es
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram Assaye Derbie

El canal Assaye Derbie (@asayede) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 333 suscriptores, ocupando la posición 2 647 en la categoría Bloques y el puesto 2 350 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 333 suscriptores.

Según los últimos datos del 25 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -108, y en las últimas 24 horas de -4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 38.62%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 12.61% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 538 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 808 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 33.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 26 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Bloques.

14 333
Suscriptores
-424 horas
-317 días
-10830 días
Archivo de publicaciones
ብአዴን ሆይ የባሕር ዳሩን ስብሰባ እኔ የምመራው ይመስል "ስብሰባው ላይ መገኘት አለብህ" ብለህ ለምን እንደገገምክ መስከረም አበራ ላይ ተፈጻሚ ካደረግከው እገታ ተረድቻለሁ። ያም ሆኖ ግን እስራትን
ብአዴን ሆይ የባሕር ዳሩን ስብሰባ እኔ የምመራው ይመስል "ስብሰባው ላይ መገኘት አለብህ" ብለህ ለምን እንደገገምክ መስከረም አበራ ላይ ተፈጻሚ ካደረግከው እገታ ተረድቻለሁ። ያም ሆኖ ግን እስራትን ቀርቶ ሞትን ፈርቼ ለአማራ ሕዝብ ድምጽ መሆኔን የማላቆም መሆኑን እነግርኻለሁ።

ዘመነ ካሴ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔ጎጠኛ አክቲቪስቶች የሆነ ጎጥ ተወካይ ያደርጉታል፡፡ እሱ ግን በንግግሩም ሆነ በተግባሩ እንደ ኢትዮጵያ ሲያስብ ካልሆነ በቀር ከአማራነት ወርዶ ጎጥ ለጎጥ ሲሳብ የተገኘ
ዘመነ ካሴ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔ጎጠኛ አክቲቪስቶች የሆነ ጎጥ ተወካይ ያደርጉታል፡፡ እሱ ግን በንግግሩም ሆነ በተግባሩ እንደ ኢትዮጵያ ሲያስብ ካልሆነ በቀር ከአማራነት ወርዶ ጎጥ ለጎጥ ሲሳብ የተገኘበት ቀን የለም፡፡ ➔በሌላ መልኩ ደግሞ የአንድ አውራጃ ጠባቂ የሚያደርጉት ኃይሎች ‹‹እንደ ብርጋደር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ሊዳፈኑ ወይም ደግሞ እንደ ብርጋደር ተፈራ ማሞ ሊታፈኑ የሚገባቸው አማራዎችን ዘርዝራችሁ አምጡ›› የሚል ትዕዛዝ ከበላይ አካል ሲሰጣቸው ‹‹አማራ›› ብለው በቀዳሚነት የሚጽፉት የእሱን ሥም ነው፡፡ ➔ጥቅመኛ እና ተከፋይ ዙምቤዎች ካዝናውን በገንዘብ ሞልተው ይመቀኙታል፡፡ የዓላማው ግዝፈት ተረድተው የሚደግፉት ወገኖች ግን ‹‹የትኛውም ሐሳብ ያለ ገንዘብ ሊሳካ አይችልም›› በማለት ይከላከሉለታል፡፡ ‹‹ምን እንገዝህ?›› እያሉም ይጠይቁታል፡፡ ➔የመንግሥት ካድሬዎች የሕብረተሰቡን ሰላም በማጥፋት ይከስሱታል፡፡ ድፍን የባሕር ዳር ወጣት ግን ስቴዲየም ገብቶ ሥሙን እያነሳ ይዘምርለታል፡፡ ➔አንዳንድ የጎረቤት አክቲቪስቶች የሕዝባቸው ጠላት አድርገው ያብጠለጥሉታል፡፡ እሱ ግን ‹‹ክፋት ለማንም፣ በጎነት ለሁሉም›› በሚል አስተሳሰብ የሚመራ በመሆኑ ስለ አማራ እኩልነትና ነጻነት ከመናገር ባለፈ ሕዝብን ቀርቶ ፖለቲከኞችን የሚያንቋሽሽ ቃል ተንፍሶ አያውቅም፡፡ ➔በሌላ መልኩ ደግሞ እሱ እራሱን ከሌሎች የትግል ወንድሞቹ በላይ አድርጎ ያወራበት ቀን ባይኖርም የሚዘምቱበት ኃይሎች ግን ከወሬ የዘለለ ተግባር እንደሌለው በሚገልጽ ሐሜታቸው ዝቅ ዝቅ ሊያደርጉት ይሞክራሉ፡፡ ግን ደግሞ… "ፋኖ መመታት አለበት" ሲባል ቀድሞ ወደ ጭንቅላታቸው የሚመጣው የእሱ መልክና የእሱ ሥም ነው፡፡ አማራን የማጥቃት ዘመቻቸውን መጀመር የሚሹትም ከእሱ ነው፡፡ አከብርኻለሁ ክንዴ!

በአማራ ሕዝብ ላይ ከታወጀው የጥፋት ዘመቻ መሀከል እራሳቸውን ላገለሉ አማራዎች አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ በቅርብ ጊዜ ያስተናገድነው የጎንደሩ ክስተት ዋና ዓላማው ፋኖን እና የአማራ ሕዝብን በእምነት ከፋፍ
+2
በአማራ ሕዝብ ላይ ከታወጀው የጥፋት ዘመቻ መሀከል እራሳቸውን ላገለሉ አማራዎች አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ በቅርብ ጊዜ ያስተናገድነው የጎንደሩ ክስተት ዋና ዓላማው ፋኖን እና የአማራ ሕዝብን በእምነት ከፋፍሎ ማጥቃት ነበር፡፡ ከሳምንት በፊት ብአዴን ያዘጋጀው ሽልማትም ዋነኛ ግቡ ‹‹የተወሰነውን ፋኖ በመሸለም፥ አብዛኛውን ፋኖ መልቀም›› የሚል ነበረ፡፡ የሚለቀመው ፋኖ ካለቀ በኋላ ደግሞ ሜዳሊያ ከተሸለመው የፋኖ አንገት ላይ ሰንሰለት ለማሰር የሚያስችል ዘመቻ ይጀመራል፡፡ በተረፈ የአማራ ፋኖን የማፈን ዘመቻው የተጀመረው በወሎ፣ በጎጃምና በሸዋ ምድሮች ቢሆንም… እቅዳቸውን ማክሸፍ ካልቻልን በቀር ዘመቻቸው የሚጠናቀቀው ግን ከሁሉም ዞኖች በላቀ መልኩ የጎንደር አማራ ፋኖን በመምታትና የወልቃይትን መሬት ለእነ ጌታቸው ረዳ በመሥጠት እንዲሁም የአማራ ኤሊትን ሥነ ልቦና በማንኮታኮት ነው፡፡ የአማራ ተወላጆች ሆነው ሳለ በአማራ ሕዝብ ላይ የጥፋት እጃቸውን የዘረጉ የጦር መሪዎችና የክልሉ አመራሮችም ተልዕኳቸውን ባጠናቀቁ ማግስት የበላይ አካልን የክህደት ጥፊ ቀምሰውና ጸጸታቸውን ታቅፈው ይወረወራሉ፡፡ በተረፈ ጠላት ለዳግም ወረራ በተዘጋጀበት ወቅት ፋኖን የማጥፋት ዘመቻ ያስፈለገው የአማራ ሕዝብን ለማክሰም እንጂ የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ ከመሰለህ ተራህ ደርሶ ስትታፈን ወይም ደግሞ ስትወረር እውነቱ ይገባኻል፡፡ እናም ያ እንዳይሆን የምትፈልግ ከሆነ ያቀረቀረ አንገትህን የሚጨፈልቅ ጫማና በፍርሐት የተሸበበ ልብህን የሚደስቅ ሰደፍ ከማስተናገድህ በፊት በአማራ ሕዝብ ላይ የታወጀው የጥፋት ዘመቻ ይቆም ዘንድ የድርሻህን አበርክት፡፡

በመንግሥታዊ ሽብር ስትታመስ እና ደሟ ሲፈስስ የዋለችው የወልዲያ ከተማ ባሁኑ ሰዓት ጓዳናዎቿ ሰው አልባ ሆነዋል። ብአዴን ሆይ ከእንግዲህ አማራ ክልል ላይ ባርነትን የሚሸከም ሕዝብ ስለሌለ የተሰማራኽ
+2
በመንግሥታዊ ሽብር ስትታመስ እና ደሟ ሲፈስስ የዋለችው የወልዲያ ከተማ ባሁኑ ሰዓት ጓዳናዎቿ ሰው አልባ ሆነዋል። ብአዴን ሆይ ከእንግዲህ አማራ ክልል ላይ ባርነትን የሚሸከም ሕዝብ ስለሌለ የተሰማራኽበት የባሪያ ንግድ በኪሳራ መጠናቀቁ አይቀሬ ነው።

photo content

ከአማራ ሕዝብ በተጨማሪ የሜዳው ሚካኤል ካንተ ጋር ይሁን ወንድማለም‼️ በተረፈ ወደ አንተ የሚተኮስ ጥይት ብአዴንን እንደሚገረስስ ጥርጥር የለውም።
ከአማራ ሕዝብ በተጨማሪ የሜዳው ሚካኤል ካንተ ጋር ይሁን ወንድማለም‼️ በተረፈ ወደ አንተ የሚተኮስ ጥይት ብአዴንን እንደሚገረስስ ጥርጥር የለውም።

"እገሌ የተባለውን ፋኖ ሸልሙት፣ እገሌን ደግሞ አፍኑት" የሚለው ጥያቄ ከአማራ ሕዝብ የመጣ ከሆነ እርምጃ ልትወስዱ ስትሞክሩ ወንጀለኛን አሳልፎ በመስጠት ፈንታ "ልጆቼን አታፍኑም" በሚል ተቃውሞ ገንፍሎ የሚወጣው ሕዝብ ከየትኛው ክልል የመጣ ነው? አሳቻ ሠዓትና ቦታ እየመረጡ ታርጋው በተሸፈነ መኪና አፈና ማካሄድስ ለምን አስፈለገ?

እንደ ደረጀ ሃብተ-ወልድ ያሉ ደካማ ካድሬዎች ሆድ እንጂ ኅሊና ያልፈጠረባቸው በመሆኑ ‹‹አትንኩኝ›› የሚለውን የአማራ ሕዝብ ቁጣ መንግሥትን ከመገርሰስና ህውሓትን ከመመለስ ፍላጎት ጋር ሊያገናኙት ሲፍገመገሙ ‹‹በዚህ ልክ መዝቀጥ የሚቻለው እንዴት ነው›› ብዬ እጠይቃለሁ፡፡ ፋኖ የተደራጀው ‹‹የትሕነግ ወረራ እና ጥቃት መደገም የለበትም›› በሚል አቋም መሆኑ እየታወቀ የሚታፈኑትን የፋኖ መሪዎችና የጦር አመራሮች የትሕነግ አጋሮች ሊያደርጓቸው ሲሞክሩ "የጅል ዘፈን ሁልጊዜ አበባዬ" የሚለውን አባባል አስታውሳለሁ። በህውሓት ሕልውና ላይ ዙፋኑን ያደላደለ መንግሥት ተሸክመው ሳለ የሕልውና ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ሦስት ዓመት ሙሉ በተባለበት ‹‹ጁንታ›› የሚል ፍረጃ ዛሬም ለማሳቀቅ ሲጣጣሩ ‹‹ባይበላስ ቢቀር›› እላለሁ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ግን…. ➔ኬንያ ድረስ ሄዶ ከወያኔ ጋር ሲደራደር የነበረው አፋኙ ፊልድ ማርሻል እንጂ የታፈነው ጄኔራል አልነበረም፡፡ ➔ከደብረ ጽዮን ጋር በድብቅ ሲዳራ የከረመውም የእናንተው መንግሥት እንጂ በእነ ጌታቸው ረዳ አንደበት ‹‹ተስፋፊ›› ሲባል የከረመው የአማራ ኤሊት አይደለም፡፡ ➔ፋኖም ትጥቅህን ፍታ ለሚለው ትዕዛዝ ተገዢ ያልሆነው ‹‹ጠላት አለኝ›› ብሎ እንጂ እንደ ትሕ-ኦነጎች ‹‹መንግሥት ነኝ›› ብሎ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን የካድሬዎች የፌስቡክ ፖስት ከጭንቅላት የሚፈልቅ ሳይሆን እንደ በጀት ከመንግሥት የሚለቀቅ በመሆኑ መንግሥትና ህውሓት ሲደራደሩ ‹‹ከሰላም የሚልቅ ነገር›› አለመኖሩን ያስረዱኻል፡፡ እነ ጄኔራል ተፈራ ሲታሰሩ ደግሞ ‹‹ከህውሓት ጋር በመደራደር ወንጀል እንደተጠረጠሩ›› ይነግሩኻል፡፡ መንግሥት በጠላት ላይ አምርሮ ወደ ጦር ሜዳ ሲገሰግስ ‹‹ልበ-ቆፍጣና›› መሆኑን ይተርኩልኻል፡፡ ድርጎ ሰፋሪው አካል በአገር ላይ ቆምሮ ትግሉን አቋርጦት ሲመለስ ደግሞ ‹‹ልበ ሰፊ›› መሆኑን ይገልጹልኻል፡፡

የወሎ ዩኒቨርስቲ መምህር እና የደቡብ ወሎ ዞን ፋኖ አስተባባሪ የሆነው ወንድማችን ዘላለም ጫኔ ለግል ጉዳይ ወደ ጎጃም በሄደበት ወቅት እገታ ተፈጽሞበታል። ስለሆነም ይህ ወንድማችን ይፈታ ዘንድ ድምጽ
የወሎ ዩኒቨርስቲ መምህር እና የደቡብ ወሎ ዞን ፋኖ አስተባባሪ የሆነው ወንድማችን ዘላለም ጫኔ ለግል ጉዳይ ወደ ጎጃም በሄደበት ወቅት እገታ ተፈጽሞበታል። ስለሆነም ይህ ወንድማችን ይፈታ ዘንድ ድምጽ ልንሆነው ይገባል።

ዶክተር አያሌው ታለማን ያፈናችሁ የደሴ አመራሮች ወንድማችንን ልቀቁት። የሚገርመው ነገር ዶክተር አያሌው የአብን ጠቅላላ ጉባዔ አባል ቢሆንም አብን እንደ ፓርቲ አንዲት ቃል እንኳን መተንፈስ አልፈለገ
ዶክተር አያሌው ታለማን ያፈናችሁ የደሴ አመራሮች ወንድማችንን ልቀቁት። የሚገርመው ነገር ዶክተር አያሌው የአብን ጠቅላላ ጉባዔ አባል ቢሆንም አብን እንደ ፓርቲ አንዲት ቃል እንኳን መተንፈስ አልፈለገም።

ለብአዴን አሳዬ ደርቤ **** ‹‹በወቅታዊ ጉዳይ ተመካክረን አንድ አቋም እንያዝ›› በሚል እሳቤ የጄኔራል ተፈራ እስር ቤትና የአቫንቲ ሆቴል ቤት ካለበት የባህር ዳር ከተማ ባዘጋጀኸው ስብሰባ ላይ ተሳታፊ እሆን ዘንድ የላክልኝ ጥሪ ደርሶኛል። ሆኖም ግን አቋምህን ከአቋሜ ጋር ሳስተያየው በመሃከላችን ያለው ልዩነት በአንድ ስብሰባ የሚፈታ ሆኖ ስላላገኘሁት ከዚያ በፊት የፓርቲው ጉምቱ ጉምቱ አመራሮች ባንዳንድ ጉዳዮች ላይ ልምድና ተሞክሯቸውን ያካፍሉኝ ዘንድ እንደሚከተለው እጠይቃለሁ፡፡ ይድረስ ለአቶ አገኘሁ- ይድረስ ለደመቀ ይድረስ ለተመስገን- ይድረስ ለአቶ ላቀ በእንጉልፋቶ መንግሥት- ጸጉሬ፣ ጨጓራዬ- ጋይቶ ስላለቀ፤ አስተምሩኝ እስቲ- ምግብ ላይ መመሰጥ- ሕዝብ እየደቀቀ፡፡ ክቡር ፕሬዝዳንቱ- ዳግማዊ እና ብናልፍ ይታክታልና- መንግሥት በሌለበት- ስለ መንግሥት መጻፍ በነጋ በጠባ- በአገሩ በቀየው- አማራ ሲወድም ምን አገባኝ ብዬ- ከብአዴን ጋራ- እንዲይዝ አንድ አቋም ከስብሰባው በፊት- መድረክ ተዘጋጅቶ- ልምዳችሁን ልቅሰም፡፡ ምክንያቱም… አማራነት ቃር ነው- ሟች ሆኖ ሰንብቶ- ገዳይ ጋር መወገዝ አማራነት ጣር ነው- በመጣ በሄደው- በሤራ መገዝገዝ ጠላት ሲጠብቁ- ከጀርባ መደብደብ- በመንግሥት አፈሙዝ፡፡ አዴፓ ግን ሰላም- ብአዴን ግን ጤና ሕዝብን አስረክቦ-ነጭ ቪላ መቀበል- V8 መኪና ኀሊናን አስንፎ- ለከርስ መታገል- ለማይሞላ ካዝና እናም ብአዴን ሆይ- አገርና ታሪክ- በተዋረዱበት- በባንዳነት ዘመን ስቃይ ስለሆነ- የበላይ ዘለቀ- የካሳ ልጅ መሆን በሆድህ ተገዝተህ- በኦነግ ጠመንጃ- ፋኖን ስታሳድድ ‹‹ሙትቻ ድርጅት››- እያልኩ ከምጮህ- ሰርክ ከምናደድ አለማምደኝ እስቲ- ኅሊናን መረሸን- ማንነትን መካድ››

ማንን ይሆን የምታምነው? ለማን ይሆን የምትታመነው? በመንግሥትነት እና በጠላትነት መሃከል'ስ የምትወዛወዘው እስከ መቼ ድረስ ይሆን? የሆነው ሆኖ... ትናንት "መንግሥት ሁን" ስትባል ጠላት ሆነህ አ
ማንን ይሆን የምታምነው? ለማን ይሆን የምትታመነው? በመንግሥትነት እና በጠላትነት መሃከል'ስ የምትወዛወዘው እስከ መቼ ድረስ ይሆን? የሆነው ሆኖ... ትናንት "መንግሥት ሁን" ስትባል ጠላት ሆነህ አማራን ለማዳከም ስትሞክር ፋኖ እንዲፈጠር አድርገኻል። በአራት ዓመታት ውስጥ የፈጸምካቸው እኩይ ድርጊቶችም፤ ከቤተ መንግሥት ባይነቀንቁህም ከሕዝብ ልብ ውስጥ ግን ተሰናባች አድርገውኻል። እናም.... ➔አንተን አምኖ የሚቀመጥ ሕዝብ ባለመኖሩ የተነሳ ፋኖን ለማጥፋት ስትሞክር ትግሉን የሚቀላቀል እልፍ አእላፍ ወጣት እየቀሰቀስክ ነው። ➔የጦር መሪዎችን፣ ጋዜጠኞችን እና ፖለቲከኞችን አፍኖ መደበቅን እንደ መብት በቆጠርከው ቁጥርም እንቢተኛ ሕዝብ እየፈጠርክ ነው።

የጄኔራል ተፈራ ማሞ ምክትል የነበሩትና በጦርነቱ ወቅት በርካታ መስዋዕትነት የከፈሉት ኮማንደር ቢሰጥ ጌታሁን ሥልጣን ላይ ባለው ወንበዴ ቡድን ታፍነው ተወስደዋል።
የጄኔራል ተፈራ ማሞ ምክትል የነበሩትና በጦርነቱ ወቅት በርካታ መስዋዕትነት የከፈሉት ኮማንደር ቢሰጥ ጌታሁን ሥልጣን ላይ ባለው ወንበዴ ቡድን ታፍነው ተወስደዋል።

photo content

ዶክተር ይልቃል‼️ አሳዬ ደርቤ ➔ለግላዊ ሥልጣኑ ሲል ሕዝባዊ ጥያቄ ያነሱ አመራሮችን እየለየ ከአመራርነት ያስወገደ፤ ➔ብአዴንን እና አዴፓን ማስናፈቅ የቻለ እጅግ ውዳቂ እና ተንበርካኪ ክልላዊ መንግ
ዶክተር ይልቃል‼️ አሳዬ ደርቤ ➔ለግላዊ ሥልጣኑ ሲል ሕዝባዊ ጥያቄ ያነሱ አመራሮችን እየለየ ከአመራርነት ያስወገደ፤ ➔ብአዴንን እና አዴፓን ማስናፈቅ የቻለ እጅግ ውዳቂ እና ተንበርካኪ ክልላዊ መንግሥት እውን ያደረገ፤ ➔ለጌቶቹ ያለውን ታማኝነት ለመግለጽ ሲል ሕዝቡን እና ክልሉን በሚጎዳ ተግባር ተዘፍቆ ፋኖን ማሳደድ የጀመረ፤ ➔ትሕነግ እና ኦነግ አቅማቸውን ባጠናከሩበት ሁኔታ የአማራን እጅ አስሮ ለባርነት ለመሸጥ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ያለ፤ ➔ክልሉ ካስተናገዳቸው ፕሬዝዳንቶች ሁሉ ገደብ በሌለው የተላላኪነትና የአጎብዳጅነት ማጥ ውስጥ የተዘፈቀ፤ ➔የአማራ ሕዝብ ሳይወድ በግዱ ወደ ሕዝባዊ እንቢተኝነት ይገባ ዘንድ በመወስወስ ላይ የሚገኝ፤

ሜዳሊያ እንጂ ካቴና አይገባውም‼️
ሜዳሊያ እንጂ ካቴና አይገባውም‼️

ይድረስ - ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሕዝብን በገንዘብ ተክተው- በአገር ላይ ለሚቆምሩ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ የትኛውም ሤራ በተደጋገመ ቁጥር ድብቅ ቁማር መሆኑ ቀርቶ የተለመደ ተግባር ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ያህል ‹‹ጠላትን ማክሰም›› በሚል አቋም ተጀምሮ ‹‹ደጀንን ማዳከም›› ወደሚል ሤራ የተቀየረውን እና በየሩብ ዓመቱ የሚደረገውን ጦርነት ብንመለከት ቁማር መሆኑ የታወቀው መቀሌ ያስገቡትን ሠራዊት ወደ ቆላ ተንቤን ከሸኙት ጠላት ጋር ድብን አድርገው የረሱት ቀን ነበር፡፡ ግን እርስዎ ያሰቡት ሐሳብ የቱንም ያህል አገርን እና ሕዝብን ዋጋ ቢያስከፍልም ከመሆን አይዘልምና ‹‹የተበተነ ዱቄት›› ብለው የጠሩት አሸባሪ ዱቄትና ሊጥ ሳይቀር የሚዘርፍና ንጹሐንን የሚጨፈጭፍ ወራሪ ሆኖ መጥቶ መደረግ የሌለበትን ሁሉ አደረገ፡፡ የእርስዎን ዝምታ እና ይሁንታ መስበር የሚችል ሕዝባዊ ጫጫታም ሆነ ቅሬታ ባለመኖሩ አሸባሪው ኃይል እስከፈቀደሉት ጊዜና ቦታ ድረስ ተጉዞ ንብረት ሲያወድምና፣ ሕይወት ሲያከስም ከረመ፡፡ ‹‹በቃህ›› ያሉ ቀን ደግሞ ክንድዎን የሚመክት ጋሻ አጥቶ ለወራት ሲያወድም የቆየው ወሪራ በቀናት ውስጥ ወደመ፡፡ ጦሩን ከፊት ከፊት እየመሩ እስከ ራያ ከተጓዙ በኋላም ያለ ህውሓት መንግሥትዎ መጽናት እንደማይችል አስታወሱ፡፡ የተለመደውን ሤራም ጠነሰሱ፡፡ እናም አገር የመታደግ ዘመቻውን አሸባሪን ወደ መታደግ ቀይረውትና ሁለተኛውን አገራዊ ድል ወደ ሦስተኛ ሕዝባዊ ትግል አራዝመውት ተመለሱ፡፡ ከመላው ኢትዮጵያዊ ጋር ተባብሮ ከባድ ዱላውን ሲሰነዝር የታየው የአማራ ሕዝብም ጠላቱን ሳይሆን እርስዎን ማሸነፍ ተሳነው፡፡ የአማራ ገበሬም በመንግሥት እጅ ሊያካፋ የሚችለውን የክረምት ዝናብ ትቶ በመንግሥት ይሁንታ ሊያጠፋ የሚመጣውን ጠላት ልክ እንደ አምናው ሁሉ መጠበቅ ግድ አለው፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- እርስዎ እኮ መንግሥት ብቻ ሳይሆኑ ሕገ-መንግሥት ነዎት! ለዚያም ነው በኃይል የተወሰደውና በኃይል የተመለሰው የራያ ሕዝብ የማንነት ጥያቄ በሕጋዊ መንገድ መጽደቅ ሲገባው የእርስዎን ይሁንታ አጥቶ ወደ ነበረበት የተመለሰው፡፡ ሕገ-መንግሥቱን የማሻሻልና የማስቀጠል ጉዳይም በእርስዎ ዙፋን ላይ የተቀመጠ በመሆኑ አንዳንዱ አንቀጽ ለአንዳንዱ ክልል ተብሎ በቃልዎ ይሻራል፡፡ አንዳንዱ አንቀጽ ደግሞ ‹‹ላንድ ሕዝብ ተብሎ አይቀየርም›› በሚል ውሳኔ ባለበት ይቀጥላል፡፡ ሌላው ደግሞ በርካታ ምሑራን ‹‹አገር የሚባለው ምድሩ ወይሰ ፍጡሩ?›› እያሉ ሲነታረኩ እሰማለሁ፡፡ እኔ ግን አገር ማለት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚወሰን ነው" እላለሁ፡፡ እናም እርስዎ አገር ይሆን ዘንድ ይሁንታዎን የቸሩት ክልል እንደ ፋሽሽት ጣሊያን ወራሪ ሆኖ የቀድሞ አገሩን ይወጋል፡፡ የእርስዎን ፍቃድ ያላገኘ ክልል ደግሞ ባዕድ ሆኖ እንዲሁም በዞን ቀላድ ተሸንሽኖ ሲወረር ይኖራል፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- ሕገ መንግሥቱ ማንኛውም አካል ከሕግ በታች መሆኑን ይደነግጋል፡፡ የእርስዎ መንግሥት ግን ከሕግ በላይ በመሆኑ በ48 ሠዓት ውስጥ ለሕግ መቅረብ ያለበት ተጠርጣሪ እንደ ጎበዜ ሲሳይ ለ9 ቀን ሊደበቅ ወይም ደግሞ ለሕግ ቀርቦ ቅጣት ሊወሰንበት የሚገባው አሸባሪ እንደ አቦይ ስብሐት በነጻ ሊለቀቅ ይችላል፡፡ ‹‹የአጼዎቹ ሥርዓት አይመለስም›› የሚለው ዛቻም እርስዎ ላይ የማይሠራ በመሆኑ ንጉሥ ሆነው ጦር ሲያዘምቱ ብቻ ሳይሆን ቄስ ሆነው ሲገዝቱ ዐየዎታለሁ፡፡ እናም እርስዎ የገዘቱት አካል አገራዊ ሥሙ ጁንታ ብቻ ሳይሆን የቀን ጅብ ይሆናል፡፡ ግዝቱን ያነሱለት ቀን ደግሞ ከጅብነት ወደ ሰውነት ተቀይሮ ለድርድር ይቀመጣል፡፡ እርስዎ የባረኩት አሸባሪ ወራሪ ሆኖ ለሦስተኛ ዙር ወረራ ይዘጋጃል፡፡ ግዝትዎን የጣሉበት ፍጡር ደግሞ ለመወረር የተፈጠረ መሆኑን አምኖ በተመሳሳይ ስልት የሚወድምበትን ሦስተኛ ዙር ጦርነት ይጠባበቃል፡፡ መንግሥታዊ ወንበር የተቆናጠጡ ብቻ ሳይሆኑ መለኮታዊ ተዓምር የጨበጡ በመሆንዎ ‹‹ተከተለኝ›› ብለው የተጣሩ ቀን አገር ምድሩ ከኋላዎና ከጎንዎ ቁሞ አዲስ ታሪክ ይጽፋል፡፡ ‹‹በቃኝ›› ያሉ እለት ደግሞ የአምናው የጦርነት ታሪክ ሲደገምና ከኋላዎ ቁሞ የነበረው ሕዝብ ሲወድም ይታያል፡፡ እናም እልዎታለሁ… የቀጣዩ ጦርነት ውጤትም በጠላት ክንድ ሳይሆን በእርስዎ እቅድ መሠረት የሚመራ ነውና ሕዝባዊ ትግሉና መገዳደሉ ለምን ያህል ጊዜ ይቆያል? ከቀጣዩ ትግል እጅዎን አስገብተው ድል የሚጨብጡበት ቀን'ስ መቼ ይሆን?

ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ▬▬▬▬▬▬▬▬ ➔ምንም አይነት ልጅ የሌለው መሆኑ ስለቀጣይ ትውልድ እንዳያስብና የሕፃናት ሞት እንዳይሰማው ያደረገው፤ ➔የተሰው ንጹሐንን በገዳይነት ፈርጆ ኦነግ ሸኔን፣ የጉምዝ
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ▬▬▬▬▬▬▬▬ ➔ምንም አይነት ልጅ የሌለው መሆኑ ስለቀጣይ ትውልድ እንዳያስብና የሕፃናት ሞት እንዳይሰማው ያደረገው፤ ➔የተሰው ንጹሐንን በገዳይነት ፈርጆ ኦነግ ሸኔን፣ የጉምዝ ታጣቂንና ትሕነግን ሟች ያደረገ፤ ➔መንግሥትን ትቶ አንድ ሕዝብን በመታገል ላይ የሚገኝ፤ ➔"ከኢትዮጵያ ምድር ላይ አማራ የሚባል ፍጡር መጥፋት አለበት" ብሎ የሚያምን፤ ➔"ትዳር ያልመሠረትከው ምን ሆነህ ነው?" ቢባል አማራን ተጠያቂ ከማድረግ የማይመለስ፤ ➔በወረደ የጥላቻ አስተሳሰቡ ማንነቱን ከማዋረድ በዘለለ በአማራ ሕዝብ ላይ ቅንጣት ታክል ተጽዕኖ ማምጣት የማይችል፤

photo content

photo content