1 067
Suscriptores
+424 horas
-27 días
+230 días
Archivo de publicaciones
#ከኢፌዲሪ_ትምህርትና_ስልጠና_ባለሥልጣን_የተሰጠ_ማሳሰቢያ
የከፍተኛ ትምህርትና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ፈቃድ እና ፈቃድ እድሳት አሰጣጥ መመሪያ ቁጥር 988/2016 ዓ.ም አንቀጽ 6 ንዑስ አንቀጽ 4 እና 5 መሠረት፡-
ፈቃድ የተሰጠው ተቋም ተማሪ መዝግቦ ማስተማር የሚችለው ፈቃድ በተሰጠበት ተቋም፣ ካምፓስ፣ የጊዜ ገደብ፣ መርሃ-ግብር፣ ደረጃ፣ የትምህርት ወይም የስልጠና መስክ እና በተፈቀደለት ዓመታዊ የተማሪ ቅበላ መጠን መሠረት ብቻ ይሆናል፤
ማንኛውም ተቋም ፈቃድ ከማግኘቱ በፊት እና ፈቃድ ወይም ፈቃድ እድሳት ጊዜው ከተጠናቀቀ በኋላ ተማሪ ወይም ሰልጣኝ መዝግቦ ማስተማር አይችልም፡፡ ተቋማት ከባለሥልጣኑ ያገኙትን ፈቃድ ኮፒውን ለተማሪዎች እና ለአካባቢው ህብረተሰብ በሚታይ ቦታ የመለጠፍ፣ በዊብሳይት የማሳወቅ፣ ሲጠየቁም የማሳየት ኃላፊነት አለባቸው ፡፡
በመሆኑም ተማሪዎች ፤ወላጆች፣ የመንግስት አካላት እና መላው ህብረተሰብ ከፈቃድ አሰጣጥ ስርዓቱ ውጪ ተማሪ መዝግበው የሚያስተምሩ ተቋማት ሲያጋጥሙ ለባለሥልጣኑ በመጠቆም የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ እናሳስባለን፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
LMIS Website Guide Amharic
በብቁ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት ድረ-ገጽ በቀላሉ ለመመዝገብ ይህን ቪዲዮ ይመልከቱ።
ELMIS Website Guide Oromiffa
Karaa salphaa ta'een biquu gabaa hojii karaa marsariitii galmaa'uuf viidiyoo kana daawwadhaa
ELMIS Website Guide Somali
"ADEEFA BIKU EE BOGA XOGAHA SUUQA SHAQADA IYO SHAQALAHA SII AAD ISAGA DIWAAN GALISO DAAWO MUQALKANI"
#ዜና | "በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በአስተዳደሩ በሁሉም መስክ አመርቂ ድሎች ተመዝግበዋል" የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር
#DGC ሐምሌ 17/2017
የተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት በአስተዳደሩ በሁሉም መስክ አመርቂ ድሎች የተመዘገቡበት ነው ሲሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገለፁ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ኛው ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ በሁሉም መስክ በሰላምና ጸጥታ፣በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ፣በዲፕሎማሲ፣ በዲጂታል እና በሌሎች ዘርፎች ስኬታማ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።
በስራ እድል ፈጠራ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ እና ገበያን በማረጋጋት በተሰሩ ስራዎች አበረታች ለውጦች መኖራቸውን ገልጸዋል።
የዋጋ ግሽበትን በመቆጣጠር ኑሮ ውድነትን ለመቀነስ በ2017 ዓ.ም ከመጀመሪያው ከነበረው ምግብ እና የምግብ ነክ ሸቀጦች ከነበረውን 28 በመቶ የዋጋ ንረት ወደ 12 በመቶ ማውረድ መቻሉ ተገልጿል።
የዋጋ ንረት ለማረጋጋት የሸቀጦች ዋጋ በተለይም ምግብ ነክ ምርቶችን በሰንበት ገበያ ተደራሽ እንዲሆን ለማስቻል በተሰራው ስራ አመርቂ ለውጦች መጥተዋል ብለዋል ።
የአስተዳደሩን የገቢ አቅምን ከማሳደግ አንጻር በ2017 በጀት ዓመት 6.3 ቢሊየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ 5.4 ቢሊየን ብር መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን የእቅዱ 85 በመቶ ማሳካት ተችሏል።
ከዚህ ውስጥ መንግስታዊ ታክስ ገቢ 5 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 4.4 ቢሊየን ብር88 በመቶ መዘጋጃዊ ገቢ 1.3 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ብር 1 ቢሊየን ብር 77 በመቶ መሰብሰብ ተችሏል ያሉ ሲሆን ይህ አፈጻጸም አስተዳደሩ ካለው የገቢ አቅም እና የልማት ፍላጎት አንጻር በቀጣይ ዓመት ማጠናከር እንደሚገባም ነዉ አጽኖት የሰጡት።
ሰላም ለማ
ምስል፦አገኘው ሸዋረጋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ኛው ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።
በጉባዔውም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፈትያ አደን የጉባኤውን አጀንዳዎች ያቀረቡ ሲሆን የአስተዳደሩ ምክር ቤት 3ኛው ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤን ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል።
በ2017 በጀት ዓመት በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ይገኛል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በምክር ቤቱ ጉባኤ የተነሱ አንኳር ጉዳዮቹን ተከታትሎ ወደ እናንተ የሚያደርስ ይሆናል።
ሰላም ለማ
ምስል:- አገኘው ሸዋረጋ
*********************
Manni Marii Bulchiinsa Dirree Dhawaa Yaa'ii Idilee 10ffaa gaggeessuu jalqabe.
Manni Marii Bulchiinsa Dirree Dhawaa Yaa'iin Idilee 10ffaa Bara Hojii 3ffaa Waggaa 4ffaa gaggeessuu jalqabeera.
Yaa'ii kana irratti Kantiibaan Bulchiinsa Dirree Dhawaa Kabajamoo Obbo Kadiir Juhaar gabaasa Raawwii hojii Dhaabilee raawachiiftotaa Kan bara 2017 dhiheessaati jiru.
Abdi Adem
Suuraan Aganyahu Shawaaraggaa
*********************
Kalfadhiga 10aad ee sanadka sadexaad ee golaha baarlamaanka ismaamulka Dir dhaba ayaa ka furmay hoolka.shirarka ee golaha
Waxaana lagu dhagaysan doonaa warbixinta waxqabadka golaha fulinta iyo xafiisyada baarlamaanka hoosyimaada iyo ansixinta miisaaniyada ismaamulka Dir dhaba.
Shucayb daahir
Sawrika Aganywo shawaaraga
ሐምሌ 24 ፣2017 700 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀንበር። እንዘጋጅ!
July 31, 2025 #Ethiopia will attempt planting 700 million seedlings in one day. Let’s get ready as the count down begins.
#አረንጓዴዐሻራ
#GreenLegacy
#PMOEthiopia
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+8
#|በ1987 ዓ.ም በብረታ ብረት ሙያ የተመረቁ የቀድሞ የኮሌጁ ተማሪዎች በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት ጉብኝት አደረጉ፡፡
በኮሌጁ በመገኘት ጉብኝት ያደረጉት እነዚህ የኮሌጁ የቀድሞ ተመራቂዎች ስለ ጉብኝቱ አላማ ሲያስረዱ ከተመረቁ 30 አመት እንደሞላቸውና የ30ኛ አመት የምረቃ በዓላቸውን ምክንያት በማድረግ የኮሌጁን እንቅስቃሴ ለመመልከትና በቀጣይ ከኮሌጁ ጋር በጋራ ለመስራት ያለመ እንደሆነ በጉብኝቱ ወቅት አስረድተዋል ፡፡
ጉብኝቱን ምክንያት በማድረግ ያነጋገርናቸው የቀድሞ ተመራቂዎች በሰጡት አስተያየት ኮሌጁ አሁን ያለበት ደረጃ እጅግ የሚያስገርምና አስደናቂ ለውጥ ውስጥ ያለ ኮሌጅ ነው ያሉ ሲሆን በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ ያለውን የባቡር ምህንድስና የልህቀት ማእከል እንዲሁም በኮሌጁ ውስጥ እየተሰጡ ያሉ የሙያ መስኮች በሙሉ ወጣቶችን የስራ ፈጣሪ የሚያደርግና ሃገራችን ኢትዮጵያን ከድህነት የሚያላቅቁ የሞያ መስኮች ናቸው በእነዚህ የሙያ መስኮች ደግሞ ወጣቶች በመሰልጠን እራሳቸውን ሊጠቅሙ ይገባል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ከዚህ ጉብኝት በኋላ የኮሌጁን ስም እና ዝና በየቦታው በመናገር ወጣቶች የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ተመራጭ ለማድረግ በአንባሳደርነት የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሀምሌ 16/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
🔍 ሥራ እየፈለጉ ነው - የሀገር ውስጥ፣ የውጭ ሀገር ወይስ የርቀት?
የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (E-LMIS) ፍትሃዊ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ጥራት ያላቸውን የሥራ ዕድሎች በሙሉ በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ያስችልዎታል።
🌍በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ሰርቶ ለመለወጥና ካሰቡት ለመድረስ የሥራ ገበያ ስነ-ምህዳሩ ላይ ስላለው በቂ፣ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃ ያስፈልጎታል። ለዚህም የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት በእጅጉ ያግዝዎታል።
✅ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የሥራ ዕድሎች መረጃ ለማግኘት የሚከተለው ማስፈንጠሪያ ተጠቅመው አሁኑኑ ይመዝገቡ! የሥራ ገበያ መረጃውን ዓለም ይቀላቀሉ! ሁሉንም መረጃ በነፃ ያግኙ!
🔗 [lmis.gov.et]
ፍትሃዊ እና ጥራት ያለው የሥራ ዕድል ለሁሉም!
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ADRA ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ከፕሮጀክቱ ጅማሮ እስከ አሁን የተጏዘበትን ውጤታማ የአፈፃፀም ልምድ በተለያዩ ክልሎች ፕሮጀክቱን ለሚያስተገብሩ አስተባባሪዎች የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሄደ::
ADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ባለፉት አመታት በ Solar PV Installation Maintenance ስልጠና 120 ወጣቶችን አሰልጥኖ ወደ ስራ እንዲገቡ ከማድረግ አኳያ ኘሮጀክቱ ከሚተገበርባቸው ከያትኛውም አካባቢዎች የተሻለ ውጤታማ አፈፃፀም የተመዘገበበት እንደሆነም ተገልፇል::
በዛሬው እለት ከADRA ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ጋር ልምድ ልውውጥ ለማድረግ ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የመጡት የፕሮጀክቱ ቅርንጫፎች(ከአርባምንጭ፣ ከአፋር፣ ከወልቂጤ) የተገኙ ሲሆን ፕሮጀክቱ ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተዘዋውረው ተመልክተዋል::
የልምድ ልውውጡ ዋና አላማ በADRA ኢትዮጵያ በምስራቁ ክፍል ድሬዳዋ ላይ በፕሮጀክቱ አፈፃፀም የተፈጠረውን ትልቅ አቅምና ልምድ ወደተቀሩት አካባቢዎችም ማስተላለፍ እንዲቻል የመማማሪያ ሁኔታን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም በመድረኩ ተገልፇል::
የADRA ፕሮጀክት ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ከጅምሩ አንስቶ የመጣበትን መንገድና የተሰሩ ውጤታማ ተግባራትን በዝርዝር የሚያመላክት ገለፃ በፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን ለልምድ ልውውጡ በኮሌጁ የተገኙ ተሳታፊዎችም በየአካባቢያቸው ያከናወኗቸውንና ተመኩሮ ሊሆኑ የሚችሉ ተግባራትን እቅርበው የምክክር መድረክም ተካሂዷል::
የADRA ፕሮጀክት በአስተዳደሩ የሚገኙ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ የቻለ ትግበራ ማከናወኑ የተገለፀ ሲሆን ለዚህም ኮሌጁን ጨምሮ በአስተዳደሩ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጉዳዩን በባለቤትነት በመያዝ ተገቢውን ድጋፍ በማድረጋቸው ጭምር የተመዘገበ ውጤት መሆኑም በመድረኩ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሐምሌ 11/2017 ዓ.ም
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት ኢንድርስትሪው ላይ ለሚገኙ ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው የክህሎት ስልጠና ተጠቀቀ::
በኮሌጁ ለ15 ቀናት ኢንዱስትሪዎች ላይ በተለየው የክህሎት ክፍተት መሰረት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና መጠናቀቁን ተከትሎ የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት በተገኙበት የስልጠናው አጠቃላይ ሂደት የሚያመላክት የሪፖርት መድረክ ተካሂዷል::
ከተለመደው የክህሎት ክፍተት ስልጠና አሰጣት በተለየ ሁኔታ የስልጠናውን ውጤታማነት ለማረጋገጥ በኢንዱስትሪዎች ላይ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ተደርጎ ወደ ትግበራ መገባቱን ያስታወሱት የኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ አገልግሎት ዋና ስራ ሂደት ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም በኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚሰሩ ባለሙያዎች የሚሰጡ የክህሎት ስልጠናዎች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ከማላመድ ባሻገር የኢንዱስትሪዎችን ምርትና ምርታማነት በማሳገደጉ ረገድ እጅግ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረውም ገልፀዋል::
የክህሎት ስልጠናውን በማሰልጠንም ሆነ በማስተባበር የተሳፉትን አካላት ማመስገን ያስፈልጋል ያሉት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አክለውም ይህ ስልጠና ኮሌጁ በፕሮጀክቱ አማካኝነት ኢንዱስትሪዎች ላይ ከምንሰራቸው ተግባራት መካከል አንዱ መሆኑን ገልፀው የክህሎት ስልጠናው እንደ ጅማሮ ጥሩ አፈፃፀም ያገኘንበትና በቀጣይ በሌሎች የሙያ ዘርፎች ለኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ለምንሰጠው የክህሎት ስልጠና ምርጥ ተሞክሮ የተገኘበትም ነበር ብለዋል::
የክህሎት ስልጠናው ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው የነበረውን አጠቃላይ ሂደት ዝርዝር ሪፖርት የኢንዱርስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ክፍል ተጠሪ በሆኑት አቶ አቤል ዘገየ አማኝነት ለመድረኩ የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሪፖርትም የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ከማካሄድ ጀምሮ የማሰልጠኛ ሞጁል በማዘጋጀት ከኢንዱስትሪዎች ለተወጣጡ ሰራተኞች በኮሌጁ ወርክሾፖች የክህሎት ስልጠናው መሰጠቱ የተገለፀ ሲሆን እንዲሁም በስልጠናው ሂደት የተገኙ መልካም አጋጣሚዎችና የተሰተዋሉ ክፍተቶችም በሪፖርቱ ተካተው ቀርበዋል::
የክህሎት ስልጠናው በአስተዳደሩ በሚገኙ የConel Industrial P.l.c እና የFerida Plastic Recycling በተሰኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚገኙ 58 ባለሙያዎች በHydraulics,Pneumatic
በmachining እና
በWelding የሙያ መስኮች የክህሎት ስልጠናው የተሰጣቸው ሲሆን በተጨማሪም በLeadership እንዲሁም በOccupational Safety and Health (OSH) ስልጠናዎችን በመስጠትና ባለሙያዎቹን በማብቃት እንደ ኮሌጅ ውጤታማ ተግባር ማከናወን መቻሉም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሐምሌ 10/2017 ዓ.ም
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
