ግጥም
Ir al canal en Telegram
በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post ADMIN 👉 @Big_jor
Mostrar más4 823
Suscriptores
+324 horas
+557 días
+23030 días
Archivo de publicaciones
4 823
በሰው ሀሳብ ቢሆን በምድራዊ ስሜት
መቼ እንኖር ነበር ዛሬንስ ለማየት
እግዚአብሔር ፈቅዶ እንጂ ሰጥቶን ትልቅ ዋጋ
በምቾት ያለነው እንደ ባለጸጋ!!!
ሳይኖረን ያኖረን እኛን ክርስቶስ ነው
እንደኛማ ቢሆን ህይወት አዙሪት ነው
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
✍መልእክቱ✍
ለወትሮው ያለምክንያት ሳንቲም የማያወጣው ሰውዬ አሁን አዲስ የእርዳታ ተቋም ተከፈተ በተባለ ቁጥር እየሄደ እጁ ላይ ያለውን ብር በሙሉ ይሰጣቸዋል። መለገሱ ደግ መሆኑ አልበረም የከነከነኝ በአንድ ግዜ ለጋስ መሆኑ እኮ ነው ያጠራጠረኝ።
"የተፈጠረ ነገር አለ አይደል?" አልኩት ሌላ የእርዳታ ድርጅት እየሄድን "ሰውን ለመርዳት የሆነ ነገር መፈጠር?" አለበት አለ አይኔን እየሸሸ።ይሄኔ የደበቀኝ ነገር እንዳለ እርግጠኛ ሆንኩ። "ንገረኝ ችግር የለውም" አልኩት ምናልባት የሚያናድድኝ ነገር ከሆነ ብዬ "አይ ጥፋት እንኳን አይደለም" አለ ወደ መስኮት ዞሮ አይኖቹ እንባ አቅርረዋል ይሄኔ ልቤ መሸበር ጀመረ።
"ምንድንው ቢኒዬ? እያስጨነከኝ ነው" አልኩት "ሳልነግርሽ ቀኑ ተሸርሽሮ ቢያልቅ ደስ ይለኝ ነበረ... ግን አልቻልኩም... አይኖችሽን እያየሁ በየቀኑ መደበቅ አቃተኝ"
"እንዴ የምን ቀን ነው የሚሸረሸረው?? ምንድነው ያልነገርከኝ?" አልኩት እንባውን ከፊቱ ላይ እየጠረግኩ።
"ግፋ ቢል አምስት ወር ነው የቀረህ ብለውኛል..."
"ለምኑ? ፕሮሰሱ ተሳካ እንዴ?" አልኩት ሰፍ ብዬ
"የጉበት እጢ ነበረህ... እና አሁን ወደ ካንሰር ተቀይሯል ያለህ ጊዜ ከ አምስት እና ስድስት ወር አይበልጥም አሉኝ።" ሰውነቴ ቅዝቅዝ ሲል ተሰማኝ።
እነዛ ፊልም ላይ እንዳሉት፤ ወይ ታሪካቸው እንደሚወራላቸው ሰዎች ጠንካራ አልነበርኩም። ላስታምመው እና የመጨረሻዎቹን ወራቶች በጥሩ ሁኔታ እንዲያሳልፍ አላደረግኩም። ወይ ማድረግ አልሞከርኩም ራሱ።
የዛን ለታ ከተለያየን በኋላ፤ መጀመርያ ቤቴ ገብቼ ማሰብ ጀመርኩ 'እሱስ መሞቱ አይቀርም እኔ ግን እንዴት ነው ሀዘኑን የምችለው ከወዲሁ መለማመድ አለብኝ' አልኩና እሱ የሚያውቀውን ሲም ካርድ አውጥቼ በሌላ ቀየርኩት ከዛ በሳምንቱ ሌላ ሰፈር ሄጄ ተከራየሁ ደብዛዬን አጠፋሁበት። ያው እየፈለገኝ መሆኑ አይቀርም ብዬ ነው።
ህይወት ከቀጠለ፤ ያለሱ መኖርን ከለመድኩት ከብዙ ወራት በኋላ፤ ለስራ ጉዳይ አንድ ፋይል በድሮ ስልክ ቁጥሬ ላኩልኝ እና እሱን ለማየት ሲም ካርዴን መልሼ ስከተው ከሰባት ወራት በፊት የእሱን አርባ ምናምን መልክት ከሀምሳ ሶስት ሚስድ ኮል ጋር አየሁ። አልገረመኝም ይሄንኑ ሽሽት አይደል እንዴ የጠፋሁት። 'ይሄኔ እኮ ሞቶ ይሆናል' አለኝ ጭንቅላቴ። "ነፍስህን በገነት ያኑረው" ብዬ አንሾካሸኩ።
ከዛ ግን አንድ መልእክት ቀልቤን ያዘችው። የተላከው ከሌሎቹ አንፃር በቅርብ ነው። ከሶስት ሳምንት በፊት ይላል መልዕክቱም፦
"አየሽ እንዳንዴ የሰውን እውነተኛ ማንነት ለማወቅ የትንሸ ደቂቃ ትወና በቂ ነበረ። ይገርምሻል ካንሰር አልያዘኝም ። ገና ለገና ሊሞት ነው ብለሽ ግን በአንድ ቀን ትተይኛለሽ ብዬ አላሰብኩም ነበረ። ምናልባት ደንግጣ ይሆናል፤ ራሷን እስክታረጋጋ ነው እያልኩ እስክትደውዪ እስክትመጪ ስጠብቅ ነበረ። አንቺ ግን የራስወዳድነትን ጥግ አሳየሺኝ።
ይሄ ሁሉ ትወና ለምን ካልሺኝ ቀለበት ገዝቼልሽ ነበረ። በኔ ቤት propose ላደርግ እኮ ነው። ከዛ ግን ምን ሹክ እንዳለኝ አላውቅም ያደረኩትን አድርጌ ማንነትሽን አየሁበት። ደግሞ ግምትሽ ትክክል ነበረ ፕሮሰሱ አልቋል ይህን ስፅፍ ሻንጣዬን እያስፈተሽኩ ነው። በይ ደህና ሁኚ" ይላል
ከዛ ብቻ ብዥዥ ሲልብኝ ይታወቀኛል...ስልኬ ከእጄ ላይ ሲወድቅ... የቤቴ ጣራ ሰያፍ ሲንሻፍፍ... የቆሞኩበት ሲከዳኝ ይታወቀኛል... ብቻ ከስብርባሪ ሰከንዶች በኋላ ጉልበቴ ሲከዳኝ.... ተንሸራትቼ ስወድቅ አጠገቤ የነበረው ጠረጴዛ ማጅራቴን ሲመታኝ አንድ ሆነ....እያየሁት ደሜ ፈሰሰ።
✍አበቃ✍
https://t.me/justhoughtsss
4 823
Repost from Niጋስ ኢን ዘ ሁd🥶💀
Imstagram ላይ በወሩ መጨረሻ photo dump እያላቹ ምትላላጡ ወንድሞቻችን: ለወሊድ መከላከያ ደግሞ ክንዳችሁ ስር ሉኘ አስቀብሩ🙂
4 823
#ዛሬም_ካንቺ_ጋር_ነኝ
በትዝታ ፈረስ የኋሊት ተጉዤ
ፍቅርሽን ላስታዉስ ከስሩ መዝዤ
ካፍንጫዬ ሲደርስ የ ፍቅርሽ ሽዉታ
ጆሮዬ ሲገባ ድምጽሽ በሹክሹክታ
ያ ዉብ ኣካላትሽ ከፊቴ ተስሎ
ምላሴ ሲፈታ አነ ጽጌ ብሎ
ኣሁን ግን
ሲወራ ሰማሁኝ የለቺም ተብሎ
አቺን የቀማኝን ባገኘው ምን አለ
እጠይቀው ነበር ምን አንዳስጨከነው
አይቻት ሳልጠግብ ቀስሜያት ሳልረካ የልቤን ላይ ፅጌ ከኔ የነጠለው
እሱ ባይነግረኝም ባይመልስልኝም
ዛሬም ካንቺ ጋር ነኝ ምን ጊዜም ኣልቀርም
ጨረቃን ከሰማይ እመለከትና
በ ጊዮርጊስ ፈረስ ሽቅብ ጋልብና
የዝናቡ ሃይል ዉርጩ ቢያይልብኝ
የሳጥናኤል ጭፍሮች መንገድ ላይ ቢይዙኝ
ከቶ እንዳታስቢ እንዳትጨነቂ
እመጣልሻለው የኔ ተናፋቂ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
#መልካም_ምሽት_አይላቭዪ_React_ምታደርጉ 🫶
4 823
https://t.me/notcoin_bot?start=r_581063_14978408
🎁 +2.5k Notcoin as a first-time gift
🎁🎁🎁 +50k Notcoin if you have Telegram Premium @PremiumBot
4 823
እያረረ ውስጤ ጥርሴ ሲስቅ አይተሽ
ደልቶታል አትበይ እቴዋ ሞኝ ነሽ።
እየተመራሁ ነው በፈንድሻ ዘዴ
ጥርሴ የሚስቀው እያረረ ሆዴ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
#እንባችን_ባልበቃ
የከፋንን ትተን ለመኖር ስንስቅ
መስለን ደስተኛ በተስፋ ስንርቅ
የደላን መስሏቸው ይቀኑ ጀመረ
ችለነው ነው እንጂ ስንት ጉድ ነበረ
እናልቅስ ካልንማ በደረሰብን ልክ
በመከፋት ሚዛን ቢዘረዘር ታሪክ
እንባችን ባልበቃ ብሶት ማስተንፈሻ
እየሸሸግነው ነው በሳቃችን እርሻ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
ወዳጅ መስሎ ቀርቦ አቅፎ ስለሳመህ
ይሁዳን አትርሳው ስራው ትዝ ይበልህ
ስንቱ የዋህ ምስኬን በወዳጅ ጠላቱ
ተስሞ ተሽጧል ፈርሶ አይተናል ቤቱ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
•sᴛᴜᴄᴋ ɪɴ ᴀ ɢᴇɴᴇʀᴀᴛɪᴏɴ ᴡʜᴇʀᴇ ʟᴏᴠᴇ ɪs ᴊᴜsᴛ ᴀ ǫᴜᴏᴛᴇ ᴀɴᴅ ʟʏɪɴɢ ɪs ᴛʜᴇ ɴᴇᴡ ᴛʀᴜᴛʜ°•🚬
https://t.me/OFFICIAL_YANET
4 823
#በማይከፈት_ቤት!!!
ተሻለህ አትበሉኝ ዛሬም ብሶብኛል
ወይ አልሞት አልድንም ስቃይ ያኖረኛል
በሰቀቀን እንባ በሐዘን ዜማ ስልት
ግራ በተጋባ ትርጉም አልባ ቅኝት
ክራሬን ስገርፈው ብሶት እያዜመ
የአምናው በሽታየ ዘንድሮም ከረመ
ግርፉ ሲሰለቸኝ ብደረድረውም ቅኝቱን ቀይሬ
ከተለከፈበት የሗሊት አዙሪት ቆሞ ቀርቷል እግሬ
እንኳንስ መራመድ መንፏቀቅ ብርቁ ነው
በትዝታ አለንጋ በመለየት ጅራፍ የተገረፈ ሰው
ዳዴ ማለት አይችል ግፋ ቢል መንፏቀቅ
በታመነ ልቡ የናፍቆት ከበሮ ቀን በቀን መደለቅ
ክራሬን ስበሩት ድንገት ከተሻለኝ
ዋሽንቱን ሰንጥቁት ሳጣው ከቀለለኝ
በገና ማሲንቆ አደራ እንዳተሰብሩ
ካምላክ እንድታረቅ ይልቅስ ደርድሩ
አምና ዝናብ ጥሎ እህል በቅሎ ነበር
የኔ ልብ ግን ዘርቶ ድርቅ ያጠቃው ፍቅር
ከውስጥ በተዘጋ በማይከፈት ቤት
ለብቻው ነው ዛሬም በስቃይ አዙሪት
ይኸ ሰው ምን ነካው ሲሉ እየሰማሁኝ
ከንፈር እያስመጠጥኩ በህይወት አለሁኝ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
ተናገር ክራሬ የውስጤን በዜማ
ቃላት አይወጣኝም ከንግዲህ እኔማ
ሃዘን ደስታዬን ውስጤን በመረዳት
በቅኝት አስረዳ ወክለህ ንገራት!!!
በአንቺ ሆዬ ባቲ አንባሰል ትዝታ
ይገባታል እርሷ ክራሩ ሲመታ
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
#የማይጠግብ_ዝቆ
ሆድ ከአገር ይሰፋል ይሉት ብሂል ዛሬ
ተረት ብቻ አይደለም እውነት ነው ሀገሬ
ከአንቺ የሚሰፋ ወርዱ ተንቦርቅቆ
ቢበላ ቢበላ የማይጠግብ ዝቆ
ብዙ ሆዳም አለሽ ከሀገር የሰፋ
በትውልድ እድሜ ላይ ቆሞ የሚያንቀላፋ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
በስጋችን ድሎት ነፍስ ተበድላ
ከቆሻሻ ስፍራ በሃጢአት ተጥላ
መነሳት ተስኗት መቆም ከጌታ ፊት
ትርመጠመጣለች ተይዛ በዝሙት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
#ጤናችንን_ነሳን
የተጣደው ሁሉ እያደረ ጥሬ
በስሎ ማይበላ ለምን ነው? ሀገሬ
ይበስላል ስንለው ከመጣዱ ጨሰ
ጣፍጦ ላይበላ ማገዶን ጨረሰ።
ጦምን ላለማደር ጥሬን እየበላን
ምግብነቱ ቀርቶ ጤናችንን ነሳን
ብስል ሲባል ጥሬ ጥሬ ሲባል አሮ
እንዴት ብሎ ይውረድ ጣፍጦ ከጉሮሮ።
እህሉ ሳይጠፋ ሞልቶ ከጎተራ
ባለሙያ ጠፍቶ አረረ በተራ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
ሲከፋው የሰው ልጅ ለምን ሞት ይመኛል?
ድንጋይ ተንከባሎ ደልዳላ ያገኛል
ዛሬ ይሁን ያልኩት ከመሆን ቢጠፋ
ቻል አድርገው ልቤ ተው አትቁረጥ ተስፋ።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
4 823
#እኛ!!!
በጥባጩ በዛና ጠላው ደፈረሰ
ጠርቶ ሳይጠጣ በከንቱ ፈሰሰ
በመናናቅ ዜማ ሙዚቃው ተሰርቶ
አድማጭ እያነሰ ተናጋሪ ሞልቶ
በባቢሎን ሚዛን ሀገር ተለክቶ
ጠጅ ሲሉን ውሃ ውሃ ሲሉን ጠላ
ጤፍ ሲሉን ዘንጋዳ ጮማን በማሽላ
ምድር ሲሉን ሰማይ ሰማይ ሲሉን መሬት
በተቃርኖ መስሚያ በግራው መግባባት
ጥሩ ሲሉን ድፍርስ አልጋ ሲሉን መሬት
በምላስ እስክስታ ተጓዥ ነን በስሜት።
@gitm_post
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
