓለም በውስጧ! ‎ ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኤንቢሲ ኢትዮጵያ (NBC Ethiopia) ጋር ያደረጉትን የአንድ ክፍል ልዩ ቃለ መጠይቅ ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን
+4
#ኢትዮጵያ አንድ ቪዛ፣ ዓለም በውስጧ! ‎ ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኤንቢሲ ኢትዮጵያ (NBC Ethiopia) ጋር ያደረጉትን የአንድ ክፍል ልዩ ቃለ መጠይቅ ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን ከምሽቱ 2:30 ጀምሮ በተለያዩ ሚዲያዎች ይጠብቁን። #PMOEthiopia

እንጦጦ እስከ ቀበና የወንዝ ዳርቻ ሲገለጥ Entoto to Kebena Riverside Unveiled #EthiopiaUnveiled
+9
እንጦጦ እስከ ቀበና የወንዝ ዳርቻ ሲገለጥ Entoto to Kebena Riverside Unveiled #EthiopiaUnveiled

#ዜና | ጥቃቅንነና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለአጠቃላይ ኢኮኖሚው እድገት የሚያበረክቱት ሚና የጎላ መሆኑ ተገለፀ። #DGC | ሰኔ 21/2018 በድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የሞዴል ኢንተር
+9
#ዜና | ጥቃቅንነና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለአጠቃላይ ኢኮኖሚው እድገት የሚያበረክቱት ሚና የጎላ መሆኑ ተገለፀ። #DGC | ሰኔ 21/2018 በድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የሞዴል ኢንተርፕራይዞች የምርቃትና ሽግግር በዓል ተካሂዷል በመድረኩ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ በአገራችን እንዲሁም እንደ አስተዳደር የጥቃቅንና አነስተኛ ዘርፍ ያለውን የስራ አጥነት ችግር በመቀነስ እንዲሁም ዜጎች የራሳቸውን ስራ በመፍጠር ውጤታማ ከመሆን ባለፈ ለሌሎች የስራ እድል እንዲፈጥሩ እያስቻለ እንደሚገኝ ገልፀዋል። ዘርፉ በአንድ ተቋም ጥረት ብቻ አመርቂ ውጤት ለማምጣት እንደማይቻል አውስተው ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት አንደየ አግባቡ የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ አቶ ሀርቢ መልክት አሰወተላልፈዋል። አስተዳደሩ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ከመቅረፍ አኳያ እንደ መፍትሄ የሚቀርቡ እቅዶችን በቀጣይ ተግባራዊ እንዲሆኑ ተገቢውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ምክትል ከንቲባው አመላክተዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው በየዓመቱ የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ምርቃትና ሽግግር እንደሚካሄድ ገልፀዋል። በዛሬው መድረክም በከተማም በገጠርም የተለያዩ ድጋፍ ሲደረግላቸው የቆዩ ኢንተርፕራይዞች የእድገት ደረጃ እውቅና ሰርተፍኬት፣በቅድመ ሞዴልነት ተመልምለው የተደረላቸውን ድጋፍ በአግባቡ ተጠቅመው ወደ ሞዴልነት የተሸጋገሩ ኢንተርፕራይዞች እውቅና ሰርተፍኬት እንዲሁም የተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ድጋፎችን ተጠቅመው የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ አንቀሳቃሾች እውቅና እንደተሰጠ ገልፀዋል። በዳግማዊ ፍቃዱ ምስል: አገኘው ሸዋረጋ