Myfellow
Ir al canal en Telegram
1. ዘወትር ዕሁድ ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ በተስፋ ቲቪ እና በተስፋ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ ዩቱብ ቻናል። 2. ዩቨርስቲ ካምፓስ ስለሚገኙ የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት የተሟላ መረጃ ከፈለጉ ከmyfellow.et ያግኙ ስለ ፌሎሺፖቻችሁ እንቅስቃሴ የተለያዩ መረጃዎችን ለመላክ ይህንን ይጠቀሙ👇👇👇@Contact_Myfellow
Mostrar más1 281
Suscriptores
+124 horas
+387 días
+3530 días
Archivo de publicaciones
1 282
This week Episode👌🔥
በዚህ ሳምንት በMy Fellow "ኑ! እናስብ" በሚለው ሁለተኛ መፅሐፉ ያልጠሩ አስተሳሰቦችና ዐዎጆች ምክንያቶቻቸውና መፍትሔዎቻቸውን ብትንትን ግልጥልጥ አድርጎ የከተበው ቤተኛው እንግዳችን የሺጥላ ይገዙ ዕሁድ ምሽት 1:00 ሰዓት ላይ በMy Fellow ይከሰታል።
ስለመፅሐፉም ትንሽ ይለናል በእርግጠኝነት ታተርፉበታላቸውና ዕሁድ ምሽት 1:00 ሰዓት እንገናኝ ተመልከቱት ለምትወዷቸውም አጋሩት።
ለተጨማሪ ተማሪና ክርስቲያን ወጣት ተኮር ጉዳዮች ፣ የMY FELLOW ቤተሰብ መሆንና ይህን የTesfa_BN የዩትዩብ ገፅ ሰብስክራይብ ማድረግ አትዘንጉ።
🙌 JOIN MY FELLOW
1 282
"Exam ላይ መጨነቅ አቁሙ" MY FELLOW
ተመልከቱት ለምትወዷቸውም ለዘንድሮ ተፈታኞች አጋሩት።
ለተጨማሪ ተማሪና ክርስቲያን ወጣት ተኮር ጉዳዮች ፣ የMY FELLOW ቤተሰብ መሆንና ይህን የ TBN የዩትዩብ ገፅ ሰብስክራይብ ማድረግ አትዘንጉ።
🙌 JOIN MY FELLOW
1 282
ወንጌልን በመዝሙር ከገርጂ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ከኪንግደም ሳወንድ ጋር በተስፋ ብርድካስቲንግ ኔትወርክ ዩትዩብ ቻናል በቀጥታ መስመር ላይ ነን አብራችሁን አምልኩ🙏
https://www.youtube.com/live/bh9Gsgp598U?si=Uv9Q8SlrFfbj2OTU
1 282
ነገ ምሽት በMy_Fellow
የፈተና ሰሞን ጭንቀት ትጋታችሁን ሁሉ ከንቱ እንዲያደርግ አትፍቀዱ!
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና (Entrance exam)፣ የከፍተኛ ተቋማት የመመረቂያ ፈተና (Exit exam)፣ እንዲሁም የተማሪዎች ሁሉ የፈተና ወቅት እንደተቃረበ ይታወቃል። በዛሬው የMY FELLOW ዝግጅታችን፣ አማካሪና አሠልጣኝ ከሆነውና በተለይም ተማሪዎች ላይ በትኩረት ከሚሰራው እንዲሁም የAgape Spark መስራች ከሆነው ወጣት ኤልሻ አየለ ጋር ፣ የፈተና ወቅት ጭንቀትን አስመልክቶ ቆይታ አድርገናል።
# ጤናማ የሆነውና ያለሆነው ጭንቀት
# የጭንቀት እውነተኛ ምክኒያት
# የሚታዩና የተደበቁ ምልክተች
# ጤናማና ክረስቲያናዊ ምላሾች...
በእነዚህና መሰል ጉዳዮች ላይ ተጫውተናል።
ተመልከቱት ለምትወዷቸውም አጋሩት።
ለተጨማሪ ተማሪና ክርስቲያን ወጣት ተኮር ጉዳዮች ፣ የMY FELLOW ቤተሰብ መሆንና ይህን የ TBN የዩትዩብ ገፅ ሰብስክራይብ ማድረግ አትዘንጉ።
1 282
የተወደዳችሁ የMy fellow ቤተሰቦች እንዴት ሰነበታችሁ?
የጅግጅጋ ፌሎሺፕን በሰብሳቢነት ያገለገለና የMy Fellowም እንግዳችን በመሆን ቤተኛ የሆነው ወንድማችን ዘማሪ ዮሴፍ አስቻለው (ዕገሌ) ጣፍጥልኝ በሚል የሰየመውን ቁጥር #1 የዝማሬ ሰንዱቅ ይዞልን የመጣ ሲሆን ከአልበሙም ሽያጭ የሚገኘው ገቢ ሙሉ በሙሉ ለሆሳዕና ሙሉ ወንጌል ማምለክያ አዳራሽ ስራ ለቤተክርስትያን ሰጥቶታል።
እኛም በዚህ ሊንክ በመግባት ጣፍጥልኝ የተሰኘውን አልበም በመግዛትና ለሌሎችም ሼር በማድረግ በዝማሬዎቹ እየተባረክን ሸክሙንም በመጋራት አገልግሎቱንም አብረነው እናገለግል።
https://t.me/TaftlignAlbumBot
የተሰጠ!
1 282
Repost from Tesfa Broadcasting Network
+3
ተስፋ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (TBN) እና የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ዘማሪዎችና ሙዚቀኞች ማህበር (EvaSMA) ስትራቴጂካዊ የውል ስምምነት ተፈራረሙ! 🤝🎵📺✨
ግንቦት 20፣2018 ዓ.ም አዲስ አበባ_
ዛሬ ለኢትዮጵያ ወንጌላውያን መዝሙር ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ታሪካዊ ቀን ሆኖ ውሏል! ተስፋ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (TBN) እና የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ዘማሪዎችና ሙዚቀኞች ማህበር (EvaSMA) በመካከላቸው በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስትራቴጂካዊ የመግባቢያ ስምምነት (MoU) በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ትብብር የስርጭት ሚዲያን ሰፊ ተደራሽነት ከኢትዮጵያ ወንጌላውያን ዘማሪዎች፣ ሙዚቀኞችና የዘማሪ መሪዎች መንፈሳዊና ጥበባዊ ክህሎት ጋር የሚያስተሳስር ነው። TBN እና EvaSMA በጋራ በመሆን የወንጌል መዝሙር ዝግጅትን ጥራት ለማሳደግ፣ ክርስቲያን ዘማሪዎችን ለመደገፍ እና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተመልካቾችን የሚያንፁ መንፈሳዊ የአምልኮና የውዳሴ ፕሮግራሞችን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ አልመው እንደሚሰሩም ተገልጿል።
በዛሬው የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ የግሬት ኮሚሽን ሚኒስትሪ ኢትዮጵያ የሚዲያ እና ዲጂታል ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሳምሶን ኡስማኤል እና የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ዘማሪዎችና ሙዚቀኞች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት መጋቢ ሄኖክ አባይ የተሰማቸውን ታላቅ ደስታ የገለጹ ሲሆን፥ ይህ ጥምረት በከፍተኛ ጥራት በተዘጋጁ ሙዚቃዎችና በሚዲያ አማካኝነት ወንጌልን ለብዙዎች ለማድረስ ትልቅ አቅም እንደሚሆን አጽንኦት ሰጥተው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) በይፋ ተፈራርመዋል።
#TBN #EvaSMA #የወንጌልመዝሙር #የኢትዮጵያአምልኮ #የስምምነትውል #ክርስቲያንዘማሪዎች #ኢትዮጵያሚዲያ #አምልኮናሚዲያ
1 282
Repost from Tesfa Broadcasting Network
መዝሙሮቼ አናውቅህም አይሉኝም | ከዘማሪ ደረጄ ሙላቱ ጋር.....ሙሉ ቪዲዮውን በዩትዩብ ገፃችን ያገኙታል
👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/sZlsB7Jhn7w?si=mFMeULZ6SUNPmF7u
Follow tesfa on
Facebook | Tik tok | Telegram | Instagram
1 282
+7
የምስራች፡ ወጣቶች በዲጂታል ወንጌል ስርጭት ዘርፍ ሰለጠኑ! 🚀📱
ግሬት ኮሚሽን ሚኒስትሪ ኢትዮጵያ በ ጋራ ኢኖቬሽን ሀብ (Gara Innovation Hub) ላለፉት አራት ሳምንታት ሲያካሂድ የቆየው የጋራ ሚሽናል ቡት ካምፕ (Gara Missional Bootcamp) በደመቀ ሁኔታ ተጠናቀቀ።
በስልጠናው ወቅት ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት የተውጣጡ ከ70 በላይ ወጣቶች በስድስት ቁልፍ የዲጂታል ዘርፎች ክህሎታቸውን ሲያሳድጉ ቆይተዋል፦
* በቪዲዮ ኤዲቲንግ
* በፎቶግራፊ
* በሞባይል አፕሊኬሽንና ዌብ ዴቨሎፕመንት
* በግራፊክስ ዲዛይን
* በሙዚቃ ቅንብር
ቅዳሜ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በተከናወነው የዕውቅና ፕሮግራም ላይ ሰልጣኞቹ የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለዋል። በዕለቱም የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የወጣቶች ኮሚሽን ተወካዮች እንዲሁም በመላው ዓለም የሚገኙ ክርስቲያኖች በኦንላይን ተገኝተው የደስታው ተካፋይ ሆነዋል።
እነዚህ ሰልጣኞች በቤተክርስቲያናቸውና ባሉበት ስፍራ ሁሉ የዲጂታሉን ዓለም በመጠቀም ወንጌልን ለማሰራጨትና ቤተክርስቲያን የተሰጣትን ታላቁን ተልዕኮ እንድትፈጽም ለማገዝ ሙሉ ዝግጁነታቸውን አሳይተዋል።
እንኳን ደስ አላችሁ! ✨
#GreatCommission #GaraInnovationHub #DigitalMission #YouthEmpowerment #Ethiopia #GaraMissionalBootcamp
1 282
Dear student leaders
You are invited to the Africa SLM Online Multiplying Disciples Gathering. This gathering is bringing together all Multiplying disciples from across Africa.
If you are leading, teaching, mentoring, or disciplining, you can join. Do you have 2 engage disciples in your schools?
#You_can_register_to_be_a_part. Link 👇👇👇👇
https://bit.ly/africamdgathering
Join us on March 13 for the Africa SLM MD Gathering on Zoom
See you there…
@slmethiopia
1 282
ግሬት ኮሚሽን ሚኒስትሪ ኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የወጣቶች ኮሚሽን አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።
የግሬት ኮሚሽን ሚኒስትሪ ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ግርማ አልታዬ እንደተናገሩት፣ ይህ ስምምነት ተቋማዊ ትብብርን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግርና ኃይልን የሚያባዛ ነው።
"ካውንስሉ በኢትዮጵያ የሚገኙ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ጥላ በመሆኑ፣ ከካውንስሉ የወጣቶች ኮሚሽን ጋር በጋራ መስራታችን በአገልግሎት መስኩ ትልቅ ተፅዕኖ እንድንፈጥር ያስችለናል" ብለዋል።
በካውንስሉ የመንፈሳዊ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት ፓስተር ስንሻት ተካ በበኩላቸው፣ አገራችን ባለችበት በዚህ ወሳኝ ወቅት ወጣቱ ትውልድ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ፓስተር ስንሻት ማብራሪያ፣ ሁለቱ ተቋማት በዋናነት በሚከተሉት ሶስት ዘርፎች ላይ በቅንጅት ይሰራሉ፦
ዲጂታልና ሚዲያ፦ በቴክኖሎጂ የታገዘ የወንጌል ስርጭትና በክርስቲያናዊ ስነምግባር የታነጹ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ማፍራት።
ተማሪዎች፦ በትምህርት ተቋማት የሚገኙ ወጣቶችን መድረስ።
ተተኪ ወጣት መሪዎች፦ አዳዲስና ብቁ የሆኑ ወጣት መሪዎችን ማፍራት።
"ግሬት ኮሚሽን ሚኒስትሪ ኢትዮጵያ ቀድሞውኑ በዘርፉ ሰፊ ልምድ ያለውና በአሁኑ ጊዜም በመስኩ ላይ ያለ ተቋም በመሆኑ አብሮ መስራቱ ትልቅ ዕድል ነው" ያሉት ፓስተር ስንሻት፣ የወንጌል አማኝ ወጣቶች ለሚመጣው ታላቅ መከር ልባቸውን እንዲያዘጋጁ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ሙሉ ቪዲዮን በዩትዩብ ገፃችን ያገኙታል
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/Z8luO8fPasU?si=iNZDU3SzdJAubDMa
Follow tesfa on
Facebook | Tik tok | Telegram | Instagram
1 282
Day 1
መጽሐፍ ቅዱሴን እወደዋለሁ፤ የእግዚአብሔርም ሕያው ድምፅ ነውና አነበዋለሁ። ቃሉ ሕያው ነው፤ ዛሬም ይናገራል::
ስለምወደው አነበዋለሁ፤ ስለማነበው ይለውጠኛል።
ሁለት አፍ ያለው ሰይፍ በትክክል እና በኃይል እንደሚቆርጥ፤ መጽሐፍ ቅዱሴን ሳነብ፡ በልቤ ያለን ኩራት ያጠፋልኛል ፥ፍርቴን ያስጥለኛል፥ ሳምናቸው የኖሩኩትን ልክ ያልሆኑ ሀሳቦቼን ያስወግድልኛል፥
ከመታለልም ይጠብቀኛል።
መጽሐፍ ቅዱሴን ስለምወደው መቆረጥን አልፈራም፤ ሲቆርጥ እንደሚፈውስኝ አውቃለሁና።
መጻሕፍ ቅዱሴን ሳነብ፤ ወደ ልቤ ዘልቆ እውነትን ያበራልኛል።
የውስጥ ማንነቴን ያጠናክራል። ነገሮችን ከሰዎች ልደብቅ እችል ይሆናል፤ ከእግዚአብሔር ቃል ግን መደበቅ አልችልም እናም ስለምወደው እንዲያገኘኝ እና እንዲፈውሰኝ እፈቅድለታለሁ።
የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ስለሆነ ጥልቅ የሆኑትን ክፍሎች ማየት የሚችል ነው። በልብዎ ውስጥ ያለውን በትክክል ይገልጣል እና በእግዚአብሔር ፊት በእውነት እንዲኖሩ መፅሐፍ ቅዱሶን እንዲያነቡ ዛሬ እንጋብዞታለን።
ዕብራውያን 4:12 የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤#መጽሐፍ_ቅዱሴን_እወደዋለሁ!
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
