916
Suscriptores
Sin datos24 horas
+47 días
-430 días
Archivo de publicaciones
ግንቦት 01/2018 ዓ/ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የማኒፈስቶ፣ የምርጫ ምልክት የማስተዋወቅ እና የይምረጡኝ ቅስቀሳ ፕሮግራም ከመሀል አምባ ወጣቶች ጋር የውይይት መድረክ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የወረዳው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተማም አደም ለመድረኩ የተዘጋጃ መወያያ ሰነድ አቅርበዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደሪ እና የወረደው የክልል ምክር ቤት እጩ አቶ ሚፋታ ሁሴን በመድረኩ እንደተናገሩት የስንዴ ነዶ በጥምር የተቀናጀ ህብረትንና አንድነት ማሳያ በመሆኑ ወጣቶችም በህብረትና በአንድነት ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሻገር ተቀናጅታችሁ የብልፅግና ልዕልናን ለመጨበጥ እናንተም የምርጫ ምልክታችን የስንዴ ነዶ መሆኑን አውቃችሁ ብልፅግና መምረጥ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
አቶ ሚፋታ አክለውም ወጣቶችን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ማምጣታቸውን ጠቀሰው እነዚህ ተግባራት ቀጣይነት እንዲኖራቸው ብልጽግናን መምረጥ አማራጭ የሌለው መንገድ መሆኑን ተናግረዋል።
የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ኃላፊ እና የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ የፓርላማ እጩ ወይዘሮ ነጅብያ ማህሙድ በበኩላቸው ወጣቶች የዛሬ የሀገር ባለቤትና የነገ ተረካቢ በመሆናቸው ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሻገር በሚደረገው ጉዞ ሚናቸው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸው ወጣቶች በማህበራዊ ሚዲያ የጥላቻ ንግግሮች አካባቢን በማጠልሸት ከእውነት የራቁ መረጃዎችን በመታገል እንዲታረሙ በማድረግ በመተባበርና የአንድነት ምልክት የሆነውን
የምርጫ ምልክታችን የስንዴ ነዶ በመሆኑ ብልጽግና ፓርቲን እንዲመርጡ መልእክት አስተላልፈዋል።
የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙራድ ረሻድ የፓርቲው ዓላማ ምርጫውን ሙሉ በሙሉ ሠላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ታኣማኒነት ያለው ሆኖ ለማሸነፍ መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው ወጣቶች በትጋት እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ወጣቶች ለኢትዮጵያ ብልፅግና በጋራ የምንሰራበት ወደ ተምሳሌት ሀገር የሚናሸጋግርበት ወቅት በመሆኑ በአካባቢያችን የሠላም ተምሳሌት በመሆን አባሎቻችን ብልፅግናን እንዲመርጡ ወጣቱ ትልቁን ድርሻ እንድትወስዱ በማለት አቶ ሙራድ ረሻድ ጥሪ አቅርበዋል።
የመድረኩ ተሳታፊ ወጣቶች በበኩላቸው እንደ ሀገር ፣በወረዳ ደረጃ እንዲሁም በመሀል አምባ ከተማ ላይ የተጀመረው ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማስቀጠል ምርጫን ብልጽግና በማድረግ ምርጫው ሠላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የበኩላቸውን እንደሚወጡ አስገንዝበዋል።
ሚያዚያ 27/2018 ዓ/ም
ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶች ይበልጥ እንዲጎለብቱና በቀጣይ የተቀመጡ ታላላቅ አገራዊ ግቦች ከግብ እንዲደርሱ የሴቶች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተገለጸው "ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር" በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የሴቶች ክንፍ የብልጽግናን ፓርቲ የምርጫ መወዳደሪያ ምልክትና ማኒፌስቶ ማስተዋወቂያ መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው።
በመድረኩ ላይ ላለፉት አምስት ዓመታት በብልጽግና ፓርቲ መሪነት የተከናወኑ ስኬቶችና በቀጣይ የሚሠሩ ታላላቅ ግቦች ላይ ትኩረት ያደረገ የመወያያ ሰነድ የወረዳው ሴቶችና ህጻናት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፈትያ መህዲ አማክኝነት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን በመድረኩ ተገኝተው እንደገለጹት ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገርነት ለማሻገር የሴቶች ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በሀገር አቀፍና በወረዳ ደረጃ የተከናወኑ የልማት ተግባራት ተጨባጭ ስኬቶችን እያስመዘገቡ መሆኑንም ገልጸዋል።
ዋና አስተዳዳሪው አክለውም ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶች ይበልጥ እንዲጎለብቱና በቀጣይ የተቀመጡ ታላላቅ አገራዊ ግቦች ከግብ እንዲደርሱ የሴቶች ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ኃላፊ እና የወረዳው የፓርላማ እጩ የሆኑት ወ/ሮ ነጅብያ ማህሙድ በበኩላቸው ብልፅግና ፓርቲ ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር በመፈፀም ለቃሉ የታመነ እና በስራው ውጤታማነት በተጨባጭ ያስመሰከረ ፓርቲ መሆኑን ገልፀዋል።
ብልጽግና ፓርቲ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸው የልማትና የዴሞክራሲ ግንባታ ስራዎች ውጤታማ እንዲሆን የአብሮነት፣ የጥንካሬ እና የአንድነት መገለጫ የሆነውን "የስንዴ ነዶ" በሁሉም አካባቢ እንዲመረጥ ሴቶች ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ወ/ሮ ነጅብያ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ፓርቲያችን ያስቀመጣቸውን የብልጽግና ግቦች ለማሳካት በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸው የተጀመረው የብልፅግና ጉዞ ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የስንዴ ነዶን መምረጥ እንደሚገባ አስታውቀዋል።
ሚያዚያ 26/2018 ዓ/ም
በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በተገኘ ድጋፍ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደነብ ቀበሌ ነፍሰ-ጡርና አጥቢ እናቶች እንዲሁም የስርዓተ ምግብ ጉድለት ላለባቸው ህፃናት 50 ፍየል ድጋፍ በዛሬው እለት ተደረገላቸው።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም አማካኝነት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ በደነብ ቀበሌ በተመረጡ ሞዴል መንደሮች በአራት መቶ ሺህ ብር በጀት በመመደብ
ለ50 እናቶች ለእያንዳዳቸወ 1 ሴት ፍየል በድምሩ 50 ፍየል ተሰራጭቷል።
ሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም መቀንጨርንና መቀጨጭን በማስቀረት ጤናማ እና አምራች ዜጋን ለመፍጠር እየሰራ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
ሴት ፍየሎች የተሰጡበት ዋና አላማ የፍየል ወተት ስርዓተ ምግብን ለማሟላት ከላም ወተት የተሻለ ንጥረ ነገር በመያዙ ሲሆን ፍየሎችን በአግባቡ በመያዝ ወተታቸው ከሁለት አመት በታች ላሉ ህፃናትና አጥቢ እናቶች መጠቀም እንዳለባቸው ስልጠና ተሰጥቷል።
መረጃው የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ነው።
ሚያዚያ 25/2018 ዓ/ም
በ3ኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻንፒዮና ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ
🆚 ሚቶ ወረዳ በነገው እለት ይካሄዳል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በ3ኛው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻንፒዮና ላይ በሃላባ ቁሊቶ ከተማ እየተሳተፈ የሚገኘው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሁለተኛ የምድብ ጫወታውን ከሚቶ ወረዳ ጋር ያካሂዳል።
በነገው የጨዋታ መርሐ ግብር የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ 🆚 ከሚቶ ወረዳ ሰኞ ሚያዚያ 26/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ያካሄዷሉ።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እግር ኳስ ቡድን መልካም ውጤት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን!!!
የጫወታውን ትክክለኛ ውጤት ለሚገምቱ የፔጃችን የመጀመሪያዎቹ 5 ተከታዮች ባለ 100 ብር የሞባይል ካርድ እንሸልማለን!!!
የሳምንቱ ዓብይት ዜናዎች
ሚያዝያ 25/2018 ዓ.ም
🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤትባለፉት 5 ዓመታት የወረዳውን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ማከናወኑን ገልጿል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 የመንግስት በጀት በአግባቡ በመጠቀም፣ በመቆጣጠርና በመከታተል በጀቱ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በማድረግ የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ እግር ኳስ ቡድን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ለመሳተፍ ወደ ሀላባ ቁሊቱ ከተማ ሽኝት ተደረገላቸው።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጅማ ወለኔ ከተማ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የብልፅግና ፓርቲን በጎዳና ላይ ቅስቀሳ መረሀ ግብር ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በተገኘ ድጋፍ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የጎምራ ቀበሌ ነፍሰ-ጡርና አጥቢ እናቶች እንዲሁም የስርዓተ ምግብ ጉድለት ላለባቸው ህፃናት 50 ፍየል ድጋፍ ተደረገላቸው።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 አካል ጉዳተኞችን እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች በመደገፍ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ ባለድርሻ አካላት ሊያግዙ እንደሚገባ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሚሆኑ የጎምራ ቀበሌ ነፍሰ-ጡርና አጥቢ እናቶች እንዲሁም የስርዓተ ምግብ ጉድለት ላለባቸው ህፃናት 500 ዶሮ ድጋፍ ተደረገላቸው።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 ባለፉት አምስት የለውጥ ዓመታት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፎች ለተመዘገቡ ስኬቶች የወጣቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የአፋልጉኝ ማስታወቂያ
ከታች በፎቶው ላይ የምትመለከቱት ወጣት አብድልጀሊል ሳኒ ሀሰን(ደምስስ) የተባለው ወንድማችን ውልደቱ እና እድገቱ ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጥላሞ ቀበሌ መሃልምባ ዙሪያ (ደቄኖ) አካባቢ ሲሆን ለስራ ብሎ ወደ አዲስ አበባ ከሄደ በኀላ 2012 ዓ.ል ጀምሮ ከቤተሰው ጋር የነበረው የስልክም ሆነ የአካል ግንኙነት ተቋርጧል፡፡
ስለሆነም ይህንን ወንድማችን ያያችሁት ወገኖቻችን በሚከተለው አድራሻ ብታሳውቁን ስንል በአክብሮት እንጠይቃል፡፡ ቤተሰቦቹ(አብድል ፈታ ሳኒ)
0920124564
0938081547
መረጃውን ሼር በማድረግ እንተባበር!!!
