916
Suscriptores
Sin datos24 horas
+47 días
-430 días
Archivo de publicaciones
ግንቦት 10 /2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አስመልክቶ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው!!
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ለሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወረዳው መሀልአምባ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው ።
"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር "በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሔደ ባለው የድጋፍ ሰልፍ ያለፉት ስምንት የለውጥ አመታት ስኬቶችን የሚዘክሩና የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክቶች እየተስተጋቡ ይገኛል።
በድጋፍ ሰልፉ ምርጫዬ ብልጽግና ነው፣ትላንትን ማከም ነገን መተለም፣የጸና ሰላም የተቃና ስርዓት፣ከገጠር የተሰናሰለ ከተሜነት እና ሌሎችም መፈክሮች ተስተጋብተዋል።
በድጋፍ ሰልፉ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙና የዞኑ አስተባባሪዎች፣ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ጨምሮ፣የክልል የዞን ፣የወረዳና ፓርቲውን ወክለው በምርጫ ክልል የሚወዳደሩ እጩዎች ፣የፓርቲው አባላት፣ደጋፊዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ግንቦት 10 /2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አስመልክቶ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው!!
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ለሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወረዳው መሀልአምባ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው ።
"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር "በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሔደ ባለው የድጋፍ ሰልፍ ያለፉት ስምንት የለውጥ አመታት ስኬቶችን የሚዘክሩና የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክቶች እየተስተጋቡ ይገኛል።
በድጋፍ ሰልፉ ምርጫዬ ብልጽግና ነው፣ትላንትን ማከም ነገን መተለም፣የጸና ሰላም የተቃና ስርዓት፣ከገጠር የተሰናሰለ ከተሜነት እና ሌሎችም መፈክሮች ተስተጋብተዋል።
በድጋፍ ሰልፉ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙና የዞኑ አስተባባሪዎች፣ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ጨምሮ፣የክልል የዞን ፣የወረዳና ፓርቲውን ወክለው በምርጫ ክልል የሚወዳደሩ እጩዎች ፣የፓርቲው አባላት፣ደጋፊዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ አማካኝነት በተለያዩ ቀበሌዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትና እጩ የማስተዋወቅ ውይይት መድረክ ተካሄዷል።
ግንቦት 7/2018 ዓም (መሀል አምባ)
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ አማካኝነት በተለያዩ ቀበሌዎች የይምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ምልክት እጩ የማስተዋወቅ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በውይይቱ ባለፉት የለውጥ አመታት የተገኙ ስኬቶች ና የብልፅግና ፓርቲ የቀጣይ ትልሞች የማስገንዘብ ስራ በመስራት 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ሰላማዊ ዲሞክራሲያዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በማድረግ ሁሉም የበኩሉ እንደሚወጣ ገልጿል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፓርቲ በጉራጌ በአበዘት ክላስተር ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደርበት ምልክት ማኒፌስቶና እጩዎችን የማስተዋወቅና የይምረጡኝ የቅስቀሳ ስራ በፎቶ በከፊሉ:-
ግንቦት 05/2018 ዓ/ም
"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል የብልፅግና ፓርቲ ማኑፌስቶ ፣ የመወዳደርያ ምልክት እና እጩ ትውውቅ እንዲሁም ይፋዊ ቅስቀሳ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በኢንጌ ከተማ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
“ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል፣ በዛሬው ዕለት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በኢንጌ ካችመነት የሚገኙ ቀበሌዎች ታላቅ ይፋዊ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ በደማቅ ሁኔታ ተካሄዷል።
በዚህ ይፋዊ የይምረጡን ቅስቀሳ ላይ ከክልል፣ ከዞንና ከወረዳ የተውጣጡ ከፍተኛ የፓርቲ አመራሮች፣የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ እጩዎች፣የፓርቲው አባላት እንዲሁም የኢንጌ አገልግሌት ነዋሪዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች በነቂስ በመውጣት ለፓርቲው ያላቸውን ጽኑ አጋርነት ገልጸዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች "ብልፅግናን መምረጥ ልማትንና አብሮነትን መምረጥ ነው”የሚሉና ሀገራዊ አንድነት፣ ልማት፣ ሰላምና የዴሞክራሲ ሂደት እንዲጠናከር የሚጠይቁ መልዕክቶችን የያዙ ፅሁፎችና መፈክሮችን አሰምተዋል።
በመድረኩ የተገኙ አመራሮች እና የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ እጩዎች በንግግራቸው፣ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋገር የሁሉም ዜጎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ህዝቡ በመጪው ምርጫ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት ሀገሪቱ በበርካታ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ፈተናዎች ውስጥ ብታልፍም፣ በግብርናውና በታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ረገድ አመርቂ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
ለቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ትኩረታችን የጀመርናቸውን የልማት ስራዎች በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ማምጣት ነው" ብለዋል።
በሁሉም ዘርፎች የሚታየውን እድገት በማስቀጠል የኢትዮጵያን ብልፅግና እውን ለማድረግ ህዝቡ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፓርቲው ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
ዛሬ የተካሄደው የቅስቀሳ መርሃ ግብር የብልፅግና ጉዞ የማይገታ መሆኑን ያሳየና ለቀጣዩ ምርጫ ትልቅ መነቃቃትን የፈጠረ እና የአባላቱንና የህዝቡን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ከመሆኑም ባለፈ፣ በቀጣይ ለሚከናወኑ የልማትና የፖለቲካ ስራዎች ትልቅ የሞራል ስንቅ የሚሆን መሆኑ ተመላክቷል።
የሳምንቱ ዓብይት ዜናዎች
ሚያዝያ 25/2018 ዓ.ም
🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የማኒፈስቶ፣ የምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ እና የይምረጡኝ ቅስቀሳ ፕሮግራም ከመሀል አምባ ወጣቶች ጋር የውይይት መድረክ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የብልጽግናን ፓርቲ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክት ማስተዋወቂያና የይምረጡኝ ቅስቀሳ ከየቀበሌው ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ጋር የውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በበጀት አፈጻጸም ዙሪያ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤትገለጸ፡፡
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶች ይበልጥ እንዲጎለብቱና በቀጣይ የተቀመጡ ታላላቅ አገራዊ ግቦች ከግብ እንዲደርሱ የሴቶች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በተገኘ ድጋፍ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደነብ ቀበሌ ነፍሰ-ጡርና አጥቢ እናቶች እንዲሁም የስርዓተ ምግብ ጉድለት ላለባቸው ህፃናት 50 ፍየል ድጋፍ ተደረገላቸው።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በ3ኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻንፒዮና ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ 🆚 ሚቶ ወረዳ ተጨወተ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
