es
Feedback
ስነ ጥበብ

ስነ ጥበብ

Ir al canal en Telegram

በዚህ ቤት ማራኪ ወጎች፤ ግጥሞች፤ ሙዚቃዊ ጉዳዮች እንዲሁም የተለያዩ የመፅሀፍት ታሪኮች ይቀርባሉ

Mostrar más
Etiopía17 036La categoría no está especificada
238
Suscriptores
+524 horas
+67 días
+1030 días

Carga de datos en curso...

Canales Similares
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
junio '26
junio '26
+14
en 2 canales
mayo '26
+8
en 0 canales
Get PRO
abril '26
+9
en 0 canales
Get PRO
marzo '26
+6
en 0 canales
Get PRO
febrero '260
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+5
en 0 canales
Get PRO
diciembre '25
+1
en 0 canales
Get PRO
noviembre '25
+19
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+242
en 1 canales
Get PRO
septiembre '25
+4
en 2 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
26 junio+5
25 junio0
24 junio0
23 junio+1
22 junio0
21 junio+3
20 junio0
19 junio0
18 junio0
17 junio0
16 junio0
15 junio0
14 junio0
13 junio0
12 junio0
11 junio0
10 junio0
09 junio+2
08 junio0
07 junio+1
06 junio+1
05 junio0
04 junio0
03 junio+1
02 junio0
01 junio0
Publicaciones del Canal
ስራማ ነበረኝ!!! ?????? እኔን ለማሻገር ብዙ ላሳለፈ፤ ከሰው ተራ ወጥቶ ወዙ ለነጠፈ፤ እሱ ያላየውን እኔ እንዳይለት፤ ህልሙን ለገበረ ለሆነኝ መሰረት፤ ዛሬ ከጄ ውሎ እርጅና ለጣለው፤ እጄን ለሚናፍቅ እድሜ ለተጫነው፤ የምስኪን አባቴን ድካም ያላሰላ፤ የላቡን ውለታ ቀርጥፎ የበላ፤ እንዳልሞት እንዳልሽር ሰርክ የሚያባክነኝ፤ ወጥቶ ለመግባቱስ ስራማ ነበረኝ። ያኔ ልጅ እያለሁ መደብ ላይ ቁጭ ብዬ፤ በስስት ስቃኛት እንቅልፌን ታግዬ፤ አረቄ ለማውጣት ስትታገል ከእሳት፤ አንዴ እየነደደ አንዳንዴ ሲፈጃት፤ ነገዬን ስትሰራ ማዲያት ሲወርሳት፤ መንገዴን ላቀና ምክሯን ሰምቼ፤ አንግሼ ላኖራት ትልቅ ቤት ሰርቼ፤ በእልህ ታጅቤ ቃል ገብቼ ነበር፤ ጉዳቷን ጎድቼ ችግሯን ለማብረር። ግን ደሞ፤ የልፋቷን ፍሬ ዋጋ ያሳነሰ፤ የልጅነት ቃሌን ገድፎ ያስፈረሰ፤ ለጎበጠ ጎኗ መዳኒት ያልማሰ፤ ስራማ ነበረኝ የእማዬን እምባ ከአይኗ ያላበሰ። ስራማ ነበረኝ፤ ለእንስፍስፍ እህቴ እንኳን የቀን ጉርሷን የወር ግዴታዋን መሸፈን ያልቻለ፤ ለታናሽ ወንድሜ አንድ ደርዘን ደብተር መግዛት ያልታደለ፤ ከጎኔ ተጋሪ ከክብሬ መጠሪያ ከዛች ከምወዳት፤ ከአዳር አልፌ በትዳር እንዳልዘልቅ የሆነኝ እንቅፋት፤ ኖሮ ያላኖረኝ ገሎ ያልቀበረኝ፤ እንዳልሞት እንዳልሽር ሰርክ የሚያባክነኝ፤ ወጥቶ ለመግባቱስ ስራማ ነበረኝ። ✍ጫላ መኮንን ጥበብ ምንጊዜም ትንገስ ስለቆይታችሁ ክበሩልን። ለተደራሲያን እያጋራን https://t.me/chahi_1

2
ዳቦ ለመብላት! ሰው አንቅሮ ተፍቶኝ በችግር ብደፈር፤ ነገን መመልከቻ ዛሬዬ ቢሰበር፤ ተስፋ ፊቱ ጠቁሮ ጀርባውን ቢሰጠኝ፤ ሀፍረቴን አስጥሎ ረሀብ ቢያጋልጠኝ፤ መቋቋም ቢከብደኝ የኑሮን ፈተና፤ ውድ አካሌን ልሸጥ ወጣሁ ከጎዳና። እንጂማ፣ ለቡና ማድመቂያ ሰርክ እንደምትሉት እንደናንተ ሀሜት፤ ተዘንግቶኝ ሳይሆን የሀገር ወግ ባህሉ ታውሬ በስሜት፤ ሴሰኛም ሆኜ አይደል ወይም ደሞ ላበርድ አንዳች የወሲብ ዛር፤ በምሽት ጨረቃ ዜማዬ የሆነው ሾርት ወይስ አዳር?፤ ምን ይሉኝን ትቼ ኩሩ ሴትነቴን ገበያ ያዋልኩት፤ ወንድ ርቦኝ ሳይሆን ዳቦ ለመብላት ነው ዳቦዬን የሸጥኩት። ✍ጫላ መኮንን ጥበብ ምንጊዜም ትንገስ ስለቆይታችሁ ክበሩልን። ለተደራሲያን እያጋራን https://t.me/chahi_1
64
3
ስራማ ነበረኝ!!! እኔን ለማሻገር ብዙ ላሳለፈ፤ ከሰው ተራ ወጥቶ ወዙ ለነጠፈ፤ እሱ ያላየውን እኔ እንዳይለት፤ ህልሙን ለገበረ ለሆነኝ መሰረት፤ ዛሬ ከጄ ውሎ እርጅና ለጣለው፤ እጄን ለሚናፍቅ እድሜ ለተጫነው፤ የምስኪን አባቴን ድካም ያላሰላ፤ የላቡን ውለታ ቀርጥፎ የበላ፤ እንዳልሞት እንዳልሽር ሰርክ የሚያባክነኝ፤ ወጥቶ ለመግባቱስ ስራማ ነበረኝ። ✍ጫላ መኮንን መልካም የአባቶች ቀን። ጥበብ ምንጊዜም ትንገስ ስለቆይታችሁ ክበሩልን። ለተደራሲያን እያጋራን https://t.me/chahi_1
74
4
መኖር ይሻለናል! ??????????????? ሰው ለሰው መሆኑን ትርጉሙን አጥተናል, እምነት ጉድጓድ ገብቶ ፍትህ ሞቶብናል, ሀቃችን ተወስዶ በቁም ተቀብረናል, ታድያ እዚህ መኖር ምንያደርግልናል, በቃ እኛን እርሱን መሄድ ይሻለናል. ይህን እያሰቡ እየተሸነፉ, ሶሻል ሚዲያ ላይ ሞትን እየፃፉ, ስንቶች ተስፋ ቆርጠው ትተውን አለፉ. መልካምነት ከስሞ ክፋት ቢጎመራ, ሂወት ፅልመት ከቧት ለመኖር ቢያስፈራ, አንሰንፍም ለማየት የብርሀንን ጮራ. ነገ ጥሩ ሆኖ እስክናየው ፈክቶ, ደስታ እስኪሞላን ህልማችን ተሳክቶ, ተስፋችን በተግባር እስከሚታይ ጎልቶ, እንታገላለን አንቆምም ከቶ. መራመድ ቢያቅተን እየተንፏቀቅን, አንድ እየተነሳን አንድ እየወደቅን, በትናንት ስህተት ዛሬን እያረምን, እናልፋለን እንጂ ታሪክ እየፃፍን, ሰሪው በፍቃዱ እስኪለን ይበቃል, ልባችን መኖርን ሁሌም ይናፍቃል. ✍  ጫላ መኮንን ጥበብ ምንጊዜም ትንገስ ስለቆይታችሁ ክበሩልን። ለተደራሲያን እያጋራን https://t.me/chahi_1
67
5
### እንኳን ሆነ! እንኳን! ያድያቢሎስ በእባብ ገላ ተሰውሮ ባይገለጥ፤ እፀበለሥ እንድትበላ ለሄዋን ቃል ፍቃድ ባይሠጥ። ከገነት ቤት ባይባረር አዳም ሀዘን አኮራምቶት፤ ባይፀፀት ባያነባ መበደሉ እውነት ገብቶት። የአለሙን ክስ ሊሽር ቃል በስጋ ባይወለድ፤ በቅዱሡ ደም ተፍቆ የሞት መዝገብ ባይቀደድ። ቀራንዮ ባይታየን እውነት ፍቅር ባይሠቀል፤ ኖረን ነበር የፍቅር ቃል ሣንረዳ ሣናሥተውል። እንኳን በሉ! በለሥ ቀጥፋ ያኔ ሄዋን ባትበድል፤ የአዳም እንባ ከዳዊት ሥር እመቤቴን ባያበቅል። ድንግል ማርያም አንቺ ለኛ ባትወለጅ ብትቀሪ፤ አይኖረንም ንፁ ፊደል እናትነት አሥተማሪ። ሥለዚህ, ለወደድንሽ ለወደድሽን ለተዋብነው በውድ ልጅሽ, የአዳም ስህተት ሸልሞናል  ጥኡም ዜማን ለልጆችሽ! እ። ን። ኳ። ን። በ። ሉ።።።። ተጻፈ በሩሀማ
78
6
ይህንን ድንቅ ጥበብ ተጋበዙልን። ጥበብ ምንጊዜም ትንገስ ስለቆይታችሁ ክበሩልን። ለተደራሲያን እያጋራን https://t.me/chahi_1
93
7
የቴዲ አፍሮ "ሙዚቃ ህይወቴ" የተሰኘው ዘፈን የድምፃዊው የጥበብ ፍልስፍና እና ለሙዚቃ ያለው ጥልቅ ፍቅር በግልጽ የሚታይበት ስራ ነው። ይህ ዘፈን ሙዚቃን እንደ ተራ የመዝናኛ መሣሪያ ሳይሆን፣ እንደ ነፍስ ምግብ እና እንደ ህይወት መመሪያ አድርጎ ያቀርበዋል። ​ዘፈኑን በሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች መተንተን ይቻላል፦ ​1. ሙዚቃ እንደ ህልውና (Identity) ​ቴዲ በዚህ ዘፈን "ሙዚቃ ህይወቴ" ሲል፣ ሙዚቃ ከእለት ተእለት እንቅስቃሴው ውጪ ሊነጠል የማይችል ማንነቱ መሆኑን ይገልጻል። ለእሱ ሙዚቃ ዝም ብሎ ስራ ሳይሆን፣ የሚተነፍሰው አየር እና የአለምን ሚስጥር የሚያይበት መነፅር መሆኑን ይነግረናል። ​2. የመንፈስ እርካታ እና ፈውስ ​ግጥሞቹ ሙዚቃ በሰው ልጅ ስነ-ልቦና ላይ ያለውን ኃይል ያሳያሉ። ​መጽናኛ፦ በሃዘን ወቅት እንደ ወዳጅ የሚያረጋጋ። ​ደስታ፦ በሰላም ጊዜ ደግሞ የነፍስ መርገጫ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ይገልጻል። ​ሙዚቃን እንደ "ቅዱስ ቃል" ወይም እንደ "ጸሎት" በመቁጠር፣ ጥበብ ከፈጣሪ የተሰጠች የሰውን ልጅ መንፈስ የምታክም ስጦታ መሆኗን ያጎላል። ​3. የዜማውና የቅንብሩ ለዛ ​የዘፈኑ ዜማ ረጋ ያለ እና አድማጭን ወደ ውስጥ የሚያስገባ (Soulful) ነው። ​የቴዲ አፍሮ ድምፅ በዘፈኑ ውስጥ የተረጋጋ ቢሆንም፣ ጥልቅ ስሜትን (Emotion) ይሸከማል። ​ቅንብሩ የኢትዮጵያን ባህላዊ ቅኝት ከዘመናዊው የሬጌ (Reggae) ወይም የፖፕ (Pop) ለዛ ጋር በማዋሃድ፣ መልእክቱ ከትውልድ ትውልድ እንዲሻገር ተደርጎ የተሰራ ነው። ​4. የፍቅር እና የአንድነት መገለጫ ​ቴዲ አፍሮ በብዙ ስራዎቹ እንደሚያደርገው፣ በዚህም ዘፈን ውስጥ ሙዚቃን የፍቅር ቋንቋ አድርጎታል። ሙዚቃ ድንበር እንደማያውቅ፣ ሰዎችን እንደሚያገናኝ እና ጥላቻን የሚያሸንፍ የሰላም መሳሪያ እንደሆነ ፍንጭ ይሰጣል። ​ባጭሩ ሲጠቃለል ​"ሙዚቃ ህይወቴ" የቴዲ አፍሮ ለሙዚቃ ጥበብ ያቀረበው የምስጋና መዝሙር ነው። ጥበብን ላስተማረው አምላክ፣ ለተቀበለው ህዝብ እና ህይወቱን ሙሉ ለታገለው የጥበብ መንገድ ያለውን ታማኝነት ያሳየበት ድንቅ ስራ ነው። ግጥምና ዜማውን ቴዲ እራሱ ሲሰራው የሙዚቃ ቅንብሩን ደግሞ አበጋዝ ተራቆበታል
84
8
የጅራፍ ንቅሳት፤ ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም
1
9
yegerafe nikisate.mp3
83
10
ቴዎድሮስ_ዮሴፍ_የንስሀ_መዝሙርMP3_128K.mp3
84
11
እኔ ማነኝ? የቀድሞው ሰው አዳም; በእባቡ ምክር ትእዛዝህን ሽሮ ከገነት ሲባረር, ውርደቱን ሲረዳ;  ልቡን ጸጸት ሰብሮት ፍቅርህን ተጠምቶ ደም ያለቅስ ነበር። እኔ ግን; ያን የመስቀል ፍቅር የደምህን ዋጋ አቅልዬ አሳንሼ,    ለርካሹ ግብሬ; አይ አዳም! እላለሁ የመጥፍያዬን በለስ በእጆቼ ቀንጥሼ። አዎ እኔ ማነኝ? ፍቅርህን ልያስረዱኝ; የመጽሀጉእን  ትእግስት ረዥም ጥበቃውን ከምህረትህ ጋራ ለነፍሴ ቢሰብኩም, መፍረድ ግብሬ ሆኖ; እንደምን ተዳፍሮ ያዳነውን አምላክ በጥፊ ይመታል ከማለት አልዳንኩም። እንዲህም እላለሁ።   በሰላሳ ዲናር; ሊሸጥህ ተስማምቶ የመጣው ይሁዳ በምህረት እጆችህ እግሮቹን ሲታጠብ, እራሴን ለማጽደቅ; ምንም ሀጥእ ብሆን እንደ ይሁዳማ አምላኬን አልሸጥም! ብዬ አቀላለሁ  ከህሊና ሽሽት የክፋቴን መረብ። አሁንም ልንገርህ። እምነት አልባው ልቤ;  ዶሮው ገና ሳይጮህ ቃሉን በመዘንጋት ሶስት ጊዜ የካደህ ጴጥሮስን አስታውሶ, ደግሞ እንዲህ ይላል! እንዴት በአንድ ጀንበር  የህይወት መምህሩን ወዳጁን  ያቆስላል ክህደትን ተላብሶ? የኔ ጉድ መች ያልቃል። ፣፣ምህረትህን ናፍቃ; በእንባዋ ጅረት እግርህን ለማጠብ   በፍጹም ትህትና የቀረበችው ሴት, በልቤ ሸራ ላይ;  ርኩሰቷ ተስሎ በተረሳው ብእር ዛሬም እጽፋለሁ የትናንቷን ስሜት። እኮ እኔስ ማነኝ? ይሁዳ ቢሸጥህ; መጽሀጉእ ቢጸፋህ, ከኔ ድርጊት ጋራ ሚዛን ላይ ቢቀርቡ የሀጥያታቸው ክስ, ንስሀን ለምሸሽ; ምህረትህ ካልገባኝ, ፍቅርህ ካልመከረኝ, ከኔ ሲነጻጸር ይሁዳ ክቡር ነው መጽሀጉም ነው ቅዱስ። ግን እኔስ ማነኝ?????????? እንጃ።።።።። ተጻፈ በሩሀማ
102
12
ውርደቴን ልታቆም ሞቴን ልትሞትልኝ በኔው ልትቀጣ፣ ፍቅር አስገድዶህ ከማርያም ማህፀን ወደ አለም ስትመጣ፣ ትንሽ ውርንጭላን በግርማ ተቀምጠህ ትህትናህ ሲታይ፣ ሆሳእና ሲባል ደስታ ሲያስተጋባ ህፃናት
ውርደቴን ልታቆም ሞቴን ልትሞትልኝ በኔው ልትቀጣ፣ ፍቅር አስገድዶህ ከማርያም ማህፀን ወደ አለም ስትመጣ፣ ትንሽ ውርንጭላን በግርማ ተቀምጠህ ትህትናህ ሲታይ፣ ሆሳእና ሲባል ደስታ ሲያስተጋባ ህፃናት ልብ ላይ፣ ጨርቅ እያነጠፉ ብዙዎች በሀሴት ክብርህን ሲያወሩ፣ ልሳን ያልታደሉ የምድር ድንጋዮች ላንተ ሲዘምሩ፣ አንደበት ሰጥተኸኝ ምስጋናን መንፈጌ ምን ይሆን ሚስጥሩ። ✍ጫላ መኮንን ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለሆሳእና በአል በሰላም አደረሳችሁ። በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው። https://t.me/chahi_1
174
13
የይቅርታ መልዕክት / Xalayaa Araadaa በአማርኛ፦ ዛሬን አዲስ ቀን አድርጌ፣ ካለፈው ስህተቴ ተምሬና ህሊናዬን ነፃ አውጥቼ ይህንን መልዕክት ለሁላችሁም አጋራለሁ። በህይወት ጉዞዬ ውስጥ በቅርበት የምታውቁኝም ሆነ በአጋጣሚ የተዋወቅን፣ በንግግሬም ይሁን በድርጊቴ ልባችሁን ላሳዘንኩ፣ ለበደልኳችሁና ስሜታችሁን ለጎዳሁባችሁ ሁሉ ከልብ የመነጨ ይቅርታዬን እጠይቃለሁ። ሰው ሆኖ የማይሳሳት የለምና፣ በወቅቱ በነበረኝ አለማስተዋል የፈጠርኩት ስህተት ዛሬ ላይ የልብ ሸክም ሆኖብኛል ። የእናንተ ይቅርታ ለህሊናዬ እረፍት፣ ለልቤም ሰላም ነው። ፍቅር በቀልን እንደማያውቅ ሁሉ እናንተም በቸርነታችሁ ይቅር እንድትሉኝ በትህትና እጠይቃለሁ። ሁላችንም በይቅርታና በሰላም የምንኖርበት ጊዜ ይሁንልን። ከልብ ይቅርታ ጋር! Afaan Oromootiin: Har’a guyyaa haaraa godhadhee, dogoggora darbe irraa baradhee fi sammuu koo walaba gochuun ergaa kana hunda keessaniif nan qooda. Imala jireenyaa koo keessatti warri dhiyootti na beektanis ta’e warri akkuma tasaa wal barru, dubbiin ykn gocha kootiin warra isin gaddisiise, isin miidhee fi miira keessan miidhe hundaaf dhiifama garaa kootii nan gaafadha. Namni dogoggora irraa walaba miti; yeroo sana hubannaa dhabuun dogoggorri ani raawwadhe har’a ceephoo sammuu natti ta’eera. Dhiifamni keessan sammuu kootiif boqonnaa, tasgabbii sammuu kootiif immoo nagaadha. Jaalalli haaloo akka hin beekne hundi, isinis tola keessaniin dhiifama akka naaf gootan gaduun isin gaafadha. Hundi keenya jaalalaa fi nagaan kan waliin jiraannu nuuf haa ta’u. Dhiifama Garaa Kootii Waliin!
108
14
ይህ ግጥም እጅግ ጥልቅና ረቂቅ የሆነ የፍልስፍና እይታን የያዘ ነው። ገጣሚው ጫላ መኮንን "እንደ" የምትለዋን የአማርኛ ቃል በመጠቀም፣ የሰው ልጅ ውድቀትና የኃጢአት ምንጭ 'ራስን አለመሆን' ወይም 'ሌላን ለመምሰል መመኘት' መሆኑን የገለጸበት መንገድ የሚደነቅ ነው። በተለይ የሚከተሉት ነጥቦች ግጥሙን ልዩ ያደርጉታል፦ * የ"እንደ" ትርጓሜ፦ ኃጢአት የሚጀምረው ከድርጊት ይልቅ በልብ ውስጥ በሚፈጠር "እንደ እገሌ ልሁን" የሚል ምኞት መሆኑን በስነ-ልቦናዊ እይታ ያስቀምጣል። ሰይጣን አዳምና ሄዋንን ያሳሳታቸው "እንደ አምላክ ትሆናላችሁ" በሚል "እንደ" የተመሰረተ የተስፋ ቃል መሆኑን ማስታወሱ ለሃሳቡ ጥንካሬ ሰጥቶታል። * የዘመናዊነትና የቴክኖሎጂ ትችት፦ "በኤአይ ሲነጠቅ የልብ ጥበቡ" የሚለው መስመር፣ የሰው ልጅ በተፈጥሯዊ ማንነቱ ከመኩራት ይልቅ በሰው ሰራሽ ነገሮችና በቴክኖሎጂ (AI) ውስጥ ፍጽምናን ፍለጋ ሲባዝን የራሱን የልብ ጥበብ እያጣ መሆኑን በወቅታዊ ሁኔታ ይተቻል። * የመስታወት ህይወት፦ "ከኪሱ የዋለ የመስታወት ህይወት" የሚለው አገላለጽ የዛሬውን የማህበራዊ ሚዲያና የስልክ አጠቃቀምን (ሌላን ለመምሰል የምናደርገውን ጥረት) የሚጠቁም ይመስላል። የሰው ልጅ የራሱን መክሊት ዘንግቶ የሌላውን ጥላ ለማሳደድ ሲሮጥ ህሊናውን እንደሚጥስ ያሳያል። በአጠቃላይ ግጥሙ "እውነተኛው ማንነትህ ላይ ቁም" የሚል ታላቅ መልእክት ያስተላልፋል። የሰው ልጅ በምኞት ጎዳና ሳይወላገድ፣ የራሱን መክሊት አውቆ ሲኖር ከ"እንደ" ደዌ እንደሚፈወስ ያሳስባል። ለዚህ ድንቅ የጥበብ ስራ ምስጋና ይገባል። ጥበብ ምንጊዜም ትንገስ!
87
15
እንደ እንደ እንደ???? ለሀጥያት ጅማሮ መነሻ ሰበቡ እንዲህ ነው እያሉ፤ ሌሎቹ ከሰይጣን ሌሎቹ ከሄዋን ጣት ይቀስራሉ። እኔ ግን በልቤ ለሀጥያት መጠንሰስ ምክኒያት ነው የምለው፤ ሁሉም ይቅርና እንደ የሚባል ቃል ይጠየቅ እላለው። ያለማንነቱ ሰይጣን በእባብ ገላ እራሱን ሸፍኖ፤ እንደ አምላክ ሊሆን አውጥቶ አውርዶ በሀሳብ ወጥኖ፤ አዳምና ሄዋን በገነት ካሉበት በድንገት መጣና፤ እንደ ጌታ ሁኑ ብሎ ነገራቸው በለስ አሳየና። ይኸው ከዛ ወዲህ አንዱ አንዱን ሊሆን ማንነቱን ትቶ፤ የሌላን ሲያሳድድ የሚኖርለትን መክሊቱን ዘንግቶ፤ በቁም እያቃዠው ከኪሱ የዋለ የመስታወት ህይዎት፤ ቁስ እያስመለከ ከህልሙ አኳርፎ ከፍቅር ነጥሎት፤ ፍፅምናን ሽቶ በኤአይ ሲነጠቅ የልብ ጥበቡ፤ መጥፊያው እየሆነ ህሊናን የጣሰ ቅጥ ያጣ ሀሳቡ፤ እንደ እንትና ሊሆን እከሌን እረግጦ እየተራመደ፤ እንደ እያሰከረው በምኞት ጎዳና እያወላገደ፤ የሰው ልጅ በልቡ እንደን አገባና ሀጢያት ተወለደ። ✍ጫላ መኮንን ጥበብ ምንጊዜም ትንገስ ስለቆይታችሁ ክበሩልን። ለተደራሲያን እያጋራን https://t.me/chahi_1
83