ዲ/ን ወ/አረጋዊ
Ir al canal en Telegram
የተለያዩ ትምህርታዊ የሆኑ ጽሑፎች የሚለቀቅበት channel ነው።“ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?” — ማርቆስ 8፥36
Mostrar más178
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
-330 días
Archivo de publicaciones
178
2 ክርስቶስ የተጠማው ምንድነው ?
😍 ውኃ ነው
ጌታችን እውነተኛ ሰው ስለሆነ ጠምቶ ነበር።
“ኢየሱስም ከመንገድ ድካም የተነሣ በጕድጓዱ አጠገብ ተቀመጠ...” (ዮሐ. 4፥6)ከዚያም ለሳምራዊቷ ሴት፦“ውኃ አጠጪኝ” (ዮሐ. 4፥7)አላት። ይህ እውነተኛ ሰውነቱን ያሳያል።
😍ክርስቶስ የተጠማው የሰው ልጅ ነፍስ ድህነት
“የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአል።” (ሉቃ. 19፥10)
እና“እኔ የምሰጠውን ውኃ የሚጠጣ ለዘላለም አይጠማም።” (ዮሐ. 4፥14)ይህ ያሳያል ክርስቶስ የጠየቀው የቁሳዊ ውኃ ብቻ ሳይሆን ሴቲቱን ወደሕይወት ውኃ ለማምጣት እንደነበረ ነው።
😍 የሰው ፍቅር
ዮሐንስ 4:9
ስለዚህ ሳምራዊቲቱ። አንተ የይሁዳ ሰው ስትሆን ሳምራዊት ሴት ከምሆን ከእኔ መጠጥ እንዴት ትለምናለህ? አለችው፤ አይሁድ ከሳምራውያን ጋር አይተባበሩም ነበርና።
😍 የሰው ልጅን ንስሐ
የ“ንስሐ” ትርጉም በክርስቲያናዊ እምነት ውስጥ ሰው ከኃጢአቱ በልቡ ተጸጽቶ፣ ስህተቱን አውቆ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ማለት ነው። ንስሐ የአእምሮ፣ የልብ እና የኑሮ ለውጥን ያካትታል፤ ሰው የቀድሞ ኃጢአተኛ መንገዱን ትቶ በጽድቅ መኖር ሲጀምር እውነተኛ ንስሐ አድርጓል ይባላል።
😍የንስሐ አስፈላጊነት
1 ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ግንኙነት ያድሳል – ኃጢአት ሰውን ከእግዚአብሔር ይለያል፤ ንስሐ ግን ወደ እርሱ ይመልሳል።
2 ኃጢአት ይቅርታ ያስገኛል – ሰው በቅን ልብ ሲናዘዝ እና ሲጸጸት የእግዚአብሔርን ምሕረት ይቀበላል።
3 መንፈሳዊ እድገት መሠረት ነው – ንስሐ የአዲስ ሕይወት ጅማሬ ሲሆን ሰውን ወደ ቅድስና ያመራል።
የልብ ሰላም ያመጣል – ስህተትን አምኖ ይቅርታ ማግኘት ከውስጣዊ ጭንቀት እና ከነቀፋ ያሳርፋል።
3❤ የሕይወት ውኃ የተባሉት
178
የሳምራዊቷ ሴት ታርክ እና ትምህርት
በደንብ አንብቡት በቀን 5/10/2018 በአርብ ጸሎት ላይ እንማማራለን ብየ አስበው የነበረው ትምህርት ነው ከተሞቻችሁ በክፍል ክፍል እለቃለሁ የጽሑፉን
። ውኃ አጠጪኝ ፤ዮሐንስ 4:7
ቃሉን የተናገረው በቃሉ .....ጌታችን መድሃንታች ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ቃሉ የተነገረላት በሰማርያ በምትባል መንደር ላይ ትኖር ለነበረችው ለአንድት ሳምራዊት ሴት ነው።
ዮሐንስ 4:7 ከሰማርያ አንዲት ሴት ውኃ ልትቀዳ መጣች። ኢየሱስም። ውኃ አጠጪኝ አላት፤
የክርስቶስ አምላካችን ደቀመዛሙርት መብዛት በጀመሩ ጊዜ ከይሁዳ ምድር ወደ ገሊላ .......በሰማርያ ምትባል መንደር ልያልፍ ግድ ሆነበት ...... ዮሐንስ 4 ተመልከቱ
***አራት ቁልፍ ሀሳቦችን እንመልከት ።
==1ለምን ውኃ አጠጪኝ ብሎ ለመናት? 2 ክርስቶስ የተጠማው ምንድነው ? 3 የሕይወት ውኃ የተባሉት ምንድናቸው ? 4 ዛሬ ላይ ክርስቶስ አምላካችን ከእኛ የሚፈልገው ውሃ ምንድነው ?
❤1 ለምን ውኃ አጠጪኝ ብሎ ለመናት?
ክርስቶስ አምላካችን ሁሉን ማድረግ የሚችል አምላክ ነው በምድር ላይ ሁሉን ያከናወነ መጽሐፍ እንዳለ ሁሉ በእርሱ የሆነ ነው ።. ሁሉ በእርሱ ሆነ፥ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ አልሆነም።ዮሐንስ 1:3 ስለዚህ ሁሉን ማድርግ እየቻለ ለምን ውኋ አጠጭኝ አላት ? የሚከተለሉትን ነጥቦች ልያስተምረን ነው
1:::እውነተኛ ሰው መሆኑን ለማሳየት
ክርስቶስ ፍጹም አምላክ እንደሆነ ሁሉ ፍጹም ሰውም ነው።ድካም፣ ረሃብ እና ጥማት እንደ ሰው ተቀብሎ ነበር።
“ውኃ አጠጪኝ” ማለቱ ጥማቱን ያሳያል።6. በዚያም የያዕቆብ ጕድጓድ ነበረ። ኢየሱስም መንገድ ከመሄድ ደክሞ በጕድጓድ አጠገብ እንዲህ ተቀመጠ፤ ጊዜውም ስድስት ሰዓት ያህል ነበረ።ዮሐንስ 4:6 በእግሩ ብዙ ምዕራፍ በመጓዙ ለስም አጠራሩ አምልኮትና ሰግደት ይሁንና በለበሰው ስጋ ተጠማ ተራበ በዚህም ሁሉ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን ገለጠልን ።ቅዱስ ቀርሎስ ዘእስክንድርያ እንደተናገሩት ፣ ጌታ የሰውን ባሕርይ በእውነት ስለ ተዋሐደ ጥማትን፣ ድካምንና ረሃብን በሰውነቱ ተቀብሏል፤ ነገር ግን እነዚህ መለኮቱን አይቀንሱም።
2 ሳምራዊቷን ሴት ወደ እምነት ለማቅረብ
ውይይቱን የጀመረው በውኃ ጥያቄ ነበር።
ከዚያም ሴቲቱን ወደ “ሕይወት ውኃ” ማለትም ወደ መንፈሳዊ ጸጋ አመራት።
3 ትሕትናውን ለማሳየት
የዓለም ፈጣሪ ሆኖ ሳለ ከአንዲት ሴት ውኃ ጠየቀ።
ይህ የታላቅ ትሕትና ምሳሌ ነው።
2 ክርስቶስ የተጠማው ምንድነው ?
178
አስራት ምንድን ነው?
አስራት ማለት ከሰው ገቢ፣ ምርት ወይም ንብረት አስረኛውን (10%) ለእግዚአብሔር መለየት ማለት ነው። "አስራት" የሚለውም ቃል ከ"አስር" የተገኘ ነው።
የአስራት ታሪክ
1. ከሕግ በፊት በአብርሃም ዘመን
አስራት የጀመረው በሙሴ ሕግ አይደለም። ከሙሴ በፊት በብሉይ ኪዳን አባቶች ዘመን ይታያል።
አብርሃም ነገሥታትን ድል ካደረገ በኋላ ከያዘው ምርኮ አስረኛውን ለመልከ ጼዴቅ ሰጠ (ዘፍጥረት 14፥20)።
ይህ የሚያሳየው አስራት ከሕግ በፊትም እንደ ምስጋናና እንደ አምልኮ መቅረቡን ነው።
2. በያዕቆብ ዘመን
ያዕቆብ በቤቴል እግዚአብሔርን ሲማጸን፦
"ከምትሰጠኝ ሁሉ አስረኛውን ለአንተ እሰጣለሁ"
ብሎ ተሳለ (ዘፍጥረት 28፥22)።
ይህም አስራት ከእግዚአብሔር በረከት ጋር የተያያዘ መሆኑን ያሳያል።
3. በሙሴ ሕግ
እግዚአብሔር ለእስራኤል ሕዝብ አስራትን እንዲያቀርቡ አዘዘ።
የአስራት ዓላማዎች፦
ሀ. ለሌዋውያን
ሌዊ ወገን ለቤተ መቅደስ አገልግሎት ተለይቶ ነበር፤ የራሱ የመሬት ርስት ስላልነበረው ሕዝቡ ከአስራታቸው ይደግፉት ነበር። (ዘኍልቍ 18፥21)
ለ. ለቤተ መቅደስ አገልግሎት
የመቅደስ አገልግሎት፣ መሥዋዕት እና ሌሎች ቅዱሳን ሥራዎች በአስራት ይደገፉ ነበር።
ሐ. ለድሆች
በየሦስት ዓመቱ የሚሰበሰብ አስራት ለመጻተኞች፣ ለድሆች፣ ለድሀ አደጎችና ለመበለቶች ይውል ነበር (ዘዳግም 14፥28-29)።
4. በነቢያት ዘመን
ሕዝቡ አስራት መስጠት ሲተው እግዚአብሔር በነቢዩ ሚልክያስ አማካኝነት እንዲህ አለ፦
"ሙሉ አስራቱን ወደ ጎተራ አምጡ" (ሚልክያስ 3፥10)
ይህ የተነገረው ሕዝቡ የቤተ መቅደስን አገልግሎት ችላ ስላለ ነበር።
5. በአዲስ ኪዳን
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስራትን በቀጥታ አልሻረውም፤ ነገር ግን ከአስራት ይልቅ ፍትሕ፣ ምሕረትና እምነት እንዳይረሱ አስተማረ።
"እነዚህን ማድረግ ሳይተዉ ያንንም ማድረግ ይገባችኋል" (ማቴ 23፥23)
በሐዋርያት ዘመን ምዕመናን ከአስረኛ በላይ እንኳ ንብረታቸውን ለችግረኞችና ለቤተ ክርስቲያን ያካፍሉ ነበር (ሐዋ. 4፥32-35)።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቤተ ክርስቲያኒቱ አስራትን እንደ ቅዱስ ልማድ ትቀበላለች። ምዕመናን ከገቢያቸው አስረኛውን ለቤተ ክርስቲያን፣ ለካህናት አገልግሎት፣ ለድሆች እና ለወንጌል ሥራ እንዲያወጡ ትመክራለች።
ነገር ግን አስራት በፍርሃት ወይም በግዴታ ሳይሆን፣ በፍቅርና በምስጋና መሰጠት አለበት። ቅዱስ ጳውሎስም፦
"እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፤ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም፤ እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጥን ይወዳል" (2ኛ ቆሮ. 9፥7)።
የአባቶች ማብራሪያ
የኦርቶዶክስ አባቶች አስራትን እንደ "የምስጋና መጀመሪያ ፍሬ" ይመለከቱታል። ሰው 100% ያለው ሁሉ የእግዚአብሔር ስጦታ መሆኑን በመቀበል 10% በመለየት ለፈጣሪው ምስጋና ያቀርባል።
ስለዚህ በኦርቶዶክስ አስተምህሮ አስራት የገንዘብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የእምነት፣ የምስጋና እና የታዛዥነት ጉዳይ ነው።
178
ሐዋርያት ጌታ ከሰማየ ሰማያት ወረደ፤ ከድንግል ማርያም ተወለደ፤ ተጠመቀ ታመመ መከራ ተቀበለ ተሰቀለ ሞተ ተቀበረ፤ ሞትን ድል ድርጎ ተነሣ፣ ዐረገ ዳግም ለፍርድ ይመጣል ብለው እንዲሰብኩ ድፍረቱን የሰጠ ምሥጢሩን የገለጠ ይኸው መንፈስ ቅዱስ ነውና!
(፪/፫)
178
( ... ከላይኛው የቀጠለ - ክፍል ፪)
በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስ ለምን ዓላማ ወረደ?
፩. ኀይልን ለመስጠት
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ በሰጣቸው ተስፋ መሠረት በበዓለ ሃምሳ ለደቀዛሙርቱ መንፈስ ቅዱስን ስለላከላቸው፣ ደቀ መዛሙርቱ በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ድኩማን የነበሩ ኀያላን፤ ፈሪዎች የነበሩ ደፋሮች ሆነው በራቸውን ዘግተውና ተደብቀው ከነበሩበት ቤት በድፍረት ወጥተው በቤተ መቅደሱ አካባቢ በተለያዩ ሥፍራዎች ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በይፋ ያለ አንዳች ፍርሃት ማስተማር ጀምረዋል። በዚያ የተሰበሰቡት የአይሁድ ሕዝቦች በሁለት ነገር እጅግ ተደነቁ፣ አንደኛ ሐዋርያት ለእነሱ እንግዳ የሆነ ስለ ክርስቶስ አዲስ ትምህርት ማስተማራቸው ሲሆን፣ ሁለተኛ ደቀ መዛሙርቱ በተለያዩ ቋንቋዎች ሲነጋገሩ ማየታቸውና መስማታቸው ነበር። ፈሪ ልብ የነበራቸው ሐዋርያት ይህንን አልጫውን ዓለም በወንጌል ጨውነት ለማጣፈጥ ጨለማውን ዓለም ወደ ብርሃን ለመለወጥ ከአርያም ልዩ ኀይል ያስፈልጋቸው ስለነበር ጎይልን ሊያለብሳቸው ወርዷል። ጌታችን ሊያርግ ሲል እንዲህ ብሎ ተስፋ ሰጥቷቸው ነበር፦
❝እነሆም አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ አልክላችኋለሁ፣ እናንተ ግን ከላይ ኀይል እስክትለብሉ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ❞— ብሏቸው ስለነበር በዚያ ቃል ኪዳን መሠረት መንፈስ ቅዱስ ኀይል ሰማያዊ ሊያጎናጽፋቸው ወረደላቸው (ሉቃ ፳፬፥፵፱ ፤ የሐዋ ፩፥፰)። ፪. ሐሰተኛውን ዓለም ለመውቀስ ሽፍታው በርባን እንዲፈታላት ጻድቁ ክርስቶስ እንዲሰቀልላት አብዝታ የጮኸችው ሐሰተኛዋ ዓለም መንፈስ ቅዱስና መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው ካልሆነ በስተቀር ደፍሮ ሊወቅሳት የሚችል ኀይል አልነበረም:: ምክንያቱም በውስጧ የሚኖሩ ሐስተኞች ናቸውና:: ለበርባን ነጻነትን፣ ለክርስቶስ ሞትን የደገሰችውን ዓለም መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት አድሮ ወቅሷታል። ጌታችን በቅዱስ ወንጌሉ፦
❝እርሱም መጥቶ ስለኀጢአት ስለጽድቅም ስለፍርድም ዓለምን ይወቅሳል❞ — ብሎ በተናገረው መሠረት መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት አንደበት ይህቺን ግፈኛ ዓለም ወቅሷታል - (ዮሐ ፲፮፥፲፪)። በእውነተኛው ጌታ አለማመን፤ ድል ስለተነሣው ጠላት ስለዲያብሎስ ውድቀት አለማወቅ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቀደመ ክብሩ መመለሱን አለማመን ትልቅ በደል ስለሆነ ይህንኑ በሐዋርያት ላይ አድሮ ግልጥ አድርጎ ለመውቀስ መንፈስ ቅዱስ ወረደ:: ስለዚህ ድንቅ ምሥጢር ባሕረ ጥበባት ቅዱስ ያሬድ ሲዘምር፦
❝አውጽኦሙ አፍአ እስከ ቢታንያ እንሥእ አዴሁ ወባረኮሙ ወይቤሎሙ ሰላም ለክሙ አዐርግ ሰማየ ኀበ አቡየ ወእቡክሙ ካዕበ እመጽእ ወእነሥአክሙ እነ እሄሉ ምስሌክሙ እፌኑ ለክሙ ጰራቅሊጦስሃ መንፈስ ጽድቅ — እስክ ቢታንያ አወጣቸው እጁን አንሥቶ ባረካቸው ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው ወደ አባቴ ወደ አባታችሁ ዐርጋለሁ፤ ዳግመኛም እመጣለሁ እወስዳችኋለሁ፤ እኔ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ፤ የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስንም አልክላችኋለሁ❞ — በማለት ተቀኝቷል፡፡ ፫. ሰዎችን ወደ እውነት ለመምራት ሕይወታችንን ወደ እውነት የሚመራን መንፈስ ቅዱስ ነው፤ ወይም በእውነት ጸንተን ስለእውነት እንድንመስክር የሚያደርገን መንፈስ ቅዱስ ነ
ው። ❝ወይቤሎሙ እፌኑ ለክሙ መንፈሰ ጽድቅ ጸራቅሊጦስሃ ዘይሄሉ ዘልፈ ምስሌክሙ ኢየጎድገክሙ ዕጓለ ማውታ ትኩኑ ዘኢይክል ዓለም ነሢኦቶ — ከእናንተ ጋር የሚኖር የእውነት መንፈስ ጰራቅሊጦስን እልክላችኋለሁ፤ እንደ እጓለ ማውታ አልተዋችሁም❞ ነቢዩ ዳዊት ወደ ጽድቅ ጎዳና ወደ እውነት ቦታ የሚመራ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ሲ
ዘምር፦ ❝ወመንፈስከ ቅዱስ ይምርሐኒ በምድረ ጽድቅ — ቅዱስ መንፈስህ ወደ ጽድቅ ምድርይምራኝ❞ — ብሎ እግረ ነፍሳችንን ወደ መንስተ ሰማያት፣ እግረ ልቡናችንን ወደ ወንጌል የሚያቀናልን መንፈስ ቅዱስ ነው! አሁን መንፈስ ቅዱስ ወደ እውነት ይመራል ሲባል ያለፈቃዳችን ይወስዳል ማለት አይደለም፤ ልቡናችን በጎ ሐሳብ እንዲያስብ ያደርገዋል፣ ሐሳብ ያሰበ ልቡና ደግሞ ወደ በጎ ስፍራ ይሄዳል ማለት ነው (መዝ ፻፵፩፥፲) ፤ ወደ እውነት የሚመራን መንፈስ ቅዱስ በመሆኑ ሁላችንም በዚህ መንፈስ ምሪት ልንጓዝ ያስፈልጋል። እውነተኞች ክርስቲያኖች ያለመንፈስ ቅዱስ ቅኝት በራሳቸው ምኞት አንዳችም ነገር አያደርጉም፤ የክርስቲያኖች የሕይወት አቅጣጫ ጠቋሚያቸው መንፈስ ቅዱስ ነው። ሐዋርያው ቅዱስ
ጳውሎስ፦ ❝እናንተ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ቢኖር በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም የክርስቶስ መንፈስ ከሌለው ግን የእርሱ ወገን አይደለም፣ ክርስቶስ በእናንተ ውስጥ ቢሆን ሰውነታችሁ በኀጢአት ምክንያት የሞተ ነው፤ መንፈሳችሁም በጽድቅ ምክንያት ሕያው ነው❞ — በማለት መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው በምድርም ቢኖር ኑሮው ግን ሰማያዊ ነው፤ በሥጋ ቢታይም ሕይወቱ ግን መንፈሳዊ መሆኑን ነግሮናል። ለኀጢአት ሙ መሆን ማለት ኀጢአት አለመሥራት ማለት ነው፣ ለጽድቅ ሕያው መሆን ማለት ደግሞ ለጽድቅ ሥራ መትጋት ማለት ነው (ሮሜ ፰፥፱)። ልጅነታችንን ከምናስመስክርበት ወይም ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር ከምናሳይበት መንገድ አንዱ በምንኖረው ኑሮ ውስጥ በእግዚአብሔር መንፈስ መመራት መቻላችን ነው፤ ሐዋርያው ቅ
ዱስ ጳውሎስ፦ ❝በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመራ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸው❞ — ሲል ያስረዳናል (ሮሜ ፰፥፲፬)። አባቶቻችን «ጻድቃንን ወደ ገዳም ሰማዕታትን ወደ ደም የሚወስድ መንፈስ ቅዱስ ነው»፡፡ ይላሉ:: ይህ ማለት ጸድቃን በገዳማት ሰማእታት በምስክርነት ጸንተው እንዲኖሩ ኀይል ብርታት የሚሰጥ መንፈስ ቅዱስ ነው ለማለት ነው (ዮሐ ፲፮፥፲፫ ፤ ዮሐ ፳፩፥፲፰)። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያት ከዕርገቱ በፊት እንዲህ ሲል ተስፋውን
ነግሯቸው ነበር፦ ❝እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ይመራችኋል የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይናገርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል፤ እርሱ ያከብረኛል፤ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና❞ — በማለት ሐዋርያት ለእውነትና በእውነት መኖር እንዲችሉ በሥራቸው ሁሉ መንፈስ ቅዱስ እንደማይለያቸው ነግሯቸዋል (ዮሐ ፲፮፥፲፫)። መንፈስ ቅዱስ ኀጢአተኞችን ወደ ንስሐ ይመራል (መዝ ፲፬፥፰)። በክርክር ጊዜም እውነቱን ይገልጣል (ማቴ ፲፥፳ ፤ ዮሐ ፲፬፥፮ ፤ ፩ኛ ቆሮ ፲፪፥፫)። ፬. ስለ እግዚአብሔር ወልድ ለመመስከር ዓለም እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስን ስላላወቀው ስለ ወልደ እግዚአብሔር በሐዋርያት አድሮ ለመመስከር ተገለጠ:: ስለዚህ አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስ ምሥጢሩን ካልገለጠለት በቀር ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌትነት ማወቅና መመስከር አይችልም (ዮሐ ፲፭፥፳፮)። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ስለጌታችን ስለኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ ልጅነት፥ ጌትነትና ከሃሊነት መመስከር የሚቻለው በመንፈስ ቅዱስ ኀይል
እንደሆነ ሲናገር፦ ❝ስለዚህ ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ ሲናገር ኢየሱስ የተረገመ ነው የሚል እንደሌለ፤ በመንፈስ ቅዱስ ካልኾነ በቀር ኢየሱስ ጌታ ነው ሊል አንድ እንኳን እንዳይችል አስታውቃችኋለሁ❞ — በማለት ያለመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት የክርስቶስን ጌትነት መመስከር እንደማይቻል ተናግሯል (፩ኛ ቆሮ ፲፪፥፫)።
178
Repost from ሀገረ ማርያም መሰረተ ተዋሕዶ ሰ/ት/ቤት
ሰላም ተወዳጆች ይህ ትንሽዬ pdf በጣም ደስ የሚል ጽሑፍ አለው እናታችን ሰንበት ትምህርት ቤት ለእኛ ብዙ ነገርን አድርጋልናለች አኛ ግን ምን አደረግንላት? ሰዎች እንድቀልዱባት እና እንድያፈዙባት አደረግን እንጅ የእናታችን የሰንበት ትምህርት ቤታችን ትንሳኤዋን ሁላችንም እየተጠባበቅን መሆኑን አውቃለሁ ግን አውቀን መሆን አለበት አላማውን ተልዕኮዋን ድርሻዋን .... መሰረተ ተዋሕዶ ቤታችን የብዙዎቻችን ብዙ ወዳጅ ዘመድ ያፈራንበት ቤታችን አፍ የፈታንበት ቋንቋችን ናት። ሰለ ሆነም ይህንን pdf ሁላችንም በማንበብ በፍታችን ባለው በሰንበት ትምህርት ቤቶች ቀን እየፈረሰና አንደ ግመል ሽንት ወደኋላ እየሄደ ያለውን ቤታችንን አንደ ቅዱሱ አባታችን እንደ ሀብቢ ጊዮርጊስ እንድንታደግና ሰለቤታችን ጉዳይ ግድ እንድለን የሚያደረግ ስለሆነ ሁላችንም በማንበብ የራሳችንን ድርሻ እንድንወጣ እና ያንቀላፋነውን የሚታነቃ ስልጠና ስለሆነች አንብቡት ሰላም እደሩ መልካም በዓል
178
Repost from ደብረ ዘይት ሚዲያ
Yaa'ii Afuuraa guddaa Ayyaana haadha keenya Qulqulleettii Dubree Maariyaam sababeeffachuun Caamsaa 20/2018_23 ni gaggeeffamaa. Nama guyyaa sanaa nu haa taasisu.
የእግዚአብሔር ድምፅ ከተማይቱን ይጠራል።
በቡሌሆራ ደ/ገ/ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ታላቅ የወንጌል ጉባኤ ተዘጋጅቷል።
#ታዲያ
እርሶዎም በቦታው ተገኝተው ለነብስዎ እረፍትን
ለሥጋዎ በረከትን ይቀበሉ ዘንድ ተጋብዘዋል።
አይቀርም!!!!!!
178
በቡሌ ሆራ ልዩ ወረዳ ማዕከል በማህበረ ቅዱሳን በቦረና ዞን በተልተሌ ግንኙነት ጣቢያ በኩልቻ ቅዱስ አቡነ ግብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን 41 ነፍሳት የሥላሴ ልጅነት አግኝቷል። ስለ ሁሉም ነገር አምላኬ ቅዱሳን እግዘብሔርን ይመስገን
አምላኬ ቅዱሳን እግዚአብሔር ከውጭ ያሉትን በጎቹን በቸርነቱ ወደ በረቱ ይስብስብልን። አሜን!!!
178
ብርሃናችሁ በሰዎች ፊት ይብራ።5:16
ቃሉን የተናገረው ጌታችን መዳንታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው
ቃሉ የተነገረላቸው ደግሞ በደብረዘይት ተራራ ለተሰበሰቡ ክርስቲያኖችና ሐዋርያት ነው
የትምህረቱ አላማ እኛ አገልጋዮች ራሳችንን መፈተሽ እንድንችል ማድረግና ለክርስቲያኖች መብራት መሆን እንዳለብን ማስረዳት ነው።
ማቴዎስ 5:13-16
13 “እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው የጨውነት ጣዕሙን ቢያጣ ጣዕሙን መልሶ ሊያገኝ ይችላልን? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ጥቅም አይኖረውም።
14 “እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ፤ በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትደበቅ አትችልም፤
15 ሰዎችም መብራት አብርተው ከዕንቅብ ሥር አያስቀምጡትም፤ በቤት ውስጥ ላሉት ሁሉ እንዲያበራ በመቅረዝ ላይ ያስቀምጡታል እንጂ።
16 እንደዚሁም ሰዎች መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማይ ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ በሰዎች ፊት ይብራ።
1 ጨው
ጨው በሰው ሕይወት ውስጥ በጣም አስፈላጊ ንጥረ ነገር ነው። ዋናው ክፍሉ ሶዲየም (Sodium) እና ክሎራይድ (Chloride) ሲሆን በምግብ፣ በጤና እና በኢንዱስትሪ ብዙ ጥቅሞች አሉት።
❤❤❤የጨው ባሕርይ
ነጭ ነው።
በተፈጥሮ ከባሕር ውሃ ወይም ከጨው ክምችት ይገኛል።
❤❤❤የጨው ጥቅሞች
:::ምግብን ለማጣፈጥ
:::ምግብንምግብን ጣፋጭ እና ምቹ ያደርጋል።
:::ምግብንምግብን ለማስቀመጥ
ስጋ፣ ዓሣ እና ሌሎች ምግቦች እንዳይበላሹ ለማድረግ
በአጭሩ ጨው ናቹ ስንባል
1=በመልካም ሥራ ሌሎችን “የሚታጣፈጡ” ናችሁ።
2==ከኃጢአት እና ከክፉ ልምዶች ራስን ንጹሕ ማድረግን ይወክላል።
3=ታማኝነትን፣ ጽናትን እና መንፈሳዊ ጥራትን አላችሁ ።
የአለም ብርሃን ናችሁ
......
የብርሃን አይነቶች በተለምዶ እንዲህ ይከፈላሉ፦
😍1ተፈጥሯዊ ብርሃን ፦– ከተፈጥሮ የሚመጣ
ምሳሌ፦ የፀሐይ ብርሃን፣ ኮከብ ብርሃን፣ መብረቅ
😍2ሰው ሠራሽ ብርሃን፦ – በሰው የተፈጠረ
ምሳሌ፦ ኤሌክትሪክ መብራት፣ ሻማ፣
ብርሃን የተባለው
1ሀይማኖት ነው
ዘፍ22:1
ምሳሌ አባታችን አብርሃም
2 በጎ ምግባር ነው
ያዕቆብ 2:26
ከመንፈስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ፣ ከሥራም የተለየ እምነት የሞተ ነው።
3 ብርሃን የተባለው መንፈሳዊ የቤተክርስቲያን አውቀት ነው።
2 ቆሮንቶስ 4:6
በክርስቶስ ፊት እግዚአብሔር የክብሩን ዕውቀት ብርሃን ይሰጠን ዘንድ፣ “በጨለማ ብርሃን ይብራ” ያለው እግዚአብሔር ብርሃኑን በልባችን አብርቷልና።
ከትምህርቱ ምን እንማራለን
😍 ጨው የሆነውን አለም በበጎ ምግባር መጣፈጥ እንዳለብን
😍ንጽሕናን ከቅድስና ጋር አስተባብረን መያዝ እንዳለብን
😍በአኗኗራችን እና በአካሄዳችን አምላካችን ማሰደብ እንደሌለብን
178
ማንንም አልተቀየመችም
በምድር ላይ እንደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያዘነ፤ ሊያዝንም የሚችል ሰው ሊኖር አይችልም። አንድ ልጇን ይዛ ገና በልጅነቷ ነበር ወደማታውቀው ስደት የገባችው። ከጠላት ለመደበቅ ቀንና ሌሊት ያለ እረፍት ተጉዛለች።
ልጇ በሠላሳ ዓመቱ ወደ አደባባይ ወጥቶ ሲያስተምርም በብዙ መልኩ ሲፈተንና ሲነቀፍ አይታለች።
ምንም በደል ሳይኖርበት በሐሰት ተከስሶ ሲፈረድበት “ልጅሽ በአደባባይ ሊሰቀል ነው ነይ እይ” ተብላ ስትጠራ በጅራፍ ሲገረፍ፣ ራቁቱን አደባባይ ላይ ተሰቅሎ ምንም ልታደርግለት እንደማትችል ምስኪን ከመስቀል ስር ቆማ ደም አልቅሳለች።
እኔን የሚደንቀኝ ይሄ ሁሉ ሆኖባትም እርሷ ግን ማንንም አልተቀየመችም፤ ኧረ ቂሙን ተዉት ማዘኗን እንኳ አልነገረችንም። ዓለም ተሰብስቦ አንዱን ንጹሕ ልጄን ሰቀሉብኝ ብላ አልተናገረችም፤ ጴጥሮስን
'ለምን ልጄን ጥለኽው ሸሸህ?' አላለችውም። ሁሉንም በልቧ ጠበቀችው።
እኛ ልጃችን ተሰቅሎ አይደለም 'ሰው ገላመጠኝ ፤ ክብሬን ነካው' ብለን የምንጣላና የምንኳረፍና የምንጠላላ ግብዞች አሁን እውን እመቤታችንን «እናቴ» የማለት ምግባር አለን? እንደው ትኩር ብለው ቢያዩን ግን ምናችን የድንግል ማርያም ልጅ ይመስላል?
ሰአሊ ለነ ቅድስት!
❝ምንተኑ ንሰምየኪ ኦ ምልዕተ ጸጋ፥ አንቀጸ መድኃኒት አንቲ፤ ኆኅተ ብርሃን አንቲ፤ ወለተ መንግሥት አንቲ፤ ሰማይኑ ንብለኪ? ፀሐየ ጽድቅ ወልድኪ ... ❞— አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ
178
ስለ ጌጠኛ ልብስ - ፬
....አንቺ ሴት እመኚኝ! ባልሽ ምንም ያህል ዕውቀት የሌለው ቢኾን እንኳን እንዲህ እንደነገርኩሽ ብታጌጪ ቅዱስ እንዲኾን ማድረግ ይቻልሻል፡፡ ምንም ያህል ትምክሕተኛ፣ ትዕቢተኛ እንዲሁም አባካኝ ቢኾንም ከዚህ የተለየ እንዲኾን ማድረግ ይቻልሻል፡፡ አንቺ እንደምታስቢው ባልሽን ደስ ለማሰኘት ብለሽ በአፍአ ብዙ ብታጌጪ ግን ከእነዚህ ክፉ ምግባራት የተለየ እንዲኾን ማድረግ አይቻልሽም፡፡
የምናገረው ነገር ለጊዜው ላይገባሽ ይችላል፡፡ እንዲህ እንደነገርኩሽ በማድረጋቸው ባላቸውን ደስ ያሰኙት ግን ያውቁታል፡፡ ልዩ ልዩ ጌጣጌጦችን አድርጋችሁ ራሳችሁን ብታቆነጃጁ ግን ባለቤታችሁ ዘማዊ ከኾነ ከእናንተ ይልቅ በተሻለ ጌጥ ወዳጌጠችው ይኼዳል፡፡ ባልሽ ንጹህ ከኾነ ግን ጌጠኛ ልብስ በመልበስ ደስ አታሰኚውም፤ በበጎ ምግባርሽ ነው እንጂ፡፡ እንደዉም እንዲህ እርሱን ደስ አሰኘዋለሁ ባልሽው ተግባር ይበልጥ እንደምታሳዝኚው በእውነት እነግርሻለሁ፡፡ ከእግዚአብሔር ይልቅ ይህን ዓለም እንደምትወጂ ያስባልና፡፡ ምንም ያህል በጎ ሕሊና ቢኖረዉም መናገር አፍሮ በልቡ ይጠረጥርሻል፡፡ ቅናተኛ እንዲኾን ታደርጊዋለሽ፡፡ እንዲህ በማድረግሽ ከእርሱ ማግኘት የነበረብሽን ደስታ ታጫለሽ፡፡ ይህም ብቻ አይደለም፤ ትፋቻለሽ፡፡
ምናልባት በምናገረው ነገር ተበሳጭታችሁ “ለወንዶች አግዞ ሴቶች እንዳያጌጡ ይቃወማል” ልትሉኝ ትችላላችሁ፡፡ ነገር ግን አይደለም፡፡ ወንድ ስለኾንኩኝ ለወንዶች አድልቼ አይደለም፡፡ እንዲህ አድርጌ የምናገረው እናንተው ራሳችሁ ትዳራችሁን እንዳታፈርሱ ብዬ ነው እንጂ፡፡ ከአላፊና ጠፊ ግብር እንድለያችሁ ብዬ ነው እንጂ፡፡
አምራችሁ አጊጣችሁ መታየትን ትወዳላችሁን? እኔም እግዚአብሔር በሚወደውና ሰማያዊው ንጉሥ በመረጠው መንገድ ታጌጡ ዘንድ እወዳለሁ (መዝ.45፡11)፡፡
ይቀጥላል...
(የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች ቅዱስ ዮሐንስ_አፈወርቅ እንደአስተማረው ገጽ 47-55➛ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
178
Repost from ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
“ማግባት ለሚሹ”
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር
ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡
ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡
አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡
እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡
እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡
እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡
የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
