1 071
Suscriptores
+224 horas
+37 días
+230 días
Archivo de publicaciones
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ በ2017 በጀት ዓመት በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የደረሱበትን የዕቅድ አፈፃፀም ደረጃ በመገምገም የታዩ ጠንካራ ጎኖችን ለማስቀጠል እንዲሁም በአፈፃፀም ላይ ውስንነት የታየባቸውን ተግባራት ለይቶ አፋጣኝ መፍትሄዎችን ለማስቀመጥና የዓመታዊ ዕቅድ አፈፃፀም ውጤትን በላቀ ደረጃ መፈጸም የሚያስችል አቅም ለመፍጠር በቢሮው እና በስሩ ከሚገኙ ኮሌጆች አመራርና ባለሞያዎች ጋር ውይይት አካሄደ፡፡
በአጠቃላይ በሪፖርቱ ከተመላከቱ ስራዎች መካከል በ3 የመንግስት እና በ5 የግል ኮሌጆች የቅበላ መጠን ስንመለከት የአዲስ ሰልጣኞች ቅበላ ወንድ 2319 ሴት 2662 በድምሩ 4981 የአዳዲስ ሰልጣኞች ቅበላ የተከናወን ሲሆን በዚህም በእቅድ ከተያዘው 4924 የቅበላ መጠን አንፃር 4981 የተንነ ሆን የ101.2 በመቶ አፈፃፀም ያለው ሲሆን የነባር ሰልጣኞች ቅበላ ወንድ 2087 ሴት 3164 በድምሩ 5251 የነባር ሰልጣኞች ቅበላ ተከናውኗል ይህም በእቅድ ከተያዘው 5380 የቅበላ መጠን አንፃር የ97.6 በመቶ አፈፃፀም ሲኖረው በገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናዎችን 2689 ገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠናዎችን ለማከናወን ታቅዶ 1201 ወንድ 1456 ሴት ጠቅላላ 2657 ስልጠናን ማከናወን የተቻለ ሲሆን ይህም ከግማሽ ዓመቱ ዕቅድ አንፃር የ98.8 በመቶ አፈፃፀም መድረስ ተችሏል፡፡
ቢሮው ከከሌጆች ጋር ዕቅዱን በመናበብ የመከለስ፣ የድጋፍና ክትትል ስራውን ማጠናከር፣ የመደበኛ ሰልጣኝ ማብቃት ላይ ኢንስፔክሽን በየጊዜው በማድረግ ዞኒንግ እና ዲፈረንሼሽን ላይ በዚህ በጀት አመት በተዘጋጀው መውጫ ዕቅድ ወደ ተግባር በመግባት፤ የከተማዋን ነዋሪ ችግር የሚፈቱ ከዚህ ቀደም ተሰርተው የተቀመጡትን በማሻሻል መጠቀም እንዲሁም ትምህርትና ስልጠናውን በተሻለ መልኩ ለመምራት የሚያስችሉ መመሪያዎችን በማዘጋጀት ወደ ስራ ማስገባትና ዲጂታላይዜሽን ላይ የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር ወደ ልህቀት ማሳደግ ላይ በቀጣይ ስድስት ወራት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 20/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+7
በሶማሌ ኢሳ ማህበረሰብ ዘንድ ሰላምን በማስፈን እና አብሮነትን ለማጠናከር ለበርካታ መቶ ዓመታት የቆየው ”ሔር ኢሴ “ ቃላዊ ህግና የዳኝነት ስርዓት በዩኔስኮ በወካይ የማይዳሰስ የሰው ልጆች ቅርስነት መመዝገቡን ተከትሎ በድሬዳዋ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል
በድሬዳዋ አለማቀፍ ስቴዲየም በሺዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ባህላዊ አልባሳትን በመልበስ እየታደሙበት የሚገኘው የእውቅና መርሃ-ግብር መካሄድ ጀምሯል።
በዝግጅቱ ከጅቡቲ ፣ ከሱማሊያ ፣ ከሱማሌ ብሔራዊ ክልል መንግስት የመጡ ልኡካን ቡድኖች እና ተጋባዠ እንግዶች እየታደሙ ነው ።
በትዕግስት ቶሎሳ
ፎቶ፦ አገኘሁ ሸዋረጋ
#ዜና በሶማሌ ኢሳ ማህበረሰብ ዘንድ ሰላምን በማስፈን እና አብሮነትን ለማጠናከር ለበርካታ መቶ ዓመታት የቆየው ”ሔር ኢሴ “ ቃላዊ ህግና የዳኝነት ስርዓት በዩኔስኮ በወካይ የማይዳሰስ የሰው ልጆች ቅርስነት መመዝገቡን ተከትሎ በድሬዳዋ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።
ዛሬ ከሰዓት በኋላ በድሬዳዋ ወጣቶች አካዳሚ የኢሳ እናቶች ያዘጋጁዋቸው የማህበረሰቡ ባህላዊ ምግቦች ቅምሻን ለመታደም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በስፍራው ተገኝተዋል ፡፡
የማህበረሰቡን አኗኗርና ባህል እና የአመጋገብ ስርዓት ጭምር እንዲያጸባርቅ ተደርጎ በተዘጋጀው የባህላዊ ምግቦች ትርኢትና ቅምሻ ላይ ከጅቡቲ ፣ ከሱማሊያ እና ከሱማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትና የመጡ እንግዶች እና ልኡካን ቡድን አባላት የታደሙ ሲሆን ለህዝቦች የእርስ በእርስ ከቀራረብ ሚናው ከፍተኛ ከመሆኑም በላይ ወጣቶች ባህልና ወጋቸውን እንዲማሩም አስተዋጾው የጎላ መሆኑም ተወስቷል ፡፡
ይህ ዝግጅት ነገ ቅዳሜም በድሬዳዋ አለማቀፍ ስቴዲየም በሺዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ባህላዊ አልባሳትን በመልበስ የሚታደሙበት የእውቅና መርሃግብር እንደሚካሔድ እና ምሽት ላይ በወጣቶች አካዳሚ በሚዘጋጅ ደማቅ የሙዚቃ ኮንሰርት ማጠቃለያ እንደሚደረግ ከወጣው መርሐ ግብር መረዳት ተችሏል፡፡
"ሔር ኢሴ" በተባበሩት መንግስታት የትምህርትና የባህል ተቋም /ዩኔስኮ/የዓለም ቅርስ ሆኖ መመዝገቡን ምክንያት በማድረግ ከዛሬ ጀምሮ በድሬዳዋ በዓሉ በተለያዩ መርሀ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል ።
የሶማሌ ኢሳ ማህበረሰብ ፍትሃዊ ያልተጻፈ መተዳደሪያ ሕግ “ሔር ኢሴ” በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የሰው ልጆች ወካይ ዓለም አቀፍ የማይዳሰስ ባህላዊ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ መመዝገቡን ምክንያት በማድረግ በዛሬው ዕለትም የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና ኢንድስትሪ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮን የ2017 በጀት አመት የመጀመሪያው 6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የመውጫ ውይይት አካሄደ ።
==========================
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች በስራቸው የተደለደሉትን የአስተዳደሩ ተቋማት ዕቅድ አፈፃፀም ለመገምገም ያለመ የመስክ ምልከታ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆኑ በዛሬው ዕለትም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ፣ ንግድ ና ኢንዱስትሪ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ክትትልና ቁጥጥር ከሚያደርግባቸው የአስተዳደሩ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነውን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በመገኘት የ2017 በጀት አመት የመጀመሪያውን የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የመውጫ ውይይት አድርጓል።
ቋሚ ኮሚቴው በቢሮው ስር ያሉ ተጠሪ ተቋማትና ፕሮጀክቶች ከክህሎት ልማትና ስራ ዕድል ፈጠራ ጋር ተያያዝነት ያላቸውን ተግባራት አፈፃፀም ያሉበትን ደረጃ ባለፉት ቀናት የመስክ ምልከታ ሲያደርጉ ቆይቶ በዛሬው ዕለትም ከቢሮው ማኔጅመንት አባላት ጋር በተቋሙ የግማሽ አመት ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት በማድረግ በአፈፃጸም ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና በውስንነት የተለዩ ጉዳዮች መታረም እንዳለባቸው የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የመውጫ ግብረ መልስ ተሰጥቷል።
በዚህም የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ለቋሚ ኮሚቴው በክህሎት ልማት በመደበኛና አጫጭር ስልጠናዎች፣ በከተማ እና ገጠር ስራ ዕድል ፈጠራ፣ በኢንተርፕራይዝ ልማት ፣ በአሰሪና ሰራተኛው ዘርፍ እንዲሁም የካፒታል ፕሮጀክቶች አፊፃፀም ባለፉት ስድስት ወራት የተሰሩ ስራዎችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ የታሰቡ ጉዳዮችን ጠቅሰው ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአጠቃላይ ቢሮው በ2017 ዓ.ም የ6 ወር ዕቅድ አበረታች አፈፃፀሞች መታየቱንና በዘርፉ በውስንነት የተለዩትን እንዲታረሙ በማድረግ በቀጣይ በተለይ የሥራና ክህሎት ምክር ቤትን በመጠቀም ሁሉም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት የተጀመረውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክሮ በማስቀጠል በስፋትና በጥራት የክህሎት ልማትና የከተማና የገጠር ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥተው መስራት እንዳለባቸው የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል ።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 15/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚሰጠው የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው የውጭ ሀገር ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ዝርዝር።
ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ይሁኑ!
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡
ጥቅምት 16፤ 2017
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols
ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና የኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኮሌጁን መደበኛ ፣ በኮሌጁ በሚገኙ ፕሮጀክቶች የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወር የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አከናወነ፡፡
የኮሌጁን መደበኛ ፣በኮሌጁ በሚገኙ ፕሮጀክቶች የ2017 በጀት ዓመት የ6ወር የእቅድ አፈጻጸም ከዝግጅት ምእራፍ አንስቶ እስከ ግማሽ በጀት አመቱ ማጠቃለያ ድረስ በከፍተኛ ትጋትና የሁሉም ተሳትፎ በጋራ በማካተት እየሰራን እንገኛለን ፡፡ ያሉት የቋሚ ኮሚቴውን ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የኮሌጁን ሁኔታ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ የእቅዱን አፈጻጸም በአብዛኛው ፐርሰንት ያሳካንበት የ6ወር አፈጻጸም ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ኮሌጁ በ ቴክኒክና ሙያ አዲሱ እሳቤ አንጻር ከእቅዱ ጋር በማስተሳሰር እየሠራን እንገኛለን ብለዋል። አያይዘውም የከተማው አስተዳደሩ እየሠጠን ያለውን ሃላፊነት ተቀብለን ያለምንም እንከን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
የቋሚ ኮሚቴውን ልኡክ ቡድን የመሩት ወ/ሮ አይናለም ተዘራ እንዳሉት ኮሌጁ በመደበኛ እንዲሁም በኮሌጁ ባሉ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ከእቅዱ አንጻር አመርቂ ውጤት የታየበት ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም ተቋሙን ሞዴል እንዲሆን የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት የተገኙ ልምዶችና ውጤቶች ለሌሎች ተቋማት የማካፈል ስራዎች ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል፡፡በመጨረሻም ልኡክ ቡድኑ በኮሌጁ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የመስክ ምልከታውንና ሪፖርቱን መሰረት በማድረግ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
+1
አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ለከተራና ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
የተከበራችሁ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።
ከጥምቀት በዓል በዋናነት ትህትናን፣ ይቅርታን እና ታዛዥነት እንማራለን። ስለዚህ በዓሉን ስናከብር ሆነ ከበዓሉ በኋላ እነዚህን ሦስት ነገሮችን በተሰማራንበት መስክ ሁሉ ማሰብና መተግበር ይጠበቅብናል።
በዓሉ ከኃይማኖታዊ በዓልነቱ ባሻገር የአብሮነታችን መገለጫ ከመሆኑም በተጨማሪ የሀገርና የህዝብ ሃብት እንዲሁም የዓለም ቅርስ ሆኖ በዩኔስኮ የተመዘገበ ስለሆነ በዓሉን ስናከብር ሀገራዊ ገፅታን በሚያሳድግ መልኩ ማክብር ይገባናል።
ህዝበ ክርስቲያኑም በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በማብላት በማጠጣት እንዲሁም ከሁሉም ህብረተሰብ ጋር ሠላምና አብሮነትን በሚያጎለብት መልኩ ማክበር ያስፈልጋል።
በድጋሚ እንኳን ለከተራና ለጥምቀት በዓል በሠላም አደረሳችሁ። አደረሰን መልካም በዓል።
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
በ2017 ዓ.ም በአስተዳደሩ ለሚደረገው የቴክኖሎጂና የፈጠራ ስራ ውድድር ከተቋምና ከአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች ለውድድሩ የተመለመሉ ተወዳዳሪ አሰልጣኝ መምህራኖች፣ ሰልጣኞች፣ ኢንተርፕራይዞችና ለአጠቃላይ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መምህራን ስለ ውድድሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ፡፡
በዚህም ውድድሩ በዘርፉ ያለውን ችግር ለመቅረፍ መንግስት ባወጣው ፖሊሲና ስትራቴጂ መሰረት ለአሰልጣኞችና ሰልጣኞች፤ ለመምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን በአስተዳደሩና በአገር አቀፍ ደረጃ በየአመቱ በማወዳደር ለማበረታታትና ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ያለው ፋይዳ ላቅ ያለ ነው፡፡
በተጨማሪ በአስተዳደሩ ያለውን የቴክኖሎጂ እድገት ለህብረተሰቡ በማስተዋወቅ የተያዘውን የቴክኖሎጂ መቅዳትና ማሸጋገር ሂደት ለማቀላጠፍ እንዲያስችል የቴክኒክና ሙያ መር የገበያ ትስስር የሚፈጥር ሲሆን በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ የካቲት እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ መጋቢት ላይ ውድድሩ የሚካሄድ ይሆናል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ከጋንቤላ አፔኖ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና ከደቡብ ምዕራብ ቴፒ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተወጣጣ ልኡካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ልምድ ልውውጥ አደረገ፡፡
ኮሌጆቹ በነበራቸው የልምድ ልውውጥ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያለውን የላቀ አፈፃፀም ሂደት በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በተለያዩ ተግባራት እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎችም በኮሌጁ ዲኖች አማካኝነት ሰፋ ያለ ገልፃ ተደርጎላቸዋል::
ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ ባደረጉት ምልከታና የተደረገላቸው ገለፃን መነሻ በማድረግ በተካሄደው የጋራ ውይይት ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያደረገው ያለው እንቅስቃሴ አስደናቂ መሆኑን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ እያሳየ ያለው የላቀ አፈፃፀም ለሌሎች አቻ ተቋማትም ምሳሌ መሆን የሚችልበት የአፈፃፀም ደረጃ ላይ እንደሚገኝም በውይይታቸው ወቅት አንስተዋል::
በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች እንዲሁም ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን እዚህ በኮሌጁ ያገኙትን በርካታ ልምዶችንም ቀምረው በመጡባቸው ኮሌጆች ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩም ገልፀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥር 9/2017 ዓ.ም
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
