917
Підписники
+124 години
+57 днів
-330 днів
Архів дописів
ከአዲስ አበባ ወደ ጉራጌ ዞን የኢደል-ዓድሃ የአረፋ በዓል ለማክበር ለምትመጡ እንግዶች በአዲስ አበባ አማራጭ የባስ የትራንስፖርት አገልግሎት እንድታገኙ የጉራጌ ዞን አስተዳደር ከፌደራል ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፦
በዚህም መሰረት ከግንቦት 16 /2018 ጀምሮ
በአዲስ አበባ ባሶች የሚገኙበት ቦታዎች
#በአየር ጤና
#በሉካንዳ
#በየሺ ደበሌ
#በካራቆሬ
#በቄራ
#በጀሞ
#በቤተል
#በአለም ባንክ
#በዘነበወርቅ
#በሎሚ ሜዳ
#በላምበረትና በሁለቱ መናሀሪያዎች ከግንቦት 16/2018 ዓመተ ምህረት ጀምሮ አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናል።
ለጉራጌ ዞን ለአረፋ በዓል ተጓዦች በሙሉ
ከአዲስ አበባ መነሻና የጉራጌ ዞን ወረዳዎች መድረሻ ፣
ያደረገ የትራንስፖርት አገልግሎት የታሪፍ መጠን ይፋ የተደረገ ሲሆን ለሚፈጠሩ ቅሬታዎች ስልክ ቁጥሮች ተያይዘዋል።
መረጃው የጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ነው!!!
ግንቦት 11/2018 ዓ.ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ
7ተኛውን ጠቅላላ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ አስመልክቶ
በአረዳ ክላስተር ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደርበት ምልክት ማኒፌስቶና እጩዎችን የማስተዋወቅ እንዲሁም ይፋዊ የይምረጡኝ የቅስቀሳ
ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ በአረዳ ክላስተር በኮኪር ምርጫ ክልል የሚወዳደሩ እጩዎቹ የምርጫ ምልክትና ማኒፌስቶ ለህዝብ የማስተዋወቅ መርሐ-ግብር በዛሬው እለት አካሂዷል።
በዚህ የይምረጡኝ የቅስቀሳ መድረክ የማዕከላዊ ኢትዮጰያ ክልል መሬት አስተዳደር ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ አብድልሀፊዝ ሁሴን፣ የጉራጌ ዞን ዋና አፈጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣ የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ነጅብያ ማህሙድ፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣ የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፈትያ መህዲን ጨምሮ የዞንና የወረዳ የስራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
በዝርዝር ዜና እንመለሳለን።
ግንቦት 10/2018 ዓ.ም
በመደመር እሳቤ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር የማድረስ ራዕያችንን ለማሳካት በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በተግባር ማሳየት ይኖርብናል፦ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና 7ኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መሀል አምባ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።
በመድረኩ የተገኙት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ እንደገለጹት፣ የኢኮኖሚ ሪፎርሙና የብልጽግና ጉዞ የዜጎችን ተጠቃሚነት ማዕከል ያደረገ ሲሆን፣ በዞኑ በተለይም በትምህርት፣ በግብርና፣ በጤና፣ በውሃና በመንገድ ልማት ዘርፎች በርካታ ውጤቶች ተመዝግበዋል።
አክለውም በባህልና ቋንቋ፣ በከተሞች ልማት፣ በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ፣ በገቢ ማሻሻያና በሌሎችም አበረታች የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በግብርና ዘርፍ ከ100 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ወደ እርሻ በማስገባት ከ5 ሚሊየን ኩንታል በላይ ተጨማሪ ምርት መገኘቱን ጠቁመዋል።
እንዲሁም የጉራጊኛ ቋንቋ የትምህርት፣ የስራና የሚዲያ ቋንቋ እንዲሆን የተሰሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸው፣ ከ96 ሺህ በላይ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እየተማሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
በትምህርት ልማት ላይ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ሰፊ ስራዎች መከናወናቸውንና አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን ገልጸዋል።
በተጨማሪም በንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ላይ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ከ208 ሺህ በላይ ህዝብ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆኑን አስገንዝበዋል።
እንደ አቶ ላጫ ጋሩማ ገለጻ፣ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ 1 ሺህ 213 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገዶች ተሰርተዋል።
በዞኑ የተከናወኑ የልማት ስራዎች የዜጎችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት በማሳደግ ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ እያሸጋገሯት መሆናቸውን ገልጸዋል አቶ ላጫ ጋሩማ።
“በመደመር እሳቤ ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር የማድረስ ራዕያችንን ለማሳካት በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በተግባር ማሳየት ይኖርብናል” ሲሉም መልእክት አስተላልፈዋል።
በመድረኩ የተገኙት የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ እና የፓርቲው የኮኪር ምርጫ ክልል የፓርላማ ተወካይ ወ/ሮ ነጅሚያ መሀመድ በበኩላቸው፣ ብልጽግና ፓርቲ ካለፉት ልምዶች መልካሙን ወስዶ፣ የጎደለውን በማሟላትና ስህተቶችን በማረም ለህዝብ ጥቅምና ለሀገር ለውጥ የሚተጋ ፓርቲ መሆኑን ገልጸዋል።
ግንቦት 24 የነገዋን ውብና የበለጸገች ኢትዮጵያ ለመገንባት ቃል ኪዳናችንን የምናረጋግጥበትና ድጋፋችንን በተግባር የምናሳይበት ቀን በመሆኑ ሁሉም በእለቱ ወጥቶ ድምጹን እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።
ፓርቲው ትውልድ ተሻጋሪ ስራዎችን በማከናወን ከሀገር አልፎ በዓለም ደረጃ የሚታወቁ ስራዎችን በመስራት የኢትዮጵያን ገናናነት ማስመስከሩን ጠቁመዋል።
በመሆኑም እነዚህ አበረታች የለውጥ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና ኢትዮጵያ ተምሳሌት ሀገር እንድትሆን በመደመር እሳቤ ምርጫውን ማሳካት የሁሉንም ዜጋ ትብብርና ርብርብ እንደሚጠይቅ ገልጸዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን እንደገለጹት፣ በወረዳው የመንግስት፣ የባለሀብቶች፣ የተራዶ እና የበጎ አድራጊ ድርጅቶችን አቅም በማቀናጀት አመርቂ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል።
በተለይም በመንገድ፣ በመብራት፣ በትምህርት፣ በንጹህ መጠጥ ውሃና በጤና ዘርፍ ፕሮጀክቶች በመገንባትና በማስመረቅ የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መቻሉን ገልጸዋል።
ከዚህ በፊት በወረዳው አንድ ማዘጋጃ ቤት ብቻ ከነበረው አሁን ወደ 6 ማዘጋጃ ቤቶች ማደጉን የገለጹት አቶ ሚፍታ፣ ከተሞቹ ለኑሮ አመቺና ሳቢ እንዲሆኑ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
አክለውም በግብርና፣ በባህልና ቋንቋ፣ በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ፣ በሰላምና ጸጥታ እንዲሁም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፎች አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አብራርተዋል።
ግንቦት 10 /2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አስመልክቶ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው!!
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ለሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወረዳው መሀልአምባ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው ።
"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር "በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሔደ ባለው የድጋፍ ሰልፍ ያለፉት ስምንት የለውጥ አመታት ስኬቶችን የሚዘክሩና የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክቶች እየተስተጋቡ ይገኛል።
በድጋፍ ሰልፉ ምርጫዬ ብልጽግና ነው፣ትላንትን ማከም ነገን መተለም፣የጸና ሰላም የተቃና ስርዓት፣ከገጠር የተሰናሰለ ከተሜነት እና ሌሎችም መፈክሮች ተስተጋብተዋል።
በድጋፍ ሰልፉ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙና የዞኑ አስተባባሪዎች፣ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ጨምሮ፣የክልል የዞን ፣የወረዳና ፓርቲውን ወክለው በምርጫ ክልል የሚወዳደሩ እጩዎች ፣የፓርቲው አባላት፣ደጋፊዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ግንቦት 10 /2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ አስመልክቶ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው!!
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት እና ለሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በማስመልከት በወረዳው መሀልአምባ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው ።
"ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር "በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሔደ ባለው የድጋፍ ሰልፍ ያለፉት ስምንት የለውጥ አመታት ስኬቶችን የሚዘክሩና የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክቶች እየተስተጋቡ ይገኛል።
በድጋፍ ሰልፉ ምርጫዬ ብልጽግና ነው፣ትላንትን ማከም ነገን መተለም፣የጸና ሰላም የተቃና ስርዓት፣ከገጠር የተሰናሰለ ከተሜነት እና ሌሎችም መፈክሮች ተስተጋብተዋል።
በድጋፍ ሰልፉ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ኸይሩ መሀመድ፣የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙና የዞኑ አስተባባሪዎች፣ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ጨምሮ፣የክልል የዞን ፣የወረዳና ፓርቲውን ወክለው በምርጫ ክልል የሚወዳደሩ እጩዎች ፣የፓርቲው አባላት፣ደጋፊዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ አማካኝነት በተለያዩ ቀበሌዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትና እጩ የማስተዋወቅ ውይይት መድረክ ተካሄዷል።
ግንቦት 7/2018 ዓም (መሀል አምባ)
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ አማካኝነት በተለያዩ ቀበሌዎች የይምረጡኝ ቅስቀሳና የምርጫ ምልክት እጩ የማስተዋወቅ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በውይይቱ ባለፉት የለውጥ አመታት የተገኙ ስኬቶች ና የብልፅግና ፓርቲ የቀጣይ ትልሞች የማስገንዘብ ስራ በመስራት 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ሰላማዊ ዲሞክራሲያዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በማድረግ ሁሉም የበኩሉ እንደሚወጣ ገልጿል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፓርቲ በጉራጌ በአበዘት ክላስተር ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚወዳደርበት ምልክት ማኒፌስቶና እጩዎችን የማስተዋወቅና የይምረጡኝ የቅስቀሳ ስራ በፎቶ በከፊሉ:-
