fa
Feedback
ር ግ ብ የ 🕊

ር ግ ብ የ 🕊

رفتن به کانال در Telegram

“ርግቤ🕊️ መደምደሚያዬም አንዲት ናት፤ ለእናትዋ አንዲት ናት ለወለደቻትም የተመረጠች ናት። ቈነጃጅትም አይተው አሞገሱአት፥ ንግሥታትና ቍባቶችም አመሰገኑአት።”⛪🤍 — መኃልየ. 6፥9

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
356
مشترکین
-224 ساعت
+37 روز
+4530 روز
آرشیو پست ها
"ክርስቲያኖችን የሚጠሉና የሚገድሉ ሰዎችን ልንጸልይላቸውና ልናዝናላቸው ይገባል፤ ምክንያቱም ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁምና። ጌታችን በሰቀሉት ጊዜ 'የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው' እንዳለ፣ እኛንም የሚገድሉን ሰዎች በእኛ ላይ ሳይሆን በገዛ ነፍሳቸው ላይ የዘላለም ፍርድን እያመጡ መሆኑን የማያውቁ ምስኪኖች ናቸው።"
+ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ +

ወደ ህይወት መንገድ ይመራኛል ጌታ 💗🥹

photo content

⭐️በጽድቁ ከሚመካ ጸድቅ ሰው ይልቅ ስለ ኃጢአቱ የሚያለቅስ ዘማዊን እግዚብሔር ይወዳል።✅ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
⭐️በጽድቁ ከሚመካ ጸድቅ ሰው ይልቅ ስለ ኃጢአቱ የሚያለቅስ ዘማዊን እግዚብሔር ይወዳል።✅
ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

☦️"እኔ እለምናለሁ አንቺ ጸሎቴን ታሳርጊያለሽ ልጅሽም ኃጢአቴን ያስተሰርያል። የልቤን ግዳጅ ይሰጠኛል። እኔ ቁስለኛ ነኝ አንቺ የመድኃኒት ሙዳይ ነሽ። ልጅሽም ባለ መድሀኒት ነው።"
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ(መፅሀፈ 📖አርጋኖን)

⭐ የTelegram Star መሸጥ የምትፈልጉ 😊 በተመጣጣኝ ዋጋ ልንገዛቹ ብቅ ብለናል መሸጥ የምትፈልጉ አሁኑኑ DM አናግሩኝ👉 @Ortho_29
ካቅም በላይ ዋጋ አጠይቁ  😁

✅“ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤”🩵
— ሮሜ 6፥5

❤️"ፍቅር ማለት ሁልጊዜ መግባባት ብቻ አይደለም፤ ፍቅር ማለት ባልተግባባችሁበት ጊዜ እንኳ እርስ በርስ የምታሳዩት መከባበርና መቻቻል ነው። እውነተኛ ፍቅር የአጋሩን ዝምታ እንደ ቁጣ ሳይሆን እንደ መከፋት ተረድቶ፣ 'ምን ላግዝህ/ሽ?' ብሎ ቀድሞ የሚጠይቅ ንቁ ልብ አለው።"✔️
+ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ +

☦️ብዙዎች ነቢያትና ጻድቃን አንቺን ሊያዩ ወደዱ አላዩም ምሳሌሽን እንጂ፤፤ የልጅሽን የመለኮትነቱን ምሥጢር ያየን እኛ ግን በቅድስት ጠረጴዛ ሥጋውንና ደሙን ቁርባኑን ተቀበልን አንድ አካል አንድ አምሳል በመሆናችን የተመሰገንን ነን☦️
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መጽሐፈ አርጋኖን ምዕራፍ ፭ ክፍል ፲፭

💙ስለ እግዚአብሔር ሀያልነት ለማወቅ ግዴታ እንደ ፍርኦን መቅሰፍት እስኪያገኝህ አትጠብቅ ✔️ይልቁንም በፍቅሩ ሰንሰለት ታሰር
✍✍Esuye ከሀጢያተኞች ዋና

ተወዳጅ የሆኑ መንፈሳዊ Channel ማግኘት ይፈልጋሉ ? የተለያዩ የኦርቶዶክስ አስተምሕሮ አዳዲስ መዝሙሮች የኦርቶዶክስ ስእላት እናም የተለያዩ ነገሮችን የምታገኙበት Channel ከስር Join በማለ
ተወዳጅ የሆኑ መንፈሳዊ Channel ማግኘት ይፈልጋሉ ? የተለያዩ የኦርቶዶክስ አስተምሕሮ አዳዲስ መዝሙሮች የኦርቶዶክስ ስእላት እናም የተለያዩ ነገሮችን የምታገኙበት Channel ከስር Join በማለት add Channel በመቀላቀል ያግኙ 😊

⭐️"ክርስቲያን ነኝ እያልክ በልብህ ቂም ይዘህ የምትዞር ከሆነ፣ ገና ክርስትና አልገባህም። ፍቅር ማለት የበደሉህን ሰዎች መውደድ ብቻ አይደለም፤ ለአንተ ክፉ ለሚያስቡትም ጭምር ከልብህ በጎ መመኘትና መጸለይ ነው። ክርስቶስ በመስቀል ላይ የፈሰሰው ደሙ ጠላቶቹን ጭምር ይቅር ለማለት እንደነበረ አትርሳ።"✅
+ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ +😇

✔️''ጠቢባንስ እግዚአብሔርን ያለጥርጥር በሙሉ ልብ የሚያምኑት፤ አምነውም እንደ ፈቃዱ የተከተሉት፤ በክንፈ ጸጋ ተመስጠው ከልብ በሚወጣ ውዳሴ ከእርሱ ጋር ተዋሕደው የሚኖሩ ናቸው፡፡የነፍሳቸውን ረብሕ ጥቅም አውቀው ዕለት ዕለት ያንን የሚለማመዱ በእውነት ጠቢባን እነዚህ ናቸው፡፡''✅
[ቅዱስ አባ እንጦንስ]

ቅኔ ማህሌቱ በደምህ ረሰረሰ መቅደስ ተቃጥሎ መሰውያዉ ፈረሰ ጮሁ ደናግላን ደም እንባ አለቀሱ በቅድሱ ስፍራ ታርዷልና ቄሱ