es
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

Ir al canal en Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

Mostrar más
3 309
Suscriptores
-224 horas
-97 días
-3630 días
Archivo de publicaciones
#በዚህች ቀንም ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጎ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ
#በዚህች ቀንም ልደቱን ባከበረ ጊዜ ወለተ ሔሮድያዳ በዘፈን አጥምዳ አስማለችው:: እርሱም የታላቁን ነቢይ ራስ አስቆርጦ በወጪት አድርጎ ሰጣት:: አበው "እምሔሶ ለሔሮድስ ይብላዕ መሐላሁ - ሔሮድስ መሐላውን በበላ በተሻለው ነበር" ይላሉ:: #የቅዱስ_ዮሐንስ ራሱ በርራ ስትሔድ አካሉን ግን ደቀ መዛሙርቱ ቀብረውታል:: (ማቴ. 3:1, ማር. 6:14, ሉቃ. 3:1, ዮሐ. 1:6) ርጉም ሔሮድስ አንገቱን ካስቆረጠው በሁዋላ #የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ራሱ የጸጋ ክንፍ ተሰጥቷት ጌታችን ወዳለበት #ደብረ_ዘይት ሔዳ በፊቱ ሰገደች:: #ቅዱሳን_ሐዋርያት በአዩት ነገር ተገርመው ራሱን እጅ ነሷት:: ከዚሕ በሁዋላ ጌታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ ለቅዱስ ዮሐንስ ራስ የማስተማር ስልጣን ሰጥቶ አሰናበታት:: በመላው ዓለም #ለ15 ዓመታት ስትሰብክ ኑራ ሚያዚያ 15 ቀን ዓረቢያ ውስጥ ዓርፋለች:: "አስማተ-ዮሐንስ መጥምቅ (የመጥምቁ ዮሐንስ ስሞች)" 1.ነቢይ 2.ሐዋርያ 3.ሰማዕት 4.ጻድቅ 5.ካሕን 6.ባሕታዊ/ገዳማዊ 7.መጥምቀ መለኮት 8.ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ) 9.ድንግል 10.ተንከተም (የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ) 11.ቃለ አዋዲ (አዋጅ ነጋሪ) 12.መምሕር ወመገሥጽ 13.ዘየዐቢ እምኩሉ (ከሁሉ የሚበልጥ) #ጌታችን_መድኃኔ_ዓለም #የመጥምቁ_ዮሐንስን ምትረት አስቦ ይቅር ይበለን:: ጸጋውን: በረከቱንና ክብሩንም ያሳድርብን!🙏🙏 ©መጽሐፈ ስንክሳር # እንኳን_አደረሰን! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 t.me/GhionBookStore1623

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼#ተወዳጅ ግዮናውያን እንኳን ለዘመነ ቅዱስ ማርቆስ በሰላም አሸጋገረን! #እንኳን_አደረሳችኹ!🌼
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 🌼#ተወዳጅ ግዮናውያን እንኳን ለዘመነ ቅዱስ ማርቆስ በሰላም አሸጋገረን! #እንኳን_አደረሳችኹ!🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼☘️☘️☘️☘️☘️☘️☘️☘️☘️☘️🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 #አምላካችን  ቅዱስ እግዚአብሔር አእምሮን ኹሉ የምታልፍ ሰላሙን እየቸረን በቁጣ ያይደለ በምህረቱ ዘወትር እየተዘከረን 'ይህችን ዓመት ተወኝ' ስንለው ልቡን ሳያጸና የተወደደችውን ይህችን ዕለት ያሳየን የጨመረልን ፤ ይመስገንልን ! እርሱ ዓመትን ሲጨምርልን በእኛ ላይ አላማ አለውና እኛም መጪውን ዘመን #በይቅርታ፤ በፍቅር፤በትኅትና፤ በበጎነት፤በታጋሽነት፤በየዋኀት ና በንጽሕና .... በመሰሉት በጎ ምግባራት ኹሉ ጥሙዳን ለመኾን አላማ ይዘን ደግሞም ሱታፌ አምላክ እያገኘን ወደ ቅዱስ እርሱ እርሱንም ወደ መምሰል የምናድግበት ያድርግልን ዘንድ በጎ ፈቃዱ ይኹንልን! ✨#ግዮን_መጻሕፍት ለመላው #የግዮን ቤተሰቦች ፳፻፲፰ የተባረከ ዓመት ይኾን ዘንድ እነህዲኹም ዓመቱን ብቻ ሳይኾን ስብእናችንም የሚቀየርበት፤ በዓሉም የፍቅርና የመተሳሰብ ያድርግልን፥ እያልን  በአያሌው የመሻት ስሜት ኾነን የሀገራችንን ሰላም እና አንድነት የቤተክርስቲያንንም ሰላምና ሉአላዊነት ሰፍኖ የምናይበት ይኹንልን ብለን ተመኘን  !🙏 #መልካም_አዲስ_ዓመት

📖'አባቶችህን፡ እወቅ'📖 'አባቶችህን፡ እወቅ፡ 'በሚል ፡ርዕስ ፡የተዘጋጀው፡ ይህ ፡መጽሐፍ ፡የዚህን ፡ነገረ ፡አበው፡ ትመህርት ፡ዓላማ፡ ለማሳካት፡ በሚረዳ መልኩ፡ ጥሩ ፡ኾኖ ፡የተዘጋጀ ፡መጽሐፍ
📖'አባቶችህን፡ እወቅ'📖 'አባቶችህን፡ እወቅ፡ 'በሚል ፡ርዕስ ፡የተዘጋጀው፡ ይህ ፡መጽሐፍ ፡የዚህን ፡ነገረ ፡አበው፡ ትመህርት ፡ዓላማ፡ ለማሳካት፡ በሚረዳ መልኩ፡ ጥሩ ፡ኾኖ ፡የተዘጋጀ ፡መጽሐፍ ፡ነው። #እኔ፡በበኩሌ፡ እንዲዘጋጁ ከምመኛቸው፡መጻሕፍት፡መካከል፡ አንደኛው፡ይህ ፡መጽሐፍ  ፡ነበር ።ስለኾነም ብዙ ፡ምንጮችን  ፡መመልከትን፡ የሚያሻውንና፡ ለይቶ፡ ጨምቆ ፡ለማቅረብ ብዙ ድካም ፡የሚጠይቀውን ፡ሥራ  በመሥራት፡ይህን መጽሐፍ  ፡አዘጋጅቶ ስላቀረበልን ወንድማችን #ዲያቆን_አቤል_ካሳሁንን ፡ከልብ ፡እያመሰገንኩ፡ እኛም፡ አንብበን ፡እንጠቀምበት ፡ዘንድ፡ እግዚአብሔር ፡ይርዳን ፡እላለሁ ። #መምህረ_ቤተክርስቲያን_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ ➮ለተወሰነ ጊዜ ጠፍቶ የነበረው ይህ እጅግ ተፈላጊ እንዲኹም አስፈላጊ መጽሐፍ በድጋሚ የታተመ ቢኾንም ጥቂት ኮፒ ብቻ ስለኾነ የታተመው እንዳያመልጠን ..! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

ጷግሜ ፫ ✨ እንኳን አደረሰን✨ ዛሬ የበረቱ የዚኽቺ ኅብረት አባሎች ዘሬ ሌሊት [ጳጕሜን 2 ለ3 አጥቢያ] እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር በዓመቱ ቀኖች ቍጥር ልክ [365 ጊዜ] 'አቡነ ዘበሰማያት'ን ሲ
ጷግሜ ፫ ✨ እንኳን አደረሰን✨ ዛሬ የበረቱ የዚኽቺ ኅብረት አባሎች ዘሬ ሌሊት [ጳጕሜን 2 ለ3 አጥቢያ] እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር በዓመቱ ቀኖች ቍጥር ልክ [365 ጊዜ] 'አቡነ ዘበሰማያት'ን ሲጸልዩ በምስጋና ነደው እየበሩ መላእክትን በግብር መስለው ያድራሉ። እኛ በእነሱ ልክ [አባታችን ኾይን 365 ጊዜ] መጸለይ ቢያቅተን በአቅማችን ልክ [7 ጊዜም 12 ጊዜም እንደየተቻለን..] በምስጋና እንተባበራቸው። ነፍሳችን በጸሎት ቅዱሳኑን ትተባበራቸው ዘንድ #እግዚአብሔር ያበረታልን!!            ♱♱♱♱♱♱♱ 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623a

🌿🌿🌿🌿🌿 ጷግሜ ፫ ✨ እንኳን አደረሰን✨ ዛሬ የበረቱ የዚኽቺ ኅብረት አባሎች ዘሬ ሌሊት [ጳጕሜን 2 ለ3 አጥቢያ] እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር በዓመቱ ቀኖች ቍጥር ልክ [365 ጊዜ] 'አቡነ
🌿🌿🌿🌿🌿 ጷግሜ ፫ ✨ እንኳን አደረሰን✨ ዛሬ የበረቱ የዚኽቺ ኅብረት አባሎች ዘሬ ሌሊት [ጳጕሜን 2 ለ3 አጥቢያ] እንቅልፍ በዓይናቸው ሳይዞር በዓመቱ ቀኖች ቍጥር ልክ [365 ጊዜ] 'አቡነ ዘበሰማያት'ን ሲጸልዩ በምስጋና ነደው እየበሩ መላእክትን በግብር መስለው ያድራሉ። እኛ በእነሱ ልክ [አባታችን ኾይን 365 ጊዜ] መጸለይ ቢያቅተን በአቅማችን ልክ [7 ጊዜም 12 ጊዜም እንደየተቻለን..] በምስጋና እንተባበራቸው። ነፍሳችን በጸሎት ቅዱሳኑን ትተባበራቸው ዘንድ #እግዚአብሔር ያበረታልን!! ♱♱♱♱♱♱♱ ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖ኦሪት ዘፍጥረት 📚 ...✍️ኦሪት ዘፍጥረት የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ-ፍጥረት፣ ... መሠረት ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት ብዙ መተር
📖ኦሪት ዘፍጥረት 📚 ...✍️ኦሪት ዘፍጥረት የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ዋና ትምህርቶች ማለትም የነገረ ድኅነት፣ የነገረ ሰብእ፣ የነገረ ሥነ-ፍጥረት፣ ... መሠረት ነው፡፡ ኦሪት ዘፍጥረት ብዙ መተርጉማን ትኩረት ሰጥተው በስፋትና በጥልቀት ካብራሯቸውና ከተረጎሟቸው ቅዱሳት መጻሕፍት አንዱ ነው፡፡ #እኔ_ያደረግሁት ከእነዚህ የተለያዩ አባቶች፣ ሊቃውንት እና መተርጉማን ሐሳቦች መካከል የተወሰኑትን አሰባስቦ ማቅረብ ነው፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን መርሐ ግብር በተከታታይ ከቀረበው የኦሪት ዘፍጥረት ማብራሪያ ትምህርት የመጀመሪያዎቹ ዐሥር ምዕራፎች ትምህርት (ከምዕራፍ 1 -10) በዚህ መጽሐፍ ቀርቧል፡፡ በመጻሕፍት ትርጓሜ ውስጥ ልብ ሊባሉ የሚገባቸው ጉዳዮች አሉ። ከእነዚህ አንዱ ጉዳይ በቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ አስተምህሮ (ዶክትሪን) እና በመተርጉማን ግላዊ አስተያየቶች መካከል ያለውን ልዩነት በሚገባ ለይቶ ማወቅ ነው፡፡ ..... በዚህ #መጽሐፍ የቀረቡትን የመተርጉማን ትርጓሜዎችና ማብራሪያዎች በአግባቡ ተረድተን #ለሕይወት እንድንጠቀምበት #የቃሉ ባለቤት #እግዚአብሔር ይርዳን፡፡ አሜን! #ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ #ኦሪት ዘፍጥረትን ብትን አድርጎ የሚያብራራ ብሎም ገቢውን ለታላቁ ማኅበር #ማኅበረ_ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት የተበረከተ ነው። ፨ይህ#መምህረ_መምህራን_ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ አበርክቶት ጥቂት ብቻ ነው የቀረ ሲኾን ይያዝ!!! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖📖📖📖📖 #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ_እና_ሥራዎቹ #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ መንግሥት አጠቃላይ ቅጥር ግቢው በሁለት ዙር የተከበበ እና የታጠረ ሥፍራ ሲሆን፤ በአጥሩ ዙሪያም በቁጥር አሥራ ሦስት የሚደርሱ
📖📖📖📖📖 #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ_እና_ሥራዎቹ #አፄ_ዘርዐ_ያዕቆብ መንግሥት አጠቃላይ ቅጥር ግቢው በሁለት ዙር የተከበበ እና የታጠረ ሥፍራ ሲሆን፤ በአጥሩ ዙሪያም በቁጥር አሥራ ሦስት የሚደርሱ የተለያዩ መጠሪያ ሥምና ተግባር(ግብር) ያላቸው በሮች (ዕድሞዎች) እናገኛለን። እነዚህ በሮች እያንዳንዳቸው የተለያየ ተግባር እና ስም ያላቸው ናቸው፡፡ ተግባራቸውን ወደ ኋላ የምናየው ሆኖ በስም ደረጃ ውድነሽ ደጅ፣ ጸር ዋጀት ደጅ፣ መርድ ደጅ፣ መጋረጃ ደጅ፣ መስቀል ደጅ፣ ውላጅ ደጅ፣ ግምጃ ማርያም ደጅ፣ ኢየሱስ ደጅ፣ ቁልፍ ደጅ በመባል ይታወቁ ነበር፡፡ በቤተ መንግሥቱ ውስጥ በርካታ ቤቶችና ድንኳኖች የነበሩ ሲሆን፤ የቀኝ በሀልቲሐት ቤት፣ የግራ በሀልቲሐት ቤት፣ የባሀልቲሐት ሽና ቤት፣ የንግሥቷ እናት ቤት፣ የዐቃቢ ሰዓት ቤት፣ የቀኝ ብሕትወደድ ቤት፣ የግራ ብሕትወደድ ቤት፣ የግብፅ ጳጳስ ቤት፣ የንጉሥ ዋና አዳራሽ ቤት፣ የሰቀላ (የጥበቃዎች ቤት፣ የአንበሶች ቤት፣ ከዚህ በተጨማሪ የቀኝ ጀጎላ ሦስት የተለያዩ ድንኳኖች(ደበና)ነበሩት፡፡ በመካከላቸው የተተከለው ድንኳን ዱለት ቤት፣ በቀኝ በኩል ያለው ግምጃ ድንኳን እና በግራ በኩል ያለው አቋት ግምጃ ድንኳን ተብሎ ይጠራ እንደነበረ ተዘግቦ ይገኛል።       [ከውስጥ ገጽ..] 🌿#ይህ የንጉሡ ዜና መዋዕል እኛ ዘንድ አለ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖❖ ሀብታም እና ደሀ📖 ...ባለጸጋው ድሀውን በየዕለቱ ደጃፉ ላይ ዓይኑ ስር ወድቆ እያየው ምንም ዓይነት ምጽዋት አልሰጠውም፡፡ ይህ ምስኪን ድሀ በጎዳና ወይም በተሰወረ በጠባብ መተላለፊያ ስላልወ
📖❖ ሀብታም እና ደሀ📖 ...ባለጸጋው ድሀውን በየዕለቱ ደጃፉ ላይ ዓይኑ ስር ወድቆ እያየው ምንም ዓይነት ምጽዋት አልሰጠውም፡፡ ይህ ምስኪን ድሀ በጎዳና ወይም በተሰወረ በጠባብ መተላለፊያ ስላልወደቀ ባለጸጋው አንዴ ወይም ሁለቴ ወይም ብዙ ጊዜ ሲገባና ሲወጣ አይቶታል፡፡ ነገር ግን ሲገባም ሆነ ሲወጣ በውድም ሆነ በግድ ሊያየው በሚችልበት ....... ...ስለ መተላለፋችን ምንም ዓይነት ቅጣት የማንቀበል ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር ሕሊናን የሚያህል ፈራጅ ዳኛ በውስጣችን አይፈጥርም ነበር፡፡ በዚህም እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን ፍቅር አሳይቷል፡፡ እግዚአብሔር ስለ መተላለፋችን ከዚህ በኋላ በሚኖረው ሕይወት የሚጠይቀን ቢሆንም የማያዳላውን ዳኛ ሕሊናን ግን በውስጣችን ፈጠረ፡፡ ይህ ዳኛ በዚህ ዓለም ሳለ ይረዳናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ያለው ..... [ከመጽሐፉ የተወሰደ] ➮ወገን ራስን ለመፈተሽ አይነተኛ መርማሪ ነው ...! እመነኝ የት ጋር እንዳለህ ይነግርሀል!..ይያዝዝ📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ጾመ ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ📖 #የቅዱስ ያሬድ ዋና ሥራ አባቶቻችን በልዩ ትጋትና ጥንቃቄ ባደራጁበት ስልት ተተርጉሞ መቅረቡ ለብዙኃን ግልጋሎት እንዲሰጥ ስለሚያስችል የትርጉም ሥራው አስፈላጊነት አጠ
📖#ጾመ ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ📖 #የቅዱስ ያሬድ ዋና ሥራ አባቶቻችን በልዩ ትጋትና ጥንቃቄ ባደራጁበት ስልት ተተርጉሞ መቅረቡ ለብዙኃን ግልጋሎት እንዲሰጥ ስለሚያስችል የትርጉም ሥራው አስፈላጊነት አጠያያቂ አይደለም። ድንቅ ሥራ ነው። የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐተ ማኅሌት ምን ያኽል ድንቅና ውስብስብ እንደኾነ ያሳያል። እያንዳንዱ የድጓ ዘር ከየትኛው የቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚጣቀስ፣ ምን እንደሚጨምር፣ ለዝማሬ ስልት ሲባል ምን ቃላት መደበኛ ሥፍራቸውን እንደሚለውጡ፣ ኹነኛ ቃላትን በመደጋገም የዕለቱን ዋና ጭብጥ እንዴት እንደሚያጎሉ፣ በጥቅሉም ቅዱስ ወንጌል በጾም ሳምንታት እንደምን ባለ ክብርና ሞገስ እንደሚሰበክ ለመማር ለሚፈልጉ መጽሓፉ ራሱን ችሎ መማሪያ ይኾናል። የጥንታዊት ኢትዮጵያዊት ርትዕት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ነገረ መለኮትም ኾነ ያሬዳዊ ሥርዐተ አምልኮ የተቀረው ክርስቲያናዊ ዓለም ገና ወደፊት እየተሳበ የሚቀርብበት እንጂ የገቡት ሳይቀሩ የሚወጡበት እንዳይኾን በደገኛ ትውፊቶቻችን ላይ በትጋት የሚሠሩ የትርጉም ሥራዎች እጅግ አስፈላጊ ናቸው። ይኸው ሥራ አንዱ ነው። መልካም ንባብ! #ይኩኖ አምላክ መዝገቡ የኢትዮጵያ [ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት ዋና ዳይሬክተር] 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ትምህርተ ጽድቅ📖 መጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ዓይነት ሰብሎችን እንደሚያፈራ ሰፊና ለም እርሻ በመኾኑ በጥሬው እሸታቸው ሊበላ የሚችሉ ዓይነት የኾኑ ለማንም ሰው ለመረዳት ቀላል የኾኑ ሐሳቦች እንዳሉት ሁሉ፡ ካልበሰሉ በቀር ለጤና ከባድ አንደ ኾኑ አትክልቶች ከመሠረታዊው የቤተ ክርስቲያን ትምህርት አንጻር ካልተብራሩና ካልተተረጎሙ በገጸ ንባብ ብቻ እንውሰዳቸው ከተባለ ለሕይወት ከበድ የሚሉ ሐሳቦችም አሉት። መጽሐፍ ቅዱስን ያስገኘችውና በቀኖና ለይታና ጠብታ የሰጠችን ቅድስት ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን እንደ ኾነች ሁሉ ሐሳቡን ለመረዳትም ይህቺ ቤተ ክርስቲያን የግድ ታስፈልገናለች። ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ስሙ ካልኾነ በስተቀር አውነተኛ ወንጌል ሊኖር አይችልምና። ዲያቆን ዮሐንስ በዚህ መጽሐፉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በነገረ ክርስቶስ ዙሪያ ያሉ ጠንከር ባለ ኹኔታ የተገለጹ ጉዳዮችን አያነሣ ጥሩ በኾነ ስፋትና ጥልቀት አብራርቷቸዋል። ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅና በእርሱ ማመን ማለት እርሱ ራሱን በገለጠበትና በኾነው ትክክለኛ ማንነቱ ማመን ነው እንጂ እንዲሁ አያንዳንዱ ሰው ለራሱ በመሰለው መንገድ ማመን ማለት አይደለም። ስለዚህ በነገረ ክርስቶስ ዙሪያ ያሉ ጠንካራ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሐሳቦችን ቤተ ክርስቲያናዊ በኾነ መንገድ መረዳት ለመዳን የግድ ነው። ይህ የዲያቆን ዮሐንስ መጽሐፍ በዚህ ረገድ መልካም አስተዋጽኦ የሚያደርግ መጽሐፍ ነው። ከዚህም በተጨማሪ በዚህ መጽሐፉ በነገረ ማርያም ዙሪያ የሚነሡ አንዳንድ ጉዳዮችንም እንደዚሁ ማብራሪያ ሰጥቶባቸዋል። ዲያቆን ዮሐንስ መጽሐፉን ለመጻፍ ከተጠቀማቸውና ከጠቀሳቸው ምንጮች አንጻር ሲታይ እንኳ ሰፊ የንባብ አድማስ ያለው መኾኑን በግልጽ ማየት ይቻላል። በመጽሐፉ ያካተታቸው ጉዳዮችና ጉዳዮቹን ለማብራራት የሄደበት ርቀትና ስፋት አሰይ! በርታልን! እደግልን! የሚባል ወንድም መኾኑን ይመስክራሉ። ወንድማችንም ለወደፊቱም በዕውቀትና በመንፈስ የበለጠ ጎልብቶ ለቤተ ክርስቲያን የጀመረውን አገልግሎት አስፍቶ እንዲቀጥል ተስፋዬና ምኞቴ ታላቅ ነው። ይህን መጽሐፍ አንብቡት ትጠቀማላችሁ! ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ©መጽሐፏም እኛ ዘንድ ውስን ቅጂ ብቻ ያለ ሲኾን እንዳታልቅባችኹ ከወዲኹ ትያዝ......! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።  [ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?] 📱ይደውሉልን ፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

አዎ:- የእመቤታችን የማርያም ዐሳብ እንደ አምላክ ዐሳብ ነው! ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "እኛ የክርስቶስ ልብ አለን" ብሏል። ፩ቆሮ ፪: ፲፮። ልብ ማለት አዕምሮ ነው። ዐሳብ የሚቀዳው ከልብ ነው። "
አዎ:- የእመቤታችን የማርያም ዐሳብ እንደ አምላክ ዐሳብ ነው! ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "እኛ የክርስቶስ ልብ አለን" ብሏል። ፩ቆሮ ፪: ፲፮። ልብ ማለት አዕምሮ ነው። ዐሳብ የሚቀዳው ከልብ ነው። "አምላክህንም እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ፥ በፍጹምም ነፍስህ፥ በፍጹምም ኀይልህ ውደድ።" ሲል አዕምሮን ወይም ዐሳብን ያመለክታል። ዘዳ ፮ : ፭። ዐሳብ፣ ልብ እና አዕምሮ የሚሉትን የሚተካኩ ቃላት በተለዋዋጭነት ልንጠቀምባቸው እንችላለን። ቅዱስ ጳውሎስ እኔ ብቻ የክርስቶስ ልብ አለኝ አለማለቱንም ልብ እንበል። እኛ ነው ያለው። እኛ ሲል እርሱን የሚመስሉትን፣ የሚያኽሉትን፣ የሚበልጡትንም ኹሉ ያጠቃልላል። ከሚበልጡት አንዷ ድንግል ማርያም ናት። ቅዱስ ዳዊትን እግዚአብሔር እንደ ልቤ ብሎታል። "እንደ ልቤ የኾነ ሰው ፈቃዴንም ኹሉ የሚያደርግ የእሴይን ልጅ ዳዊትን አገኘሁ" እንዲል። ሥራ ፲፫: ፳፪። እግዚአብሔር የእጁን ፍጡር እንደ ልቤ ብሎታል። እርሱ ያልቸገረውን አንተን ለምን ይቸግርሃል? ቅዱስ ጳውሎስ እኛ ካላቸው መኻል ከኹሉ በላይ ቀዳሚ የምትኾነው የእመቤታችን ዐሳብ እንደ አምላክ ዐሳብ ነው ማለት እጅግ በጣም ትክክል መኾኑን ተመልከት። በተለያየ ጥፋት ሲወድቁ ሲነሡ የኖሩት ቅዱስ ዳዊት እና ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ደረጃ ሲገለጡ በዘመኗ ኹሉ ያለ ስሕተት ያለ ኃጢአት በፈቃደ እግዚአብሔር ብቻ የኖረች እመቤት እንዲህ ስትገለጥ ለምን አመመህ? ነው ወይስ ከአምላክ ሕሊና እኩል ያደረግናት ይመስልሃል? እንደ እርሱ ማለት እንዳልኾነ ቅዱስ ዳዊት እና ቅዱስ ጳውሎስ የተገለጡበትን መላልሰህ አንብብ።

# ከ መምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተገኙ እንቁ መጻሕፍት ©አነዚኽን ጣፋጭ ምግቦች ተመግበዋቸው ይኾን...? 📚#ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ሕይወቱ እና ትምህርቱ እና # ቅዱስ ዮሐ
# ከ መምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተገኙ እንቁ መጻሕፍት ©አነዚኽን ጣፋጭ ምግቦች  ተመግበዋቸው ይኾን...? 📚#ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ሕይወቱ እና ትምህርቱ እና # ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ #ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ሕይወቱ እና ትምህርቱ ከሕይወቱ ቅምሻ [....አባ እለእስክንድሮስም አትናቴዎስን በመንበረ ፓትርያርኩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርትና ሥርዓት እያስተማረ አሳደገው፤ እርሱም ተወዳጅ ልጅ ሆነው፡፡ ከዚሁም ጋር ሰዋስው፣ ፍልስፍና፣ ክሂሎተ ነቢብና ሌሎች በዘመኑ የነበሩ ትምህርቶችንም በሚገባ ተማረ፡፡ ቆይቶም ለመዓርገ ምንኵስና በቃ᎓᎓ በቅድስናው፣ በሞያውና በግብረ ገብነቱ እንከን የሌለው ወጣቱ አትናቴዎስ በ23 ዓመቱ ....] #ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ ከሕይወቱ ቅምሻ [....ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ራሱን ከዚህ ዓለም የበለጠ ለመሰወርና ብቻውን ዘግቶ ለመኖር በመፈለጉ ወደ ዋሻ ውስጥ ገብቶ በብሕትውናና በጽኑ ትኅርምት ለሁለት ዓመት ሲጋደል ኖረ። በዚያም በትጋሃ ሌሊት፣ ለራሱ ዕንቅልፍ በመከልከል፣ በቀዊም፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን በቃል በማጥናት፣ በጸሎትና በተዘክሮ ኖረ በመቀጠልም ....] 【#ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ】 [..ሁሉም የሌሊት ቅዠቶች ኖረዋል፡፡ ሌሊቱ አልፎ ቀኑ በመምጣቱ ከጨለማው ጋር አብረው የጠፉ ህልሞች ብቻ ነበሩ፡፡ ያለ መስሎ ታይቶ እንደጠፋ ጥላ፣ ወደ አየር ተኖ እንደጠፋ ጢስ፣ ሟሙቶ እንዳለቀ አረፋ፣ እንደተበጣጠሰ የሸረሪት ድር ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሁል ጊዜ ይህንን መንፈሳዊ መዝሙር እንዘምራለን፡- “ሁሉ ከንቱ፣ የከንቱ ከንቱ ነው” የሚለውን፡፡]›› 👉መጻሕፍቱን በግዮን መጻሕፍት ያገኙታል ! ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

#በእረፍታቸው ጊዜ የጻድቁ_አባታችን_ወርቃማ_ምክሮች አብረዋቸው ለነበሩት ደቀመዛሙርቶቻቸው የመከሩት የመጨረሻ ምክር] ገድለ-አቡነ ተክለሃይማኖት ምዕ ፶፬፥፴፪-፵፪ ፵. ይኽንንም ብትጠብቁ በእውነት ል
#በእረፍታቸው ጊዜ የጻድቁ_አባታችን_ወርቃማ_ምክሮች አብረዋቸው ለነበሩት ደቀመዛሙርቶቻቸው የመከሩት የመጨረሻ ምክር] ገድለ-አቡነ ተክለሃይማኖት ምዕ ፶፬፥፴፪-፵፪ ፵. ይኽንንም ብትጠብቁ በእውነት ልጆቼ ናችኹ ፣ የሕይወትንም ፍሬ የምታፈሩ ትኾናላችኹ ፤ ወደ-እግዚአብሔርም ፊት በክብር ትደርሳላችኹ ፤ ኤልሳዕም ስለ-እኔ አባት ይኹናችኹ እስክልክባችኹም ድረስ ከእኔ በኋላ ይቁምላችኹ ፤ ነገር ግን በሹመቱ አይቆይበትም። ፵፩. ልጆቼ! ሰላም ለእናንተ ይኹን ፤ እንግዲኽ ወዲኽ ግን ተሰናበትኋችኹ ፤ #የእግዚአብሔር ፍቅሩ የክብሩም ባለሟልነት የረዳትነቱም ሀብት ዘወትር ከእኔና ከኹላችኹም ጋር ለዘለዓለሙ በእውነት ይኑር።                       ♱♱♱ ለቅዱሳኑ ምልጃ የማይጸን ፣ ኃይል በምታደርግ ክብርት ጸሎታቸው ሲያስቡን እኛም በእነሱ ጸሎት/ምልጃ ለመጠቀም የሚያስችል ሕይወት ለመኖር ፣ አኹንም ለድክመታችን ጸሎታቸው ትርዳን። የከኮበ-ቅዱሳን የአባታችን #የአቡነ_ተክለሃይማኖት ጸሎት እና በረከት ለኹላችንም ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች በያለንበት ቦታና ኹኔታ ይድረሰን ለዓለም ለዘለዓለሙ አሜን!!🙏