1 085
Suscriptores
+924 horas
+207 días
+1530 días
Archivo de publicaciones
በድሬዳዋ አስተዳደር በቴክኖሎጂ እና በፈጠራ ስራ እምቅ አቅም ያላቸውን የኮሌጅ፣ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም ኢንተርፕራይዞችን ያሳተፈ ውድድር ተጠናቀቀ፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ችግር ፈቺ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በዘርፉ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን እና ባለሙያዎች እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል፡፡
ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው ውድድር በማጠናቀቂያው የአሰልጣኝ መምህራንና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ለውድድሩ በተመረጡ ዳኞች ፊት ቴክኖሎጂዎቻቸውን በማቅረብ ተወዳድረዋል የቴክኖሎጂ ውድድሩን በበላይነት የሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎችም በአስተዳደር ደረጃ እውቅና እና ማበረታቻ የሚደግላቸው ይሆናል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 15/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#ዜና | የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ፥ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ፥ 'ብሩህ' የተሰኘ የንግድ ፈጠራ ሀሳብ ውድድር አካሄደ።
ውድድሩ የስራ ፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶች፥ ሀሳባቸውን ወደ ተግባር መለወጥ እንዲችሉ የሚያግዝ ነው ተብሏል።
የድሬዳዋ ስራ፥ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፥ ቢሮው የአስተዳደሩን ተጨባጭ ሁኔታ በማገናዘብ ለዜጎች የስራ እድል የመፍጠርና የማመቻቸት ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመው፥ በዚህ ውድድሩ የተሳተፉ ወጣቶችን በሀሳብ ከመደገፍ በተጨማሪ ለአሸናፊዎች የገንዘብ ሽልማት መዘጋጀቱን ገልፀዋል።
በቢሮው የስራ እድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማስተባበሪያ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው፥ በውድድሩ የተሻለ የንግድ ፈጠራ ሀሳብ መኖሩን ከማሳየት ባሻገር፥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተሸላሚ የሚሆኑ የድሬዳዋ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች እንደሚወጡ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ፥ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ባዘጋጀው ውድድር ላይ የተሳተፉ ተወዳዳሪዎች ፥ ፕላስቲክን መልሶ የመጠቀም ቴክኖሎጂ፥ የዲጂታል ህክምና አገልግሎት እና የአልባሳት ንድፍ ሥራን ጨምሮ በርካታ የፈጠራ ሀሳቦችን ማቅረባቸው ታውቋል።
©️ ድሬ ቲቪ
ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት በድሬዳዋ አስተዳደር የሁለተኛ ዙር ትግበራ የህይወት ክህሎት ስልጠና ወስደው ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ኢንደስትሪዎች ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የስራ ልምምድ እንዲያደርጉ ገለጻ ስለ ተቋሞቻቸው በማብራራት ወደ ስራ የማስገባት ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
ራስዎን ከህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎች እና አጭበርባሪዎች ይጠብቁ!
ወደ ውጭ ሀገራት የሚደረግ የሥራ ሥምሪት የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ክብር የጠበቀ እንዲሆን ለማስቻል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በቴክኖሎጂ የታገዘ የምዝገባ ሥርዓት አልምቶ ወደ ሥራ አስገብቷል፡፡
በዚሁ ሥርዓት ላይ ተመዝግበው መስፈርቱን ያሟሉ በርካታ ዜችን ህጋዊ መንገድን በመከተል በተለያዩ መዳረሻ አገሮች ለሥራ ማሰማራት ተችሏል፤
ይሁን እንጂ በሚኒስቴር መ/ቤቱ ስም የውጭ አገር የሥራ ስምሪት ምዝገባ እናካሄዳለን በማለት ህገወጥ ድርጊት የሚፈፅሙ አካላት እንዳሉ ደርሰንበታል፡፡ የድርጊቱ ፈፃሚዎች በህግ እንዲጠየቁ ተገቢውን ክትትል እያደረግን እንገኛለን፡፡
የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገልግሎቱን ለማግኘት ዜጎች ምንም አይነት ክፍያ የማይጠየቁ መሆኑን አውቀው ከህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎችና ከአጭበርባሪዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ እናሳስባለን።
በአንፃሩ ክፍያ የሚጠይቁ አካላትን በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጥቆማ መሰጫ ስርዓት https://pfs.mols.gov.et/ ወይም በስልክ ቁጥር +251116671356 እንዲሁም በተዋረድ ላለው የዘርፉ መዋቅር ወይም በአቅራቢያችሁ ለሚገኙ የሕግ አስከባሪ አካላት ጥቆማ እንድትሰቱን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
በውጭ ሀገር ሥራ ሥራ ስምሪቱ ለመጠቀም ፍላጎት ያላችሁ ዜጎች ሚኒስቴር መ/ቤቱ ባዘጋጀው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ( https://lmis.gov.et/ ) መመዝገብ እና አስፈላጊውን ሙያዊ ስልጠና ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡
ከዚህ ውጭ በሆነ ህገ-ወጥ መንገድ ለሥራ ወደ ውጭ ሀገራት የሚደረግ ጉዞ የከፋ ችግር ውስጥ የሚጥል መሆኑን በመገንዘብ ዜጎች ህጋዊ አማራጮችን ብቻ እንዲጠቀሙ እናሳስባለን፡፡
ለበለጠ መረጃ በአካባቢችሁ ወደሚገኙ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢዎች ወይም የሥራና ክህሎት ፅ/ቤቶች በመሄድ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ራስዎን ከህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎች እና አጭበርባሪዎች ይጠብቁ!
ወደ ውጭ ሀገራት የሚደረግ የሥራ ሥምሪት የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ክብር የጠበቀ እንዲሆን ለማስቻል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በቴክኖሎጂ የታገዘ የምዝገባ ሥርዓት አልምቶ ወደ ሥራ አስገብቷል፡፡
በዚሁ ሥርዓት ላይ ተመዝግበው መስፈርቱን ያሟሉ በርካታ ዜችን ህጋዊ መንገድን በመከተል በተለያዩ መዳረሻ አገሮች ለሥራ ማሰማራት ተችሏል፤
ይሁን እንጂ በሚኒስቴር መ/ቤቱ ስም የውጭ አገር የሥራ ስምሪት ምዝገባ እናካሄዳለን በማለት ህገወጥ ድርጊት የሚፈፅሙ አካላት እንዳሉ ደርሰንበታል፡፡ የድርጊቱ ፈፃሚዎች በህግ እንዲጠየቁ ተገቢውን ክትትል እያደረግን እንገኛለን፡፡
የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አገልግሎቱን ለማግኘት ዜጎች ምንም አይነት ክፍያ የማይጠየቁ መሆኑን አውቀው ከህገ-ወጥ አዘዋዋሪዎችና ከአጭበርባሪዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ እናሳስባለን።
በአንፃሩ ክፍያ የሚጠይቁ አካላትን በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጥቆማ መሰጫ ስርዓት https://pfs.mols.gov.et/ ወይም በስልክ ቁጥር +251116671356 እንዲሁም በተዋረድ ላለው የዘርፉ መዋቅር ወይም በአቅራቢያችሁ ለሚገኙ የሕግ አስከባሪ አካላት ጥቆማ እንድትሰቱን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
በውጭ ሀገር ሥራ ሥራ ስምሪቱ ለመጠቀም ፍላጎት ያላችሁ ዜጎች ሚኒስቴር መ/ቤቱ ባዘጋጀው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ( https://lmis.gov.et/ ) መመዝገብ እና አስፈላጊውን ሙያዊ ስልጠና ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡
ከዚህ ውጭ በሆነ ህገ-ወጥ መንገድ ለሥራ ወደ ውጭ ሀገራት የሚደረግ ጉዞ የከፋ ችግር ውስጥ የሚጥል መሆኑን በመገንዘብ ዜጎች ህጋዊ አማራጮችን ብቻ እንዲጠቀሙ እናሳስባለን፡፡
ለበለጠ መረጃ በአካባቢችሁ ወደሚገኙ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢዎች ወይም የሥራና ክህሎት ፅ/ቤቶች በመሄድ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ስርዓተ ስልጠናዎች(ስርኣተ ትምህርቶች)፤ ማስልጠኛ መርጃ መሳሪያዎች እና የአሰልጣኙ መምሪያዎች እንዲሁም በአሰስመንት ፓኬጆች ላይ በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማረሚያ ቤት ማዕከል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋም አሰልጣኞች እና ስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት ተጀመረ፤
ይህም ስልጠና በዋናነት በማረሚያ ቤቱ በተለይም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና እንቅስቃሴን ለመደገፍ ቢሮውና በስሩ የሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ሲያደርጉ የነበረውን ድጋፍ አጠናክሮ በማስቀጠል የተቋሙ አሰልጣኝ መምህራን እና የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ጊዜው የሚጠይቀውን እና የሚፈልገውን ክህሎት ተላብሰው ተልዕኮ መፈጸም እንዲችሉ ታስቦ በአጠቃላይ ስልጠና አሰጣጥና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ለተከታታይ ቀናት የሚሰጥ መሆኑ ታውቋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት14/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+4
በድሬዳዋ አስተዳደር የተዘጋጀው፥ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ውድድር ዛሬም ቀጥሎ ተካሄደ።
ይህ ውድድር በስራ፥ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በቴክኒክና ሞያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ እንዲሁም በሳይንስ፥ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኤጀንሲ የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ነው።
በቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ውድድሩ ተሳታፊ ከሆኑት መካከል፥ የማርያም ሰፈር 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነው ያብስራ ከበደ አንዱ ነው፡፡
በፀሀይ ሀይል የሚሰራ ጄኔሬተር በመስራት ለውድድር የቀረበው ተማሪ ያብስራ ከበደ፥ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራው ችግር ፈቺ ሆኖ ስላገኘው ለውድድይዞ መቅረቡን ተናግሯል፡፡
የተለያዩ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በማበልፀግ በአስተዳደሩ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ፥ ይህ የፈጠራ ስራዎች ውድድር ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክትም ተገልጿል።
የድሬዳዋ ስራ፥ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የዘርፍ ሽግግር ባለሞያ አቶ ሸመልስ ፍሰሃ በበኩላቸው፥ በየአመቱ የሚካሄደው ይህ ውድድር ለወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር እና ከውጪ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለማምረት የሚደረገውን ጥረትም ያግዛል ብለዋል፡፡
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተጀመረው የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ውድድር ላይ ከአስተዳደሩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች፥ መምህራን እና ኢንተርፕራይዞች እየተካፈሉ ይገኛሉ።
©️ DireTVአማርኛ | ግንቦት 2016 ዓ.ም
ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራትና የሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚብሽን (Job fair) በማዘጋጀት ሥራ አጥ ዜጎችን ከሥራ ጋር ማስተሳሰር ተቻለ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ይህን ሥራና ሠራተኛ የሚገናኙበት መድረክ ሲያዘጋጅ የሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚብሽኖች አሰሪውና ሥራ ፈላጊው በአንድ ቦታ የሚገናኙበትና ሥራ ፈላጊዎች አሰሪው ላቀረበው ክፍት የሥራ ቦታ ያመለከቱበትና ቀጣሪው ቃለመጠይቅ ያደረገበት መድረክ ሆኗል፡፡
በዚህም መድረክ ላይ ተሳታፊ የሆኑ በአጠቃላይ ሥራ ፈላጊውና (job seekers) እና ቀጣሪዎች (Employers) በቀላሉ መገናኘት እንዲችሉ መንግሥት ከሚሰጣቸው የስራ ስምሪት አገልግሎቶች መካከል ሥራና ሰራተኛ ማገናኘት ኤግዚብሽን (Job fair) በተለይም ከኢንደስትሪዎች ጋር በማስተሳሰሩ ረገድ የላቀ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 12/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደር ደረጃ የ2016 ዓ.ም የቴክኖሎጂና የሥራ ፈጠራ ውድድር መካሄድ ጀመረ፤
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምርና ስልጠና ኤጀንሲና የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኤጀንሲ በጋራ ባዘጋጁት የ2016 ዓ.ም የቴክኖሎጂና የሥራ ፈጠራ ውድድር በአስተዳደሩ በሚገኙት የመንግስትና የግል ኮሌጆች በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተዋናዮች (በሰልጣኝ፣ አሰልጣኝ እና አንቀሳቃሾች እንዲሁም ተቋማት) በተጨማሪም የአጠቃላይ ት/ቤት ተማሪዎችና መምህራን የሚያሳትፍ ይሆናል፤
የውድድሩ ዋናው አላማም በአስተዳደሩ የሚገኙ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ችሎታ ያላቸውን ወጣቶችና የሙያ ባለቤቶች መካከል ከፍተኛ የውድድር ተነሳሽነትን መንፈስ በመፍጠር በመሰረታዊ የስራ ፈጠራ፤ ተግባራዊ ምርምር እና ቴክኖሎጂዎችን የመቅዳት፣ የማሻሻል፣ የመፍጠር የማለማመድ እና የማሸጋገር ስራዎቻችን ላይ ከፍተኛ የሆነ የጥራት ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥር ይታሰባል፤
በውድድሩ ማስጀመሪያ ላይ በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደተናገሩት በአዲሱ የዘርፉ ፖሊሲ በተመላከተው መሰረት የክህሎትና የቴክኖሎጂ አቅምን ሊያሳዩና ሊያሳድጉ የሚችሉ ውድድሮችን ማድረጉ በዘርፉ ተሳታፊ የሆኑ አካላትን ከማነቃቃት በዘለለ ከኢንደስትሪው ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ሲሆን አስተዳደሩም የተለየ ትኩረት ሰጥቶ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 9/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የማህፀን በር ካንሰርን ለመከላከልና ቅድመ ምርመራ በማድረግ ከበሽታው ራስን ብሎም ማህበረሰብን ማዳን በሚቻልበት እንዲሁም በስራ ቦታ የኤች አይቪ ኤድስን የመከላከልና መቆጣጠር ፅንሰ ሀሳብ ላይ ለድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ፡፡
በቢሮው የሴቶች ወጣቶችና ኤች አይ ቪ ኤድስ ማስተባበሪያ አዘጋጅነት ከአስተዳደሩ ጤና ቢሮ በተጋበዙ የጤና ባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው የተሰጠ ሲሆን አመራሩና ሰራተኛው ከጊዜ ወደ ጊዜ አሳሳቢ እና ትኩረት በተሰጣቸው ሴቶችን፣ አምራችና ሰራተኛ ሀይሉን ተጠቂ የሚያደርጉ በሽታዎችን በመረዳት እራሱን በምርመራ በማወቅና በመጠበቅ የነቃ እንዲሆን የሚያስችለው ይሆናል፡፡
በመድረኩ ላይ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ተገኝተው በተለይ የኤች አይ ቪ ጉዳይ በማህበረሰባችን ዘንድ የሚታየው መዘናጋትና በበሽታው የሚከሰተውን ችግሮች መቅረፍ እንዲቻል መሰል መድረኮችን ማመቻቸት የሚገባ ሲሆን ለዚህም ሁሉም የቢሮው ማህበረሰብ የድርሻውን በትብብርና በኃላፊነት መወጣት እንዳለበት ተናግረዋል፡፡
የማህፀን በር ካንሰርን መከላከልና ቅድመ ምርመራ በማድረግ ስርጭቱንና ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት መቀነስ አሁን ላይ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው መሆኑንና የሴቶች ጉዳይ ብቻ አድርጎ መመልከት ሳይገባ ወንዶችም ከሴቶች ጎን በመሆን መከላከሉን እና ቅድመ ምርመራውን ሴቶች እንዲያደርጉ ሊያበረታቱ እንደሚገባ ተሳታፊዎች አንስተዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 7/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
