የጥበብ እመቤት 📜
رفتن به کانال در Telegram
╱◥██████◣ │∩│🪟▤│🪟│ ▓▆▇█▓🚪▓█▇ 🍹❤️🔥✨🍁𝐖𝐄𝐋𝐂𝐎𝐌𝐄🍁✨ 𝚜𝚞𝚌𝚌𝚎𝚜𝚜 እንኳን ደህና መጡ ወደ የጥበብ እመቤት "ሕይወት ትጠይቃለች፣ ጥበብ ትመልሳለች " https://Wisdomlady
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
270
مشترکین
+224 ساعت
+107 روز
+15330 روز
آرشیو پست ها
271
የተፃፈልንን ነው የምንኖረው❓
"ህይወታችን አስቀድሞ ተፅፏል፤ ከተፃፈው ውጪ መኖር አንችልም"የ40 ቀን እድል ነው የሚሉ ብዙ አሉ። "እጣ ፈንታዬ ነው" እያሉ ባሉበት መቆየትን የሚመርጡም ጥቂት አይደሉም።
271
የማለዳ ቅኔ
የውጭው ዓለም ጎህ፣በፀሐይ ቢፈካ፣
የውስጥህ ማንነት፣ጨለማን ከተካ፤
ቀኑ ቀን አይሆንም፣ፀሐይ ስለወጣች፣
እውነተኛው ንጋት፣ሰውነትህ ላይ ነች።
የማለዳ ውበት፣ የንጋቷ ጀምበር፤
ተፈለገች ትውጣ፣ ቢሻት በዛው ትቅር፤
በውስጥህ ላይ ያለው፣ ተስፋና ደግነት፤
አብሮ ካልነቃልህ፣ አይኖርህም ሕይወት።
271
ሕልመኛ ነበር። እንደ ሁሉም ወጣት ሀብታም መሆን፤ አዋቂ መሆን፤ ቤተሰቦቹን የመርዳት ሕልም ነበረው። የተንሸዋረረ አራድነት አሳስቶት የለኮሳት ሲጋራ፤ ለሳቅ ብሎ የተጎነጫት አረቄ፣ ለሙድ ብሎ የቀነጠሳት የጫት ቅጠል ስትደጋገም አፈዘዘችው፤ ሕልሙን ወጣትነቱን ክብሩን አረገፈችው።
ማንም ብርቱ ነኝ ቢል ታግሎ የማያስመልሳትን ወጣትነቱን ለማያቀው ጣዖት እየሰዋት ነው።
📚አዎ! እሱ ጋ ያመኛል!
✍️አድሃኖም ምትኩ
271
“When you establish a destination by defining what you want, then take physical action by making choices that move you towards that destination, the possibility for success is limitless and arrival at the destination is inevitable.”
— Steve Maraboli
271
በህይወቴ ብዙ ደስ የሚልና ጠቃሚ ነገሮችን አውቃለሁ፤ ነገር ግን ስለ እኔም ሆነ ስለማደርገው ነገር ሰዎች ምን እንደሚሉ አለመጨነቅን ያህል አርኪና ሙሉ የሚያደርግ ነገር አላቅም እስካሁን።የዉላቹ ክፉ፣ደግ፣አረመኔ፣ሩህሩህ፣ይገባሃል፣አይገባህም፣አልቅስ፣ተደሰት፣--- ሰዎች ቢልህ ጥቅሙን አስቦ ነው የሚናገረው፣ውስጥህ የሚልህን አድርግ ለድርጊትህ ሃላፊነት ውሰድ።
ምክንያቱም መጨረሻ ላይ እያንዳንዱ ሰው ነገሮችን የሚረዳውና የሚያየው በራሱ እይታና መንገድ ብቻ ነው::
ነጻነት #የውስጥሰላም #እርካታ
271
መኖር
በፍላጭ ሰከንዶች፤
በሽራፊ ሰዓት፤
በደቂቃ ቅንጣት፤
እለት እየገፉ፤
ወራት እያለፉ፤
እየጣሉ አመታት፤
በዘመን ምትሀት፤
በአንዲት የጊዜ ጋት፤
መኖር መሳብ አይደል፤
ወደሞት መጠጋት ?🥺
271
" መንፈሴን አመመኝ!!!
ሰምቶ ለሚያሰማ ችግሬን ነግሬ፣
ስሜ አደባባይ ነው የሚውለው ዛሬ፣
ይረዳኛል ያልኩት ያመንኩት ቢከዳኝ፣
አልቅስ አልቅስ አለኝ በድንገት ሆድ ባሰኝ፣
ለካስ እህ እያለ ችግሬን መስማቱ፣
ሊረዳኝ አይደለም አቤት ሰው ከፋቱ፣
ደግፈኝ ያልኩት ሰው ገፍትሮ ቢጥለኝ፣
ከስጋዬ በላይ መንፈሴን አመመኝ።
ከአረገልኝ በላይ ያደረገኝ ብሶ፣
ሆዴን እየባሰው ይቀናኛል ለቅሶ።
271
የጠቢባን ንግግር 📜
ጠቢብእንዲህ አለ
<< በጨለማ ማየት እችላለሁ...!>> የጠቢቡን አባባል ያልተረዳ ሰነፍ ደግሞ ጠየቀ ፦
<< በጭለማ ማየት ከቻልክ ታድያ ለምን መብራት ይዘህ ትሄዳለህ?>>ጠቢቡብ ከሰነፍ የሚጠብቀው ጥያቄ ነውና ሳይደነቅ መለሰለት ፦
<<እንዳንተ ዓይነቱ በጨለማ ማየት የማይችል መጥቶ እንዳይገጨኝ ነው >> አለው ።
ጠቢብ መሆን ባይቻልብየጠቢብን ብርሃን ማየት ይቻላል ።
📖📖📖
ለሰነፍ ጨለማ የጠቢብ ብርሃን መድኃኒቱ ነውና ትንሽ እንጨምር ፦
፧
አንድ ቀትር ረሃብ የጎዳው ጎልማሣ አንዲት ደረቅ ዳቦ በእጁ ይዞ የሚበላበትን ነገር ለመለመን በመንገድ ዳር ወደሚገኝ ምግብ ቤት ተጠግቶ ይቆማል ። ብዙም ሳይቆይ ከምግብ ቤቱ የሚወጣው የተጠበሰ ስጋ ሽታ አፉን በምላቅ ይሞላውና ዳቦውን በምግቡ ሽታ እያጣጣመ መብላት ጀመረ ። በዚህ መሃል ግን የምግብ ቤቱ ባለቤት ነገሩን ይረዳና ሲሮጥ ወጥቶ የደሀውን አንገት አንቆ ያሸተተበትን እንዲከፍል ይወዘውዘው ጀመር ። ደሀውም ምንም ገንዘብ በኪሱ እንደሌለ ይነግረውና እንዲለቀው ካልሆነም ወደዳኛ እንዲሄዱ ይጠይቀዋል ።
📜📜📜
የምግብ ቤቱ ባለቤትም ወደዳኛ ይዞት ይቀርባል ። ዳኛው ነገሩን በሚገባ ካዳመጠ በኋላ "ደሀው ያሸተተበትን ይከፍል ዘንድ ተገቢ ነው በማለት ፍርዱን ይሰጥና የምግብ ቤቱ ባለቤት ወደእሱ እንዲጠጋ ያዘዋል ። የምግብ ቤቱ ባለቤትም እንደታዘዘው ወደዳኛው ሲጠጋ ፈጠን ብሎ ከኪሱ ሣንቲም ያወጣና በጆሮው ላይ አቃጭሎ ድምጹን አሰምቶ ወደኪሱ ከተተው ፦
"እነሆ ለደሀው እኔ ከፍዬለታለሁ ፤ ወደቤታችሁ ሂዱ!"አለ ።
📖📖📖
ግራ የተጋባው የምግብ ቤቱ ባለቤት ፦
"ዳኛ ሆይ ፣ የሳንቲምህን ድምፁን አሰማህኝ እንጂ መች ሰጠኸኝ" አለው ። ዳኛውም መልሶ
"ድሀውም እኮ አሸተተ እንጂ አልበላም እኮ" ሲል መለሰለት
271
" በአራት ስንኝ የእኛ ታሪክ "
ሀገሬ ድንቅ ናት ፣ ዜጋን ትወዳለች፤
ሲኖር ታቀልና ሲሞት ታከብራለች።
በቁም ተገፋፍቶ ፣ ሲሞቱ መወደድ፤
ከኖረው ሰው ይልቅ እሬሳ አለው ዘመድ።
271
አምላክ ልብ ይስጣቸው❤
ተጠቅመው ለጣሉን በግዜ ለከዱ፣
ስንሻቸው ጠልተው ሲሹን ለሚወዱ፣
ውለታን ዘንግተው ጥለውን ለሄዱ፣
በወረት ሸምጥጠው ለሚረማመዱ፣
ምን አልባት አንድ ቀን ከስህተት ቢማሩ፣
አምላክ ልብ ይስጣቸው በህይወት ይኑሩ።
271
አለማመንን፣ከማመን ይልቅ ከባድ ሆኖ ነው ያገኘውት ሰው ሲያምን አንዴ ነው ያንን እምነት መጠበቅም ማበላሸትም እምነት የተጣለበት ሰው ኃላፊነት ነው ስለዚህ ያመነው ሰው ኑሮውንና ስራውን በሰላም መምራት ይችላል አለማመን ግን በየደቂቃውና በየቅፅበቱ ስጋትን የሚፈጥር፣ግንኙነትንና ፍቅርን የሚያቀጭጭ አረም ነው።
📚የተቆለፈበት ቁልፍ
271
When you need someone
desperately no noe has a
minute To spend with you
But !! wen u want to be
Alone ,people have life to
Spend with you!!! 🤗
271
ዓለም እንደዚህ ናት
አንዱ ቁርስ አግኝቶ፣ ባዶ ከርስ ሲሞላ፤
ሌላው ነፍሱን ሊያተርፍ፣ጠፍቶበታል መላ፤
የአንዱ ሕይወት ለአንዱ፣እየሆነ ምግብ፤
እንደ አሸን ይረግፋል፣ህይወት ያለ ገደብ።
የአንዱ ዕንባ፣ የአንዱ እራት፤
ተፈጥሮ ሆነና፣ዓለም እንደዚህ ናት፤
የአንዱ መሞት ላንዱ፣እየሆነ ህይወት፣
የአንደኛው ውድቀት ነው፣የሌላኛው ስኬት፣
271
_<<ተወዳጆች ሆይ! ✨_*
_በዚህች ምድር ላይ ስንኖር ሁሉንም ነገር አሟልተን ሰላም የምናገኝ ይመስለናል።_
ነገር ግን
👉ገንዘብ ኖሮን ደስታ፣
👉ጤና ኖሮን እርካታ፣
👉ትዳር ኖሮን እውነተኛ ፍቅር ስናጣ
👉“አለኝ” ስንል “የለኝም” በሚል ባዶነት ውስጥ እንወድቃለን።
*ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ* ፦ "ሰላም የሚገኘው ከውስጥ እንጂ ከውጪ ከሚታይ ቁስ አይደለም" ሲለን፣
አውግስጢኖስም፦ "ልባችን በአንተ ውስጥ እስካላረፈ ድረስ ፈጽሞ ሰላም አያገኝም" በማለት እውነተኛው እረፍት የት እንደሚገኝ ያስገነዝቡናል። የዓለምን ክብር መናቅን ያስተማረን ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊም ወደ ፈጣሪ መመለስ ማዕበሉን ሁሉ ጸጥ እንደሚያደርገው ይመሰክራል።
*እውነት ነው!* ዓለም በቁስ ልታሳርፈን አትችልም። መምህር ሳሙኤል እንዳስተማሩን፦ "አንተ ጌታዬ እግዚአብሔር ግን በማንነትህ ብቻ ታሳርፋለህና!" ዛሬ የምንሮጥለትን ምድራዊ ድካም ጥቂት ገታ አድርገን፣ ነፍሳችንን በቅዱሳን ምክር እንመግባታ። ጌታ ሆይ! የምስጋና ነጻ መንበርህ በልባችን ይንገስ!
271
_<<ተወዳጆች ሆይ! ✨_*
_በዚህች ምድር ላይ ስንኖር ሁሉንም ነገር አሟልተን ሰላም የምናገኝ ይመስለናል።_
ነገር ግን
👉ገንዘብ ኖሮን ደስታ፣
👉ጤና ኖሮን እርካታ፣
👉ትዳር ኖሮን እውነተኛ ፍቅር ስናጣ
👉“አለኝ” ስንል “የለኝም” በሚል ባዶነት ውስጥ እንወድቃለን።
*ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ* ፦ "ሰላም የሚገኘው ከውስጥ እንጂ ከውጪ ከሚታይ ቁስ አይደለም" ሲለን፣
አውግስጢኖስም፦ "ልባችን በአንተ ውስጥ እስካላረፈ ድረስ ፈጽሞ ሰላም አያገኝም" በማለት እውነተኛው እረፍት የት እንደሚገኝ ያስገነዝቡናል። የዓለምን ክብር መናቅን ያስተማረን ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊም ወደ ፈጣሪ መመለስ ማዕበሉን ሁሉ ጸጥ እንደሚያደርገው ይመሰክራል።
*እውነት ነው!* ዓለም በቁስ ልታሳርፈን አትችልም። መምህር ሳሙኤል እንዳስተማሩን፦ "አንተ ጌታዬ እግዚአብሔር ግን በማንነትህ ብቻ ታሳርፋለህና!" ዛሬ የምንሮጥለትን ምድራዊ ድካም ጥቂት ገታ አድርገን፣ ነፍሳችንን በቅዱሳን ምክር እንመግባታ። ጌታ ሆይ! የምስጋና ነጻ መንበርህ በልባችን ይንገስ! 🙏
271
Not every day is good, but there's something good in every day
እያንዳንዱ ቀን ጥሩ አይደለም፣ ነገር ግን በየቀኑ ጥሩ ነገር አለ።
