Usmanic Islamic psychology/ ስለ ሰው ልቡና
رفتن به کانال در Telegram
- እውነተኛ የህይወት ታሪኮች - ኢስላማዊ የስነልቦና ምክሮች ፣ ጥያቄዎች እና አገልግሎቶችን ያገኛሉ። - ስለ ኢስላማዊ ሳይኮሎጂ ይማራሉ። - ሳምንታዊ ሽልማቶች ለሁሉም በማጋራት የሙስሊሙ ኡማ የአይምሮ ጤና የሚጠበቅበትን ይህን ቻናል እናሳድግ ጥያቄ ለማቅረብ እና አገልግሎት ለማግኘት @usmanoman ላይ ያናግሩን።
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
787
مشترکین
+2324 ساعت
+1617 روز
+36130 روز
آرشیو پست ها
ኢስላማዊ የስነልቦና አገልግሎት ለምትፈልጉ በሙሉ
የትዳር የቤተሰብ እና የስራ ጉዳይ ድብርት ወይም ጭንቀት ውስጥ ካላችሁ ወይም ለሌላ ማንኛውም ጉዳይ @usmanoman ላይ አዋሩኝ (ሁሉም በሚስጥር የሚጠበቅ ነው)
ወይም 0912027023/ 0921390122 ደውሉ
ከታች የተያያዘውን ሊንክ በመንካት ፎርም መሙላት አይርሱ ሲጨርሱ ከላይ በሰፈሩት አድራሻዎች ያሳውቁን። 👇👇👇
____
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdl5ehGATYpwQpFCLs66NcS26Laedz36GRjQze0Gxyw1SzzBA/viewform?usp=header 🔗📝
__
መልስ .1
መረጃዎች እንደሚያሳዩት በአለም አቀፍ ደረጃ የሴቶች የጋብቻ እድሜ ድሮ ከነበረበት በብዙ እጥፍ ከፍ ብሏል።
ቀጥለን በምንጠቃቅሳቸው ምክንያቶች አለም ላይ ብዙ ሴቶች ዘግይቶ በማግባት ፣ ፍፁም ባለማግባት ወይም ባልተሳካ ትዳር ቀውስ ምክንያት ጥልቅ ጭንቀት ውስጥ እያለፉ ይገኛሉ።
ከምክንያቶቹም-: የሴቶች በትምህርት ለአመታት የመቆየት ባህል መስፋፋት ፣ የተዛባ የጋብቻ እሳቤ ፣ የወንዶች በጊዜ ማግባት ያለመፈለግ ፣የኑሮ ጫና ፣ የሴቶች ትዳርን የነፃነት ፀር አድርጎ በመቁጠር ሳያገቡ የመቆየት ፍላጎት ፣ የወንዶች በጣም በእድሜ የምታንሳቸውን ሴት የመምረጥ ልምድ፣
የፍቺ መስፋፋት ፣ አለም ላይ የተነዛው የምእራብያውያን ሴራ የወለደው የሴቶች ንቅናቄ ግልፅ እና ስውር ተፅእኖ ፣ በግል የትዳር አጋርን የመምረጥ መብትን ተከትሎ የተፈጠረው ገደብ የሌለው መስፈርት የማብዛት አባዜ ....ወዘተ....ይጠቀሳሉ። (የብዙ ሴቶች አለማግባት ከቂያማ/የምፅአት ቀን መቃረብ ምልክቶችም ጭምር መሆኑን ሊቃውንቱ ይገልፃሉ)
ይህ ጉዳይ (የሴቶች ቶሎ አለማግባት) የሩቅ ሀገር ተረት ሳይሆን የሁላችንንም በር ያንኳኳ ማህበረሰቡ አፍኖት እየኖረ ያለው ጭንቀት እና የራስ ምታት ነው።
የእህቶች በጊዜ አለማግባት ወይም በፍቺ ምክንያት በላጤነት የመኖር ወረርሽኝ መስፋፋት ማህበረሰባችን ቤተሰብ መመስረት ላይ እየደረሰበት ያለውን ሁለንተናዊ ቀውስ ግልጽ ማሳያ ነው።
እህቴም አገባቸዋለው ብላ ያሰበቻቸው ወንዶች የውሀ ሽታ እየሆኑ መጥፋት እና እስካሁን አለማግባቷ የራስ ምታት እንደሆነባት በአፅንኦት ትገልፃለች።
እህታችን ሆይ! በጊዜ ለማግባት ከነበረሽ እቅድ አንፃር 31 አመት ድረስ መቆየትሽ ጭንቀት ሊፈጥርብሽ እንደሚችል የሚጠበቅ ቢሆንም ብዙ ሴቶች ከዚህም ከፍ ባለ እድሜ አግብተው ደስተኛ ህይወት መመስረት እና አይናቸውንም ባይናቸው ማየት ችለዋል።
ግን ሁሌም ህይወት መልከ ብዙ እና ፈታኝ እንደመሆኗ መጠን ለምንፈልገው ብቻ ሳይሆን አላህ እኛ ላይ ስለወሰነው ነገርም ጭምር ዝግጁ መሆን መቻል አለብን።
ትዳርን እንደ ማንኛውም እርዚቅ ወይም ሲሳይ የአላህን ፍቃድ የሚጠይቅ እና በእኛ እጅ የሌለ ነገር ግን ለማግኘት ሁሉን ሰበብ የምናደርስለት ጉዳይ መሆኑን አስታውሰሽ በመልካም ትእግስት እና በዱአ ውስጥ የጌታሽን ውሳኔ ያለ ቀቢፀ ተስፋ የመምረጥ ሚዛንሽን ሳታዛንፊ ግን ደግሞ በጣም ሳትለጥጪ አላህ የሚልክልሽን ሰው በትእግስት መጠበቅሽን ቀጥይ።
በመታገስሽ የምታገኚው ገደብ የሌለው ምንዳ እና የአላህን ውዴታ እያስታወስሽ ሀብቱ ብዙ ከሆነው ጌታ ደጅ ሳትሰልቺ የልብሽን ሰው ጠይቂ ከዛ ውሳኔውን ለአላህ አሳልፈሽ ስጪው።
ይህ ካልሆነም የአማኝ ሀገሩ አዱኒያ ብቻ አይደለም እና በዚህ ከንቱ አለም ያጣሽውን ደስታ በቀጣዩ አለም በእጥፍ አባዝቶ እንደሚለግስሽ አምነሽ የጌታሽን ውሳኔ በደስታ መቀበል የሚያስችል ኢማን አዳብሪ።
አላህ መልካም ትዳርን ለእህቶቻችን በሙሉ ይስጣቸው!!
[ጥያቄው በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተዋቀረ (case study) ነው።]
✍️ ኡስማን ሙስጠፋ ከኡስማኒክ ሳይኮሎጂ።
ለጥያቄ እና አገልግሎት ለማግኘት @psychosman1 ላይ ያናግሩን።ምስጢራዊነቱ የተጠበቀ ነው
ጥያቄ .1
አሰላሙአለይኩም እኔ (ስሜ ለጊዜው ይቆይ) ሙስሊም የ 31 አመት ሴት ስሆን እስካሁን የትዳርን ወግ አላየሁም።በ 24 አመቴ የማግባት እቅድ ስለነበረኝ ያለ ትዳር የማሳልፋት እያንዳንዷ ቀን ለኔ ከባድ ጫና አላት።
አለማግባቴ ቁሞ ቀር የመሆንን ስሜት እያሳደረብኝ ነው።
አንዳንዴም የተረገምኩና ምንም ጥቅም የሌለኝ ሰው የሆንኩ እየመሰለኝ መኖር ያስጠላኛል።
ያገቡኛል ብዬ ሰፍ ብዬ የጠበኳቸው ወንዶች ሳላስበው ድንገት የውሀ ሽታ ሆነው ይሰወራሉ።
ድሮ ወንድን ለትዳር የምመርጥበት ትላልቅ መስፈርቶች የነበሩኝ ቢሆንም አሁን ሁሉም ተሸርሽረው በጣም ጥቂቶቹ ቀርተዋል።
በዚህ ከቀጠልኩኝ 'ወንድ ይሁን ብቻ እንጂ አገባለው' ወደሚል ቀቢፀ ተስፋ (ተስፋ መቁረጥ) ውስጥ እንዳልገባ እፈራለሁ እባክህ ሀሳብህን አካፍለኝ።
(የጥያቄውን ምላሽ በ 24 ሰአት ውስጥ ቻናላችን ላይ ይጠብቁ ኢንሻአላህ!)
#ኡስማኒክ_ኢስላማዊ_ስነልቦና
ለጥያቄ እና አገልግሎት ለማግኘት @psychosman1 ላይ ያናግሩን።
የሰው ልጅን በአካል እና አይምሮ ብቻ።
የአይምሮ ህመሞች እና የማንነት ቀውሶች እጅግ የበዙበት መዛግብትን አገላብጠን የማንጨርሰው (disorders )የህሊና መዛባት አይነቶች የበረከቱበት አሳዛኝ የኑሮ ተጨባጭ ላይ ደርሰናል።
ወደ ሩቃ/መንፈሳዊ ሀኪም ቤት ሳይካትሪስት እና ሳይኮሎጂስቶችን ደጅ መጥናት መደበኛ የእለት ተእለት ኑሯችን እስኪከሆን ድረስ መላቅጡ የጠፋውን የህይወታችንን ሰንኮፍ ታቅፈነው እየኖር ነው።
የህክምናው ሳይንስ እና የአይምሮው ጥናት እውቀት የሰው ልጅን አካል እና አይምሮ (mind and body) ብቻ ብሎ ለሁለት ከፍሎ የሩህን እና የልቦናን የህይወት መሠረታዊያንን (essence) ነቅሎ ጥሎ የሚታየውን ብቻ ለማከም ይታገላል።
የብዙ ሰዎች ችግር ከረቂቁ ማንነታቸው የመነጨ የነፍስ እና የቀልብ መታመም ተፈጥሯችን ከምትራበው እና የአለም ስርአት ቆርጦ ካስወገደው መለኮታዊ ምግብ የሆነው የመልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) አስተምህሮ እና የጌታዋ ቃል ቁርአን ረሀብ የወለደው መታወክ ነው።
ስለዚህ ሁሉም ዲሲፕሊኖች ውስጥ ይህን ሰማያዊ መድሀኒት በመጨመር ብዙዎችን መታደግ ይቻላል። ኢንሻአላህ!!
🖊️ usman mus
#ስለ_ሰው_ልቡና
