es
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Ir al canal en Telegram
1 064
Suscriptores
-124 horas
-47 días
+530 días
Archivo de publicaciones
በተለያዩ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ሰራተኞችን በቴክኒክና ሙያ ዘርፎች የበቁ እንዲሆኑ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ እንደሚሰራ አስታወቀ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ስር ላሉ የፖሊስ አባላት ሶስተኛ ዙር በመሰረታዊ የኮምፒውተር ክህሎት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ጀመረ፡፡ በስልጠናው ማስጀመሪያ እለት በመገኘት ስልጠናውን ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ሁለተኛ ተቋማችሁ ወደሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን ኮሌጁ በሁሉም ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ሰራተኞችን ለማብቃት በርካታ የአጫጭር ስልጠናዎችን እንዲሁም ከ12 በላይ ትምህርት ክፍሎች የተለያዩ የሞያ ትምህርቶችን አዘጋጅቶ እየሰጠ ይገኛል ያሉ ሲሆን አያይዘውም የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከዚህ ቀደም ከስራና ክህሎት ቢሮ ጋር በተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ እንዲሁም ከኮሌጃችን ጋር ባለ መልካም ግንኙነት አብሮ ለመስራት ኮሌጁ ቁርጠኛ ነው፡፡የፖሊስ አባላቱንም በአዳዲስ ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ የበቁ እንዲሆኑ በጋራ ከጠቅላይ መምሪያው የሚሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በስልጠናው ላይ በመገኘት የስራ መመሪያ ያስተላለፉት በድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የፖሊስ አካዳሚ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮማንደር ጌታቸው መገርሳ እንዳሉት የፖሊስ አባሎቻችንን የቴክኖሎጂ ችሎታቸውን ለማዳበር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራን እንገኛለን ያሉ ሲሆን አያይዘውም ይህንን ስራችንን ደግሞ ወደ ተግባር እንድንቀይር ትልቁን ድርሻ የሚወስደው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ነው ብለዋል፡፡ ለዚህ ስልጠና መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱት የኮሌጁ እንዲሁ የፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ኃላፊዎችን አመስግነዋል፡፡ በመጨረሻም ስልጠና የሚወስዱ የፖሊስ አባላት ስልጠናውን በአግባቡ በመውሰድ የሰለጠኑትን ሙያ በመጠቀም ተቋማቸውን ሊያገለግሉ ይገባል ብለዋል፡፡ ኮሌጁ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዙር ከ127 በላይ ሰልጣኞችን በመሰረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና ያሰለጠነ ሲሆን ዛሬ በተጀመረው የሶስተኛ ዙር ስልጠና ከ60 በላይ የፖሊስ አባላት ስልጠናን እንደሚወስዱ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 25/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ፣ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ቢሮ ክህሎት መር የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ #DGC | ጥር 24/2018 ዓ.ም የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ በ 100 ቀናት ዕቅድ በምግብ ዋስትና እና በምርት ዘርፍ የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ገልጸዋል። በዶሮ እርባታ፣ በማር ምርት እና በመንገድ ዳር ፈጣን ምግቦች (Street Food) ዝግጅት ላይ የሚሰማሩ አምስት ማህበራት መደራጀታቸውን አቶ ሮቤል አመላክተው በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አማካኝነት ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች፣ የዶሮ ቤቶች፣ የዶሮ መኖ ማቀነባበሪያ ማሽኖች እና የከተማዋን ውበት በሚመጥን ሁኔታ ዘመናዊ የጎዳና ላይ ምግብ መሸጫ ጋሪዎች በፈጠራ ዘምነውና እርስ በርስ ተመጋጋቢነት እንዲኖራቸው ተደርገው መሰራታቸውን ጠቁመዋል። ዘመናዊ የንብ ቀፎ በወጣቶች ለተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ቢሮ ከግብርና ውሃ መአድንና ኢነርጂ ቢሮ ጋር በመሆን የሚያከፋፍል መሆኑንም አቶ ሮቤል ተናግረዋል። አቶ ሮቤል አያይዘውም ቢሮው በከተማ እርስ በርስ ተመጋጋቢ የሆኑ ሶስት እንዲሁም በገጠር ሁለት በድምሩ አምስት አዳዲስ ኢንተርፕራይዞችን ስራ በማስጀመር የስራ አጥነትን ቁጥር መቀነስን ትኩረት ያደረገ ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ያብራሩ ሲሆን ኢንተርፕራይዞቹ የሚጠቀሙባቸው ማሽነሪዎችና የፈጠራ ውጤቶች በቢሮው ስር ባሉት ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በራስ አቅም ፈጠራ ታክሎባቸው የተመረቱ መሆናቸውን አመላክተዋል። ቢሮው በስሩ የሚገኙ ሁለት የመንግስት ኮሌጆችና ስድስት የግል ኮሌጆች ውስጥ የሚሰሩ ሰባት ሺህ ሶስት መቶ አርባ ስድስት ሰራተኞች ሙሉ በሙሉ ፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ተጠቃሚዎች መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸው በቢሮውም ሆነ በኮሌጆቹ አገልግሎት ለማግኘት የሚመጡ ተገልጋዮች የፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንደሚገባቸው አመላክተዋል። በሌላ በኩል፣ የቴክኖሎጂ ክህሎትን ለማሳደግ እየተተገበረ ባለው የኢትዮ ኮደርስ (Ethio Coders) ፕሮግራም፤ በኢትዮ-ጣልያን እና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሚገኙ ሰራተኞችና ተማሪዎችን ጨምሮ 2,600 ሰዎችን ለማሰልጠን ታቅዶ እስካሁን ከ2,500 በላይ ሰልጣኞች ስልጠናውን በመከታተል ላይ እንደሚገኙ አቶ ሮቤል ተጠቁመዋል በከበደ ካሳ ፎቶ፦ ቴድሮስ ልዑልሰገድ

ከነገ ጀምሮ በፕላስቲክ ከረጢት እቃ መያዝም ሆነ መሸጥ በሕግ እንደሚያስቀጣ ያውቃሉ?  *** ከነገ ጀምሮ በፕላስቲክ ከረጢት እቃ መያዝም ሆነ መሸጥ በሕግ ያስቀጣል። ታዲያ ለገበያ ምን ይዘን እንውጣ? ከቤትዎ ሲወጡ የጨርቅ ከረጢት ወይም ዘላቂ የሆኑ የሸመታ ከረጢቶችን መያዝዎን ያረጋግጡ። ይህ አዲስ መመሪያ የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ ትልቅ እርምጃ ነው። የፕላስቲክ ከረጢቶች በአካባቢ ላይ የሚያደርሱትን ጉዳት ለመቀነስ የሚደረገው ጥረት የሚደነቅ ቢሆንም፣ የኅብረተሰቡን የዕለት ተዕለት ፍላጎት ለማሟላት በቂ ተኪ ምርቶች ተዘጋጅተው ይሆን? በዚህ ጉዳይ  ምላሽ የሰጡት በፌደራል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የከተማ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ ክትትል ዴስክ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን አለሙ እንደገለጹት ፤ መንግሥት እና የግል ባለሀብቶች ፕላስቲክ ከረጢትን ተኪ ምርቶች ላይ እየሰሩ ስለመሆናቸው ነው ከኢቢሲ ዶት ስትሪም ጋር በነበራቸው ቆይታ ያነሱት ። ያቀረቧቸውን ነጥቦች መሠረት በማድረግ፣ ስለ ተኪ ምርቶቹ እና ስለ ሕጉ አፈጻጸም ዝርዝር መረጃዎችን በሚከተለው መልኩ ማጠቃለል ይቻላል፦ ✅ ከጥጥ ጨርቅ የሚሰሩ ከረጢቶች፦ እነዚህ ከረጢቶች ታጥበው ለረጅም ጊዜ የሚያገለግሉ በመሆናቸው ለዘላቂነት ተመራጭ ናቸው። ✅ ከካኪ (ወረቀት) የሚሰሩ ምርቶች፦ በተለይ ለደረቅ ዕቃዎች እና ለምግብ ነክ ግብይቶች ውጤታማ ናቸው። ✅ የማምረት አቅም፦ በአሁኑ ወቅት ሶስት ትላልቅ ተቋማት በቀን እስከ 55,000 የሚደርሱ የጨርቅ ከረጢቶችን እያመረቱ ሲሆን፣ በርካታ ጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችም በስፋት እየተሳተፉ ይገኛሉ። የመንግሥት ድጋፍ እና ማበረታቻ ሕጉን ተግባራዊ ለማድረግ መንግሥት የሚከተሉትን ማበረታቻዎች እያቀረበ ይገኛል፦ ✅ከቀረጥ ነፃ መብት፦ ተኪ ምርቶችን የሚያመርቱ ማሽኖችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ከቀረጥ ነፃ መብት ተሰጥቷል። የፋይናንስ ድጋፍ፦ አምራቾች ካፒታል እንዲያገኙ ከባንኮች እና ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር የውይይት መድረኮች ተመቻችተዋል። ጥሬ ዕቃ፦ ምንም እንኳን በጥሬ ዕቃ ላይ የተወሰነ ቀረጥ ቢኖርም፣ ምርቱን ለማሳደግ ጥረቶች እየተደረጉ ነው። ✅ሊታረሙ የሚገባቸው የተሳሳቱ አመለካከቶች ባለሙያው እንደገለጹት፣ "ያልተሸመነ ጨርቅ" (Non-woven fabric) ከፕላስቲክ ጋር ተመሳሳይነት ስላለው እና ለረጅም ጊዜ ስለማያገለግል፣ አምራቾችም ሆኑ ሸማቾች ከዚህ ምርት ይልቅ ዘላቂ የሆኑ የጨርቅ ከረጢቶችን እንዲጠቀሙ ይመከራል። ✅የሸማቹ ሚና ሕጉ ውጤታማ እንዲሆን የሸማቹ ተሳትፎ ወሳኝ ነው። ✅ከቤት ይዞ መውጣት፦ እያንዳንዱ ሸማች ለገበያ ሲወጣ የራሱን ዘላቂ ከረጢት (Reusable bag) የመያዝ ልምድ ማዳበር ይኖርበታል። ✅ግንዛቤ፦ ፕላስቲክ የሚያስከትለውን የጤና እና የአካባቢ ጉዳት በመገንዘብ ሕጉን ማክበር።

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ብልጽግና ህብረት አባላት በልሳነ ብልጽግና ቅፅ 1 ቁጥር 7 መጽሔት ይዘቶችና ጠንካራ አደረጃጀት ለተሳካ ምርጫ በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ተወያዩ፡፡ በልሳነ ብልፅግና መጽሔት የተዳሰሱ ዋናዋና ነጥቦች 1, ዲሞክራሲያዊነት እና ምርጫ እሳቤያዊ ተቃርኖዎች እና የፓርቲያችን ማስታረቂያ መንገዶች። 2, ካለፉት ምርጫዎች የሚቀሰሙ ትምህርቶች ። 3, የ7ኛ ሀገራዊ ምርጫ አስቻይ ሁኔታዎችና ተግዳሮቶች ። 4, የምርጫ ግቦቻችን እና የአመራርና አባላት ሚና ሲሆን። በአጠቃላይ በመጽሔቱ ላይ እና ጠንካራ አደረጃጀት ለተሳካ ምርጫ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን አባሉ በመጪው 7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ላይ በንቃት እንዲሳተፍና ኃላፊነቱን እንዲወጣ አቅም የሚፈጥርለት እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 22/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአገር በቀል እውቀት፣ ክህሎት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ ተካሄደ።       በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አገር በቀል እውቀትና ክህሎት ምንነትና መረጃ አሰባሰብ ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠር የሚያስችል መድረክ በሙያው ላይ ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች፣ ለወረዳ አንድ ማዕከላትና ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት አዘጋጀ።      በግንዛቤ ማስጨበጫና በውይይት መድረኩ ላይ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆኑ አገር በቀል እውቀቶችንና ክህሎቶችን በመለየት እያዳበሩ የሚያድጉበትና በቴክኖሎጂ የሚደገፉበትን አመቺ ሁኔታ ማመቻቸት ላይ በተለይ በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ በተመላከተው መሰረት ለአገር በቀል እውቀቶችንና ክህሎቶችን ማልማት ትኩረት መሰጠቱ ትልቅ አቅም መሆኑም ተገልጿል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥር 21/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር በጋራ መስራታቸው የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ለውጥ ማምጣት እንዲችል አድርጎታል ተባለ፡፡ Hope Enterprise ከ SEED Project፣MasterCard foundation እንዲሁም ከ EDI ጋር በመተባበር ለድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለአሰልጣኝ መምህራኖች እና ለሃሮማያ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራኖች ለተከታታይ 3 ቀናት ሲሰጥ የነበረውን የ ToT ስልጠና በዛሬው ተጠናቀቀ። በዛሬው እለት የተጠናቀው ይህ ስልጠና በዋናነት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በገበያ መር አጫጭር ስልጠና ለዜጎች ተደራሽ መሆን እንዴት እንደሚቻል ግንዘቤ ለመፍጠርና ስልጠናዎችን ኢንዱስትሪ መር ለማድረግ ታልሞ የተዘጋጀ ስልጠና እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ። በተጨማሪም ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አካታች እንደመሆናቸው መጠን ስልጠናቸውን ሲሰጡ ሴቶችንና አካል ጉዳተኞችን ያማከለ ማድረግ እንዳለባቸው በስልጠና በቂ ግንዛቤ መፍጠር ተችሏል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በስልጠናው ማብቂያ እለት ከኢንዱስትሪዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር የፓናል ውይይት የተደረገ ሲሆን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተሞክሮ የቀረበ ሲሆን ኢንዱስትሪዎች ከኮሌጁ ጋ ባላቸው ቅርብ ግንኙነት የተመዘገቡ ለውጦች እጅግ አበረታችና ሌሎች ኮሌጆች በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያለውን ምርጥ ተሞክሮ ሊካፈሉት ይገባል ተብሏል። የሶስቱን ቀን ስልጠና እና የዛሬውን የፓናል ውይይት ያዘጋጀው ከኮሌጁ ጋር ቀደም ብሎ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ያለው እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከኢንዱስትሪዎች ጋር የማቀራረብ ስራ የሚሰራው Hope Enterprise ሲሆን በቀጣይም በርካታ ስራዎችን ከድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በጋራ እንደሚሰራ ለማወቅ ተችሏል ፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ጥር 21/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችን ያቀፈ ልዑካን ቡድን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ፡፡ የቦንጋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክት ከሚተገበርባቸው 24 የሚሆኑ የሀገሪቱ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አንደኛው ሲሆን በዚህም የኮሌጁን ዲኖች ጨምሮ የተለያዩ የስራ ሀላፊዎችን ያካተተ የልዑካን ቡድን በኮሌጃችን ያለውን የስራ እንቅስቃሴ ለመመልከት እንዲሁም በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ያለውን ተሞክሮ ለመውሰድ የሚያስችላቸውን የስራ ልምድ ልውውጥ በኮልጁ ማካሄድ ችለዋል:: ልዑካን ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ መርሃ-ግብር ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ የEASE ፕሮጀክት ትግበራን ጨምሮ ጠቅላላ በተቋም የተመዘገቡ የአፈፃፀም ውጤቶችን በዝርዝር የተመለከቱ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ ከምስረታው አንስቶ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ የነበረውን ሂደት እና ያከናወናቸውን ዘርፈ ብዙ የለውጥ እንቅስቃሴዎችን በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገለፃና ማብራሪያም ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ በተደረገላቸው አቀባበልና በተመለከቱት የኮሌጁ እንቅስቃሴ መነሻ በማድረግ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች አስደናቂ መሆናቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ካሳየው የስራ አፈፃፀም ብዙ ልምዶችን መቅሰም መቻላቸውንም ገልፀዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የስልጠና ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በነበራቸው የልምምድ ልውውጥ መርሃ-ግብርም የተሳካ ቆይታን በኮሌጃችን ማድረግ ችለዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጥር 21/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የመላ ኢትዮጵያውያን የሕልውና ጉዳይ የሆነው የባሕር በር ጥያቄ ** የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ያገኝ ዘንድ ሁሉም ኢትዮጵያውያን በጋራ የቆሙ መሆኑን የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና የዲፕሎማሲ ባለሙያው አቶ ጥላሁን ሊበን ገልጸዋል። የባሕር በር ጥያቄው የአንድ መንግሥት ወይም የፖለቲካ ድርጅት ፍላጎት ብቻ ሳይሆን፣ የመላው ኢትዮጵያውያን የሕልውና ጥያቄ መሆኑን ባለሙያው ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የባሕር በር በማጣቷ በየዓመቱ የምትከፍለው የወደብ ኪራይ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ አቶ ጥላሁን አንስተዋል። ለወደብ ኪራይ የሚወጣው ከፍተኛ ወጪ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ትልቅ ሀብት መሆኑን የጠቀሱት ባለሙያው፤ የባሕር በር ማጣት በዲፕሎማሲና በሀገር ሉዓላዊነት ላይም የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ እንዳለው አስረድተዋል። በአዲስ አበባ የጉለሌ ክፍለ ከተማ አርሶ አደሮች ለኢቢሲ በሰጡት አስተያየት፥ የባሕር በር አለመኖር በኑሯቸውና በሥራቸው ላይ ከፍተኛ ጫና እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል። አርሶ አደሮቹ እንዳሉት፥ ከውጭ ለሚገባው ማዳበሪያ ዋጋ መናር እንዲሁም ያመረቱትን ምርት በጥሩ ዋጋ ለውጭ ገበያ ማቅረብ ያልቻሉበት ዋነኛው ምክንያት የባሕር በር ማጣት ነው። "የባሕር በሩ ቢገኝልን አርሶ አደሩም፣ ነጋዴውም ሆነ ሸማቹ ተጠቃሚ ይሆናል" ሲሉ አርሶ አደሮቹ ተስፋቸውን ገልጸዋል። የባሕር በር ጥያቄው ተገቢ መሆኑን በመጥቀስ፣ ለስኬቱ አስፈላጊውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። የባሕር በር ጥያቄው ውጤት እንዲያመጣ ወጣቱ ትውልድ እና ሚዲያዎች የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስቀደም ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እንዲያከናውኑ ጥሪ ቀርቧል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ባሕር በር ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ እና በድርድር ምላሽ እንዲያገኝ መንግሥት በጽኑ እንደሚሠራ መግለፃቸው ይታወሳል።