ar
Feedback
የጥበብ እመቤት 📜

የጥበብ እመቤት 📜

الذهاب إلى القناة على Telegram

╱◥██████◣ │∩│🪟▤│🪟│ ▓▆▇█▓🚪▓█▇ 🍹❤️‍🔥✨🍁𝐖𝐄𝐋𝐂𝐎𝐌𝐄🍁✨ 𝚜𝚞𝚌𝚌𝚎𝚜𝚜 እንኳን ደህና መጡ ወደ የጥበብ እመቤት "ሕይወት ትጠይቃለች፣ ጥበብ ትመልሳለች " https://Wisdomlady

إظهار المزيد
لم يتم تحديد البلدالفئة غير محددة
271
المشتركون
-124 ساعات
+77 أيام
+15230 أيام
أرشيف المشاركات
የተፃፈልንን ነው የምንኖረው❓ "ህይወታችን አስቀድሞ ተፅፏል፤ ከተፃፈው ውጪ መኖር አንችልም"የ40 ቀን እድል ነው የሚሉ ብዙ አሉ። "እጣ ፈንታዬ ነው" እያሉ ባሉበት መቆየትን የሚመርጡም ጥቂት አይደ
የተፃፈልንን ነው የምንኖረው❓ "ህይወታችን አስቀድሞ ተፅፏል፤ ከተፃፈው ውጪ መኖር አንችልም"የ40 ቀን እድል ነው የሚሉ ብዙ አሉ። "እጣ ፈንታዬ ነው" እያሉ ባሉበት መቆየትን የሚመርጡም ጥቂት አይደሉም።

የማለዳ ቅኔ ​የውጭው ዓለም ጎህ፣በፀሐይ ቢፈካ፣ የውስጥህ ማንነት፣ጨለማን ከተካ፤ ቀኑ ቀን አይሆንም፣ፀሐይ ስለወጣች፣ እውነተኛው ንጋት፣ሰውነትህ ላይ ነች። የማለዳ ውበት፣ የንጋቷ ጀምበር፤ ተፈለገች
የማለዳ ቅኔ ​የውጭው ዓለም ጎህ፣በፀሐይ ቢፈካ፣ የውስጥህ ማንነት፣ጨለማን ከተካ፤ ቀኑ ቀን አይሆንም፣ፀሐይ ስለወጣች፣ እውነተኛው ንጋት፣ሰውነትህ ላይ ነች። የማለዳ ውበት፣ የንጋቷ ጀምበር፤ ተፈለገች ትውጣ፣ ቢሻት በዛው ትቅር፤ በውስጥህ ላይ ያለው፣ ተስፋና ደግነት፤ አብሮ ካልነቃልህ፣ አይኖርህም ሕይወት።

ሕልመኛ ነበር። እንደ ሁሉም ወጣት ሀብታም መሆን፤ አዋቂ መሆን፤ ቤተሰቦቹን የመርዳት ሕልም ነበረው። የተንሸዋረረ አራድነት አሳስቶት የለኮሳት ሲጋራ፤ ለሳቅ ብሎ የተጎነጫት አረቄ፣ ለሙድ ብሎ የቀነጠ
ሕልመኛ ነበር። እንደ ሁሉም ወጣት ሀብታም መሆን፤ አዋቂ መሆን፤ ቤተሰቦቹን የመርዳት ሕልም ነበረው። የተንሸዋረረ አራድነት አሳስቶት የለኮሳት ሲጋራ፤ ለሳቅ ብሎ የተጎነጫት አረቄ፣ ለሙድ ብሎ የቀነጠሳት የጫት ቅጠል ስትደጋገም አፈዘዘችው፤ ሕልሙን ወጣትነቱን ክብሩን አረገፈችው። ማንም ብርቱ ነኝ ቢል ታግሎ የማያስመልሳትን ወጣትነቱን ለማያቀው ጣዖት እየሰዋት ነው። 📚አዎ! እሱ ጋ ያመኛል! ✍️አድሃኖም ምትኩ

“When you establish a destination by defining what you want, then take physical action by making choices that move you toward
“When you establish a destination by defining what you want, then take physical action by making choices that move you towards that destination, the possibility for success is limitless and arrival at the destination is inevitable.” —  Steve Maraboli

በህይወቴ ብዙ ደስ የሚልና ጠቃሚ ነገሮችን አውቃለሁ፤ ነገር ግን ስለ እኔም ሆነ ስለማደርገው ነገር ሰዎች ምን እንደሚሉ አለመጨነቅን ያህል አርኪና ሙሉ የሚያደርግ ነገር አላቅም እስካሁን።የዉላቹ ክፉ፣ደግ፣አረመኔ፣ሩህሩህ፣ይገባሃል፣አይገባህም፣አልቅስ፣ተደሰት፣--- ሰዎች ቢልህ ጥቅሙን አስቦ ነው የሚናገረው፣ውስጥህ የሚልህን አድርግ ለድርጊትህ ሃላፊነት ውሰድ። ምክንያቱም መጨረሻ ላይ እያንዳንዱ ሰው ነገሮችን የሚረዳውና የሚያየው በራሱ እይታና መንገድ ብቻ ነው:: ነጻነት #የውስጥሰላም #እርካታ

መኖር በፍላጭ ሰከንዶች፤ በሽራፊ ሰዓት፤ በደቂቃ ቅንጣት፤ እለት እየገፉ፤ ወራት እያለፉ፤ እየጣሉ አመታት፤ በዘመን ምትሀት፤ በአንዲት የጊዜ ጋት፤ መኖር መሳብ አይደል፤ ወደሞት መጠጋት ?🥺           

𝚝𝚑𝚎 𝚙𝚎𝚛𝚜𝚘𝚗 𝚠𝚑𝚘 𝚑𝚊𝚜 𝚕𝚎𝚊𝚛𝚗𝚎𝚍 𝚝𝚘 𝚕𝚘𝚟𝚎 𝚌𝚊𝚗 𝚗𝚎𝚟𝚎𝚛 𝚋𝚎 𝚏𝚒𝚕𝚕𝚎𝚍 𝚠𝚒𝚝𝚑 𝚎𝚐𝚘,,,
𝚝𝚑𝚎 𝚙𝚎𝚛𝚜𝚘𝚗 𝚠𝚑𝚘 𝚑𝚊𝚜 𝚕𝚎𝚊𝚛𝚗𝚎𝚍 𝚝𝚘 𝚕𝚘𝚟𝚎 𝚌𝚊𝚗 𝚗𝚎𝚟𝚎𝚛 𝚋𝚎 𝚏𝚒𝚕𝚕𝚎𝚍 𝚠𝚒𝚝𝚑 𝚎𝚐𝚘,,,

" መንፈሴን አመመኝ!!! ሰምቶ ለሚያሰማ ችግሬን ነግሬ፣ ስሜ አደባባይ ነው የሚውለው ዛሬ፣ ይረዳኛል ያልኩት ያመንኩት ቢከዳኝ፣ አልቅስ አልቅስ አለኝ በድንገት ሆድ ባሰኝ፣ ለካስ እህ እያለ ችግሬን መስማቱ፣ ሊረዳኝ አይደለም አቤት ሰው ከፋቱ፣ ደግፈኝ ያልኩት ሰው ገፍትሮ ቢጥለኝ፣ ከስጋዬ በላይ መንፈሴን አመመኝ። ከአረገልኝ በላይ ያደረገኝ ብሶ፣ ሆዴን እየባሰው ይቀናኛል ለቅሶ።

የጠቢባን ንግግር 📜 ጠቢብእንዲህ አለ  << በጨለማ ማየት እችላለሁ...!>> የጠቢቡን አባባል ያልተረዳ ሰነፍ ደግሞ ጠየቀ ፦ << በጭለማ ማየት ከቻልክ ታድያ
የጠቢባን ንግግር 📜 ጠቢብእንዲህ አለ  << በጨለማ ማየት እችላለሁ...!>> የጠቢቡን አባባል ያልተረዳ ሰነፍ ደግሞ ጠየቀ ፦ << በጭለማ ማየት ከቻልክ ታድያ ለምን መብራት ይዘህ ትሄዳለህ?>>ጠቢቡብ ከሰነፍ የሚጠብቀው ጥያቄ ነውና ሳይደነቅ መለሰለት ፦ <<እንዳንተ ዓይነቱ በጨለማ ማየት የማይችል መጥቶ እንዳይገጨኝ ነው >> አለው ። ጠቢብ መሆን ባይቻልብየጠቢብን ብርሃን ማየት ይቻላል ። 📖📖📖 ለሰነፍ ጨለማ የጠቢብ ብርሃን መድኃኒቱ ነውና ትንሽ እንጨምር ፦ ፧ አንድ ቀትር ረሃብ የጎዳው ጎልማሣ አንዲት ደረቅ ዳቦ በእጁ ይዞ የሚበላበትን ነገር ለመለመን በመንገድ ዳር ወደሚገኝ ምግብ ቤት ተጠግቶ ይቆማል ። ብዙም ሳይቆይ ከምግብ ቤቱ የሚወጣው የተጠበሰ ስጋ ሽታ አፉን በምላቅ ይሞላውና ዳቦውን በምግቡ ሽታ እያጣጣመ መብላት ጀመረ ። በዚህ መሃል ግን የምግብ ቤቱ ባለቤት ነገሩን ይረዳና ሲሮጥ ወጥቶ የደሀውን አንገት አንቆ ያሸተተበትን እንዲከፍል ይወዘውዘው ጀመር ። ደሀውም ምንም ገንዘብ በኪሱ እንደሌለ ይነግረውና እንዲለቀው ካልሆነም ወደዳኛ እንዲሄዱ ይጠይቀዋል ። 📜📜📜 የምግብ ቤቱ ባለቤትም ወደዳኛ ይዞት ይቀርባል ። ዳኛው ነገሩን በሚገባ ካዳመጠ በኋላ "ደሀው ያሸተተበትን ይከፍል ዘንድ ተገቢ ነው በማለት ፍርዱን ይሰጥና የምግብ ቤቱ ባለቤት ወደእሱ እንዲጠጋ ያዘዋል ። የምግብ ቤቱ ባለቤትም እንደታዘዘው ወደዳኛው ሲጠጋ ፈጠን ብሎ ከኪሱ ሣንቲም ያወጣና በጆሮው ላይ አቃጭሎ ድምጹን አሰምቶ ወደኪሱ ከተተው ፦ "እነሆ ለደሀው እኔ ከፍዬለታለሁ ፤ ወደቤታችሁ ሂዱ!"አለ ። 📖📖📖 ግራ የተጋባው የምግብ ቤቱ ባለቤት ፦ "ዳኛ ሆይ ፣ የሳንቲምህን ድምፁን አሰማህኝ እንጂ መች ሰጠኸኝ" አለው ። ዳኛውም መልሶ "ድሀውም እኮ አሸተተ እንጂ አልበላም እኮ" ሲል መለሰለት

🙏🙏🙏

" በአራት ስንኝ የእኛ ታሪክ " ሀገሬ ድንቅ ናት ፣ ዜጋን ትወዳለች፤ ሲኖር ታቀልና ሲሞት ታከብራለች። በቁም ተገፋፍቶ ፣ ሲሞቱ መወደድ፤ ከኖረው ሰው ይልቅ እሬሳ አለው ዘመድ።
" በአራት ስንኝ የእኛ ታሪክ " ሀገሬ ድንቅ ናት ፣ ዜጋን ትወዳለች፤ ሲኖር ታቀልና ሲሞት ታከብራለች። በቁም ተገፋፍቶ ፣ ሲሞቱ መወደድ፤ ከኖረው ሰው ይልቅ እሬሳ አለው ዘመድ።

አምላክ ልብ ይስጣቸው❤ ተጠቅመው ለጣሉን በግዜ ለከዱ፣ ስንሻቸው ጠልተው ሲሹን ለሚወዱ፣ ውለታን ዘንግተው ጥለውን ለሄዱ፣ በወረት ሸምጥጠው ለሚረማመዱ፣ ምን አልባት አንድ ቀን ከስህተት ቢማሩ፣ አምላ
አምላክ ልብ ይስጣቸው❤ ተጠቅመው ለጣሉን በግዜ ለከዱ፣ ስንሻቸው ጠልተው ሲሹን ለሚወዱ፣ ውለታን ዘንግተው ጥለውን ለሄዱ፣ በወረት ሸምጥጠው ለሚረማመዱ፣ ምን አልባት አንድ ቀን ከስህተት ቢማሩ፣ አምላክ ልብ ይስጣቸው በህይወት ይኑሩ።

አለማመንን፣ከማመን ይልቅ ከባድ ሆኖ ነው ያገኘውት ሰው ሲያምን አንዴ ነው ያንን እምነት መጠበቅም ማበላሸትም እምነት የተጣለበት ሰው ኃላፊነት ነው ስለዚህ ያመነው ሰው ኑሮውንና ስራውን በሰላም መምራ
አለማመንን፣ከማመን ይልቅ ከባድ ሆኖ ነው ያገኘውት ሰው ሲያምን አንዴ ነው ያንን እምነት መጠበቅም ማበላሸትም እምነት የተጣለበት ሰው ኃላፊነት ነው ስለዚህ ያመነው ሰው ኑሮውንና ስራውን በሰላም መምራት ይችላል አለማመን ግን በየደቂቃውና በየቅፅበቱ ስጋትን የሚፈጥር፣ግንኙነትንና ፍቅርን የሚያቀጭጭ አረም ነው። 📚የተቆለፈበት ቁልፍ

ቤተ ሰሬ በዝቶ ማገር ማገር ይላል፣ መገንባቱን እንጂ መኖሩን ማን ያውቃል።
ቤተ ሰሬ በዝቶ ማገር ማገር ይላል፣ መገንባቱን እንጂ መኖሩን ማን ያውቃል።

When you need someone desperately no noe has a minute To spend with you But !! wen u want to be Alone ,people have life to Sp
When you need someone desperately no noe has a minute To spend with you But !! wen u want to be Alone ,people have life to Spend with you!!! 🤗

𝙞 𝙙𝙤𝙣'𝙩 𝙘𝙖𝙧𝙚 𝙬𝙝𝙖𝙩 𝙤𝙩𝙝𝙚𝙧 𝙥𝙚𝙤𝙥𝙡𝙚 𝙩𝙝𝙞𝙣𝙜 𝙤𝙛 𝙢𝙚 𝙞 𝙚𝙣𝙟𝙤𝙮 𝙢𝙮 𝙡𝙞𝙛𝙚 𝙬𝙞𝙩𝙝 𝙢𝙮 𝙤𝙬𝙣 𝙧𝙬𝙡𝙚𝙨

ዓለም እንደዚህ ናት አንዱ ቁርስ አግኝቶ፣ ባዶ ከርስ ሲሞላ፤ ሌላው ነፍሱን ሊያተርፍ፣ጠፍቶበታል መላ፤ የአንዱ ሕይወት ለአንዱ፣እየሆነ ምግብ፤ እንደ አሸን ይረግፋል፣ህይወት ያለ ገደብ። የአንዱ ዕንባ
ዓለም እንደዚህ ናት አንዱ ቁርስ አግኝቶ፣ ባዶ ከርስ ሲሞላ፤ ሌላው ነፍሱን ሊያተርፍ፣ጠፍቶበታል መላ፤ የአንዱ ሕይወት ለአንዱ፣እየሆነ ምግብ፤ እንደ አሸን ይረግፋል፣ህይወት ያለ ገደብ። የአንዱ ዕንባ፣ የአንዱ እራት፤ ተፈጥሮ ሆነና፣ዓለም እንደዚህ ናት፤ የአንዱ መሞት ላንዱ፣እየሆነ ህይወት፣ የአንደኛው ውድቀት ነው፣የሌላኛው ስኬት፣

_<<ተወዳጆች ሆይ! ✨_* _በዚህች ምድር ላይ ስንኖር ሁሉንም ነገር አሟልተን ሰላም የምናገኝ ይመስለናል።_ ነገር ግን 👉ገንዘብ ኖሮን ደስታ፣ 👉ጤና ኖሮን እርካታ፣ 👉ትዳር ኖሮን እውነተኛ ፍቅር ስናጣ 👉“አለኝ” ስንል “የለኝም” በሚል ባዶነት ውስጥ እንወድቃለን። *ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ* ፦ "ሰላም የሚገኘው ከውስጥ እንጂ ከውጪ ከሚታይ ቁስ አይደለም" ሲለን፣ አውግስጢኖስም፦ "ልባችን በአንተ ውስጥ እስካላረፈ ድረስ ፈጽሞ ሰላም አያገኝም" በማለት እውነተኛው እረፍት የት እንደሚገኝ ያስገነዝቡናል። የዓለምን ክብር መናቅን ያስተማረን ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊም ወደ ፈጣሪ መመለስ ማዕበሉን ሁሉ ጸጥ እንደሚያደርገው ይመሰክራል። *እውነት ነው!* ዓለም በቁስ ልታሳርፈን አትችልም። መምህር ሳሙኤል እንዳስተማሩን፦ "አንተ ጌታዬ እግዚአብሔር ግን በማንነትህ ብቻ ታሳርፋለህና!" ዛሬ የምንሮጥለትን ምድራዊ ድካም ጥቂት ገታ አድርገን፣ ነፍሳችንን በቅዱሳን ምክር እንመግባታ። ጌታ ሆይ! የምስጋና ነጻ መንበርህ በልባችን ይንገስ!

_<<ተወዳጆች ሆይ! ✨_* _በዚህች ምድር ላይ ስንኖር ሁሉንም ነገር አሟልተን ሰላም የምናገኝ ይመስለናል።_ ነገር ግን 👉ገንዘብ ኖሮን ደስታ፣ 👉ጤና ኖሮን እርካታ፣ 👉ትዳር ኖሮን እውነተኛ ፍቅር ስናጣ 👉“አለኝ” ስንል “የለኝም” በሚል ባዶነት ውስጥ እንወድቃለን። *ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ* ፦ "ሰላም የሚገኘው ከውስጥ እንጂ ከውጪ ከሚታይ ቁስ አይደለም" ሲለን፣ አውግስጢኖስም፦ "ልባችን በአንተ ውስጥ እስካላረፈ ድረስ ፈጽሞ ሰላም አያገኝም" በማለት እውነተኛው እረፍት የት እንደሚገኝ ያስገነዝቡናል። የዓለምን ክብር መናቅን ያስተማረን ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊም ወደ ፈጣሪ መመለስ ማዕበሉን ሁሉ ጸጥ እንደሚያደርገው ይመሰክራል። *እውነት ነው!* ዓለም በቁስ ልታሳርፈን አትችልም። መምህር ሳሙኤል እንዳስተማሩን፦ "አንተ ጌታዬ እግዚአብሔር ግን በማንነትህ ብቻ ታሳርፋለህና!" ዛሬ የምንሮጥለትን ምድራዊ ድካም ጥቂት ገታ አድርገን፣ ነፍሳችንን በቅዱሳን ምክር እንመግባታ። ጌታ ሆይ! የምስጋና ነጻ መንበርህ በልባችን ይንገስ! 🙏

Not every day is good, but there's something good in every day               እያንዳንዱ ቀን ጥሩ አይደለም፣ ነገር ግን በየቀኑ ጥሩ ነገር አለ።