የወራቤ ሰለፊዮች መገናኛ
رفتن به کانال در Telegram
📝👉በአላህ ፍቃድ በዚህ ቻነል በወራቤ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ መድረሳዎች የሚሰጡ የሰለፊዮች ደርስ ፣ሙሃደራ እንዲሁም መልእክቶች የሚተላለፉበት ይሆናል !!! https://t.me/ibnbaz1212
نمایش بیشترکشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
2 028
مشترکین
+1624 ساعت
+1987 روز
+47730 روز
آرشیو پست ها
2 033
Aselamaleykum werahmetulahi
Ibnu baz medresa kenege eske ehud ke subhi behuala ተንቢሃት new yemikeraw
2 033
Repost from አቡ ኑህ አስ'ስልጢይ [ Misbah Mohammed ]
🔷የቢደዐህ ሰዎችን ቡዱንተኞችን በደምብ የሚገልጽ ምርጥ ንግግር
(أهل الأهواء يُعظِّمون من وافقهم ، وإن كان فاسقًا فاجرًا !!
ويذمّون من خالفهم ، وإن كان من أولياء الله المتقين) .
📚الفتاوى (٣/٣٤)
➥ሸይኹል ኢብኑ ተይሚየህ እንዲህ ይላል ፦
➨የቢደዐህ ሰዎች ከነሱ የተስማማውን ሁሉ ያከብራሉ ያልቁታል አመፀኛ እነ በዳይ ቢሆንም እንኳን እነሱ ጋ ክቡር ነው
➸እነሱን የማይስማማ ከሆነ ምንም እንኳን ትክክለኛና አላህን ፈሪ ከደጋጎች ቢሆንም እንኳን ይተቹታል ያነውሩታል ።
📚መጅሙዐል ፈታዋ 3/34
📝ተጨማሪ ትምህርቶችን ለመከታተል
የቴሌግራም Channeሉን ይቀላቀሉ !
https://t.me/MisbahMohammed_6682
2 033
Repost from የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ
🔷ምስጋና
በመዋደዳችሁ ፣ በመተዛዘናችሁ ፣ በርህራሄያችሁ የምንቀናባችሁ ባህር ዳር የምትገኙ የአህለሱና ተርጓሚዎች አሏህ ጀዛችሁን ይክፈላችሁ።
በሁሉም ቦታ የሚገኙ ሰለፍዮች ምን ነው (የእናንተን አካሄድ) በተከተሉ!!
ኢስላምና ሙስሊሞችን በእናንተ ይጥቀም! አሏህን በመታዘዝ ላይ እድሜያችሁን ያርዝመው! ሰለፍይ ተርጓሚዎችንም እንዲሁ! አምሳያችሁን ያብዛው! እስከሞት ድረስ በተውሂድ በሱና ያጽናችሁ!!
በዶክተር ሸይኽ ሁሰይን ብን ሙሐመድ
اللهم آمين
https://t.me/alateriqilhaq
كن على بصيرة
2 033
Repost from 𝐒𝐞𝐦𝐢𝐫 𝐉𝐞𝐦𝐚𝐥 (𝐀𝐛𝐮 𝐇𝐚𝐟𝐬𝐚𝐡)
እናንተ ሸይኾች ሆይ! ፣እናንተ ዳዒዮች ሆይ!፣እንዲሁም እናንተ ኡስታዞች! ኧረ ይህንን ላባዊ ምክር ሰምታችሁ ተግባራዊ እድርጉ!
—⭑⋆⋆⋆⭑—
🎙🎙 ዶክተር ሸይኽ ሑሰይን ሙሐመድ (ሀፊዘሁላሁ ተዓላ) በዚህ አጭር የድምፅ ፋይል ላይ የሚከተሉት አበይት ነጥቦችን ዳስሰዋል፦
ꪜ ነቢዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ባልደረቦቻቸውን (ሶሃቦችን) ያከብሯቸው ነበር፣እንዲሁም ከእነርሱ ጋር ይሳሳቁ (ይቀልዱ) ነበር።
ꪜ ሶሃቦችም (ረዲየላሁ ዐንሁም) በተመሳሳይ መልኩ እርስ በርሳቸው ይዋደዱ ነበር። አላህም በቃሉ ይህንን መስክሮላቸዋል፡- «በመካከላቸው አዛኞች ናቸው» (ሱረቱል ፈትሕ፡ 29)።
ꪜ በተመሳሳይ መልኩ ሰባቱ ፉቀሃኦች: ሙጃሂድ፣ አል-አዕመሽ፣ መንሱር፣ ሁለቱ ሱፍያኖች (ሱፍያን አስ-ሰውሪይ እና ሱፍያን ኢብኑ ዑየይነህ)፣ኢብኑ መህዲ፣ የሕያ አል-ቀጧን፣አሕመድ፣አል-ቡኻሪ እና ሌሎችም...በሕይወት ታሪካቸው ውስጥ በእነርሱና በተማሪዎቻቸው መካከል ያለውን የፍቅር፣ የመዋደድ፣ የእውነተኛነት እና እርስ በርስ የመመካከር ሁኔታን ታገኛለህ።
ꪜ ከአቡ ደርዳእ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተወራው፡- "በሱጁዳቸው ወቅት ለሶሃባ ጓደኞቻቸው ስም እየጠሩ ዱዓእ ያደርጉ ነበር።"
ꪜ እንዲሁም ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ሙሐዲሶች (ኢማሞች) በሱጁዳቸው ውስጥ ለ"አህሉስ-ሱናዎች"ዱዓእ ያደርጉ ነበር፤ እንደ ኢብኑ መህዲ፣ አሕመድ እና ሌሎችም።
ꪜ ሸይኽ ሰዕድ ቢን ዐብዱረሕማን አል-ሑሰይን እንዲህ ብለውኛል፡- በሱጁድ ውስጥ ለኢማሙ አሕመድ፣ ለኢብኑ ተይሚየህ፣ ለኢብኑ ባዝ፣ ለአልባኒ እና ሱናን ለሰዱ ለሌሎችም ዱዓእ ያደርጉ ነበር
ꪜ ተማሪዎቻችሁን በመካከላችሁ ባለው ፍቅርና መዋደድ ላይ አሳድጓቸው (ኮትኩቷቸው)። በአህሉስ-ሱነህ ላይ መልካምን አደራ ተባባሉ!፤ እነርሱ ከሰዎች ሁሉ በጣም ጥቂቶች ናቸውና።
ꪜ ለአንድ ሸይኽ ተማሪውን ማማት በፍጹም አይገባውም፤ ከእርሱ (ከተማሪው) አንድ ነገር ቢሰማ እንኳ ማረጋገጥ አለበት!፤ ከዚያም ትክክለኛውን አቅጣጫ ሊያሳየውና ሊመክረው ይገባል።
ꪜ ያንተ ሰለፊ ወንድምህ እና ተማሪህ ከሌላው ይልቅ ለመመከር ይበልጥ የተገባ ነው!፤ "ዲን ማለት እኮ ምክር ነው።"
ꪜ ከተንኮለኛና አደገኛ በሽታዎች ተጠንቀቁ፤ እሱም፡ በተማሪህ ፊት በአንድ ፊት (በወዳጅነት) መጥተህ፣ ከዚያ ዞር ስትል ደግሞ የምታማው መሆንህ ነው። ይህ በአንተ ውስጥ በሽታ መኖሩን ያሳያል፤ ከዚህ በሽታ ራስህን አፅዳ፣ አላህንም ፍራ።
ꪜ ሸይኽ ረቢዕ ብን ሓዲ አል-ዑመይር አል-መድኸሊ (ረሂመሁላህ)
“...እኔ መካ ሳለሁ የሆነ ቤት ተከራይቼ ነበር፤የተከራየሁበት ቤት ውስጥ ቀድሞ የነበረው ሰውዬ ቴሌቪዥን ነበረው፤ ሰውየው በጊዚያዊነት ቴሌቪዥኑን በአደራ መልክ ትቶት ሄዷል...ይህ በንዲህ እንደለ እኔ በተከራየሁበት ቤት ውስጥ ሌላ ጓደኛዬ ለሸይኽ ረቢዕ እንዲህ በማለት ይነግራቸዋል፦ "ሑሰይን ቤት ቴሌቪዥን አለ..."
ሸይኹም በሌላ ቀን እራት ከተበላ በኃላ፣ ወደ መኝታ ክፍላቸው ይዘውኝ ሄዱ መሀላችን ማንም አንነበረም...እንዲህም ብለው አሉኝ፡ "አንተ ሑሰይን ሆይ! አንተ ቤት ቴሌቪዥን አለ ሲባል ሰምቼ ነበር እውነት ነውን?!..."
ꪜ አሽ-ሸይኽ ሑሰይን ክስተቱን እንዲህ በማለት እውነታውን ነገሯቸው፡ "ሸይኽ ሆይ! እኔ በተከራየሁበት ቤት ውስጥ መጀመሪያ ተከራይቶ የነበረው የሰውዬው ቴሌቪዥን ነው እንጂ የኔ አይደለም...ሰውየው ይቀመጥ ብሎ ነው የሄደው...." በማለት ሸይኽ ሑሰይን ለቀረባለቸው ጥያቄ በአጭሩ ለሸይኽ ረቢዕ አስረዷቸው።
ꪜ በመጨረሻም አሽ-ሸይኽ ረቢዕ ለሸይኽ ሁሰይን እንዲህ አሏቸው፡ "ይቅርታ አድርግልኝ!" አቤት ፍትህ!፤አቤት ጥበብ!፤አቤት አካሄድ!...አቤት አጠያያቅ!...
ꪜ በሌላም ጊዜ (ከዚህ አዲዮ ውጪ) አሽ-ሸይኽ ሑሰይን አስ-ሲልጢ (ሀፊዘሁላህ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፦
“...አንድ ሊቢያዊ "አቡል ፈድል" የተሰኘ ሰውዬ ነበር፤ ሌለኛው ደግሞ መጥቶ ለሸይኽ ረቢዕ እንዲህ ይላቸዋል: "አቡል ፈድል እንዲህ አለ፣ይህን ፈፅመ፣እንዲህ ይላል.." ሸይኹም እንዲህ አሉት: ማስረጃ አምጣ...አቡል ፈድል እኔ ዘንድ ከበላጮቹ ነው..." ወረኛውም ተንቀጠቀጠ...”
ꪜ የሰለፊዮችን አንድነት ከሚከፋፍሉ መንገዶች መካካል ያለማስረጃ ወሬን መቀበል፣ሳያጣሩ ብይን መስጠት፣ወረኛውን አደብ አለማስያዝ...ወረኛውን "ሀ" ብሎ መስማት ዋጋ ያስከፍላል....
https://t.me/HussinAssilty/3343
2 033
Repost from N/a
🌿 ታላቅ የደዕዋ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም 🌿
📢 ልዩ የደዕዋ ፕሮግራም እና ለፉርቃን መስጂድ የገቢ ማሰባሰቢያ
ውድ ሙስሊም ወንድሞችና እህቶች፣ በዚህ ታላቅ የደዕዋ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በመገኘት የፉርቃን መስጂድን ድጋፍ እንድታደርጉ በክብር ተጋብዛችኋል።
🎙 የእለቱ ብርቅዬ ተጋባዥ መሻኢኮች እና ኡስታዞች
1️⃣ ሸይኽ ሙሀመድ ሀያት — ከሀራ
2️⃣ ኡስታዝ አቡ ሙኣዝ — ከወራቤ
3️⃣ ኡስታዝ አቡ ፉረይሃን — ከጦራ
4️⃣ ኡስታዝ አቡ ቂርጣስ — ከዳሎቻ
5️⃣ ኡስታዝ አቡ ያሲር ሰለፊ — ከአዲስ አበባ
📅 ቀን: እሮብ 10/09/2018 ዓ.ም.
🤲 እንዳያመልጣችሁ! በመገኘት የደዕዋው እና የመስጂዱ ድጋፍ ተካፋይ ይሁኑ።
ፕሮግራሙ የሚካሄደው ኢሞ መድረሰቱ ዳሩል በያን ሲሆን ሊንክ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇. Click the link to join us! https://s.imoim.net/xps1iH?from=copy_linkየቴሌግራም ጉሩፕ ሊንክ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/Furqanmesjidgruop2
ሼር አድ በማድረግ ሌሎችን ወደ መልካም ስራ ልንጠራቸው ይገባል ጥሪው ሁሉንም ሰለፊይ ወንድም እህቶችን በተለይም የጉሩፕ የቻናል ባለቤት የሆናቹህ ሼር አድርጉልን ስንል ከትልቅ አክብሮት ጋ ነው
2 033
الرسول صلى الله عليه وسلم يجل أصحابه ويحترمهم ويضاحكهم .
_الصحابة كذلك يحب بعضهم بعضا وشهد الله لهم بذلك بقوله (رحماء بينهم)
_وكذلك الفقهاء السبعة ومجاهد والأعمش ومنصور والسفيانان وابن مهدي ويحيى القطان وأحمد والبخاري وغيرهم تجد في تراجمهم روح المحبة والمودة والصدق والمناصحة بينهم وبين طلابهم .
-وقد ذكر عن أبي الدرداء رضي الله عنه أنه كان يدعو في سجوده لأصحابه من الصحابة.
_وكذلك عدد من أئمة الحديث كانوا يدعون في سجودهم لأهل السنة كابن مهدي وأحمد وغيرهما.
-وقد قال لي الشيخ سعد بن عبد الرحمن الحصين أنه كان يدعو في سجوده لأحمد وابن تيمية وابن باز والألباني وغيرهم ممن نصر الكتاب والسنة على منهاج النبوة.
-ربوا طلابكم على المحبة والمودة فيما بينكمواستوصوا بأهل السنة خيرا وهم أقل الناس
_لا يليق بالشيخ أن يغتاب تلميذه فعليه إن سمع عنه شيآ يتثبت فيقوم بتوجيهه ومناصحته.
_أخوك السلفي وتلميذك أحق بالنصيحة من غيره والدين النصيحة.
-تجنبوا من الأمراض الخبيثة والفتاكة تأتي إلى تلميذك بوجه ثم تروح وتغتابه وهذا يدل على مرض فيك تخلص منه واتق الله تعالى .
2 033
Repost from ጅብሪል ሱልጣን & ሙሀመድ ሰልማን
አንድ ግዜያዊ ምክር
------------
ለሁላችንም አሁን ያለንበት ግዜ በተለይ ለተማሪዎች ለልጆች እረፍት የሚያደርጉበት ግዜ ስለሆነ ግዜያችሁን በከንቱ አታበላሹት ከቻላችሁ
- የተለያዩ መድረሳዎችን በመግባት በተለያዩ ፈኖች ጀግናችሁ እረፍታችሁን መጭረስ
- ባላችሁበት ጎን ለጎን አጫጭር አካዳሚክ ኮርሶችን መውሰድ በተለይ እንደ ግዜያችን በጣም አስፈላጊ የሆኑ ቴክኖሎጂ ነክ ኮርሶችን መውሰድ
ምናልባት እንደኔ ግን እነዚህን አካዳሚክ የሆኑ ኮርሶችን በተለይ ቴክኖሎጂ ነክ የሆኑ አጫጭር ኮርሶችንና ትምህርቶችን ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን ከተማሪ ውጭ ያላችሁም ኡስታዞችም ጭምር ብትወስዱት ባይ ነኝ ምክንያቱም አንደኛ ዲናችንንም በቻልነው አቅም ባገኘንበት አጋጣሚ ከግዜው ጋር በሚሄዱ ቴክኖሎጂዎች ልናስፋፋ ይረዳናል ያ ባይቻል እንኳን የምንኖረው ዱኒያ ላይ ነውና ከዱኒያም እጣ ፋንታህን አትርሳ ነውና ለዱኒያዊ ጥቅሞቻችንም በአላህ ፈቃድ ይጠቅመናል ያም ብቻ አይደለም የኢስላም ጠላቶች በተለያዩ በቴክኖሎጂዎች እስልምናን ለማጥቃት ሲሞክሩ እኛም ቴክኖሎጂዎችን ካወቅናቸው በዛው ልንመክትበት ይረዳናል ።
እንደው አንድ ምሳሌ ልንገራችሁ የሆነ ሰሞን ታስታውሱ እንደሆነ የተለያዩ የቁርዓን ተፍሲር ፣ የኪታብ ቂርዓት ሪከርዶች ደዕዋዎችን ፈትዋዎችን ወደ አፕ ለመቀየር እስከ ስንት ብር ይጠየቅ እንደነበር ታውቃላችሁ እስከ ሀምሳ ሺህ ብር ይጠየቅ ነበር ኋላ ላይ ግን ሰለፊዮችም ይህን አፕ አሰራሩን ማወቅ ሲጀምሩ እንዲሁም ከሰለፊዮች ውጭ ያሉትም ይህን አፕ የሚሰሩት መብዛት ሲጀምሩ ምን ያህል እንደሆነ ከማናችንም አይደበቅም ።
እንደው እሱም ብቻ አይደለም እኔን የገጠመኝን ልንገራችሁ በቅርብ ቀን እራሱ ከአንድ ወንድም ጋር ሆነን አንድ የተለየ ለየት ያለ አፕ አለና ሜጋባይቱ ትንሽ የሆነ የሸይኻችንን በየቀኑ የሚቀሩ ደርሶችን ደዕዋዎችን ኹጥባዎችን እራሱ አፕዴት አድርጎ የሚጨምር አፕ ልናሰራ ስንጠይቅ አምስት መቶ ሺህ ብር ነው የተባልነው ያው እኛም አቅሙ ዬለንም አላህ ካለ አቅሙ ያለው ሲመጣ አልያ አፑን አሰራሩን የሚያውቅ ሰለፊይ ምናልባት ከመሃላችን ሲመጣ ያሰራው ይሆናል ብለን ተውነው ።
ይህን የሚነግራችሁ የቴክኖጂውን ጥቅም እንድታውቁ ነው ስለዚህ በአጭሩ ኡስታዞችም ደረሶችም ተማሪዎችም ሴቶችም ወንዶችም እንደዚህ ያሉ ክፍተቶች ሲገኙልን እነዚህን ከግዜው ጋር የሚሄዱ ኮርሶችንና ትምህርቶችን ጠንክረን ልንማር እንጂ ልንሸሻቸው አይገባም ። በመሰረቱ ይህ እያወራንበት ያለነው ቴሌግራም አፕም ቴክኖሎጂ ነው ስለዚህ ውድ ሰለፊዮች ከቴክኖሎጂ አትሽሹ ተመሩት ተመራመሩበት እወቁት ሁሉም ነገር እንደኛ አጠቃቀም ነውና ።
አላህ ዕውቀትን ይጨምርልን !! አሚን
✍አቡ ሙስዐብ ኢብን ሱልጣን
✔️ ሰዎች አወደሱህም አወገዙህም በዲንህ ላይ ቀጥ በል!!
https://t.me/Abumuseab
2 033
ሸይኽ ረቢይዕ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ:
"ሸይኽህ ሃቅን ከተፃረረ ሸይኽህን ተውና ሃቅን አጥብቀህ ያዝ እቺም ናት እውነተኛ ሰለፍያ""
https://t.me/ibnbaz1212
2 033
📙 عنوان الرسالة: مجمل عقيدة السلف الصالح لشيخ صالح بن فوزان الفوزان
(የሸይኽ ሷሊሃልፈውዛን ሪሳላ የሆነችው ሙጅመሉ ዓቂደቲ አሰለፍ አሷሊህ)
ክፍል ስድስት (06)
🎙በኡስታዝ አቡ ሙዓዝ
📚የኪታቡን pdf ለማግኘት👇👇
https://t.me/ibnbaz1212/66
📆 ዕለተ ጁሙዓ ዙልሂጃ 26, 1447
🕌 በመድረሰቱል ኢኽላስ ለሁልባረግ የሴቶች ጀመዓ የተሰጠ ኮርስ
የቴሌግራም ቻነል
https://t.me/ibnbaz1212
2 033
Repost from አቡ ኑህ አስ'ስልጢይ [ Misbah Mohammed ]
➽የቶንኮል ጉድጓድ ስትቆፍር ኣታርቀዉ ራስህ ልትገባበት ትችላለህና ።
➥ጅብና ተኩላ ቀበሮን ለማስገደል ሴራ በመሸረብ ለአንበሳ ሄደው ቀበሮ እኮ አሪፍ ጫማ መስራት ትችልበታለች ለምን ይሆን በባዶ እግሮ እየሄዱ ዝም ያለችው ? ብለው አቃጠሩ !
➸አንበሳም ተናዶ ቀበሮን መፈለግ ጀመረ በመጨረሻም ቀበሮ ጉድጓዷ በር ለይ ተገኘች አንበሳም ትንሽ ከንጎራደደ በኋላ ግርማ ሞጎሱ ተላብሶ ተቀመጠና እንዲህ አለ "ለመሆኑ ምን ያህል ብትኒቅኝ ነው ጨማ መስራት እየቻልሺ በዶ እግሬን ስሄድ እያየሽ ዝም ያልሺኝ " አላት ።
➽ቀበሮም ይህ ጥንስስ ሴራ የጅብና ተኩላ መሆኑን በመገንዘብ እንዲህ አለች "መስራቱንስ እሰራለሁ ነገር ግን ለእርሶ የሚመጥን ደረጃውን የጠበቀ አሪፍ ጫማ ለመስራት ጥሬ እቃው አይገኝም ብዬ ነው " አለች ። አንበሳም እንዲህ በማለት መለሰላት "ነገሩ እንደዛ ነው እንዴ ታዲያ ለኔ የሚሆን ጫማ ለመስራት የሚያስችለው ጥሬ እቃው ከምንድንነው የሚገኘው " በማለት በለሙያዋን ቀበሮ ጠየቃት ቀበሮም "ከጅብ ቆዳና ከተኩላ ጅማት ነው "አለች ። ይህኔ አንበሳም ጅብንና ተኩላን እየተመለከተ የኔ ጫማ መሰራት ስላለበት እናንተ መሞት አለባችሁ በማለት ነገራቸው በውጤቱም ጅብና ተኩላ ተገደሉ።
➨ከዚህ አስተማሪ ታሪክ የምንማረው ፦
➢ጅብና ተኩላ የተገደሉት ሴራን ማሴር የጀመሩ ግዜ ነው
መገደላቸውን ያወቁት ደግሞ የሴራቸው ውጤት ተፈፅሞ ለማየት በመጓጓት ቦታውን በተገኙበት ሰዐት ነው ።
➥ሴረኞች የሴራቸው ውጤት እራሳቸው ጋ እንደሚመለስ ቢያውቁት ኖሮ በሌላ ሰው አያሴሩም ነበር ስለዚህ ነው በሁሉም ሴረኞች ስግብግብነትና ድንቁርና የሚስተዋልባቸው ።
ሴረኛ ከሳሾች የተከሳሽን መልስ ቢያውቁ ኖር በተንኮል ለመክሰስ ከቤታቸው አይወጡም ነበር ነገር ግን በሴረኝነታቸው የተነሳ ከተንኮል ውጪ ምንም የማያውቁ ፀሐይና ዝናም የማይፈራ የተጋደመ ግንድ ናቸው ።
➧በሌሎች ለይ መጥፎ ናፋቂ ምቀኛ እነ ሴረኛ ሆይ እወቅ የስራ ውጤት አንተ ለይ እንጂ ማኑም ጋ አይደርስም ።
ስለዚህ የተንኮል ጉድጓድህን ስትቆፍር ሳትርቅ በቅርብ ቆፍራው የምትገባበት አንተው እራስህ ሊሆን ይችላልና ።
◈◀ قال الله تعالى
{ وَلا يَحِيقُُ المَكْرُ السَّيِّئُ إِلا بِأَهْلِه }
[ فاطر : ٤٣ ]
➸የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል
"የመጥፎ ሴራ ጉዳቱ በባለቤቱ ለይ እንጂ በሌላ በማኑም አይደርስም ።"(ፋጢር 43)
📝ተጨማሪ ትምህርቶችን ለመከታተል
የቴሌግራም Channeሉን ይቀላቀሉ !
https://t.me/MisbahMohammed_6682
2 033
ውሸትን እንጠንቀቅ!!
———
በተለይ እራሳችን ወደ ሰለፊይነት ያስጠጋን ሰዎች በሐቀኝነት፣ ውሸት አጥብቀን በመጠየፍና በመጠንቀቅ ለሰዎች ጥሩ አርኣያ ልንሆን ይገባል!! የውሸትን ሀራምነትና ፀያፍነት የሚገልፁ የተለያዩ የቁርኣንና የሐዲስ ማስረጃዎች እጅግ በጣም በርካታ ናቸው። ይህ ከመሆኑም ጋር ግን አላህ ይጠብቀንና ብዙዎች በዚህ በሽታ ሲወድቁ ይስተዋላል፣ ይልቁንም ሰዎችን መልካም የሚያስተምሩ "አገሌማ አይዋሸም…" ተብለው የሚገመቱ ሰዎች በማይታሰብ መንገድ ውሸትና ያልተረጋገጠ ወሬ ሲያወሩ በሰማሀው ጆሮህ እስከማፈር ትደርሳለህ።
ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ዶ/ር ረቢዕ ቢን ሃዲ'ል መድኸሊይ (ሀፊዘሁላህ) እንዲህ ይላሉ:-
“በአላህ ይሁንብኝ አንድ ሰለፊይ ይዋሻል ብዬ አዕምሮዬ ላይ መቅረፅ አልችልም!። ለሚስት (በአንዳንድ ከአቅም በላይ በሆኑ ነገሮች ላይ ለማረጋጋት ሲባል) መዋሸት እንደሚፈቀድ አውቃለሁ፣ ነገር ግን አላደርገውም! ልዋሻት አልችልም። ለወንድ ልጅ (በአንዳንድ አስገዳጅ ሁኔታዎች ለቤተሰቡ፣ለሚስቱና ለልጆቹ) መዋሸት በስሱ የተፈቀደበት ሁኔታ አለ፣ ነገር ግን ወላሂ እኔ በቤተሰቤ ላይ ይህንም ቢሆን አላደርገውም። በእውነት ቢሆን እንጂ አልኗኗራቸውም። እኔ ቤተሰቦቼንም ልጆቼንም የማሳድገው በእውነት ነው፣ አልሀምዱ ሊላህ ምልክቱን (ውጤቱንም) እየተመለከትኩባቸው ነው። ተማሪዎቼንም የማንፀው፣ ሙስሊሙንም ማህበረሰብ በሙሃዶራዎቼና በኪታቦቼ የምመክረው በእውነተኝነት ነው። ከውሸት በማስጠንቀቅ!! በዲናዊና በዱኒያዊ ጉዳዮች ላይ ያለውን አደገኝነቱንም አብራራላቸዋለሁ!!።” [አል-ፉሱል አል'ሙዲየህ ሚን ሲረቲ ሸይኽ ረቢዕ 146-147]
ይህ የሸይኽ ረቢዕ ንግግር ለሚገባው ትልቅ መልእክት አለው!! የአንዳንድ ሰዎች ሁኔታ በጣም ይደንቀኛል!፣ "አይዋሸኝም" ብሎ የሚያስባቸውን ሰው በማስረጃ እስኪይዛቸው ዓይን ያወጣ ውሸት ይዋሹታል፣ በማስረጃ ሲጋለጥ ደግሞ ለራሱ ከኪሱ አውጥቶ በሰጠው ፈትዋ "ከዚህ ከዚህ… አንፃር መስለሃ አለው ብዬ ነው" ብሎ የሌባ አይነ ደረቅ… እንደሚባለው ድርቅ ሲል ይስተዋላል።
ውሸትን እንጠንቀቅ!! ውሸትን እንጠየፍ!!
✍🏻ኢብን ሽፋ
#join ቴሌግራም ↘️↘️ ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa
Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel:
⤵️⤵️https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f
2 033
➥ይህ በወራቤ ከተማ አስተዳደር የሰለፊዮች ኢሕሳን መድረሳ ➀ደርሶችና
➁ሙሐደራዎች የሚለቀቁበት ጉሩፕ ነው
➴➴➳➴➴➴➵➴➴
https://t.me/Ehsanmedresaworabe
2 033
📙 عنوان الرسالة: مجمل عقيدة السلف الصالح لشيخ صالح بن فوزان الفوزان
(የሸይኽ ሷሊሃልፈውዛን ሪሳላ የ ሆነችው ሙጅመሉ ዓቂ ደቲ አሰለፍመ አመሷሊህ)
ክፍል አምስት (05)
🎙በኡስታዝ አቡ ሙዓዝ
📚የኪታቡን pdf ለማግኘት👇👇
https://t.me/ibnbaz1212/66
📆 ዕለተ ጁሙዓ ዙልሂጃ 26, 1447
🕌 በመድረሰቱል ኢኽላስ ለሁልባረግ የሴቶች ጀመዓ የተሰጠ ኮርስ
የቴሌግራም ቻነል
https://t.me/ibnbaz1212
2 033
Repost from አቡ ኑህ አስ'ስልጢይ [ Misbah Mohammed ]
➽ለረሱላችን ﷺ በኛ ለይ የላቸው ትልቁ ሐቃቸው ◄
صلوا عليه (6) - صلى الله عليه وسلم
https://t.me/MisbahMohammed_6682
2 033
በአላህ ፈቃድ በሌላ ርእስ እመለሳለሁ…
✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)
#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
2 033
እውነተኛ ሠለፊይ ነኝ ካልክ፣
በቢድዐህ ሰዎች ላይ ትክክለኛ የሠለፎች አቋም ይኑርህ!!
—————
ልብህ የተምይዕ በሽታ ሳይመርዘው ከቢድዐህ ባለ ቤቶች ጋር ያለህን መቀራረብ በፍጥነት አቋርጥ።
አንተ እውነተኛ የሀቅ ተከታይ ከሆንክ ስለ ቢድዐ ሰዎች ጠንከር ያለን ንግግር ስትሰማና ስታነብ አትበርግግ!። ይልቅ በስምህ ወደ ሰለፎች እንደተጠጋህ ሁሉ በተግባርህም ተከተላቸው!!
ብዙ ምስኪን የሆኑ ሰለፊይነትን የሚሞግቱ ወንድም እህቶች በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ ከተለያዩ የቢድዐህ ባለ ቤቶች ግንኙነት አላቸው፣ ለዚያም ነው በየ ጊዜው አቋማቸውን የሚቀያይሩና በአቋማቸው መፅናት ሲያቅታቸው የሚስተዋለው። አንድ ሠለፊይ ነኝ ያለ ሰው በምንም መንገድ ከቢድዐህ ባለ ቤቶች ጋር የሚገናኝበትና ንግግራቸውን የሚያደምጥበት መንገድ ሊኖር አይገባም!!። ምናልባት ጠንካራ እውቀት ኖሮት ረድ ሊያደርግባቸው (በስህተታቸው በማስረጃ መልስ ሊሰጥባቸው) አስቦ ካልሆነ በስተቀር ተንኮላቸውን አውቄያለሁ አልሸወድም ብሎ የትኛውም አካል ማድመጥም ሆነ የነሱን ፅሁፍ ማንበብ አይፈቀድለትም!! ትላልቅ እውቀት የነበራቸው ከቀደምቶችም በዚህ ዘመንም ስንቶች ከቢድዐህ ባለ ቤቶች ጋር ባላቸው መቀራረብና ማድመጥ የተቀየሩ አሉ። ከቢድዐህ ባለ ቤቶች ጋር በመቀራረብ ሰበብ ከተቀየሩ ቀደምት ሰው አንዱን ልጥቀስ…
የህ ኢብኑ መዒን (ረሂመሁላህ) የቡኻሪ ሸይኽ ናቸው እንዲህ አሉ:-
“ዳውድ ኢብኑ ሚህራን በሀዲስ የታወቀ ሀዲስን የሚፅፍ ሰው ነበር፣ ሀዲሱን ትቶ ከሙዕተዚላህ የሆኑ ሰዎችን ጓደኛ አድርጎ ያዘና አበላሹት።” [ተህዚቡል ከማል ፊ አስማኢ ሪጃል ገፅ 444 እና ተህዚብ አት-ተህዚብ ሊብኒ ሀጀር 3/174]
ታዲያ ኡሱል አስ-ሰላሳን እንኳን አስተካክሎ ያልቀራ ምስኪን በምን አቅሙ ነው የጥመት ባለ ቤቶችን ብዥታ እችላለሁ ብሎ ከስርስራቸው የሚልከሰከሰው?!፣ ታላላቅ የዲን መሪዎች እኮ ናቸው የቢድዐህ ባለ ቤቶችን ብዥታ በመፍራት በሩቁ ይጠነቀቁ የነበረው። የዲን ተማሪ የሆነ ሰው የአህሉሱንና መሻይኾችን ት/ት እየቀሰመ በመተግበር በተቻለው አቅም ሁሉ ለሌሎችም እንዲደርስ ሊያሰራጭ ይገባል እንጂ ማህበራዊ ሚዲያ ቀረበኝ ቀለለኝ ብሎ ከቢድዐህ ባለ ቤቶች ማህበራዊ ሚዲያም ሆነ በአካል ከስርስራቸው ሊልከሰከስ አይገባም!!
የቢድዐህ ባለ ቤቶችን ድምፅ መስማትም ሆነ ፅሁፍ ማንበብ ሀራም እንደሆነ እያወቀ ወደነሱ ማህበራዊ ሚዲያዎች የሚልከሰከስ ሰው በሰለፊይነቱ ሊጠነክርም ሆነ ሊፀና አይችልም።
ደጋግ ቀደምቶቻችን በቢድዓ ሰዎች ላይ የሚከተለው አይነት አቋም ነው የነበራቸው፣ እውነት ከልብ እነሱን እንከተላለን ካልን በቢድዐህ ባለ ቤቶች ላይ ይህ የሠለፎች አቋም ሊኖረን ይገባል!!
ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁ) ስለ ቀደሪዮች መከሰትና በቀደር ላይ ያላቸው የተዛባ የፈጠራ አመለካከታቸው ሲነገረው እንዲህ አለ:-
“…እነዚህን ሰዎች ካገኘሃቸው ንገራቸው:- እኔ ከነሱ የጠራሁኝ ነኝ፣ እነሱም ከኔ የጠሩ ናቸው። በዚያ ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር በሚምልበት ጌታ (በአላህ) ይሁንብኝ እነዚህ ሰዎች የእሁድን ተራራ ያህል ወርቅ ቢኖራቸውና ሶደቃ ቢያደርጉት በቀደር እስኪያምኑ አላህ አይቀበላቸውም።” [ሙስሊም፣ ነሳኢይ፣ አቢዳውና ትርሚዚይ ዘግበውታል]
በይሀቂይ (ረሂመሁላህ) ስለ ኢማሙ ሻፊዒይ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ:-
“ኢማሙ ሻፊዒይ (ረሂመሁላህ) በአፈንጋጮችና በቢድዓ ሰዎች ላይ ጠንካራ ነበሩ፣ በነርሱም ላይ ያላቸውን ጥላቻቸውንና ኩርፊያቸውን ግልፅ ያወጡት ነበር።" [መናቂቡ ሻፊዒይ ጥራዝ 1/469]
ኢማሙ አህመድ (ረሂመሁላህ) እንዲህ ብለዋል:-
“አንድ ሰው በሙብተዲዕ ላይ ሰላምታን ካቀረበ እሱ ያንን የቢድዐ ሰው ይወደዋል ማለት ነው።" [ጦበቃቱል ሀናቢላ ጥራዝ 1/196]
ይህ የኢማሙ አህመድ ንግግር የቢድዐ ሰዎችን መውደድ እንደማይፈቀድና ጭራሹኑ እነሱን መዝጋት ተገቢ እንደሆነ አመላካች ነው።
ዐብዱላህ ኢብኑ ሙባረክ (ረሂመሁላህ) እንዲህ ይሉ ነበር:-
“አላህ ሆይ! እኔ ዘንድ ለቢድዐህ ባለቤት ውለታን አታድርግለት፣ (ውለታ ካለብኝ) ልቤ ይወደዋልና።" [ሸርህ ኡሱል ኢዕቲቃድ አህሉሱንነቲ ወልጀማዐህ ጥራዝ 1/140]
የቢድዐ ሰው ውለታ ያለበት እውነታውን ቢያውቀውም መናገር ይከብደዋል። ይህ ደግሞ አላህ ይጠብቀንና በተጨባጭ የታየ ነገር ነው። ብዙዎችን ገደል የከተተውም ይሄው ነው።
ፉደይል ኢብን ዒያድ (ረሂመሁላህ) እንዲህ ብለዋል:-
“የቢድዐ ባለቤቶችን የወደደ ሰው አላህ ስራውን አበላሽቶበታል፣ የእስልምናን ብርሃንም ከልቡ አውጥቶበታል።"
[ሸርሁ ሱንነህ ሊልበርበሃሪይ 138–139 አል ኢባነህ ሊብኒ በጣህ ጥራዝ 2/460]
ልብ በሉ የቢድዐህ ባለ ቤትን መውድ ያለው አደጋ!!
ዐብዱላህ ኢብኑ ዳውድ (ረሂመሁላህ) እንዲህ ብለዋል:-
“ከሀቅ ምልክቶች ሀይማኖትን በስሜት የሚይዝን ሰው መጥላት ነው። ሀቅን የወደደ ሰው በእርግጥም የስሜት ባለቤቶችን (የቢድዓ ሰዎችን) መጥላት ግዴታ ሆኖበታል።"
[ሲየር አስሰለፍ አስሷሊሂን ሊተይሚይ ጥራዝ 3/1154]
ሙሀመድ ኢብኑ ሲሪን (ረሂመሁላህ) ዘንድ ሁለት የስሜት ባለ ቤት የሆኑ ሰዎች ገቡና እንዲህ አሉት:-
“አንተ የበክር አባት ሆይ! አንድ ሀዲስ እንንገርህ? አሉት፣ በጭራሽ አይሆንም፣ አላቸው፣ አንድ የቁርኣን አንቀፅ እንኳን እንቅራልህ? አሉት፣ በጭራሽ አይሆንም!፣ አላቸውና ትነሳላችሁ አለያ እኔ ተነስቼ እወጣላችኋለሁ፣ አለ፣ ተነስተው ወጡ። ከወጡ በኋላ ከአጠገቡ የነበሩ ሌሎች ሰዎች፣ የበክር አባት ሆይ! ቁርኣን ቢያነቡልህ ምንችግር አለው? ብለው ጠየቁት፣ እንዲህ በማለት ድንቅ መልስ መለሰ:- የቁርኣኑን አንቀፅ አንብበውት ያለ ትርጉሙ አዛብተው ተርጉመውት በልቤ እንዳይቀር ፈርቼ ነው።” [ሲየር አዕላም አንኑበላእ ሊዘሀቢይ ጥራዝ 11/285]
ይህ ታላቅ የኢስላም ሊቅ በዚህ መልኩ ከፈራ አንተ ማን ነህ እንደ ዝምብ ሁሉም ላይ ዘለህ ጥልቅ የምትለው?!፣
የጣውስ ልጅ (ረሂመሁላህ) አንድ የቢድዐህ ባለ ቤት የሆነ ሰው እያናገረው ለልጁ እንዲህ አለው:-
“ልጄ ሆይ የሚናገረውን እስከማትሰማ ድረስ ጣቶችህን ጆሮህ ውስጥ ክተታቸው፣ ከዚያም ቀጠል አደረገና በደንብ ጠንከር አድርገህ አስገባ አጠንክር። አለው” [አላለካኢይ እና ሲየር አዕላም አንኑበላእ]
በዚህን ጊዜ ሰለፊይነት ስም ብቻ እስኪመስል ድረስ አንዳንድ ወንድምና እህቶች ዘንድ ከቢድዐህ ሰዎች ጋር ሊኖር የሚገባው ጠንካራ የሰለፎች አቋም ወርዷል። የሰለፎቻችን በቢድዐህ ሰዎች ላይ የነበራቸው ጠንካራ አቋም ኪታብ ላይ ይቀራል ተግባር ላይ ግን አደጋ ላይ ነው። በተለይ ብዙ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያ ፕሮፋይል ላይ ሰለፊነትን ለማንፀባረቅ ማሻአላህ ናቸው፣ በተግባር ግን ከሙመይዓና ከኢኽዋን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስሮች ስር ሲልከሰከሱ ይስተዋላሉ፣ አላህ ይጠብቀንና የሆነ ኮሽታ ሲፈጠር ወደዚያው ለመጠቃለል ቅርብ ናቸው፣ ከዚህ ተግባር ልንቆጠብና ከቢድዐህ ባለ ቤቶች የተኛውንም መልእክታቸውን ከሚያብራሩባቸው የማህበራዊ ሚዲያም ሆነ ሌሎች መድረኮች መራቅና መጠንቀቅ ግዴታ ነው። ሙመይዓዎች ወርደው ከአል ኢኽዋኑል ሙስሊሚን ጋር የተደመሩበት አንዱ አደጋ ይህ ነበር። ሰለፊይ ነን ካልን በአቋማችን የፀናን ልንሆን ይገባል!! የሰለፎችን አቋም በሁለመናችን ተግባራዊ ልናደርግ ግድ ይለናል!! አላህ በሐቅ ላይ ያፅናን!!
