es
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Ir al canal en Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

Mostrar más
668
Suscriptores
-124 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
"ጾም ነፍስን ያነጻል አእምሮን ያሳድጋል፣ ሥጋን ለነፍስ ያስገዛል፣ የምኞት ደመናን ይበትናል፣ የፍትወት እሳትን ያጠፋል፣ የንጽሕና እውነተኛ ብርሃን ያበራል።" /ቅዱስ አውግስጢን/ የአሰላ ደ/መ/መ/
"ጾም ነፍስን ያነጻል አእምሮን ያሳድጋል፣ ሥጋን ለነፍስ ያስገዛል፣ የምኞት ደመናን ይበትናል፣ የፍትወት እሳትን ያጠፋል፣ የንጽሕና እውነተኛ ብርሃን ያበራል።"  /ቅዱስ አውግስጢን/ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇  👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel

መንፈሳዊ ፆም በዚህ ትምህርታዊ ጹሑፍ ስለ ጾም አራት ነጥቦችን እናያለን። 1ኛ. የጾም ትርጉም 2ኛ. ጾም ያስፈለገበት ምክንያት 3ኛ. የጾም ጥቅሞች 4ኛ. በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን፡፡
+1
መንፈሳዊ ፆም በዚህ ትምህርታዊ ጹሑፍ ስለ ጾም አራት ነጥቦችን እናያለን። 1ኛ. የጾም ትርጉም 2ኛ. ጾም ያስፈለገበት ምክንያት 3ኛ. የጾም ጥቅሞች 4ኛ. በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን፡፡ ከላይ ከ1-4 ተራ ቍጥር የተገለጹትን እንደሚከተለው በዝርዝር እናያለን፡፡   1ኛ. የጾም ትርጉም ጾም:- ማለት ክርስቲያን የሆነ ሰው ሁሉ ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ከእህል ከውኃ ተከልክሎ መቆየት ማለት ሲሆን ከሥጋ፣ከቅቤና፣ከእንቁላል ደግሞ እንድንጾምባቸው የተወሰኑ የአጽዋማት ሳምንታት እስኪጠናቀቁ የምንከለከልበት ማለት ነው፡፡ (ፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 15) ከዚህም ጋር ጾም ማለት:- ዓይን ክፉ ከማየት ጆሮ ክፉ ከመስማት፣ አንደበት ክፉ ከመናገር፣ እጅ ክፉ ከመሥራት በአጠቃላይ ሰውነት የኃጢአት ሥራ ከመሥራት የሚገታበት፣ የሚከለከልበት ማለት ነው። (ቅዱስ ያሬድ) ጾም፡- ሁለት ዓይነት ነው ይኸውም ሀ.የአዋጅ ጾም ነው፡- ይህም በስውር ሳይሆን ሁሉ አውቆት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ይህም መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት አለው፡፡ “በጽዮን መለከትን ንፉ ጾምንም ቀድሱ ጉባኤውንም አውጁ” /ኢዩ 2፡15/ ሰባቱ አጽዋማት የአዋጅ ጾሞች ናቸው፡፡ እነዚህም እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል   ፩. የነቢያት ጾም ፪. የገሀድ ጾም ፫. የነነዌ ጾም ፬. ዐቢይ ጾም ፭. የሐዋርያት ጾም ፮. ጾመ ድኅነት (ረቡዕና ዓርብ) ፯. ጾመ ፍልሰታ 👇👇👇  👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel

እኔ ነኝ የእርሱን ፍቅር እገልፅበት ዘንድ በለስን ቢፈጥርልኝ ከእርሱ ለመለየት ወስኜ የበላሁት እኔ ነኝ። አጋዤ እረዳቴ ይሆን ዘንድ በጨነቀኝ ጊዜ ያማክረኝ ዘንድ አቤልን ቢፈጥርልኝ በዝሙት መንፈስ ተነስቼ ያልተፈቀደችልኝን ሉድን ተመኝቼ የአባቴን ትዕዛዝ ትቼ ወንድሜ አቤልን የገደልሁት ነፍሰ ገዳይ እኔ ነኝ። እግዚአብሔር አክብሮ በአምሳሉ ቢፈጥረኝ እንስሳዊ በሆነ ፀያፍ ዝሙት እራሴን ዘሬን አርክሼ እግዚአብሔርን እስኪፀፀት አሳዝኜው በንፍር ውሀ አለም እስኪጠፋ የሚያደርስ ሀጥያት የሰራሁት ሰበዓ ትካት እኔ ነኝ። እግዚአብሔር እረዳት ትሆነኝ ዘንድ ዘር እንድተካልኝ ከዝሙት ትጠብቀኝ ዘንድ ሔዋንን ቢፈጥርልኝ በትዕቢት ተወጥሬ የተሰጠኝን ትቼ ያልተሰጠኝን ሽቼ ከወንድሜ ጋር ተጋብቼ ርኩሰትን ፈፅሜ ሀገሬን በእሳት እንድትጠፋ ያደረግሁኝ የሰዶምና ገሞራው ሰው እኔ ነኝ። አባቴ ቢወደኝ እንዳይርበኝ ብሎ ለወንድሜ ምግብ ቢልክልኝ ህብስትና ማይ ይዞ የመጣውን ወንድሜን ለግብፅ ነጋዴዎች የሸጥሁት የያዕቆብ የበኩር ልጅ እኔ ነኝ። ከስደት ሊያወጣኝ ከባርነት ነፃ ሊያደርገኝ ነብዩ ሙሴንና ወንድሙ አሮንን ልኮ ቢያወጣኝ ለእኔ መውጣት ታላላቅ ታምራት አድርጎ ደግብፃዊያንን በኩር ገድሎ የኤርትራ ባህርን አሻግሮ ጠላቶቼን አስጥሞ በበረሀው እንዳልራብ እንዳልጠማ ከሰማይ ህብስት እያወረደ ቢመግበኝ ከአለት ውሀ አፍልቆ እያጠጣ ቢያኖረኝ በታማኙ መልዓክ መንገዴን ቢመራኝ አሻፈረኝ ብዬ የፈርኦን ፍርፋሪ የግብፃዊያን ሽንኩርት የናፈኩኝ ለመሪዬ ለሙሴም ለእግዚአብሔርም ያልተመቸሁ ጠባቂ መልአኬን ያሳዘንኩኝ ከነአንም ያላየሁኝ እስራኤላዊ የነፍስ ስደተኛ እኔ ነኝ። የሰው እጅ ሥራ በሆኑት ላይ አይን እያላቸው በማያዩት ጆሮ እያላቸው በማይሰሙት የአህዛብ ጣኦት ተማርኬ የኔ አምላክ መቼ ይሆን የሚታየው ሚዳሰሰው ብዬ አምላኬ ላይ ባጉረመርም እኔን አይቶኝ መኖር የሚችል ማንም የለም ነገር ግን የክብሬ መገለጫ ከእናንተ ጋር  አፍ ለአፍ የማወራበት እኔን የምታገኙበት መገለጫ ልስጥህ ብሎ ጥያቄዬን ተቀብሎ ታቦተ ጺዮንን ቢሰጠኝም ለእርሱ ክብር የመጣውን መሰዋዕቱን አስራትና በኩራቱን የወርና የአመቱን ለግል ጥቅም በማዋሌ ይባስ ብሎ በመቅደሱ ነውር ነገር በመስራቴ ታቦተ ጺዮንን ያስማረኩኝ ሀገሬንም ያዋረድሁኝ የዘመኑ አፍኒን ፊንሐስም እኔው ሆንሁኝ።       እኔው ነኝ የሰባቱ ዋና ዋና ሀጥያቶቼ ጽዋ መሙላት ተመልክቶ አስቀድሞ የገባውን ቃል አስቦ ፍጠረኝ ሳይል የፈጠርሁትን ማረኝ ቢለኝ አልምረውም? ብሎ አምላኬ ከሰማያት ቢወርድልኝ የኔን ስጋ ተዋህዶ ላድንህ ቢለኝ እርሱ ፈቅዶ እርሱ ወዶ ከእመቤቴ ስጋ ለብሶ ተዋህዶ እንቢ አልሁኝ አሻፈረኝ ሊያድነኝ ወደዚህች ምድር ቢመጣ ህይወቴንም የገረፍሁት እራቆቱን የሰቀልሁት ተፍቼበት ያዋረድሁት ራሴንም የገደልሁት ቢያለብሰኝ ያራቆትሁት እኔው ነኝ አይሁዳዊ የእስራኤል ሰው። እናት አባቴ በጣሉኝና ዘመድ ወዳጅ በራቀኝ ጊዜ ተስፋ አጥቼ ስንሰቀሰቅ ጎብኚ አጥቼ ስብከነከን ሰላሳ ስምንት አመት ከወደቅሁበት በቃሉ ብቻ ፈቃዴ ጠይቆ ቢያድነኝ ቢያነሳኝ ከሰው እኩል ቢያደርገኝ ቢፈውሰኝ አልጋዬ ይዤ ብመላለስ  ያዳነኝን የራሳሁኝ ባዳነኝ ላይ የተፋሁት ጌታዬንም  የሰደብሁት እኔው ነኝ በሽተኛው ያ መጻጉዕ። ኧረ ይገርማል ያስደንቃል በስጋ ስራ ተጠምጄ የአይሁድ ህግ በሻርሁ ጊዜ በሙሴ ህግ ሊያስወግሩኝ የማይስማሙት ተስማምተውብኝ እኔን ሊገድሉ ሊያስፈርዱብኝ ወደ ጌታ የወሰዱኝ በጥበቡ በካሀሊነቱ ከመወገር ያዳነኝ የአላዛር እህት ማርያም እንተ ዕፍረት ያው እኔ ነኝ። በቸርነቱ ጠብቆ ሳይገባኝ ይገባሀል ብሎ የጨለመውን እንዳበራ የመረረውን እንዳጣፍጥ የወደቀው እንዳነሳ የታመመው እንድፈውስ ለምፃሙንም እንዳነፃ የጎደለው እንድሞላ አምላኬ ቢመርጠኝም ቢሾመኝም መክሊቴንም የቀበርሁት ታምኜ ሌባ የሆንሁኝ ተሾመኝን ያዋረድሁኝ የሰጠኝን ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝን በ30 ብር የሸጥሁት አገልጋዩ ያ ይሁዳ እኔ ነኝ። የታሰረው እንድፈታ ያላመነው እንዳሳምን  የራቀውን እንዳመጣ ጳውሎስ ሹሞ ቢልከኝም በጨዋታ በዳንኪራው በዘፈኑ ተታልዬ ተሰሎንቄን ያረከስሗት የጳውሎስም ደቀመዝሙር ታናሽ ዴማስ ያው እኔ ነኝ:: ሁሉ ነገር ያው እኔ ነኝ ቤተመቅደስ አስቀዳሹ ጠንቋይ ቤትም የምቀልብ ያው እኔ ነኝ በአውደምህረት የምዘምር በናይት ክለብ የምዘፍን ያው እኔ ነኝ። አሸብሻቢው ጨፋሪውም ያው እኔ ነኝ ኧረ ተዉት ምን ይባላል የራሴን ሀጥያት መመልከት ያቃተኝ በሰዎች ላይ ጣት ቀሳሪ ያው እኔ ነኝ፡፡ ሀጥያትን እንጂ ሀጥያተኛን የማይጠላ ጌታ ይቅር ይበለን። ዲ/ን አበበ ይልማ ዘደብረ መድኃኒት ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇  👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel

✨አንተ በእግዚአብሔር እጅ ያለህና በመዳፉ ላይ የተቀረጽህ ነህ። [ ኢሳ 49፣16 ] እርሱ ከክንፎቹም በታች ተማምነህ እንድትጠለል አድርጎሃል [መዝ 90 ] እርሱ በቀንና በሌሊት ከአንተ ጋር ነው መ
✨አንተ በእግዚአብሔር እጅ ያለህና በመዳፉ ላይ የተቀረጽህ ነህ። [ ኢሳ 49፣16 ] እርሱ ከክንፎቹም በታች ተማምነህ እንድትጠለል አድርጎሃል [መዝ 90 ] እርሱ በቀንና በሌሊት ከአንተ ጋር ነው መውጣትና መግባትህንም ይጠብቃል። [ መዝ 120 ] እርሱ ስለሚወድህም ልጄ ብሎ ጠርቶሃል. [1ኛ ዮሐ 3፥1 ]  እርሱ እረኛህ ስለሆነም ምንም የሚያሳጣህ ነገር የለም ። [ መዝ 22፥1]  እኛ ሁላችን የእግዚአብሔር  ስለሆንን የጋጣው በጎች ነን እርሱም መልካም እረኛ ስለሆነ በጎቹን አይዘነጋም እንደ አባትነቱም ልጆቹን አይረሳም ።        ለመንጋው ሁሉ በጎ እንደሚመኝ እንደ መልካም እረኛ እግዚአብሔርም በፍጥረታቱ በሙሉ ያለምንም ጥርጥር በዝምታ ይሠራል። ይሁን እንጂ ሰዎች በመከራ ውስጥ ሆነው የእግዚአብሔር መልስ ከዘገየባቸው እንደማይሰራ አድርገው ያስባሉ። እነርሱ እግዚአብሔር አይሰራም ብለው በሚያስቡበት ሰዓት ሁሉ እርሱ ግን ለእነርሱ በጥልቅ እየሰራ ነው። ሰዎች ይህንን ስለማይገነዘቡ የእግዚአብሔርን ሥራና የስራውን ውጤት ፈጥነው ለማየት ይፈልጋሉ። እነዚህ ሰዎች ግን በእምነታቸው ያመኑትን በዓይነቻቸው እስኪመለከቱ ድረስ ሊቆዩ ይገባቸዋል። " እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ በርታ ልብህም ይጽና እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፡፡"  መዝ 26 ፥ 14።   አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ 📌የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇  👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel

📌 ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይህንን ድንቅ ዝማሬ ይመልከቱ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://youtu.be/V-aWM_bsf7g?si=BUcqYGy
📌 ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይህንን ድንቅ ዝማሬ ይመልከቱ። 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://youtu.be/V-aWM_bsf7g?si=BUcqYGyQf575CBnS https://youtu.be/V-aWM_bsf7g?si=BUcqYGyQf575CBnS

"በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን። በቀስቴ የምታመን አይደለሁምና፥ ሰይፌም አያድነኝምና፤ አንተ ግን ከጠላቶቻችን አዳንኸን፥ የሚጠሉንንም አሳፈርሃቸው።
"በአንተ ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፥ በስምህም በላያችን የቆሙትን እናዋርዳቸዋለን። በቀስቴ የምታመን አይደለሁምና፥ ሰይፌም አያድነኝምና፤ አንተ ግን ከጠላቶቻችን አዳንኸን፥ የሚጠሉንንም አሳፈርሃቸው።" መዝ 43(44)፡5 እንኳን ለአድዋ የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇  👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel

የብርሃን እናቱ ሆይ ካንቺ በነሳው ስጋ እኛነታችንን አከበረ፡፡መዐዛሽ ስቦት አንችን በወደደ ጊዜ ድኅነታችን ተሰራ፡፡ ድንግል ሆይ እውነተኛው የሕይወት እንጀራ : ጣፋጩን የነፍስ መጠጥ አማናዊው የፅድ
የብርሃን እናቱ ሆይ ካንቺ በነሳው ስጋ እኛነታችንን አከበረ፡፡መዐዛሽ ስቦት አንችን በወደደ ጊዜ ድኅነታችን ተሰራ፡፡ ድንግል ሆይ እውነተኛው የሕይወት እንጀራ : ጣፋጩን የነፍስ መጠጥ  አማናዊው የፅድቅ ብርሀን የፈነጠቀብሽ ነሽና ከትውልድ መሀል ብፅዕናሽን እንናገራለን፡፡ ጥማችንን የቆረጠ ጥዑም ወይን፡ረሀባችንን ያጠፋ እውነተኛው መብል ካንቺ ወጥቶልናልና እንወድሻለን፡፡ ምስራቃዊት በራችን ሆይ ከሴቶች አንችን የሚመስል የለም፡፡ባንቺ ላይ ስለተደረገልን ታላቅ ነገር ዛሬም ለዘላለምም ስምሽን እናገናለን፡፡ ዝምተኛይቱ ድንግል ሆይ አንቺ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የአይሁድ ሴቶች አይደለሽም።በትሕትና ተልመሽ በንፅሕና አጊጠሽ የባህርያችንን መመኪያ ያስገኘሽልን የፅድቅ በራችን ነሽ። አንችን ማመስገን የነፍስ ምግብ የህሊና እርካታ ነው።ስናመሰግንሽ እናርፋለን ስናርፍ እናመሰግንሻለን።ክብርሽ ከሰማይ ምስጋናሽም ከአርያም ነውና አንችን ለማመስገን ልቦናችን ይብራ። ኦ ማርያም በእንተዝ ናፈቅረኪ ወናዐብየኪ እስመ ወለድኪ ለነ መብልዐ ፅድቅ ዘበአማን ወስቴ ሕይወት ዘበአማን ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇  👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel

ኦርቶዶክሳዊ ፕሮፋይል ፒክቸሮች የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌ
+4
ኦርቶዶክሳዊ ፕሮፋይል ፒክቸሮች የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇  👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel

የነነዌ ሰዎችና እኛ ከነነዌ ሰዎች በላይ ማን ክፉ ነበር? ከእነርሱ በላይ አላዋቂስ ማን ነበር? ("ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ" ተብለው ተጠርተዋልና፡፡) ነገር ግን እነዚህ አሕዛብ፣ እነዚህ አላዋቂ፣ እነዚህ አንድ ሰውስ እንኳን የጥበብን ነገር አስተምሮአቸው የማያውቁ፣ እነዚህ ከማንም ይኹን ከማን እንደዚህ ዓይነት ትእዛዝን ያልተቀበሉ ሰዎች ነቢዩ፡- “በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች” ሲል በሰሙት ጊዜ ክፉ ልማዳቸውን ኹሉ በሦስት ቀናት ውስጥ አስወግደዋል (ዮና.3፥4)፡፡ ዘማዊው ንጹህ፣ ደፋሩ ትሑት፣ ስስታሙና ጨቋኙ ራሱን የሚገዛና ደገኛ፣ ሐኬተኛውም ትጉህ ኾነ፡፡ እነዚህ ሰዎች በርግጥ ያሻሻሉት ክፋታቸውን ኹሉ እንጂ አንዱን ወይም ኹለቱን ወይም ሦስቱን ወይም አራቱን አይደለም፡፡ “እንዲህ የሚልስ የት አለ?” ብሎ የሚጠይቅ ሰው ሊኖር ይችላል፡፡ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስለታለሁ፡- እነርሱን ሲወቅሳቸው የነበረውና፣ “የክፋታቸውም ጩኸት እስከ አርያም ድረስ ወጥቷል” ብሎ የተናገረው ነቢይ መልሶ ደግሞ የዚሁ ፍጹም ተቃራኒ የኾነን ምስክርነት አስቀምጧልና፤ እንዲህ ሲል፡- “እግዚአብሔርም ከክፉ መንገዳቸው እንደ ተመለሱ ሥራቸውን አየ” (ዮና.1፡5፣ 3፡10)፡፡ ተመልከት! ከዝሙት ወይም ከአመንዝራነት ወይም ከሌብነት ራቁ አላለም፤ “ከክፉ መንገዳቸው” እንጂ፡፡ እንዴትስ ከዚያ ሊርቁ ቻሉ? ይህን እግዚአብሔር ያውቋል እንጂ ሰው ሊመረምረው አይችልም፡፡ እንግዲህ አሕዛብ በሦስት ቀናት ውስጥ ብቻ ክፋታቸውን ኹሉ ማስወገድ ከቻሉ፥ ለአያሌ ቀናት የተመከርንና የተዘከርን እኛ ግን አንዲት ክፉ ልማድን [ለምሳሌ መሐላን] ሳናስወግድ ስንቀር ልናፍር አይገባንምን? ከዚህም በላይ እነዚህ ሰዎች ቀድሞ ክፋታቸው ጣሪያ ደርሶ ነበር፤ “የክፋታቸውም ጩኸት እስከ አርያም ድረስ ወጥቷል” የሚለውን ስትሰማ ከክፋታቸው ብዛት በቀር ሌላ ምንም ልትገነዘብ አትችልምና፡፡ ነገር ግን በሦስት ቀናት ውስጥ ወደ መልካም ምግባር ፍጽምና መድረስ ተችሏቸዋል፡፡ ፈሪሐ እግዚአብሔር ባለበት ቀናት ወይም የጊዜ ብዛት አያስፈልግምና፡፡ በተቃራኒው ይህ ፍርሐት በሌለበት ደግሞ የጊዜ ብዛት ምንም ጥቅም የለውም፡፡ የዛጉ ብረቶችን በውኃ ብቻ የሚያጥባቸው ሰው ምንም ያህል ጊዜ እነርሱን በማጠብ ቢያሳልፍም እነዚያን ዝገቶች ኹሉ ማስለቀቅ አይቻለውም፡፡ ወደ እሳት ጨምሮ የሚያወጣቸው ሰው ግን አዲስ ከተሠሩ ብረቶችም ጭምር ሳይቀር እጅግ ጽሩያን ያደርጋቸዋል፡፡ በኃጢአት የዛገ ልብም እንዲሁ በትንሽ በትንሹና በግድየለሽነት ኾኖ ዕለት ዕለት ንስሐ ቢገባም ምንም ጥቅም አያገኝም፡፡ ራሱን ወደ እቶን - ይኸውም ወደ ፈሪሐ እግዚአብሔር የሚጥል ከኾነ ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ኹሉንም ማስወገድ ይቻለዋል፡፡ ዛሬ ላይ ነገን ለማነጽ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ልንገነባ ነው። #ሚዲያችንን_ይደግፉ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇  👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel

ቃና ዘገሊላ - ድንቅ የሰርግ መዝሙር | New Ethiopian Orthodox Wedding Mezmur | Kana ... https://youtube.com/watch?v=V-aWM_bsf7g&si=4Jxn8Y3wOICcuWN3

የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰሞኑን በማኅበራዊ ድረ ገጾች ራሱን "መነኩሴ"በማስመሰልና በአርሲ ሀገረ ስብከት አገልጋይ እንደሆነ በመግለጽ የሚንቀሳቀሰውን ግለሰብ የማያውቀውና ሐሰተኛ "መነኩሴ" መሆኑን ለጠ
+1
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰሞኑን በማኅበራዊ ድረ ገጾች ራሱን "መነኩሴ"በማስመሰልና በአርሲ ሀገረ ስብከት አገልጋይ እንደሆነ በመግለጽ የሚንቀሳቀሰውን ግለሰብ የማያውቀውና ሐሰተኛ "መነኩሴ" መሆኑን ለጠቅላይ ቤተክህነት በጻፈው ደብዳቤ አስታወቀ። ከየካቲት 12 ቀን 20916 ዓ.ም ጀምሮ በማኀበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ የሚገኘው ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ተችቶ የማስተቸት ድራማዊ ትዕይንት ላይ የቀረበው አስመሳይ " መነኩሴ "ግለሰብ በሀገረ ስብከታችን በተለይ በአሰላ ከተማ በቅዳሴ መምህርነት በስብከተ ወንጌል እንዳገለ በማስመሰል በሰጠው የሀሰት ምስክርነትን በተመለከተ እውነተኛ ምላሽ መስጠት ማስፈለጉን የጠቀሰው ሀገረ ስብከቱ"መንኩሴ "መሳዩ ግለሱብ  በሀገረ ስብከቱ በየተኛውም የከተማና የገጠር ገዳማትና አድባራት የማይታወቅና ምንም ዓይነት አገልግሎት ሲሰጥ ያልነበረ መሆኑን ገልጿል። በተጨማሪ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙት ሁሉንም አገልጋዮች የሚታወቁና የተመዘገቡ መሆኑን የጠቀሰው ሀገረ ስብከቱ ግለሰቡ በሀገረ ስብከቱ  ካሉት አገልጋች መካከል የማይታወቅና ያልተመዘገበ ከመሆኑም በላይ ሀገረ ስብከቱ በፍጹም የማያውቀው ቀሳጢ ነው በማለት ሐሰተኛ ማንነትን በመላበስ የቤተክርስቲያንን ስም ለማጠልሸተ የተሰማራ መሆኑን ገልጿል። ስለሆነም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ግለሰቡ የቤተ ክርስቲያናችንን ዓርማ ወይም አልባሳት በመልበስና የሀገረ ስብከታችንን መልካም ገጽታ በማጉደፉ ግለሰቡንና እዩ ጩፋ የተባለውን አጽራረ ቤተ ክርስቲያን በህግ እንዲጠይቅን ስንል በታላቅ አክብሮት እናሳስባለን፤በማለት ለጠቅላይ ጽሕፈት ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ ጨምሮ ገልጿል።

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት። ጥንታዊት፣ ታሪካዊት፣ ብሔራዊትና ዓለም አቀፋዊት በሆነችው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥር ከሚገኙት ጥንታዊያ
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት። ጥንታዊት፣ ታሪካዊት፣ ብሔራዊትና ዓለም አቀፋዊት በሆነችው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥር ከሚገኙት ጥንታዊያን ገዳማት መካከል ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አንዱና ዋነኛው መሆኑ ይታወቃል። ይህ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም በርካታ ቅርሶችና መናንያን የሚገኙበት ገዳም ሲሆን በተለያዩ ጊዜያት በተከሰተበት ዘረፋና ቃጠሎ ከባድ ጉዳቶችን ያስተናገደ መሆኑም ይታወሳል። በዛሬው ዕለት ከሀገረ ስብከቱ በደረሰን መረጃ መሰረትም፦ 1. የገዳሙ መጋቢ አባተክለማርያም ዐሥራት 2. የገዳሙ ጸሐፊ አባ ኪዳነ ማርያም ጥላሁን 3. የገዳሙ የመጽሐፍ መምህርና ቀዳሽ አባ ገ/ማርያም አበበ 4. በአመክሮ የሚኖሩ መናኝ ኃይለማርያም ወልደሰንበት የካቲት 12 ቀን "ኦነግ ሸኔ" በተባለው ታጣቂ ቡድን ከተወሰዱ በኋላ አራቱም በትላንትናው አለት የተገደሉ ሲሆን አባ ኪዳነማርያም ገ/ሰንበት የተባሉት አባት ቆስለው በገዳሙ እንደሚገኙ ታውቋል። በአሁኑ ሰዓትም ታጣቂዎቹ ወደ ገዳሙ ለመግባት እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት መንገድ እንዳይኖርና መናንያኑና የገዳሙ ቅርስ አደጋ ላይ እንዳይወድቁ የፌዴራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት ገዳማዊያኑንና ገዳሙን የመታደግ ሥራ እንዲሠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከአደራ ጭምር መልዕክቷን ታስተላልፋለች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የካቲት ፲፬ቀኝ ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም አዲስ አበባ -ኢትዮጵያ

ቃና ዘገሊላ - ድንቅ የሰርግ መዝሙር | New Ethiopian Orthodox Wedding Mezmur | Kana ... https://youtube.com/watch?v=V-aWM_bsf7g&si=4Jxn8Y3wOICcuWN3