es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 067
Suscriptores
+424 horas
-27 días
+230 días
Archivo de publicaciones
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በክህሎት መር ሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን የሚቃኝ የልምድ ልውውጥ እና የተሞክሮ ሽግግር ከሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በመጡ አመራሮችና ባለሙያዎች ተካሄደ። በልምድ ልዉዉጡ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የአደረጃጀት መስፈርትና ሂደት፣ የብድር አቅርቦት መስፈርትና መንገዶች፣ የገበያ ማመቻቸት ሂደት፣ የቦታ አቅርቦት ሂደት እንዲሁም የአንድ ማዕከል አገልግሎት የስራ ፍሰትን ተመልክተዋል፡፡ ‎ በተጨማሪም በአስተዳደሩ የሚገኙ የሞዴል ኢንተርፕራይዞችን በተመለከተ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎት እንዲሁም በከተማ ግብርና  የተደራጁ ማህበራት ላይ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ ‎ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሀምሌ 24/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

"በመትከል ማንሰራራት" በድሬዳዋ አስተዳደር የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም 🌴

3 ቀን ቀረው! ሐምሌ 24 ፣2017 700 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀንበር። እንዘጋጅ! #አረንጓዴዐሻራ #GreenLegacy
3 ቀን ቀረው! ሐምሌ 24 ፣2017 700 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀንበር። እንዘጋጅ! #አረንጓዴዐሻራ #GreenLegacy

በ4 ተኛው ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት "ዓለማቀፍ የድሬዳዋ ቀን' በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። ዛሬ ማለዳ ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ ከምድር ባቡር አደባባይ መነሻውን ያደረገ ስፖ
+5
በ4 ተኛው ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት "ዓለማቀፍ የድሬዳዋ ቀን' በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። ዛሬ ማለዳ ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ ከምድር ባቡር አደባባይ መነሻውን ያደረገ ስፖርታዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ተከትሎ የእግር ጉዞ በአስተዳደሩ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች ጉብኝት እንደዚሁም ባለፉት ሶስት ዓመታት የናፍቆት ድሬ ሳምንታት የነበሩ የበዓሉን አጠቃላይ ገፅታ የሚያስቃኝ የፎቶ አውደ ርዕይ እና የድሬ ጣፋጭና ባህላዊ ምግቦች ቅምሻ መርሐግብሮች ተከብሯል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከር ጁሀርና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ አምባሳደር ፍጹም አረጋን ጨምሮ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የመጡ ዲያስፖራዎች እንደዚሁም የከተማው ነዋሪዎች መነሻውን ከድሬዳዋ ምግብ ኮምፕሌክስ አካባቢ አድርጎ እስከ ሺኒሌ ባደረገው የባቡር ጉዞ ላይ ተሳትፈዋል። በዳንኤል አማረ ምስል:- አገኘው ሸዋረጋ

#ዜና | በ4ተኛው ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት "አለም አቀፍ የድሬዳዋ ቀን" በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድሬዳዋ እየተከበረ ነው #DGC ሐምሌ 21/2017 4ኛው ናፍቆት ድሬ አለም አቀፍ የድሬዳዋ ቀን በ
+9
#ዜና | በ4ተኛው ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት "አለም አቀፍ የድሬዳዋ ቀን" በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድሬዳዋ እየተከበረ ነው #DGC ሐምሌ 21/2017 4ኛው ናፍቆት ድሬ አለም አቀፍ የድሬዳዋ ቀን በሚል ስያሜ ከዛሬው የመክፈቻ የእግር ጉዞ የብሄር ሄረሰቦች ባህል፣ ታሪክ፣ ቋንቋና የማንነት መገለጫዎች ላይ ትኩረት ያደረጉ ሲንፖዚየም፣ የስነ-ፅሑፍ ስራዎች፣ስፖርታዊ ውድድሮች የልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝት እንዲሁም አብሮነትን በሚያጠናክሩ ሁነቶች ለቀጣይ 5 ቀናት ይከበራል። ናፍቆት ድሬ የድሬዳዋ ተወላጆች እና ወዳጆችን ከመላው ዓለም በሰባሰብ ናፍቆታቸውን ወዳጅነታቸውን የሚያጠናክሩበት ከመሆኑም ባለፈ በአስተዳደሩ በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፎ የሚያደርጉበት ነው። ሰላም ለማ ምስል:- አገኘው ሸዋረጋ

#ዜና | ዳያስፖራው ለድሬዳዋ እድገት ሊያበረክት የሚገባውን ሁለንተናዊ አቅም በአግባቡ በመጠቀም ለአገር እድገትና ብልፅግና የበኩሉን ድርሻ መወጣት አለበት ሲሉ ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። #DGC  ሐምሌ 20፣2017 4ተኛውን የናፍቆት ድሬ ሳምንት አከባበርን አስመልክቶ የድሬዳዋ አሰተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ፕሮግራሙን ለመታደም ለመጡ የድሬዳዋ ተወላጆችና ወዳጆች በድሬዳዋ ቤተ መንግስት የክብር የእራት ግብዣ መርሀግብር ተጀመረ  ። ከነገ ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት ተከብሮ የሚውለውን 4ተኛውን  ናፍቆት ድሬ በአልን አስመልክቶ በድሬዳዋ ቤተ መንግስት በተዘጋጀው የእንኳን ደህና መጣችሁ የእራት ግብዥ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከዲር ጁሃር ባደረጉት በንግግር እንዳሉት "ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት በዓል ባለፉት ሶስት ዓመታት በደመቀ መልኩ በተለያዩ ሁነቶች መከበሩ በማህበራዊ፡ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ መስክ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችንና ስኬቶችን ለማስመዝገብ ችለናል" ብለዋል። "ከዚህ በተጨማሪ ይህ በዓል የድሬ ተወላጆቿና ወዳጆቿ ስለ ድሬደዋ በመጨነቅ፣በማሰብና በመቆርቆር ትስስራቸው ይበልጥ እንዲጎለብት ያገዘ መድረክም ነው ። " ሲሉ ገልፀዋል። ከንቲባው አክለውም የድሬዳዋ ተወላጆች ወዳጆዎች፣ዳያስፖራዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላችው የበአሉ ታዳሚዎች የዘንድሮውም አራተኛውን ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት በተለያዩ ኹነቶች በማክበር የዳያስፖራውን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ እና ተጠቃሚነቱን ይበልጥ ባረጋገጠ መልኩ ለማክበር ከመቼውም ጊዜ በላይ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል። በመሆኑም በዓሉ በአስተዳደራችን ሕብረ ብሔራዊ አንድነትና የሕዝቦችን ትስስር በሚያጠናክር መንገድ፣ እንዲሁም በአስተዳደራችን ነዋሪ ዘንድ መነሳሳትንና የጋራ መግባባትን በሚያጎለብት መልኩ እንዲከበር በማድረግ የአስተዳደሩን መልካም ስምና ገጽታ ይበልጥ ለማስተዋወቅ ምቹ አጋጣሚ እንደሚፈጥር እምነታቸውን የገለፁት ከንቲባው ዳያስፖራው ለድሬዳዋ እድገት ሊያበረክት የሚገባውን ሁለንተናዊ አቅም በአግባቡ በመጠቀም ለአገር እድገትና ብልፅግና የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንደሚገባው አስገንዝበዋል። በመርሀግብሩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣በየደረጃው የሚገኙ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፌዴራል መንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣የሀይማኖት አባቶች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣ለበዓሉ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የመጡ ዳያስፖራዎች፣ በሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች የሚኖሩ ተወላጆች እና ሌሎችም እንግዶች ታድመዋል። ©️ Dire Tv

አራተኛው ናፍቆት ድሬዳዋ ሳምንት አጠቃላይ የድርጊት መረሐ ግብር
+1
አራተኛው ናፍቆት ድሬዳዋ ሳምንት አጠቃላይ የድርጊት መረሐ ግብር

🚨አስቸኳይ፡ በሀሰተኛ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ማስታወቂያዎች እንዳይታለሉ!🚨 ካናዳን ጨምሮ ህጋዊ የሥራ ስምሪት የሁለትዮሽ ስምምነት ወዳልተገባባቸው የተለያዩ ሀገራት ለሥራ እንልካለን የሚሉ ሀሰተኛ ማስታወቂያዎች በማህበራዊ ትስስር ገጾች በስፋት እየተዘዋወሩ ይገኛል፡፡ ይህም ገንዘብ ከማጭበርበር ባለፈ ለህገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ የጉልበት ብዝበዛ፣ ፆታዊ ጥቃትና መሰል የከፋ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ የሚዳርግ በመሆኑ ሁሉም በንቃት እንዲከታተለው ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡ ⚠️ የካናዳ እና  የአውሮፓ ሥራ ስምሪት እውነታዎች: ⚠️ኢትዮጵያ ካናዳን ጨምሮ ከየትኛውም የአውሮፓ ሀገር ጋር የሁለትዮሽ የሥራ ስምሪት ስምምነት የላትም፤ ⚠️የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለየትኛውም የጉዞ ወኪል ወይም ኤጀንሲ የሁለትዮሽ ስምምነት ወዳልተገባባቸው ሀገራት ዜጎችን ለሥራ እንዲያሰማራ የሰጠው ውክልናም ሆነ ፍቃድ የለም፤ ✅  ህጋዊ ሥራ ስምሪት የሚሰጥባቸው ሀገራት የትኞቹ ናቸው? የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ህጋዊና ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ለመዘርጋት ባደረገው ጥረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ሀገራት ጋር ሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ እነዚህም 👇 ⓵ሳዑዲ አረቢያ🇸🇦 ⓶የተባበሩት አረብ ኤሚሬት🇦🇪 ⓷ዮርዳኖስ🇯🇴 ⓸ሊባኖስ🇱🇧 ⓹ኳታር🇶🇦 እና ⓺ኩዬት 🇰🇼 ናቸው ⚠️ ሀሰተኛና አጭበርባሪ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ማስታወቂያዎች ዋነኛ መለያቸው ምንድን ነወ ❓ 👉የቅድሚያ ክፍያዎችን እንዲከፍሉ ይጠይቃሉ (ለቪዛ ፣ ለሥራ ማስኬጃ፣ ለህክምና እና ሌሎች በሚል፣ 👉ለቀላል ሥራዎች አማላይ ጥቅማ ጥቅም እና በከፍተኛ የደመወዝ መጠን እንደሚያስቀጥርዎት ቃል ይገባሉ፣ 👉ፈጣን ውሳኔዎችን እንዲያደርጉ ግፊት ያደርጋሉ፤ 👉ሀሰተኛ የሆነና ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የተሰጠ ፈቃድ ወይም ውክልና አለን በሚል ሰነዶችን ያሳያሉ፤ 👉በተለያዩ የውጭ ሀገር ቁጥሮች እየደወሉ አጭበርባሪነታቸው እንዳይታወቅ ጥረት ያደርጋሉ፤ 👉ወጥመዳቸው ውስጥ ያስገቧቸውን ዜጎች በአካውንት ብር እንዲያስገቡ ካደረጉ በኋላ አድራሻቸውን ይሰውራሉ፤ 📢 ህጋዊና ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት እንዴት ማግኘት ይቻላል❓ 📚 በየትኛውም ሀገር ህጋዊ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ለመሆን በመጀመሪያ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት lmis.gov.et ይመዝገቡ፤ ✅ የሚሰጠውን ስልጠና መውሰድና ብቃትዎን በምዘና ማረጋገጥ ይኖርብዎታል፣ ለመረጃ ምንጭነት 1.  ይፋዊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤታችንን ድረ ገጽና የማህበራዊ ትስስር ገጾችን 🌐 www.mols.gov.et 📘 facebook.com/MolsFDRE 📲 t.me/fdre_mols 🎵 TikTok: @mols_official 🐦 Twitter/X: @Jobs_የማስርትርት! 2.  ለተጨማሪ መረጃ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጀምሮ በየደረጃው በሚገኙ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መዋቅሮች በአካል በመገኘት መረጃ ማግኘት ይችላሉ፤ 📢መሰል አሳሳች ማስታወቂያዎችን ሲያዩ📢 አቅራቢያ ለሚገኝ የህግ አስከባሪ አካላት እንዲሁም በየደረጃው ላለው የዘርፉ መዋቅር በማሣወቅ ህገወጥነት ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ያግዙ፣ 📢 ይህን መልዕክት ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ♻️ ✅ይህንን መረጃ በማጋራት ሌሎችም ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እንዳይጋለጡ ያድርጉ❗️

የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት በአስተዳደሩ የገጠር ክላስተር ላይ ለሚገኙ ወጣቶች የSolar PV Installation & Maintenance ስልጠና በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ:: ፕሮጀክቱ ባለፉት አመታት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመቀናጀት በሁለት ዙሮች በከተማ አአስተዳደሩ የሚገኙ ወጣቶችን አሰልጥኖ ከስራ ጋር የማስተሳሰር ስራ እየሰራ ሲሆን በዚህ በ3ኛ ዙር ስልጠና የMobile training እሳቤን ወይም ወጣቶች ስልጠናውን ለመውሰድ ወደ ኮሌጅ መምጣት ሳይጠበቅባቸው ባሉበት ቢዮአዋሌ ገጠር ክላስተር የስልጠና ቦታዎችን በማመቻቸት እንዲሁም የስልጠና ግብዓቶችን በማሟላት በቃልቻ የገጠር ጤና ጣቢያ ግቢ ውስጥ በተመቻቸው ቦታ ስልጠናውን በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በSolar PV Installation & Maintenance ላይ በአጫጭርና መደበኛ ፕሮግራም ሰልጣኞችን ተቀብሎ እያሰለጠነ እንደሚገኝ የገለፁት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ምክትል ዲን አቶ ኢልያስ አህመድ ሲሆኑ አክለው በፕሮጀክቱ በመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዙር በድምሩ 91 ለሚሆኑ የአስተዳደሩ ወጣቶች በSolar PV Installation & Maintenance ስልጠና መሰጠቱን ጠቅሰው የ3ኛውን ዙር ስልጠና በአስተዳደሩ የገጠር ክላስተር ላይ በመሄድ በአካባቢው ለሚገኙ ወጣቶች እየተሰጠ የሚገኝ ስልጠና በመሆኑ ካለፉት ዙሮች ለየት ያደርገዋልም ብለዋል:: የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት አላማ ወጣቶችን አሰልጥኖ የሙያ ባለቤት ማድረግ ብቻ ሳይሆን ወጣቶቹ የስራ እድል ተመቻችቶላቸው ራሳቸውን፣ቤተሰባቸውን እንዲሁም ማህበረሰባቸውን እንዲጠቅሙና ህይወታቸውን እንዲቀይሩ ለማስቻልም ነው ያሉት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አክለውም በዚህ ሂደት ውስጥም የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት አጠቃላይ የስልጠናውን በጀት ከመሸፈን ጀምሮ የስልጠና ግብአቶችን በማሟላት የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ በመግለፅ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም ወርክሾፖችን ከማዘጋጀት ጀምሮ አሰልጣኝ መምህራንን በመመደብና የተለያዩ ለስልጠናው ውጤታማነት አስፈላጊ የሆኑ ተግባራት በማከናወን ረገድ እንደ ተቋም የሚጠበቅበትን በማበርከት በቅንጅት የሚሰራበት ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀዋል:: በቢዮአዋሌ ገጠር ክላስተር በSolar PV Installation & Maintenance ስልጠናቸውን የወሰዱ ወጣቶች በቀጣይ ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ አስፈላጊው ትብብር የሚደረግላቸው መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ወጣቶቹ የራስቸውን ህይወት ከመለወጥ በተጨማሪ የአካባቢያቸውን ማህበረሰብ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያስችላቸውም ተገፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሐምሌ 18/11/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት በአስተዳደሩ የገጠር ክላስተሮች ላይ ለሚገኙ ወጣቶች የSolar PV Installation & Maintenance ስልጠና በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ:: ፕሮጀክቱ ባለፉት አመታት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመቀናጀት በሁለት ዙሮች በከተማ አአስተዳደሩ የሚገኙ ወጣቶችን አሰልጥኖ ከስራ ጋር የማስተሳሰር ስራ እየሰራ ሲሆን በዚህ በ3ኛ ዙር ስልጠና የMobile training እሳቤን ወይም ወጣቶች ስልጠናውን ለመውሰድ ወደ ኮሌጅ መምጣት ሳይጠበቅባቸው ባሉበት የገጠር ክላስተር(የአርዳሌ ክላስተርና የቢያዋሌ ክላስተር)የስልጠና ቦታዎችን በማመቻቸት እንዲሁም የስልጠና ግብዓቶችን በማሟላት በቃልቻ የገጠር ጤና ጣቢያ ግቢ ውስጥ በተመቻቸው ቦታ ስልጠናውን በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በSolar PV Installation & Maintenance ላይ በአጫጭርና መደበኛ ፕሮግራም ሰልጣኞችን ተቀብሎ እያሰለጠነ እንደሚገኝ የገለፁት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስራ ሂደት ምክትል ዲን አቶ ኢልያስ አህመድ ሲሆኑ አክለው በፕሮጀክቱ በመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዙር በድምሩ 91 ለሚሆኑ የአስተዳደሩ ወጣቶች በSolar PV Installation & Maintenance ስልጠና መሰጠቱን ጠቅሰው የ3ኛውን ዙር ስልጠና በአስተዳደሩ የገጠር ክላስተሮች ላይ በመሄድ በአካባቢው ለሚገኙ ወጣቶች እየተሰጠ የሚገኝ ስልጠና በመሆኑ ካለፉት ዙሮች ለየት ያደርገዋልም ብለዋል:: የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት አላማ ወጣቶችን አሰልጥኖ የሙያ ባለቤት ማድረግ ብቻ ሳይሆን ወጣቶቹ የስራ እድል ተመቻችቶላቸው ራሳቸውን፣ቤተሰባቸውን እንዲሁም ማህበረሰባቸውን እንዲጠቅሙና ህይወታቸውን እንዲቀይሩ ለማስቻልም ነው ያሉት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አክለውም በዚህ ሂደት ውስጥም የአድራ ኢትዮጵያ(ADRA Ethiopia) ፕሮጀክት አጠቃላይ የስልጠናውን በጀት ከመሸፈን ጀምሮ የስልጠና ግብአቶችን በማሟላት የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ በመግለፅ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም ወርክሾፖችን ከማዘጋጀት ጀምሮ አሰልጣኝ መምህራንን በመመደብና የተለያዩ ለስልጠናው ውጤታማነት አስፈላጊ የሆኑ ተግባራት በማከናወን ረገድ እንደ ተቋም የሚጠበቅበትን በማበርከት በቅንጅት የሚሰራበት ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀዋል:: በአርዳሌ ክላስተር እና በቢያዋሌ ክላስተር በSolar PV Installation & Maintenance ስልጠናቸውን የወሰዱ ወጣቶች በቀጣይ ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ አስፈላጊው ትብብር የሚደረግላቸው መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ወጣቶቹ የራስቸውን ህይወት ከመለወጥ በተጨማሪ የአካባቢያቸውን ማህበረሰብ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያስችላቸውም ተገፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሐምሌ 18/11/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @bolsdd