es
Feedback
Ethio-Universities Salafi Community(EUSaCo)

Ethio-Universities Salafi Community(EUSaCo)

Ir al canal en Telegram

የዚህ Community ዓላማ በመላው ሀገሪቱ የሚገኝ ሰለፊይ የዩንቨርስቲ፣ኮሌጅ እና ሌሎች የትምህርት ተቋማት ኮሚኒቲን በአንድ አስተሳስሮ ትክክለኛውን እስላማዊ አስተምህሮ ለዑማው ማድረስ ነው። ኑ ሀቅን ከባለቤቶቹ እንማር! ገንቢ አስተያየትና ጥቆማዎትን @EUSaCofeedbackBot ያድርሱን። #ኢዩሰኮ #EUSaCo

Mostrar más
3 385
Suscriptores
-124 horas
-47 días
+1230 días
Archivo de publicaciones
እንዲሁ በጣም የሚያስገርመው ፡  አንዳንድ ሴቶች እና ወንዶች ከአጅነብይ (ከባእድ) ጋር በማውራት የሚስተዋለው ቸልተኛነት ነው፡፡ አስገዳጅ ነገር ሳይገጥም አጅነብይ የሆነችውን ሴት ያወራታል ፣  ያሳስቃታል እርሷም ታሳስቀዋለች በንግግሯ ይደሰታል፡፡ አንዳንድ ሴቶችም አስገዳጅ ነገር  ሳይገጥም አጅነብይ ከሆነ ወንድ ጋር ያወራሉ፡፡ በለሰለሰ ቃላት ፣  ደስ የሚል ቃል ወደርሱ ትወረውራለች፡፡  በልቡ በሽታ ያለበት ሰው ይከጅላል፡፡ በተለይም በማህበራዊ ድረ ገጽ፡፡  በትክክለኛ ሐዲስ የአላህ መልክተኛ - ዓለይሂሶለቱ ወሰላም - እንዲህ ብለዋል :- إن المرأة عورة ، فإذا خرجت استشرفها الشيطان “ሴት አውረት (አካሏ ሁሉ መታየት የማይገባት) ነች ፣ (በአደባባይ) ከወጣች ሸይጧን ይቀርባታል” ሙስሊም በሶሂህ ሐዲስ  የሚከተለውን ዘግቧል ፡ إن المرأة تقبل في صورة شيطان ، وتدبر في صورة شيطان “ሴት ስትመጣ በሸይጧን ምስል ትመጣለች፡፡ ስትሄድም በሸይጧን ምስል ትሄዳለች፡፡” ሁሉም ሙስሊም አላህን ሊፈራ ግዴታ አለበት፡፡ ባለትዳሮች ሚስጢራቸውን በአደባባይ ማሰራጨት ሳይሆን ችግራቸውን ከቤተሰብ ጋር ሆነው በትእግስት እና በጥበብ ተወያይተው መፍታት አለባቸው፡፡  ሙስሊም ወንድሜ ሆይ!   በአንተ እና በሚስትህ መካከል አለመግባባት ከተከሰተ ከማንም ጋር ግንኙነት አታድርግ ቤተሰቦችህ እንዲገኙ በማድረግ  በጥበብ ፣  በትግስት ፣  በዱዓ መፍታት ትችላለህ፡፡ ለአንተ ቅርብ እና አዛኞች የአንተ እና የሚስትህ ቤተሰቦች በመሆናቸው በመካከላችሁ ተገኝተ  ጉዳያችሁን እንዲፈቱ  አድርግ፡፡ ይህ ካልተሳካ ወደሸሪዓ ዳኞች ጉዳዩን አቅርብ፡፡  ይህ ነው አላህ የሚወድልህ ፣ የሚስትህን ሚስጢር አትበትን ፣ በቁርዓን እና በሐዲስ ጉዳይህን ፍታ - በዱንያና በአኼራ ስኬታማ  ትሆናለህና፡፡ ሙስሊም እህቴ ሆይ!  ከባልሽ ጋር አለመግባባት ከተከሰተ  አላህን ፍሪ ፣ ታገሽ  ፣ ባልሽን በመልካም ታዘዥ፡፡  አላህ ከፍ ያደርግሻል፡፡  ከአንች ዘንድ ያለውን ይወድልሻል፡፡ የሂዎትሽ ሁኔታ ካልተስተካከለ ቤተሰቦችሽን አማክሪ እንጅ ከዚያም ከዚህም ጋር አትገናኝ - ከአላህ ቁጣ ላይ ትወድቂያለሽና፡፡ በባልና በሚስት ጉዳይ ፈትዋ የሚሰጡ ሰዎች አላህን ይፍሩ፡፡ በሁለቱ መካከል በተፈጠረው ጉዳይ የተሰጣቸውን የሸሪዓ ድንበር ሊያውቁ ይገባል፡፡ ፈትዋ የሚሰጡ ሰዎች በባልና ሚስት እርቅ ጉዳይ ከቤተሰቦች የበለጡ አይደሉም፡፡ አላህ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡ ባለትዳሮችን ባልና ሚስትን በማስማማት አላህ በቁርዓኑ ያወሳው ቤተሰብን ነው፡፡  ባለትዳሮችን መምከር ፣  ሸሪዓዊ ህጉን ግልጽ ማድረግ የሚከለክል ነገር የለውም፡፡  በፍች ጉዳይ ግን የአንዱን ወገን ብቻ መስማትና ጣልቃ መግባት ተገቢ አይደለም፡፡  የሰዎችን ቤት ሚስጢራቸውንም መከታትልና መፈተሽ አይፈቀድም፡፡ ይህ የቆሻሻ ልቦች በሽታ ነው፡፡ ሙስሊሞች ከእንዲህ አይነቱ መጽዳት ግዴታ አለባቸው፡፡  ነብዩ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - እንዲህ ብለዋል:- يا معشر من آمن بلسانه ولم يدخل الإيمان قلبه ، لا تغتابون المسلمين ، ولا تتبعوا عوراتهم ، فإنه من تتبع عورة أخيه المسلم ، تتبع الله عورته ، ومن تتبع الله عورته ، يفضحه ولو في جوف بيته  “በምላሳችሁ ያመናችሁ ፣ እምነት በልባችሁ ያልገባ ሰዎች ሆይ! ሙስሊሞችን አትሙ ፣ ነውራቸውንም አትከታተሉ ፣ የሙስሊም ወንድሙን ነውር የሚከታተል የእርሱን ነውር አላህ ይከታተለዋል፡፡ የእርሱን ነውር አላህ የተከታተለው በቤቱ ውስጥ እንኳ ቢሆን ያጋልጠዋል፡፡” ሸይኽ ብን ኡሰይሚን - ረሂመሁሏህ - የሚከተለውን ጥያቄ ተጠየቁ ፡ “የቤቶቻቸውን  ጉዳይ ፣ ስለትዳራቸው ሒዎት ፣ ከባሎቻቸው ጋር ያለውን ጉዳይ ለቅርብ ዘመዶቻቸው ፣  ለጓደኞቻቸው ማውራትና ማሰራጨት በአንዳንድ ሴቶች ላይ ይበዛል፡፡  ከእነዚህ ወሬዎች ከፊሉ የቤት ሚስጢር ናቸው፡፡  ባል እንዲወራ አይፈልግም፡፡ ባል ይህን የቤት ሚስጢር  አንድም ሰው እንዲያውቅ አይፈልግም፡፡ ሚስጢርን ከቤት ውጭ  በማሰራጨት ወይም ለአንዳንድ የቤት ሰዎች በማውራት ላይ የተሰማሩ  ሴቶች ፍርድ ምንድን ነው? መልስ ፡  የቤትን ወሬ ፣ የትዳር ሂዎታቸውን ለቅርብ ዘመድ ፣ ለጓደኛ የሚያወሩ አንዳንድ ሴቶች ይህ ተግባራቸው ሐራም ነው፡፡ ማንኛዋም ሴት  የቤቷን ሚስጢር ወይም ከባሏ ጋር ያለውን ሁኔታ ለአንድም አካል ማውራት ወይም ማሰራጨት አይገባትም፡፡  አላህ የሚከተለውን ተናግሯል ፡ - فَالصَّالِحَاتُ قَانِتَاتٌ حَافِظَاتٌ لِّلْغَيْبِ بِمَا حَفِظَ اللَّهُ ۚ                    “መልካሞቹ ሴቶች (ለባሎቻቸው) ታዛዦች ፣ አላህ ባስጠበቀው (እንዲጠበቅ ባዘዘው) ነገር ሩቅን (ባሎቻቸው በሌሉበት አፍረተ ገላቸውን ፣ ንብረታቸውን ...) ጠባቂዎች  ናቸው፡፡”  (ኒሳእ : 35) ነብዩ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - የሚከተለውን ተናግረዋል :- شر الناس منزلة عند الله يوم القيامة الرجل يفضي إلى المرآة وتفضي إليه ثم ينشر سرها" “የትንሳኤ ቀን ከአላህ ዘንድ መጥፎ ሰው ብሎ ማለት ባል ለሚስቱ ሚስጢር ይነግራታል ፣ ሚስት ለባሏ ሚስጢር ትነግረዋለች ከዚያም ሚስጢሯን የሚያሰራጭ ነው፡፡” انتهى من فتاوى إسلامية (211212\3)    በዶክተር ሸይኽ ሁሰይን ብን ሙሐመድ  https://t.me/alateriqilhaq كن على بصيرة

🔷ከአንዳንድ የሐበሻ ሰዎች የሚስተዋለው አስቀያሚ ባህሪ የባልና የሚስትን ሚስጢር ማሰራጨት ክቡር በሆነችው የመካ ከተማ የክፍለ ዘመንን ሩብ የሚቃረብ ቆይታ አድርጊያለሁ - አሏህ ልቅና ይስጣት፡፡ ከፍ ያለ ምስጋናም ለአላህ ይገባው፡፡  የሱዑዲ ፣ የየመን ፣ የኩዌት ፣ የአልጀሪያ ፣ የህንድ ፣ የቱኒዚያ ፣ የፓኪስታን ፣ የሱዳንና የሌላም አገር ዜግነት ካላቸው ምርጥ ሰለፍይ ወንድሞች ጋር ተዋውቂያለሁ፡፡ ልክ በእኛ ቤት እንደሚከሰተው በእነርሱም ቤት በባልና ሚስት መካከል ግጭት ፣ አለመግባባት ይከሰታል፡፡  ከእነርሱ መካከል ሚስቱን የፈታ ፣  ከሚስቱ ጋር የተለያየም አለ፡፡ እንዲህ አይነቱን ድርጊት ቤት ይቁጠረው ፤ በተለይም ከሱዑዲ ዜጎች ዘንድ አዲስ ነገር  አይደለም፡፡  በጣም የሚገርመኝ ባል ከሚስቱ ጋር ያለውን አለመግባባትም ይሁን የቤት ሚስጢራቸውን ይፋ ሲያደርጉ አለማወቄ ነው፡፡ ግጭት ከተፈጠረም ባል ሚስቱን ይመክራል ፣ አላህ ባዘዘው መሰረት  ስርዓት በማስያዝ ላይ ይሰማራል፡፡ አላህ በተከበረው ቁርዓን እንዲህ ብሏል :- وَاللَّاتِي تَخَافُونَ نُشُوزَهُنَّ فَعِظُوهُنَّ وَاهْجُرُوهُنَّ فِي الْمَضَاجِعِ وَاضْرِبُوهُنَّ ۖ                     “እነዚያንም ማመጸቸውን የምታውቁትን ገስጿቸው፡፡ (ግሰጻው ካላስተካከላቸው) ከምኝታዎችም ተለዩዋቸው፡፡ (ከመኝታ መለየታችሁ ካላስተካከላቸው)  ምቱዋቸውም (ጉዳት ሳታደርሱ)፡፡”  (ኒሳእ ፡  35)   ሚስት ተመክራ ወደትክክለኛው ጎዳና ፣ ወደአቅሏ መመለስ ካልቻለችና በአመጸኝነቷ ከቀጠለች  የሁለቱ ባልና ሚስት ቤተሰቦች ጣልቃ ይገባሉ፡፡ ቤተሰቦች ጉዳዩን ካልፈቱትና እርቅ ካልመጣ ጉዳያቸውን ወደሸሪዓ ፍርድ ቤት ይወስዱታል፡፡ በፍርድ ቤቱ ውስጥ የምክክር ኮሚቴ የሚባል አለ፡፡ ኮሚቴው እንዲስማሙ የምክር አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ይህ ካልሆነ  ጉዳያቸው ወደፍርድ ቤት ቀርቦ ከብዙ ጥናት ፣ ክርክር ፣ ምክር በኋላ ፍርድ ቤቱ አላህ በሚከተለው አንቀጽ በተናገረው መሰረት   የመጨረሻ ሸሪዓዊ ብይን ይሰጣል፡፡ وَإِن يَتَفَرَّقَا يُغْنِ اللَّهُ كُلًّا مِّن سَعَتِهِ ۚ وَكَانَ اللَّهُ وَاسِعًا حَكِيمًا “ቢለያዩም (ቢፋቱ) ፣ አላህ ሁሉንም በችሮታው ያከብራቸዋል፡፡ አላህም ችሮታው ሰፊ ፣ ጥበበኛ ነው፡፡” (ኒሳእ ፡ 130) ይህ ነው በሱዑዲ የተመለከትሁት የአሊሞችና የሙፍቲዎች ሚና በሁለት ባለትዳሮች መካከል አለመግባባት ከተከሰተ መምከር እንጅ ጦላቅ እንዲወድቅ  ብይን መስጠት የለባቸውም - ምክንያቱም ይህ ባልና ሚስቶች በአካል ተገኝተው እነርሱን ማድመጥ ፣ ከዚያም ብይን መስጠት ይፈልጋልና፡፡ በዚህ ምክንያት የሱኡዲ ኡለሞች ለምሳሌ ፡ - ኢብን ባዝ ፣ ኢብን ኡሰይሚን ፣ ፈውዛን  እና ሌሎችም ኡለሞች እንዲሁም የሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ በባል እና ሚስት አለመግባባት ፣ ጦላቅን በመጠል  ዙሪያ  ጥያቄ ሲቀርብላቸው ፣ ሸሪዓዊ የሆነውን ህግጋት ማብራራት ፣  የምክር አገልግሎት መስጠት ፣ ጉዳያቸውን ወደሸሪዓ ፍርድ ቤት ዳኞች እንዲያቀርቡ መምከር  እንጅ  በፍጹም ፈትዋ አይሰጡም፡፡ በጣም የሚገርመው አንዳንድ የሐበሻ ሰዎች … አንድ ባል ከሚሰቱ ጋር ከተጋጨ ሚስጢሯን ላለፊ አግዳሚው ሁሉ በአደባባይ ያሰራጫል፡፡ ሚስቱም እንደዚሁ የባሏን ሚስጢር ለጎረቤት ፣ ለጓደኛ ፣ በየመድረሳው ታሰራጫለች፡፡ በዚህ ምክንያት በመካከላቸው ቂምና ጥላቻ ይወለዳል፡፡  ሁለቱም አንዱ አንዱን ለመበቀል ይፈልጋሉ፡፡ ሁለቱም ሐቁ ከእኔ ጋር ነው ብለው ይሞግታሉ፡፡  ችግራቸውን ለመፍታት  ከቁርዓንና ከሐዲስ ህግ ጋር በተቃረኑ ጊዜ  አላህ ከማይወደው ተግባር ለይ ይወድቃሉ፡፡ ሱናን መቃረን ለልቦና ጭንቀት ፣ ለነፍስ አለመረጋጋት  ምክንያት ይሆናል፡፡   አንዲት ሴት ከባሏ ጋር የተፈጠረውን አለመግባባት በስልክ ነግራኝ ነበር፡፡ የባሏን ችግር ለብዙ ወንዶችና ሴቶች እንዳወራች አመነችልኝ - ሱብሃን አላህ -  ይህች ሴት - ተቆጣጣሪዋ አላህ ሲሆን - ከደጋግ ሰለፍይ ሴቶች መካከል ናት ብዬ እገምታለሁ፡፡    “አንች ሀራም ከሆነው አሜት ወድቀሻል ፤  የአላህና የረሱልን ህግ ጥሰሻል ፣  የባልና ሚስት ችግር መፍትሄው በባል እጅ ነው ፤ እርሱ ካልፈታው  ሁሴን ወይም ሌላው ሳይሆን አላህ እንደነገረን ከሁለቱም ወገን ቅርብ ዘመዶች ጣልቃ ይገባሉ፡፡  وَإِنْ خِفْتُمْ شِقَاقَ بَيْنِهِمَا فَابْعَثُوا حَكَمًا مِّنْ أَهْلِهِ وَحَكَمًا مِّنْ أَهْلِهَا إِن يُرِيدَا إِصْلَاحًا يُوَفِّقِ اللَّهُ بَيْنَهُمَا ۗ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلِيمًا خَبِيرًا                             (እናንተ አማኞች!) የመካከላቸውንም (የባልና የሚስትን) ጭቅጭቅ ብታውቁ ፤ ከቤተሰቦቹ ሽማግሌን ፣ ከቤተሰቦቿም ሽማግሌን ላኩ፡፡ (ሽማግሌዎቹ) ማስታረቅን ቢሹ አላህ በመካከላቸው (ባልና ሚስትን) ያስማማል - አላህ ግልጽን ዐዋቂ ፣ ውስጥንም ዐዋቂ ነውና፡፡  (ኒሳእ ፡ 35) ችግሩ ከአቅም በላይ ከሆነ - ከተገኘ ወደሸሪአ ፍርድ ቤት መመለስ ነው” አልኳት፡፡ በጣም የደነገጥኩት ደግሞ በሁለቱ ግጭት መካከል አጅነብይ ወንድ ጣልቃ ገብቶ ባሏ ለእርሷ ያወራውን ለአጅነብዩ  እንደምትናገር ፣ እርሷ ለባሏ ያወራችውን ባል ለዚህ አጅነብይ እንደሚናገር በነገረችኝ ጊዜ ነው -  ሱብሃን አላህ - መፍትሄ ሰጭ የሆነውን ሱና በመቃረናቸው ምክንያት በባልና ሚስጥ መካከል ጥላቻው ቂሙ ጨመረ፡፡  እኔም ገሰጽኋት ፣ በአላህ አስፈራራኋት ፣ የባሏን ሚስጢር ከማሰራጨት መቆጠብ እንዳለባት ፣ ባሏን በመልካም መታዘዝ እንዳለባት - ከዚህ አልፎ ነገሩ በጣም የሚያጨናንቃት ከሆነ  ከቤተሰቦቿ ጋር እንድትገናኝ መከርኋት፡፡  ይህ ቆሻሻ የሆነ ባህል በሐበሻ ምድር በሙስሊሞች መካከል ከየት መጦ እንደገባ አላውቅም፡፡ ከእምነት ቁርጠኝነት ማነስና በመቀላቀል የመጣ ችግር ነው ብየ እገምታለሁ፡፡ በጣም የሚያስገርመው ነገር ፡  አንዳንድ ፈተና ላይ የወደቁ በሰዎች ጉዳይ  ጣልቃ የሚገቡ  ፊት ለፊት የምናያቸው ሰዎች አሉ፡፡ በማይመለከታቸው ጉዳይ ለሚስት ስለባሏ  የግብረስጋ ግንኙነትና ጥንካሬ  ይጠይቃሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ሚስት በባል ላይ እንድታምጽ ፣  ቀልቧ በእርሱ ላይ  እንዲሻክር ያደርጋሉ፡፡በቀላሉ ያበላሹዋታል ፤  ባሏን እንድትፈታ ያነሳሳሉ፡፡ ነብዩ - ዓለይሂሶላቱ ወሰላም - እንዲህ ብለዋል  ፡ ليس منا من خبب امرأة على زوجها “ሚስት በባል ላይ (እንድታምጽ) የሚያነሳሳ (የሚያበላሽ) ከእኛ አይደለም” ይህ ፈተና ላይ የወደቀ ጠያቂ የሸይጧን ስራ አስፈጻሚ ነው፡፡ በማንኛውም ሁኔታ በባለትዳሮች መካከል ነፍሱን ጣልቃ ሊያስገባ  አይገባውም፡፡  ከእርሱ መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ አንዲት ሴት - ለማንም አካል ሳይሆን - ባሏ የግብረ ስጋ ግንኙነት የማድረግ አቅሙ እንደሌለው ለሸሪዓ ዳኛ ብቻ መናገር ትችላለች፡፡  አንድም አካል ስለዚህ ጉዳይ ሊጠይቃት አየገባም፡፡ ይህ ከስነ ምግባር እጥረትና ከእምነት ቁርጠኝነት ድክመት ነው፡፡ 

በወንድማችን አቡበከር የሰርግ ፕሮግራም ላይ የተደረገ አንገብጋቢ ሙሓደራ! 🎤 በኡስታዝ ኑራዲስ(አቡል-በያን) ሀፊዘሁላህ ይደመጥ👌

Repost from N/a
بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ 🚨 አስቸኳይ የጥንቃቄና የማስጠንቀቂያ መልዕክት ከባህር ዳር አባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጅድ! 🚨 ​ውድና የተከበራችሁ የዲናችን እህትና ወንድሞች፤ በአሁኑ ሰዓት የባህር ዳር አባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጅድን የቴሌግራም ግሩፑን ስም፣ዲስክሪፕሽን (Description)  ጽሁፎችን እና ከዚህ በፊት የተለቀቁ ፖስቶችን እንደ ግብአት ተጠቅሞ፣ የተለየ የሐሰት ግሩፕ እና አካውንት ከፍቶ ሰዎችን እያታለለ ብር የሚሰበስብ አጭበርባሪ ግለሰብ እንዳለ ደርሰንበታል። ​ይህ አካል ከቢላል መስጅድ አስተዳደርም ሆነ ከኮሚቴው ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው እና የግል ጥቅሙን የሚያሳድድ አጭበርባሪ ነው። ስለሆነም መላው ሙስሊም ማህበረሰብ የሚከተሉትን ነጥቦች ተገንዝቦ ራሱንና ዲኑን ከማጭበርበር እንዲጠብቅ በጥብቅ እናሳስባለን፡ ​1️⃣ ትክክለኛ እና ሕጋዊ የባንክ አካውንቶቻችን፡ ለባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 11 (አባይ ማዶ) በኢትዮጵያ አህሉሱና እስላማዊ ማህበር ስር ላለው ለቢላል መስጅድ ግዢ እና ግንባታ ማሰባሰቢያ የሚውሉ እውቅና ያላቸው አካውንቶች እነዚህ ብቻ ናቸው፦ ​📌 ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000-742-45-45-45 📌 አቢሲኒያ ባንክ፦ 245566778 📌 ሂጅራ ባንክ፦ 1000-927-373-0001 👥 የአካውንት ስም፦ አሊ ሙሀመድ ፣ ጀማል ሙሀመድ እና አህመድ እስማን ​⚠️ እጅግ በጣም አስፈላጊ ማሳሰቢያ፦ ከነዚህ ከላይ ከተጠቀሱት ሶስት የባንክ አካውንቶች እና በጋራ ከተከፈቱት ከእነ አሊ ሙሀመድ፣ ጀማል ሙሀመድ እና አህመድ እስማን ስሞች ውጭ ምንም አይነት ሌላ አካውንት የሌለን መሆኑን በድጋሚ እናረጋግጣለን!2️⃣ ፍፁም ሊታወቁና ሊጠነቀቁ የሚገቡ የሐሰት መረጃዎች፡አብደላ አወል አባቦር (Abidela Awol Ababor) የሚባል ሰው በኮሚቴው ውስጥ የለም! ልጁ ወደ ግሩፑ ሲገቡ ራሱን በዚህ ግሩፕ ስም እያስተዋወቀ እና የራሱን አካውንት በመለጠፍ እያጭበረበረ ይገኛል። 👌👌👌በቢላል መስጅድ ስም በአብደላ አወል አባቦር ስም የተከፈተ ምንም አይነት አካውንት የለም! ​❌ የአዋሽ ባንክ አካውንት ፍፁም የለንም! ይህ አጭበርባሪ አካል በአዋሽ ባንክ አካውንት ከፍቶ ገንዘብ እየሰበሰበ ይገኛል። እኛ ግን በአዋሽ ባንክ ምንም አይነት አካውንት የሌለን መሆኑን ህዝቡ በደንብ እንዲያውቅና እርግጠኛ እንዲሆን እንፈልጋለን። ​✅ የሜምበር (አባላት) ቁጥር ልዩነት፦ ትክክለኛው የቢላል መስጅድ ግሩፓችን በአሁኑ ሰዓት 16,045 (አስራ ስድስት ሺህ አርባ አምስት) ሜምበር አለው (ይህ ቁጥር አባላት ሲገቡና ሲወጡ መጠኑ ከፍና ዝቅ ሊል ይችላል)። የዚህ አጭበርባሪ ግሩፕ ግን 3 ሺህ አካባቢ ብቻ አባላት ያሉት በመሆኑ በዚህ የቁጥር ልዩነት በቀላሉ መለየት ትችላላችሁ። ​3️⃣ ለተጨማሪ መረጃ እነዚህን የኮሚቴ ስልክ ቁጥሮች ይጠቀሙ፡ ማንኛውንም መረጃ ለማጣራትና ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ በሚከተሉት የእውነተኛው ኮሚቴ ስልክ ቁጥሮች ላይ በነፃነት መደወል ይችላሉ፦ 📞 0918720696 - አሊ ሙሀመድ 📞 0918702221 - ጀማል ሙሀመድ(Dr) 📞 0920257036 - ሰኢድ መህሙድ (telegram owner) ​4️⃣ የበኩላችሁን አድርጉ (ሪፖርት አድርጉ)፦ ይህን የሐሰት አካውንት ወይም ግሩፕ ስታዩ ወዲያውኑ "Report" በማድረግ እንዲዘጋ አድርጉ። ይህንን የማስጠንቀቂያ መልዕክትም ለሌሎች እህትና ወንድሞች በማጋራት (Share በማድረግ) የአጭበርባሪዎችን ሴራ እንድታከሽፉ በአላህ ስም እንጠይቃለን። ​💎 የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦«مَنْ رَأَى مِنْكُمْ مُنْكَرًا فَلْيُغَيِّرْهُ بِيَدِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِلِسَانِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِقَلْبِهِ، وَذَلِكَ أَضْعَفُ الإِيمَانِ» (رواه مسلم)"ከእናንተ መካከል መጥፎ ነገርን (ወንጀልን) ያየ ሰው በእጁ ይለውጠው(ይከልክለው)፤ ካልቻለ በምላሱ (በንግግሩ/በጽሁፉ)፤ ካልቻለ በልቡ (ይጥላው)፤ ይህም ከኢማን ሁሉ በጣም ደካማው ነው።" (ሙስሊም ዘግበውታል)የባህር ዳር አባይ ማዶ ሰለፊያ ቢላል መስጅድ ግዢና ግንባታ አስተባባሪ ኮሚቴ

የምቀኝነትና የድግምት መብዛት ምክንያቶች ——— ታላቁ ዓሊምና ፈቂህ የሆኑት ሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል'ዑሰይሚን (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- “በዚህ በመጨረሻው ዘመን ውስጥ በሰዎች ላይ ድግምትና ምቀኞች… መሰል ችግሮች የበዙበት ምክንያት ① አላህን ከማውሳት በመዘናጋታቸው ነው። ② አሸናፊና የላቀ በሆነው አላህ ላይ ያላቸው መመካት በመዳከሙ ነው። ③ በሸሪዓ የመጡትን የመከላከያ አዝካሮች መጠቀማቸው አናሳ በመሆኑ ነው። አለያማ እኛ እናውቃለን በሸሪዓ የመጡ የመከላከያ አዝካሮች የእጁጅና መእጁጅ ከተገደቡበት ግድብ በላይ ከልካይ መጠበቂያ እንደሆነ እናውቃለን። የሚያስቆጨው ነገር ብዙ ሰዎች ስለነዚህ አውራዶች አያውቁም፣ ያወቀው በብዛት ይዘናጋል፣ አለያም አዝካሮችን ሲያነብ በችለተኛ (ልቡ ሌላ ቦታ ሆኖ ነው)። ይህ ሁሉም ጉድለት ነው። ሰዎች በሸሪዓ የመጡ መጠበቂያ አዝካሮችን በአግባቡ ቢጠቀሙ ከብዙ ሸሮች ሠላም ይሆኑ ነበር። አላህን ዓፊያና ሠላምን እንጠይቀዋለን!!።”  [ተፍሲር ጁዝእ ዐመ ገፅ 358] ✍🏻ትርጉም:- ኢብን ሽፋ #Join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f

የምቀኝነትና የድግምት መብዛት ምክንያቶች ——— ታላቁ ዓሊምና ፈቂህ የሆኑት ሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል'ዑሰይሚን (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- “በዚህ በመጨረሻው ዘመን ውስጥ በሰዎች ላይ ድግምትና ምቀኞች… መሰል ችግሮች የበዙበት ምክንያት ① አላህን ከማውሳት በመዘናጋታቸው ነው። ② አሸናፊና የላቀ በሆነው አላህ ላይ ያላቸው መመካት በመዳከሙ ነው። ③ በሸሪዓ የመጡትን የመከላከያ አዝካሮች መጠቀማቸው አናሳ በመሆኑ ነው። አለያማ እኛ እናውቃለን በሸሪዓ የመጡ የመከላከያ አዝካሮች የእጁጅና መእጁጅ ከተገደቡበት ግድብ በላይ ከልካይ መጠበቂያ እንደሆነ እናውቃለን። የሚያስቆጨው ነገር ብዙ ሰዎች ስለነዚህ አውራዶች አያውቁም፣ ያወቀው በብዛት ይዘናጋል፣ አለያም አዝካሮችን ሲያነብ በችለተኛ (ልቡ ሌላ ቦታ ሆኖ ነው)። ይህ ሁሉም ጉድለት ነው። ሰዎች በሸሪዓ የመጡ መጠበቂያ አዝካሮችን በአግባቡ ቢጠቀሙ ከብዙ ሸሮች ሠላም ይሆኑ ነበር። አላህን ዓፊያና ሠላምን እንጠይቀዋለን!!።”  [ተፍሲር ጁዝእ ዐመ ገፅ 358] ✍🏻ትርጉም:- ኢብን ሽፋ #Join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa Follow Ibn Shifa's WhatsApp Channel: ⤵️⤵️ https://whatsapp.com/channel/0029VbAU7moHgZWXXXnNiL3f

አስደሳች ዜና👇 👉 ለእውቀት ፈላጊዎች በሙሉ 🔎 እነሆ በስልጤ ዞን በስልጢ ወረዳ በመነሀራ ከተማ ሸይኽ ዘይኑ የሚሰጥ አዲስ ደርስ ሊጀምር መሆኑን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው። የሚቀሩ ኪታቦች
+1
አስደሳች ዜና👇 👉 ለእውቀት ፈላጊዎች በሙሉ 🔎 እነሆ በስልጤ ዞን በስልጢ ወረዳ በመነሀራ ከተማ ሸይኽ ዘይኑ የሚሰጥ አዲስ ደርስ ሊጀምር መሆኑን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው። የሚቀሩ ኪታቦች 1, አዱሩስ አልሙሒመህ ሊዓመቲል ኡመህ የሸይኽ ኢብን ባዝ 2, አሱል አስሰላሳ የሸይኽ ሙሀመድ ኢብን አብዱል ወሃብ 3, ኪታቡ አትተውሂድ የሸይኽ ፈውዛን 4, ፊርቀቱ አንናጅያ የሙሀመድ ኢብን ጀሚል ዘይኑ 5, ሸርህ አቂደቱል ዋስጥያ የሸይኽ ፈውዛን 6, ኡምደቱ አልአህካም የሸይኽ አብዱል غንይ 7, ኢርሻድ የሸይኽ ፈውዛን 8, ፈትሁል መጂድ 9, ሸርሁ አስሱነህ የሸይኽ ፈውዛን 👉 ሌሎች ደርሶችም ይኖራሉ 🗓 ደርስ የሚጀምርበት ቀን 👉 ዙልሂጃ 29/1447 👉 ሰኔ 8/2018 📍አድራሻ፦ ከወራቤ 12km ወደ ቡታጅራ በሚወስደው አልከሶን እንዳለፋችሁ  ወይም ከቡታጅራ 33km ወደ ወራቤ በሚወስደው  ቅበት ከተማን እንዳለፋችሁ ከጦራ መስመር ምትመጡ እሎስን እንዳለፋችሁ በምትገኘዋ ከተማ (መናሀሪያ) ነው። 🌐 ተጨማሪ ጥቆማዎችን ለማግኘት እንዲሁም የተለያዩ መረጃዎችን ለመለዋወጥ የቴሌግራም ግሩፓችን join በማለት ይቀላቀሉ 👇👇👇 https://t.me/+FsV1zmJcpMZjMjFk ለበለጠ መረጃ :- 1, ሙከሚል  +251921420111 2, ከይሬ          +251920973908 3, ሙባረክ   +251939455342 ♨️ ማሳሰቢያ :- 1, ቀሪኣ ከበቂ በላይ ነው እና በሁሉም አቅጣጫዎች ተጓዳኝ ዒባዳዎችን የምንፈጽምባቸው መስጂዶች አሉ 2, የደርስ ቋንቋ በአማርኛ ነው። ♻️ ሁሉም ይህ መልዕክት የደረሳቹ ሰለፍዮች እንዲሁም የቻናል እና የግሩፕ ባለቤቶች  ላልሰሙት በማሰማት እና ላልደረሳቸው በማዳረስ ወደኸይር እንድታመላክቱ መልዕክታችን ነው።

بسم الله الرحمن الرحيم 🔊ኸድር (አለይሂ ሰላም) ሞተዋል❗️ ✏️ ቁርኣንና ሀዲስ ያለው ምርጥ ህዝብ እንዴት ተረትና ቅዠት ይከተላል ⁉️ ✏️ ሱፊያ = የሳሊሆች ጠላት ✏️ ሳሊሆችን የሚወድ አሏህን ብቻ ያምልክ ❗️ 🎤 አቡ ሀመዊያ https://t.me/joinchat/AAAAAEP0OfkzzNtGHLxVeQ

✅ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ↪️ የፊታችን እሁድ 30/09/2018 የወንድማችንን አቡበክር ሙሀመድ የጋብቻ ፕሮገራም ምክንያት በማድርግ አጓጊ እና ወሳኝ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተናል። 🪑 ተጋባዥ እን
✅ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ↪️ የፊታችን እሁድ 30/09/2018  የወንድማችንን አቡበክር ሙሀመድ የጋብቻ ፕሮገራም ምክንያት በማድርግ አጓጊ እና ወሳኝ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተናል። 🪑 ተጋባዥ እንግዶቻችን        👇👇👇 🎙 ኡስታዝ ኑር አዲስ ✅ أهمية الزواج 🎙 ኡስታዝ ዶክተር ሸምሱ ✅ التوحيد لشرك 🎙 ኡስታዝ ሙሐመድ ሸምሴ ✅حقوق الوالدين. 🎙 ኡስታዝ ኸድር ✅ الصلاة 🎙 ኡስታዝ አቡ ሙዓዝ ✅ المنهج الصحيحة 👉 አድራሻ ፦ ቅበት ከተማ አስተዳደር በቢላል መስጂድ

✅ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ↪️ የፊታችን እሁድ 30/09/2018 የወንድማችንን አቡበክር ሙሀመድ የጋብቻ ፕሮገራም ምክንያት በማድርግ አጓጊ እና ወሳኝ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተናል። 🪑 ተጋባዥ እን
✅ ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ↪️ የፊታችን እሁድ 30/09/2018  የወንድማችንን አቡበክር ሙሀመድ የጋብቻ ፕሮገራም ምክንያት በማድርግ አጓጊ እና ወሳኝ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተናል። 🪑 ተጋባዥ እንግዶቻችን        👇👇👇 🎙 ኡስታዝ ኑር አዲስ ✅ أهمية الزواج 🎙 ኡስታዝ ዶክተር ሸምሱ ✅ التوحيد لشرك 🎙 ኡስታዝ ሙሐመድ ሸምሴ ✅حقوق الوالدين. 🎙 ኡስታዝ ኸድር ✅ الصلاة 🎙 ኡስታዝ አቡ ሙዓዝ ✅ المنهج الصحيحة 👉 አድራሻ ፦ ቅበት ከተማ አስተዳደር በቢላል መስጂድ

🔷 የዓለም ጥፋት በመሃይምነት ነው !     የዚህች ምድር ውበት ሰላምና ብልፅግና በዲን እውቀት ሲሆን ጥፋትና ውድቀቱ በጅህልና መሆኑን ታላቁ ሊቅ ኢብኑል ቀይም እንዲህ በማለት ያስረዳናል  : – يقول ابن القيم – رحمه الله – " ولم يوجب الله سبحانه على الأمة إلا بما فيه حفظ دينها ودنياها وصلاحها في معاشها ومعادها ، وبإهمالها ذلك تضيع مصالحها وتفسد أمورها،  فما خراب العالم إلا بالجهل،  وما عمارته إلا بالعلم ، وإذا ظهر العلم في بلد أو محلة قل الشر في أهلها، وإذا خفي العلم هناك ظهر الشر والفساد ، ومن لم يعرف هذا فهو ممن لم يجعل الله له نورا، قال : الإمام أحمد – رحمه الله – " ولو لا العلم كان الناس كالبهائم " وقال :  " الناس أحوج إلى العلم منهم إلى الطعام والشراب ، لأن الطعام والشراب يحتاج إليه في اليوم مرتين أو ثلاثة، والعلم يحتاج إليه في كل وقت "           إعلام الموقعين  ( 2/238 ) " አላህ በኡማው ላይ ዲኑንም ዱንያውንም መኖረያውንም መመለሻውንም  የሚጠብቅለትን ገር እንጂ ግድ አላደረገበትም ። ይህንን ችላ በማለቱ ጥቅሙን አጥቷል ጉዳዩም ይበላሻል ።  የዓለም ጥፋት በመሃይምነት እንጂ በሌላ አይደለም ። ማማሩም በዒልም እንጂ በሌላ አይደለም ። ዒልም በአንድ ሀገር ወይም ቦታ ከተስፋፋ በህብረተሰቡ ውስጥ ተንኮል ይቀንሳል ። እዛ ቦታ ዒልም ከተደበቀ ክፋትና ጥፋት ይንሰራፋል ። ይህን የማያውቅ አላህ ብርሃን ያላደረገለት ሰው ነው ። ኢማሙ አሕመድ እንዲህ ብለዋል : – " እውቀት ባይኖር ኖሮ ሰው እንደ እንሰሳ ነበር "  በሌላ ቦታም እንዲህ ብለዋል : – " ሰዎች እውቀት ከምግብና መጠጥ በላይ ያስፈልጋቸዋል ። ምክንያቱም እነዚህ በቀን አንድ ወይም ሁለት ጊዜ ያስፈልጋሉ እውቀት ግን ሁሌም ያስፈልጋል ። " አላህ በእውቀት ብርሃን ቀልባቸውን ካበራላቸው ባሮቹ ያድርገን ። http://t.me/bahruteka

🚫ከቁርኣኒዮች እንጠንቀቅ!🚫 🎙 በዶክተር ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁላህ) ⏲ [Clip: 3:29 Minutes] @semirEnglish

🚫ከቁርኣኒዮች እንጠንቀቅ!!!🚫 ክፍል-1 ኢማም ኢብኑ ማጀህ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) "የነቢዩን (ﷺ) ሐዲሥ ማክበርና ማላቅ፤ እንዲሁም እሱን በሚቃረኑ ሰዎች ላይ ጠንካራ (ብርቱ መሆን" የሚል ርዕስ (Chapter) ሰጥተዋል። እዚህ ላይ "ማክበርና ማላቅ" የሚለው ትርጉም፤ ለሐዲሦች የሚገባቸውን ትልቅ ትኩረት፣ ክብደትና እንክብካቤ መስጠት፣ በጥብቅ ሙጥኝ ማለት (መያዝ) እና ሐዲሥን ከመቀበልና በእርሱ ከመመራት ረገድ ፈጽሞ ቸልተኛ አለመሆን ማለት ነው። ሐዲሥን በሚቃረኑ ሰዎች ላይ ጠንካራ መሆን" ማለት ደግሞ፣የነቢዩ (ﷺ) ሐዲሥ ከደረሳቸውና ትክክለኛነቱ ከተገለጸላቸው በኋላ፣ በሐዲሡ ላይ መጥፎ በሚናገሩ (በሚተቹ) እና በእርሱ የማይሠሩ (የማይተገብሩ) ሰዎች ላይ ጥብቅና ቆራጥ አቋም መያዝ ማለት ነው። ኢማም ኢብኑ ማጃህ በዚህ የምዕራፍ ርዕስ ሥር በርካታ የሐዲሥ ስብስቦችን አስፍረዋል። በእነዚህ ዘገባዎች ውስጥ የነቢዩን (ﷺ) ሐዲሥ ችላ ከማለት (ከማሳነስ) እና ከአላህ መልእክተኛ (ﷺ) በተረጋገጠውና በጸናው መንገድ ላይ በጥብቅ ካለመያዝ በጥብቅና በጠንካራ ሁኔታ የሚያስጠነቅቁ መልእክቶች ይገኛሉ። ከአል-ሚቅዳም ቢን ማዕዲ-ከሪብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተላለፈው የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ❝አንድ ሰው በሶፋው (በመደገፊያው) ላይ ተደግፎ ተቀምጦ፣ ከእኔ የሆነ ሐዲሥ በሚነገረው ጊዜ እንዲህ የሚልበት ጊዜ ሊመጣ ቅርብ ነው፦ "በእኛና በእናንተ መካከል ያለው የአላህ መጽሐፍ (ቁርኣን) ብቻ ነው፤ በእርሱ ውስጥ ሐላል (የተፈቀደ) ሆኖ ያገኘነውን ሐላል እናደርገዋለን፤ ሐራም (የተከለከለ) ሆኖ ያገኘነውን ደግሞ ሐራም እናደርገዋለን (ከሐዲሥ አንፈልግም)" ይላል። ተጠንቀቁ! የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) ሐራም (ክልክል) ያደረጉት ነገር አላህ (በቁርኣኑ) ሐራም እንዳደረገው ሁሉ ነው።❞ [ሐዲሱን ኢብኑ ማጃህ፣ አቡ ዳውድ፣ አት-ቲርሚዚይ እና ኢማም አሕመድ ዘግበውታል። ሸይኽ አል-አልባኒ ሶሒሕ አል-ጃሚዕ (2657) ላይ "ሶሒሕ" ብለውታል።] ሸይኽ አቡ ኸዲጀህ (ሀፊዘሁላህ) ሐዲሱን እንዲህ በማለት ያብራራዋል፦ ይህ ሐዲስ በታላቁ ሶሐባ አል-ሚቅዳም ቢን ማዕዲ-ከሪብ አል-ኪንዲ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ከተላለፈው የመጀመሪያው ሐዲሥ የተወሰደ ሲሆን፤ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) የተናገሩትን ትንቢት እንደሚከተለው ይተነትናል፦ — የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) ሐዲሥ ለእሱ በሚነበብለትና በሚነገረው ጊዜ፣ ያንን ሐዲሥ ተቀብሎ ለመሥራት ፈቃደኛ አይሆንም፣ —በምትኩ እንዲህ ይላል፦ «በእኛና በእናንተ መካከል ያለው የአላህ መጽሐፍ (ቁርኣን) ብቻ ነው፤ በእርሱ ውስጥ ሐላል (የተፈቀደ) ሆኖ ያገኘነውን ሐላል እንላለን፤ ሐራም (የተከለከለ) ሆኖ ያገኘነውን ደግሞ ሐራም እንላለን፣ —የዚህ ንግግር ዓላማ፦ «እኛ በቁርኣን ውስጥ ባለ መረጃ ብቻ ነው የምንመራው፤ ከቁርኣን ውጭ ያለውን (የነቢዩን ሱና/ሐዲስ) እንተዋለን፣ ለእርሱም ምንም አይነት ትኩረት አንሰጥም» ለማለት ነው። — እነዚህ ሰዎች በቁርኣን ብቻ እናምናለን ይላሉ እንጂ በሱና (በሐዲስ) አያምኑም። 📝 መረጃው ከሸይኽ አቡ ኸዲጀህ (ሀፊዘሁላህ) ዌብሳይት ተወስዶ የተተረጎመ ˢʰᵃʳᵉ ᵗʰᵉ ᵏʰᵃʸʳ | ʲᵒⁱⁿ ☟︎︎︎ https://t.me/semirEnglish https://t.me/semirEnglish

🚫  የኻሊድ ክብሮም የአክፍሮትና ሽርክ ጉዞ ኻሊድ ክብሮም የተባለው ግለሰብ ሰልሜያለሁ ብሎ ወደ እስልምና ከገባ በኋላ የትና ማን ጋር እንደተማረና ሸይኹ ማን እንደሆነ ሳይታወቅ ወደ ዳዕዋ ሜዳ በመግባት በተለይ ሴቶችን ያለ ሒጃብ ፊት ለፊት በማስተማር ሙሪዶቹ እንዲሆኑ ካደረገ በኋላ በጣም አደገኛ አካሄድ እየሄደ ይገኛል ። ይህ ግለሰብ እየሄደበት ያለው አካሄ በጣም መርዛማና ትክክለኛውን እስልምና የሚበርዝ ነው ። ግለሰቡ እየሄደበት ያለው አካሄድ ምእራባዊያን የሰጡት የቤት ስራ ያለ እስኪመስል እየደረሰ ነው ። ይህ ግለሰብ በረቀቀ መልኩ የነብዩን ሐዲስ ውድቅ በሚያደርግ መልኩ ቁርኣንን ብቻ መያዝና የቁርኣንን መረጃነት ብቻ መቀበል የሚለውን የቁርኣናዊያን ቡድኖች አካሄድ እያሰረፀ ነው ። በዚህ ብቻ አላቆመም ቁርኣንን ራሱ ማንም ቢያብራራው ተቀባይነት እንደሌለውና በቀጥታ ቁርኣንን ብቻ በመገንዘብ መብቃቃት እንደሚቻል መሰረት በመጣል ላይ እየሰራ ነው ። ይህን አስተምሮ በሚቀጥለው ንግግሩ ተመልከቱት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/bahruteka/7251 ይህ አካሄድ ሰለፎች ቁርኣንን የፈሰሩበትን መንገድ ውድቅ ለማድረግና ሰዎች በዝንባሌያቸውና ከስሜታቸው ጋር በሚስማማ መልኩ እንዲፈስሩት በዚህም ምእራቦች የሚፈልጉት አይነት ባህላዊ እስልምና እንዲስፋፋ ለማድረግ ያለመ አካሄድ ይመስላል ። ሌላኛው የዚሁ የፈተና ሰው ዳዕዋ ሰዎች በኢማናቸው አማካይነት የፈለጉትን የማድረግ አቅም አላቸው የሚለውን የአሕባሾች ዐቂዳን ለማስፋፋት የሚያደርገው ጥረት ነው ። ይኸው ግለሰብ የለበሱት ልብስ ለሌሎች በረከት የሚያስተላልፍ ትራፊ ውሃቸው ለሌሎች መድሃኒት የሚሆንላቸው ፍፁም የሆነ ሀይል (ፓወር) ያላቸው አሉ እያለ የሰውን ልጅ የረቂቅ ሀይል ባልተቤትና ፍፁም ነው በማለት የቀብር አምልኮና በሙታን መንፈስ ወደ መታገዝ እየተጣራ ይገኛል ። ይህንን አስተምሮ በሚቀጥለው ሊንክ ገብታቸው አዳምጡ ⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️ https://drive.google.com/file/d/1nRc3dU70O311-ljNlE_JueD3-AeG6DQe/view?usp=drivesdk ከዚህ የሚከፋውና በጣም አደገኛው ደግሞ የደጋጎችን ልብስ መልበስ የእነርሱ መንፈስ ወዳንተ እንዲተላለፍ ያደርጋል የሚለው አስተምሮ ነው ! ይሄኛውንም በሚቀጥለው ሊንክ ገብተው ያዳምጡ : – 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://drive.google.com/file/d/1dR8C1c5Tv4SIVCK1h4IyKFBd8dx75xFy/view?usp=drivesdk ተመልከቱ አንድ ጃሂል ስለጠሃራ የማያውቅ የአንድን ወልይ ልብስ ቢለብስ ወልይ መሆን ይችላል ማለት ሽርክ አይደለም እያለ ነው የሚያስተምረው ። ለማንኛውም ይህ ግለሰብ ብዙ ሴቶችና ወጣቶች ዘንድ እንዲህ አይነቱን የኩፍርና የሽርክ አስተምሮ ተቀባይነት እንዲኖረው እያደረገ ያለ ግለሰብ ስለሆነ ሙስሊሞች ከግለሰቡና ከአስተምሮቱ እንዲርቁና የኢስላም ጠላቶችን ተልእኮ እያስፈፀመ መሆኑን በማስገንዘብ መታደግ ያስፈልጋል እላለሁ ። http://t.me/bahruteka

— ርእስ፦ በየ ሚዲያው የሚደረጉ ውይይቶች ፍርድ! 🎙 ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት ሀራ -ሐፊዞሁ'ሏህ- ➵➵➵➵➵➵➵➵➵➵➵➵➵ https://t.me/SheikMohmmedHyatHara https://t.me/SheikMohmmedHyatHara

📢 የጁሙዓ ኹጥባ!      √√√√√√√√√√ 👌 ↩️ خُطْبَةُ الْـجُمُعَةِ ↪️ የጁመዓ ኹጥባ 📍ርዕስ፦➘↪️ «የዋሻው ሰዎች ታሪክ» በሚል ርዕስ የተደረገ ኹጥባ! 🎙 በወንድም አቡ ዒምራን [መሐመድ መኮንን] 🎙 لأخ أَبُو عِمرَان مُحَمَد مَكُونْنْ حَفِظَهُ اللّٰه 📅 ግንቦት 21//2018 🕌 በሸዋሮቢት ከተማ የሰለፍዮች በሆነው ፉርቃን መስጂድ የተደረገ ኹጥባ!          •┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈• 📱👇👇👇👇 https://t.me/AbuImranAselefy https://t.me/AbuImranAselefy

✨عيدكم مبارك✨ الله أكبر الله أكبر لا إله إلا الله والله أكبر الله أكبر ولله الحمد ⚜️ይህ የ ኢድ በዓል ከነቢዩሏህ ኢብራሂም እና ከልጃቸዉ ኢስማኢል ታ
✨عيدكم مبارك✨ الله أكبر الله أكبر لا إله إلا الله والله أكبر الله أكبر ولله الحمد ⚜️ይህ የ ኢድ በዓል ከነቢዩሏህ ኢብራሂም እና ከልጃቸዉ ኢስማኢል ታሪክ ለአሏህ ታማኝ መሆን ፤ ተስፋ አለመቁረጥ እና በጥበብ መጓዝን የምንማርበት ታሪክ ከጀርባዉ ያነገበ ነዉ። ♻️ሁሌም ቢሆን ወደ አሏህ እንጠጋ በአሏህ ላይ እንመካ ተስፋ ሳንቆርጥ ጉዟችንን እንቀጥል!! ዒድ ሙባረክ‼️ አሏህ ለሁላችንም መልካም በዓል ያድርግልን!! 🎆عيدكم مبارك🎆 ✍️አቡ አብዲረሕማን (አብዱሰላም) ከባ/ዳር https://t.me/BDU_Selefiyah_Students

عيد مبارك تقبل الله منا ومنكم ውድ የሱና ቤተሰቦቻችን እንኳን ለ1447 ኛው አመተ ሂጅሪያ ዒድ አል-አድሀ በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ በሱና ተውበን የአላህን ብቸኛ ተመላኪነት እያረ
عيد مبارك   تقبل الله منا ومنكم     ውድ የሱና ቤተሰቦቻችን እንኳን ለ1447 ኛው አመተ ሂጅሪያ ዒድ አል-አድሀ በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ በሱና ተውበን የአላህን ብቸኛ ተመላኪነት እያረጋገጥን የምናከብረው ይሆን ዘንድ እንመኛለን✨✨ https://t.me/EUSaCochannel https://t.me/EUSaCochannel

🪚 ስታርዱ የሚታረዱትን እንስሳት እግሮች አትሰሩ 🗡 ኡድሂያችሁንም ሆነ ሌላ እርዶ ስታርዱ እንዲህ ጠፍንጋችሁ አትሰሩ 👉 ይህ ከማሰቃየት ነው የሚቆጠረውና ◈ ሳታስሩ እረዱ ካስቸገራችሁ ለመያዣ ብቻ ተጠቀሙበት እንጅ ጠፍንጋችሁ አትሰሩ!!! ➷➴➷➴ https://t.me/hussenhas 👌 ይሄ ችግር በየቤቱ ያለ ነው። በጥንቃቄ ካላየነው ሊያስጠይቀን ይችላል። 👌 እንደሚታወቀው ሸሪዓችን በእርድ ዙሪያ ማሰቃየት እንደሌለብን ትምህርት ሰጥቷል። 👌 ማሰሩ የሚያሰቃኝ ከሆነ ደግሞ ይህንን ድንጋጌ መጣስ ይሆናል። 👌 ለሸይኽ ሷሊህ አልፈውዛን ጥያቄው ሲቀርብ እንደተባለው የሚታሰረው ደሙን ከመውጣቱ ለማቅለል ነው ተብሏል። ሸይኹም በፈቸዋቸው ይህ እሷን ከመቅጣት ነው ብለዋል። ✅ ስለዚህ ጥንቃቄ አድርጉ 🌴 🌱 ☔️ 👇👇👇 https://t.me/AbuImranAselefy/10863

ወቅታዊ እና በጣም ጠቃሚ ፈታዋዎችን የያዘች PDF ነች እና download & share አድርጓት ባረከሏሁፊኩም