1 076
Suscriptores
+224 horas
+37 días
+230 días
Archivo de publicaciones
በተዘጋጁ የቴክኖሎጂ እሴት ሰንሰለት ትንተናዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና ለድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ አመራሮችና ሰራተኞችና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከትኩረት ዘርፍ መ/ቤት ከተውጣጡ ባለሞያዎች እና የኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የእሴት ሰንሰለት ትንተና አዘገጃጀት ላይ ከዚህ በፊት በተሰጣቸው ስልጠና መሰረት የተዘጋጁ ስድስት ሰነዶች ቀርበው ገለጻ ተደርጎባቸዋል፡፡
ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ተልዕኮዎች ውስጥ አንዱ ተወዳዳሪነትን የሚያረጋግጥ አዋጭ ቴክኖሎጂ ለኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መሆኑ ይታወቃል በዚህም የምርት ወይም የአገልግሎት የአመራት ሂደት በመተንተን ክፍተቶችን በመለየት እና ለክፍተቶቹም የቴክኖሎጂዎችን መፍትሄ ለማስቀመጥ የእሴት ሰንሰለት ትንተና ሰነዶች ተዘጋጅተዋል፡፡
በመሆኑም የቢሮው አመራሮችና ባለሙያዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸውና በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ሙያዊ አስተያየት እንዲሰጥበት በማድረግ ሰነዱን በማዳበርና በማስተዋወቅ በሚለዩት ቴክኖሎጂዎች የኢንተርፕራይዞችን፣ የተቋማትን እና የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነትና ተወዳዳሪነት በመጨመር ለበርካታ ዜጎች የሥራ-ዕድል ለመፍጠር ታሳቢ ያደረገ መሆኑን በኤጀንሲው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 2/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+1
የገና በዓል ፍቅርን፣ አንድነትን፣ መተሳሰብን፣ የአብሮነት እሴቶችን በተግባር የምናሳይበት ነው በማለት እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሠላም አደረሳችሁ በማለት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ገልጸዋል።
የቢሮ ኃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው ለመላው ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸው የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው በልዩ መንፈሳዊ ሥነ ስርዓት የሚከበር ክብረ በዓል ነው በማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች የማያልቅና ፍጹም የሆነ ፍቅርን፣ አንድነትን መረዳዳትን እና መደጋገፍን እንዳስተማረን ሁሉ ህዝበ ምዕመናን በዓሉን ሲያከብሩ አቅመ ደካማ ወገኖቻችንን በማሰብ፤ ያለንን በማጋራትና የአብሮነት እሴቶቻችን በተግባር በማሳየት ሊሆን ይገባል ሲሉ አቶ ሮቤል ገልጸዋል።
በዓሉ የፍቅር እና የአንድነት በመሆኑ ምዕመኑ በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው ኢየሱስ ክርሰቶስ ያሳየውን ተምሳሌትነት ሊተገብር ይገባል በማለት በዓሉ የብልጽግና፣ የደስታ፣ የፍቅር፣ የሠላምና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን የቢሮ ኃላፊው ገልጸዋል።
መልካም የገና በዓል!
የገና በዓል ፍቅርን፣ አንድነትን፣ መተሳሰብን፣ የአብሮነት እሴቶችን በተግባር የምናሳይበት ነው በማለት እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሠላም አደረሳችሁ በማለት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ገልጸዋል።
የቢሮ ኃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው ለመላው ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸው የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ልዩ ቦታ ያለው በልዩ መንፈሳዊ ሥነ ስርዓት የሚከበር ክብረ በዓል ነው በማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች የማያልቅና ፍጹም የሆነ ፍቅርን፣ አንድነትን መረዳዳትን እና መደጋገፍን እንዳስተማረን ሁሉ ህዝበ ምዕመናን በዓሉን ሲያከብሩ አቅመ ደካማ ወገኖቻችንን በማሰብ፤ ያለንን በማጋራትና የአብሮነት እሴቶቻችን በተግባር በማሳየት ሊሆን ይገባል ሲሉ አቶ ሮቤል ገልጸዋል።
በዓሉ የፍቅር እና የአንድነት በመሆኑ ምዕመኑ በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው ኢየሱስ ክርሰቶስ ያሳየውን ተምሳሌትነት ሊተገብር ይገባል በማለት በዓሉ የብልጽግና፣ የደስታ፣ የፍቅር፣ የሠላምና የአንድነት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
መልካም የገና በዓል!
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በአጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች እና " ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ትግበራ የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ስድስት ወራት አተገባበርን በተመለከተ ከወረዳ አንድ ማዕከል አመራሮች እና ባለሞያዎች ጋር የውይይት እና የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አካሄደ፡፡
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ለዜጎች የሥራ ዕድልን ለመፍጠር አሁን ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር በተጨባጭ ለመቀነስና የሥራ ባህልን በማጎልበት የሚያስፈልጓቸውን የክህሎት ስልጠናዎች በመውሰድ ወደ ሥራ እንዲሰማሩ በማመቻቸትና ራሳቸውን ከሥራ አጥነት እንዲያላቀቁ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ሰው ተኮር የሆነ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
በዚህም በ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ስድስት ወራት በአጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራ የተከናወኑ ተግባራትን የሚመለከታቸው የቢሮው አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳ ሥራ ክህሎት ማስተባበሪያዎች በተገኙበት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎባቸዋል በተያያዘ " የብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ትግበራ የወጣቶች በኢንደስትሪዎች ላይ ባለፉት ስድስት ወራት የነበረውን የሥራ ላይ ልምምድ የተሰሩ ሥራዎች አፈጻጸም ላይ ሁሉም የወረዳ አንድ ማዕከላት አፈጻጸማቸው ቀርቦ ሰፊ ውይይት በማድረግ በቀጣይ መሠራት በሚገባቸው ሥራዎች ላይ መወያየት ተችሏል፡፡
በመድረኩም ላይ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተገኝተው በቢሮ እና በአንድ ማዕከላቱ መናበብ ለተሰሩ አበረታች ሥራዎች ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይ ስድስት ወራት የተከናወነውን ውጤታማ ሥራ ወጥነት ባለው የዕቅድና ሪፖርት መናበብ አጠንክሮ በማስቀጠል ምንያህል የሥራ ዕድል መፍጠር ችለናል የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ መሆኑን ማረጋገጥ እና ከብድር ምችችት ጋር በተያያዘ ከአሰጣጥና አመላለስ ጋር ያሉ ጉዳዮችን በማጥራት ኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚ ማድረግና ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመስራት ውጤት ለማምጣት ሁሉም ተረባርቦ ሊሰራ እንደሚገባው አሳስበዋል።
በማጠቃለያውም ለአራት አንድ ማዕከላት አዲስ የLMIS መመዝገቢያ ባዮሜትሪክስ ኪት ርክክብ የተደረገ ሲሆን በአጠቃላይ አስር መመዝገቢያ ባዮሜትሪክስ ኪት ለአንድ ማዕከላቱ ተደራሽ መደረጉ ታውቋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 26/2017 ዓ.ም
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት ለኮሌጁ አስተዳደር ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው የሁለተኛ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከድሬዳዋ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት በገባው ውል መሰረት ለ2ኛ ዙር ለኮሌጁ የአስተዳደር ሰራተኞች ለ5 ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል::
የአቅም ግንባታ ስልጠናው በEASE(Education and Skills for Employ Ability) ፕሮጀክት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን ይህ ስልጠናም በኢንስቲትዩቱ አሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየና በአገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት እና በስራ ሥነ-ምግባር ላይ ያተኮረ ስልጠናም ነበር::
የስልጠናው ዋነኛ አላማ የኮሌጁ የአስተዳደር ሰራተኞች የተለያዩ የስራ ላይ ስልጠናዎችን አግኝተው አቅማቸውን እንዲገነቡና በተመደቡበት የስራ ዘርፍ የተሻለ አገልግሎት በመስጠት ለተቋሙ ራዕይና ስኬት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ለማስቻል መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም ለስልጠናው ውጤታማነት የድሬዳዋ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት እያደረገ ላለው ትብብርም ምስጋና አቅርበዋል።
በ2ኛ ዙር ስልጠናው ማጠቃለያ መርሀ-ግብር ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይር ሀጂኑር አንደገለፁት ቢሮው ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አንዱ በአስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች እና አመራሮችን በተለያዩ ስልጠናዎች አቅማቸውን መገንባት እንደሆነ ጠቅሰው ለዚህም ኮሌጁ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በጋራ ለመስራት ውል ተፈራርሞ ወደ ትግበራ በመግባቱ አመስግነው ሰልጣኞችም የወሰዳችሁት ስልጠና በስራ ገበታቸው ላይ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል::
ኮሌጁ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ሲያደግና የተሰጠውን Resource ተፈፃሚ ለማድረግ አጠቃላይ የኮሌጁን ሰራተኛ ባስተፈ መልኩ በመሆኑ በEASE ፕሮጀክትም ቅድሚያ ትኩረት የተሰጠው ተግባር የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ለሰራተኛው መስጠት እንደሆነ የገለፁት የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ፋሲል ማዘንጊያ አክለውም በቀጣይ በዝርዝር የተለዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በተያዘላቸው መርሃ-ግብር ለሰራተኛው የሚሰጡ ይሆናልም ብለዋል::
የማጠቃለያ መርሃ-ግብሩ ላይ ስልጠናው በአግባቡ ተከታትለው ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ከእለቱ ክብር እንግዶች የምስክር ወረቀት የተበረከተላቸው ሲሆን በቀጣይ ሶስተኛ ዙር ሰልጣኞችም ስልጠናውን የሚወስዱ ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የ2017 ዓ.ም የአዲስ ገቢ ሰልጣኞች ቅበላ በመንግስትና በግል ኮሌጆች ላይ የትምህርት ማስረጃ ጥራትና አግባብነት የማረጋገጥ ሥራ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፤
በዚህም በየአመቱ በአስተዳደሩ የሚገኙ ሁሉም የግልና የመንግስት ኮሌጆች የሰልጣኝ ቅበላ ሲያካሂዱ በተላለፈላቸው የአሰራር መመሪያ ማከናወኛ መሰረት ሲሆን ከዚህ በተለየ ኮሌጆች ለራሳቸው በሚያመቻቸው መንገድ ከተቀመጠላቸው መመሪያ ውጪ በሚገባ ባልተፈተሸና ባልተረጋገጠ ሀሰተኛ ማስረጃ ሰልጣኝ ከተቀበሉ በእነዚህ እና በሌሎች ምክንያት የሚፈጠሩ ክፍተቶችን በወቅቱ ለማረምና ለመቆጣጠር የትምህርት ማስረጃ ጥራትና አግባብነት የማረጋገጥ ሥራ የሚከናወን ይሆናል፡፡
በዋናነት ኤጀንሲው ባለው ስልጣንና በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት ኮሌጆቹ ከመነሻው በወረደላቸው የቅበላ መመሪያ መሰረት ምዝገባ ማከናወናቸውን የማረጋገጥና ሰልጣኞች ያቀረቧቸው የትምህርት ማስረጃዎች ትክክለኛውን ከሀሰተኛው በመለየት ቅበላው በየደረጃው መቁረጫ ነጥብ መሆኑን ፈትሾ በሚገኙ ክፍተቶችና ከመመሪያ ውጪ በሆኑ አካሄዶች ላይ ፈጣንና አግባብነት ያለው የማስተካከያና የእርምት ስራዎችን ለመስራት አላማው አድርጎ የሚሰራ መሆኑ ታውቋል፡፡
በመሆኑም በመንግስትና በግል ኮሌጆች በ2017 ዓ/ም በአገር አቀፍ ደረጃ በተላለፈው የመቁረጫ ነጥብ መሠረት የ2017 ዓ.ም የአዲስ ገቢ ሰልጣኞች ቅበላ ላይ የትምህርት ማስረጃ ጥራትና አግባብነት ትክክለኛ መሆኑን በማረጋገጥ በተሰጣቸው ህጋዊ የማሰልጠን ፈቃድ ብቻ መስፈርቱን የሚያሟሉ ሰልጣኞችን በሞያ መስኩና ደረጃ መቀበላቸውን በተቀመጠው የቴ/ሙ/ት/ስ የስልጠና ጥራት ስታንዳርድ መሰረት መሆኑን በማስጠበቅና በማረጋገጥ ተቋማት ህግና ደንብን በሚገባ አክብረው እንዲሰሩ ኤጀንሲው ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን በመቆጣጠር በህግ የተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት እንዲወጣ ያስችለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ታህሳስ 24/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት በተቋሙ በሚከናወኑ Building & Infrastructure Renovation ስራዎች ላይ ውይይት ተካሄደ::
በመድረኩ በኮሌጁ አጠቃላይ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን 21ኛውን ክፍለ ዘመን ባማከለ መልኩ ሳቢና ለስልጠና ምቹ ከማድረግ አንፃር የሚያስፈልጉ የRenovation ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በባለሙያዎች ተለይቶ ቀርቧል::
በዚህም በቀረበው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ላይ የኮሌጁ ማኔጅመንት ጨምሮ የስልጠና ክፍል ተጠሪዎችና የኮንስትራክሽን ዲፖርትመንት አ/መምህራን በተገኙበት ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገበት ሲሆን በዚህም በጥናቱ ላይ ሊካተቱ ይገባል ያሏቸውን ነጥቦችና ማሻሻያ ያስፈልጋቸዋል ባሏቸው ጉዳዮች ላይ ለጥናቱ ግብአት የሚሆኑ ሀሳቦችንም አስቀምጠዋል::
የRenovation ትግበራው የEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5 አመት ከሚከውናቸው ትግብራዎች አንዱ ሲሆን ፕሮጀክቱ በተቋሙ በሚኖረው ቆይታም መሰል ተግባራትን የሚያካትት መሆኑም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ እና በቢሮው ስር ለሚገኙ የሚድያ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬው እለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተሰጠ፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጫው መድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም ሚድያ ትልቅ አቅም ያለው ኃይል ነው ይህንንም ኃይል ከኮሌጁ ጋር በማስተሳሰር የአካባቢው ወጣቶች ብሎም በመለው ሃገሪቱ ያሉ ማህበረሰቦች እንዲጠቀሙበት ማስቻል ይኖርብናል ብለዋል፡፡አያይዘውም በዛሬው እለት ለሚድያ አካላት የተዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር ስለ ኮሌጁ አጠቃላይ እንቅስቃሴ ጥሩ ግበአት የምታገኙነት ይሆናል ብለዋል፡፡
በመቀጠልም በስልጠናው ወቅት በመገኘት ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ብሩክ ፈለቀ እንዳሉት በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ የሚሰጡ ስልጠናዎች ማህበረሰቡን በተለይም ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ያማከለና በቴክኖሎጂ የታገዘ ትምህርትና ስልጠና ሊሰጥ ይገባል ያሉ ሲሆን ከዚህ ረገድ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየሰራ ያለበት አግባብ ከአካባቢው ማህበረሰብ አልፎ ለኢትዮጵያ የሚተተርፍ ነው ብለዋል፡፡አያይዘውም ኮሌጁ ያለውን እምቅ ሃብት ማህበረሰቡ ሊጠቀምበት ይገባል ብለዋል፡፡
በግንዛቤ ማስጨበጫው ላይ የተሳተፉ የሚድያ አካላት በሰጡት አስተያየትም ሰልጣኞች በኮሌጁ ቆይታቸው ወቅት ስልጠና ከማግኘት በዘለለ የስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ እንዲሁም ትምህርትና ስልጠናው በቴክኖሎጂ የታገዘ እንዲሆን እየሰራው ባለው ስራ እጅግ እንደተደሰቱና በቀጣይም በተለያዩ ስልጠናዎች ከኮሌጁ ጋር በጋራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
