Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 333 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 647,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 350 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 333 名订阅者。
根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -108,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.62%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.61% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 538 次浏览,首日通常累积 1 808 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 333
订阅者
-424 小时
-317 天
-10830 天
帖子存档
14 333
ብአዴን ሆይ የባሕር ዳሩን ስብሰባ እኔ የምመራው ይመስል "ስብሰባው ላይ መገኘት አለብህ" ብለህ ለምን እንደገገምክ መስከረም አበራ ላይ ተፈጻሚ ካደረግከው እገታ ተረድቻለሁ። ያም ሆኖ ግን እስራትን ቀርቶ ሞትን ፈርቼ ለአማራ ሕዝብ ድምጽ መሆኔን የማላቆም መሆኑን እነግርኻለሁ።
14 333
ዘመነ ካሴ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
➔ጎጠኛ አክቲቪስቶች የሆነ ጎጥ ተወካይ ያደርጉታል፡፡ እሱ ግን በንግግሩም ሆነ በተግባሩ እንደ ኢትዮጵያ ሲያስብ ካልሆነ በቀር ከአማራነት ወርዶ ጎጥ ለጎጥ ሲሳብ የተገኘበት ቀን የለም፡፡
➔በሌላ መልኩ ደግሞ የአንድ አውራጃ ጠባቂ የሚያደርጉት ኃይሎች ‹‹እንደ ብርጋደር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ሊዳፈኑ ወይም ደግሞ እንደ ብርጋደር ተፈራ ማሞ ሊታፈኑ የሚገባቸው አማራዎችን ዘርዝራችሁ አምጡ›› የሚል ትዕዛዝ ከበላይ አካል ሲሰጣቸው ‹‹አማራ›› ብለው በቀዳሚነት የሚጽፉት የእሱን ሥም ነው፡፡
➔ጥቅመኛ እና ተከፋይ ዙምቤዎች ካዝናውን በገንዘብ ሞልተው ይመቀኙታል፡፡ የዓላማው ግዝፈት ተረድተው የሚደግፉት ወገኖች ግን ‹‹የትኛውም ሐሳብ ያለ ገንዘብ ሊሳካ አይችልም›› በማለት ይከላከሉለታል፡፡ ‹‹ምን እንገዝህ?›› እያሉም ይጠይቁታል፡፡
➔የመንግሥት ካድሬዎች የሕብረተሰቡን ሰላም በማጥፋት ይከስሱታል፡፡ ድፍን የባሕር ዳር ወጣት ግን ስቴዲየም ገብቶ ሥሙን እያነሳ ይዘምርለታል፡፡
➔አንዳንድ የጎረቤት አክቲቪስቶች የሕዝባቸው ጠላት አድርገው ያብጠለጥሉታል፡፡ እሱ ግን ‹‹ክፋት ለማንም፣ በጎነት ለሁሉም›› በሚል አስተሳሰብ የሚመራ በመሆኑ ስለ አማራ እኩልነትና ነጻነት ከመናገር ባለፈ ሕዝብን ቀርቶ ፖለቲከኞችን የሚያንቋሽሽ ቃል ተንፍሶ አያውቅም፡፡
➔በሌላ መልኩ ደግሞ እሱ እራሱን ከሌሎች የትግል ወንድሞቹ በላይ አድርጎ ያወራበት ቀን ባይኖርም የሚዘምቱበት ኃይሎች ግን ከወሬ የዘለለ ተግባር እንደሌለው በሚገልጽ ሐሜታቸው ዝቅ ዝቅ ሊያደርጉት ይሞክራሉ፡፡
ግን ደግሞ…
"ፋኖ መመታት አለበት" ሲባል ቀድሞ ወደ ጭንቅላታቸው የሚመጣው የእሱ መልክና የእሱ ሥም ነው፡፡ አማራን የማጥቃት ዘመቻቸውን መጀመር የሚሹትም ከእሱ ነው፡፡
አከብርኻለሁ ክንዴ!
14 333
በአማራ ሕዝብ ላይ ከታወጀው የጥፋት ዘመቻ መሀከል እራሳቸውን ላገለሉ አማራዎች
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
በቅርብ ጊዜ ያስተናገድነው የጎንደሩ ክስተት ዋና ዓላማው ፋኖን እና የአማራ ሕዝብን በእምነት ከፋፍሎ ማጥቃት ነበር፡፡
ከሳምንት በፊት ብአዴን ያዘጋጀው ሽልማትም ዋነኛ ግቡ ‹‹የተወሰነውን ፋኖ በመሸለም፥ አብዛኛውን ፋኖ መልቀም›› የሚል ነበረ፡፡ የሚለቀመው ፋኖ ካለቀ በኋላ ደግሞ ሜዳሊያ ከተሸለመው የፋኖ አንገት ላይ ሰንሰለት ለማሰር የሚያስችል ዘመቻ ይጀመራል፡፡
በተረፈ የአማራ ፋኖን የማፈን ዘመቻው የተጀመረው በወሎ፣ በጎጃምና በሸዋ ምድሮች ቢሆንም… እቅዳቸውን ማክሸፍ ካልቻልን በቀር ዘመቻቸው የሚጠናቀቀው ግን ከሁሉም ዞኖች በላቀ መልኩ የጎንደር አማራ ፋኖን በመምታትና የወልቃይትን መሬት ለእነ ጌታቸው ረዳ በመሥጠት እንዲሁም የአማራ ኤሊትን ሥነ ልቦና በማንኮታኮት ነው፡፡
የአማራ ተወላጆች ሆነው ሳለ በአማራ ሕዝብ ላይ የጥፋት እጃቸውን የዘረጉ የጦር መሪዎችና የክልሉ አመራሮችም ተልዕኳቸውን ባጠናቀቁ ማግስት የበላይ አካልን የክህደት ጥፊ ቀምሰውና ጸጸታቸውን ታቅፈው ይወረወራሉ፡፡
በተረፈ ጠላት ለዳግም ወረራ በተዘጋጀበት ወቅት ፋኖን የማጥፋት ዘመቻ ያስፈለገው የአማራ ሕዝብን ለማክሰም እንጂ የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ ከመሰለህ ተራህ ደርሶ ስትታፈን ወይም ደግሞ ስትወረር እውነቱ ይገባኻል፡፡
እናም ያ እንዳይሆን የምትፈልግ ከሆነ ያቀረቀረ አንገትህን የሚጨፈልቅ ጫማና በፍርሐት የተሸበበ ልብህን የሚደስቅ ሰደፍ ከማስተናገድህ በፊት በአማራ ሕዝብ ላይ የታወጀው የጥፋት ዘመቻ ይቆም ዘንድ የድርሻህን አበርክት፡፡
14 333
በመንግሥታዊ ሽብር ስትታመስ እና ደሟ ሲፈስስ የዋለችው የወልዲያ ከተማ ባሁኑ ሰዓት ጓዳናዎቿ ሰው አልባ ሆነዋል።
ብአዴን ሆይ ከእንግዲህ አማራ ክልል ላይ ባርነትን የሚሸከም ሕዝብ ስለሌለ የተሰማራኽበት የባሪያ ንግድ በኪሳራ መጠናቀቁ አይቀሬ ነው።
14 333
ከአማራ ሕዝብ በተጨማሪ የሜዳው ሚካኤል ካንተ ጋር ይሁን ወንድማለም‼️
በተረፈ ወደ አንተ የሚተኮስ ጥይት ብአዴንን እንደሚገረስስ ጥርጥር የለውም።
14 333
"እገሌ የተባለውን ፋኖ ሸልሙት፣ እገሌን ደግሞ አፍኑት" የሚለው ጥያቄ ከአማራ ሕዝብ የመጣ ከሆነ እርምጃ ልትወስዱ ስትሞክሩ ወንጀለኛን አሳልፎ በመስጠት ፈንታ "ልጆቼን አታፍኑም" በሚል ተቃውሞ ገንፍሎ የሚወጣው ሕዝብ ከየትኛው ክልል የመጣ ነው?
አሳቻ ሠዓትና ቦታ እየመረጡ ታርጋው በተሸፈነ መኪና አፈና ማካሄድስ ለምን አስፈለገ?
14 333
እንደ ደረጀ ሃብተ-ወልድ ያሉ ደካማ ካድሬዎች ሆድ እንጂ ኅሊና ያልፈጠረባቸው በመሆኑ ‹‹አትንኩኝ›› የሚለውን የአማራ ሕዝብ ቁጣ መንግሥትን ከመገርሰስና ህውሓትን ከመመለስ ፍላጎት ጋር ሊያገናኙት ሲፍገመገሙ ‹‹በዚህ ልክ መዝቀጥ የሚቻለው እንዴት ነው›› ብዬ እጠይቃለሁ፡፡ ፋኖ የተደራጀው ‹‹የትሕነግ ወረራ እና ጥቃት መደገም የለበትም›› በሚል አቋም መሆኑ እየታወቀ የሚታፈኑትን የፋኖ መሪዎችና የጦር አመራሮች የትሕነግ አጋሮች ሊያደርጓቸው ሲሞክሩ "የጅል ዘፈን ሁልጊዜ አበባዬ" የሚለውን አባባል አስታውሳለሁ።
በህውሓት ሕልውና ላይ ዙፋኑን ያደላደለ መንግሥት ተሸክመው ሳለ የሕልውና ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ሦስት ዓመት ሙሉ በተባለበት ‹‹ጁንታ›› የሚል ፍረጃ ዛሬም ለማሳቀቅ ሲጣጣሩ ‹‹ባይበላስ ቢቀር›› እላለሁ፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ ግን….
➔ኬንያ ድረስ ሄዶ ከወያኔ ጋር ሲደራደር የነበረው አፋኙ ፊልድ ማርሻል እንጂ የታፈነው ጄኔራል አልነበረም፡፡
➔ከደብረ ጽዮን ጋር በድብቅ ሲዳራ የከረመውም የእናንተው መንግሥት እንጂ በእነ ጌታቸው ረዳ አንደበት ‹‹ተስፋፊ›› ሲባል የከረመው የአማራ ኤሊት አይደለም፡፡
➔ፋኖም ትጥቅህን ፍታ ለሚለው ትዕዛዝ ተገዢ ያልሆነው ‹‹ጠላት አለኝ›› ብሎ እንጂ እንደ ትሕ-ኦነጎች ‹‹መንግሥት ነኝ›› ብሎ አይደለም፡፡
ሆኖም ግን የካድሬዎች የፌስቡክ ፖስት ከጭንቅላት የሚፈልቅ ሳይሆን እንደ በጀት ከመንግሥት የሚለቀቅ በመሆኑ መንግሥትና ህውሓት ሲደራደሩ ‹‹ከሰላም የሚልቅ ነገር›› አለመኖሩን ያስረዱኻል፡፡ እነ ጄኔራል ተፈራ ሲታሰሩ ደግሞ ‹‹ከህውሓት ጋር በመደራደር ወንጀል እንደተጠረጠሩ›› ይነግሩኻል፡፡
መንግሥት በጠላት ላይ አምርሮ ወደ ጦር ሜዳ ሲገሰግስ ‹‹ልበ-ቆፍጣና›› መሆኑን ይተርኩልኻል፡፡ ድርጎ ሰፋሪው አካል በአገር ላይ ቆምሮ ትግሉን አቋርጦት ሲመለስ ደግሞ ‹‹ልበ ሰፊ›› መሆኑን ይገልጹልኻል፡፡
14 333
የወሎ ዩኒቨርስቲ መምህር እና የደቡብ ወሎ ዞን ፋኖ አስተባባሪ የሆነው ወንድማችን ዘላለም ጫኔ ለግል ጉዳይ ወደ ጎጃም በሄደበት ወቅት እገታ ተፈጽሞበታል።
ስለሆነም ይህ ወንድማችን ይፈታ ዘንድ ድምጽ ልንሆነው ይገባል።
14 333
ዶክተር አያሌው ታለማን ያፈናችሁ የደሴ አመራሮች ወንድማችንን ልቀቁት።
የሚገርመው ነገር ዶክተር አያሌው የአብን ጠቅላላ ጉባዔ አባል ቢሆንም አብን እንደ ፓርቲ አንዲት ቃል እንኳን መተንፈስ አልፈለገም።
14 333
ለብአዴን
አሳዬ ደርቤ
****
‹‹በወቅታዊ ጉዳይ ተመካክረን አንድ አቋም እንያዝ›› በሚል እሳቤ የጄኔራል ተፈራ እስር ቤትና የአቫንቲ ሆቴል ቤት ካለበት
የባህር ዳር ከተማ ባዘጋጀኸው ስብሰባ ላይ ተሳታፊ እሆን ዘንድ የላክልኝ ጥሪ ደርሶኛል።
ሆኖም ግን አቋምህን ከአቋሜ ጋር ሳስተያየው በመሃከላችን ያለው ልዩነት በአንድ ስብሰባ የሚፈታ ሆኖ ስላላገኘሁት ከዚያ በፊት የፓርቲው ጉምቱ ጉምቱ አመራሮች ባንዳንድ ጉዳዮች ላይ ልምድና ተሞክሯቸውን ያካፍሉኝ ዘንድ እንደሚከተለው እጠይቃለሁ፡፡
ይድረስ ለአቶ አገኘሁ- ይድረስ ለደመቀ
ይድረስ ለተመስገን- ይድረስ ለአቶ ላቀ
በእንጉልፋቶ መንግሥት-
ጸጉሬ፣ ጨጓራዬ- ጋይቶ ስላለቀ፤
አስተምሩኝ እስቲ-
ምግብ ላይ መመሰጥ- ሕዝብ እየደቀቀ፡፡
ክቡር ፕሬዝዳንቱ- ዳግማዊ እና ብናልፍ
ይታክታልና- መንግሥት በሌለበት- ስለ መንግሥት መጻፍ
በነጋ በጠባ- በአገሩ በቀየው- አማራ ሲወድም
ምን አገባኝ ብዬ- ከብአዴን ጋራ- እንዲይዝ አንድ አቋም
ከስብሰባው በፊት-
መድረክ ተዘጋጅቶ- ልምዳችሁን ልቅሰም፡፡
ምክንያቱም…
አማራነት ቃር ነው- ሟች ሆኖ ሰንብቶ- ገዳይ ጋር መወገዝ
አማራነት ጣር ነው- በመጣ በሄደው- በሤራ መገዝገዝ
ጠላት ሲጠብቁ- ከጀርባ መደብደብ- በመንግሥት አፈሙዝ፡፡
አዴፓ ግን ሰላም- ብአዴን ግን ጤና
ሕዝብን አስረክቦ-ነጭ ቪላ መቀበል- V8 መኪና
ኀሊናን አስንፎ- ለከርስ መታገል- ለማይሞላ ካዝና
እናም ብአዴን ሆይ-
አገርና ታሪክ- በተዋረዱበት- በባንዳነት ዘመን
ስቃይ ስለሆነ- የበላይ ዘለቀ- የካሳ ልጅ መሆን
በሆድህ ተገዝተህ- በኦነግ ጠመንጃ- ፋኖን ስታሳድድ
‹‹ሙትቻ ድርጅት››- እያልኩ ከምጮህ- ሰርክ ከምናደድ
አለማምደኝ እስቲ- ኅሊናን መረሸን- ማንነትን መካድ››
14 333
ማንን ይሆን የምታምነው?
ለማን ይሆን የምትታመነው?
በመንግሥትነት እና በጠላትነት መሃከል'ስ የምትወዛወዘው እስከ መቼ ድረስ ይሆን?
የሆነው ሆኖ...
ትናንት "መንግሥት ሁን" ስትባል ጠላት ሆነህ አማራን ለማዳከም ስትሞክር ፋኖ እንዲፈጠር አድርገኻል። በአራት ዓመታት ውስጥ የፈጸምካቸው እኩይ ድርጊቶችም፤ ከቤተ መንግሥት ባይነቀንቁህም ከሕዝብ ልብ ውስጥ ግን ተሰናባች አድርገውኻል።
እናም....
➔አንተን አምኖ የሚቀመጥ ሕዝብ ባለመኖሩ የተነሳ ፋኖን ለማጥፋት ስትሞክር ትግሉን የሚቀላቀል እልፍ አእላፍ ወጣት እየቀሰቀስክ ነው።
➔የጦር መሪዎችን፣ ጋዜጠኞችን እና ፖለቲከኞችን አፍኖ መደበቅን እንደ መብት በቆጠርከው ቁጥርም እንቢተኛ ሕዝብ እየፈጠርክ ነው።
14 333
የጄኔራል ተፈራ ማሞ ምክትል የነበሩትና በጦርነቱ ወቅት በርካታ መስዋዕትነት የከፈሉት ኮማንደር ቢሰጥ ጌታሁን ሥልጣን ላይ ባለው ወንበዴ ቡድን ታፍነው ተወስደዋል።
14 333
ዶክተር ይልቃል‼️
አሳዬ ደርቤ
➔ለግላዊ ሥልጣኑ ሲል ሕዝባዊ ጥያቄ ያነሱ አመራሮችን እየለየ ከአመራርነት ያስወገደ፤
➔ብአዴንን እና አዴፓን ማስናፈቅ የቻለ እጅግ ውዳቂ እና ተንበርካኪ ክልላዊ መንግሥት እውን ያደረገ፤
➔ለጌቶቹ ያለውን ታማኝነት ለመግለጽ ሲል ሕዝቡን እና ክልሉን በሚጎዳ ተግባር ተዘፍቆ ፋኖን ማሳደድ የጀመረ፤
➔ትሕነግ እና ኦነግ አቅማቸውን ባጠናከሩበት ሁኔታ የአማራን እጅ አስሮ ለባርነት ለመሸጥ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ያለ፤
➔ክልሉ ካስተናገዳቸው ፕሬዝዳንቶች ሁሉ ገደብ በሌለው የተላላኪነትና የአጎብዳጅነት ማጥ ውስጥ የተዘፈቀ፤
➔የአማራ ሕዝብ ሳይወድ በግዱ ወደ ሕዝባዊ እንቢተኝነት ይገባ ዘንድ በመወስወስ ላይ የሚገኝ፤
14 333
ይድረስ - ለጠቅላይ ሚኒስትሩ
ሕዝብን በገንዘብ ተክተው- በአገር ላይ ለሚቆምሩ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
የትኛውም ሤራ በተደጋገመ ቁጥር ድብቅ ቁማር መሆኑ ቀርቶ የተለመደ ተግባር ይሆናል፡፡ ለምሳሌ ያህል ‹‹ጠላትን ማክሰም›› በሚል አቋም ተጀምሮ ‹‹ደጀንን ማዳከም›› ወደሚል ሤራ የተቀየረውን እና በየሩብ ዓመቱ የሚደረገውን ጦርነት ብንመለከት ቁማር መሆኑ የታወቀው መቀሌ ያስገቡትን ሠራዊት ወደ ቆላ ተንቤን ከሸኙት ጠላት ጋር ድብን አድርገው የረሱት ቀን ነበር፡፡
ግን እርስዎ ያሰቡት ሐሳብ የቱንም ያህል አገርን እና ሕዝብን ዋጋ ቢያስከፍልም ከመሆን አይዘልምና ‹‹የተበተነ ዱቄት›› ብለው የጠሩት አሸባሪ ዱቄትና ሊጥ ሳይቀር የሚዘርፍና ንጹሐንን የሚጨፈጭፍ ወራሪ ሆኖ መጥቶ መደረግ የሌለበትን ሁሉ አደረገ፡፡
የእርስዎን ዝምታ እና ይሁንታ መስበር የሚችል ሕዝባዊ ጫጫታም ሆነ ቅሬታ ባለመኖሩ አሸባሪው ኃይል እስከፈቀደሉት ጊዜና ቦታ ድረስ ተጉዞ ንብረት ሲያወድምና፣ ሕይወት ሲያከስም ከረመ፡፡ ‹‹በቃህ›› ያሉ ቀን ደግሞ ክንድዎን የሚመክት ጋሻ አጥቶ ለወራት ሲያወድም የቆየው ወሪራ በቀናት ውስጥ ወደመ፡፡
ጦሩን ከፊት ከፊት እየመሩ እስከ ራያ ከተጓዙ በኋላም ያለ ህውሓት መንግሥትዎ መጽናት እንደማይችል አስታወሱ፡፡ የተለመደውን ሤራም ጠነሰሱ፡፡ እናም አገር የመታደግ ዘመቻውን አሸባሪን ወደ መታደግ ቀይረውትና ሁለተኛውን አገራዊ ድል ወደ ሦስተኛ ሕዝባዊ ትግል አራዝመውት ተመለሱ፡፡
ከመላው ኢትዮጵያዊ ጋር ተባብሮ ከባድ ዱላውን ሲሰነዝር የታየው የአማራ ሕዝብም ጠላቱን ሳይሆን እርስዎን ማሸነፍ ተሳነው፡፡ የአማራ ገበሬም በመንግሥት እጅ ሊያካፋ የሚችለውን የክረምት ዝናብ ትቶ በመንግሥት ይሁንታ ሊያጠፋ የሚመጣውን ጠላት ልክ እንደ አምናው ሁሉ መጠበቅ ግድ አለው፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- እርስዎ እኮ መንግሥት ብቻ ሳይሆኑ ሕገ-መንግሥት ነዎት! ለዚያም ነው በኃይል የተወሰደውና በኃይል የተመለሰው የራያ ሕዝብ የማንነት ጥያቄ በሕጋዊ መንገድ መጽደቅ ሲገባው የእርስዎን ይሁንታ አጥቶ ወደ ነበረበት የተመለሰው፡፡ ሕገ-መንግሥቱን የማሻሻልና የማስቀጠል ጉዳይም በእርስዎ ዙፋን ላይ የተቀመጠ በመሆኑ አንዳንዱ አንቀጽ ለአንዳንዱ ክልል ተብሎ በቃልዎ ይሻራል፡፡ አንዳንዱ አንቀጽ ደግሞ ‹‹ላንድ ሕዝብ ተብሎ አይቀየርም›› በሚል ውሳኔ ባለበት ይቀጥላል፡፡
ሌላው ደግሞ በርካታ ምሑራን ‹‹አገር የሚባለው ምድሩ ወይሰ ፍጡሩ?›› እያሉ ሲነታረኩ እሰማለሁ፡፡ እኔ ግን አገር ማለት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚወሰን ነው" እላለሁ፡፡
እናም እርስዎ አገር ይሆን ዘንድ ይሁንታዎን የቸሩት ክልል እንደ ፋሽሽት ጣሊያን ወራሪ ሆኖ የቀድሞ አገሩን ይወጋል፡፡ የእርስዎን ፍቃድ ያላገኘ ክልል ደግሞ ባዕድ ሆኖ እንዲሁም በዞን ቀላድ ተሸንሽኖ ሲወረር ይኖራል፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- ሕገ መንግሥቱ ማንኛውም አካል ከሕግ በታች መሆኑን ይደነግጋል፡፡ የእርስዎ መንግሥት ግን ከሕግ በላይ በመሆኑ በ48 ሠዓት ውስጥ ለሕግ መቅረብ ያለበት ተጠርጣሪ እንደ ጎበዜ ሲሳይ ለ9 ቀን ሊደበቅ ወይም ደግሞ ለሕግ ቀርቦ ቅጣት ሊወሰንበት የሚገባው አሸባሪ እንደ አቦይ ስብሐት በነጻ ሊለቀቅ ይችላል፡፡
‹‹የአጼዎቹ ሥርዓት አይመለስም›› የሚለው ዛቻም እርስዎ ላይ የማይሠራ በመሆኑ ንጉሥ ሆነው ጦር ሲያዘምቱ ብቻ ሳይሆን ቄስ ሆነው ሲገዝቱ ዐየዎታለሁ፡፡ እናም እርስዎ የገዘቱት አካል አገራዊ ሥሙ ጁንታ ብቻ ሳይሆን የቀን ጅብ ይሆናል፡፡ ግዝቱን ያነሱለት ቀን ደግሞ ከጅብነት ወደ ሰውነት ተቀይሮ ለድርድር ይቀመጣል፡፡
እርስዎ የባረኩት አሸባሪ ወራሪ ሆኖ ለሦስተኛ ዙር ወረራ ይዘጋጃል፡፡ ግዝትዎን የጣሉበት ፍጡር ደግሞ ለመወረር የተፈጠረ መሆኑን አምኖ በተመሳሳይ ስልት የሚወድምበትን ሦስተኛ ዙር ጦርነት ይጠባበቃል፡፡
መንግሥታዊ ወንበር የተቆናጠጡ ብቻ ሳይሆኑ መለኮታዊ ተዓምር የጨበጡ በመሆንዎ ‹‹ተከተለኝ›› ብለው የተጣሩ ቀን አገር ምድሩ ከኋላዎና ከጎንዎ ቁሞ አዲስ ታሪክ ይጽፋል፡፡ ‹‹በቃኝ›› ያሉ እለት ደግሞ የአምናው የጦርነት ታሪክ ሲደገምና ከኋላዎ ቁሞ የነበረው ሕዝብ ሲወድም ይታያል፡፡
እናም እልዎታለሁ…
የቀጣዩ ጦርነት ውጤትም በጠላት ክንድ ሳይሆን በእርስዎ እቅድ መሠረት የሚመራ ነውና ሕዝባዊ ትግሉና መገዳደሉ ለምን ያህል ጊዜ ይቆያል? ከቀጣዩ ትግል እጅዎን አስገብተው ድል የሚጨብጡበት ቀን'ስ መቼ ይሆን?
14 333
ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና
▬▬▬▬▬▬▬▬
➔ምንም አይነት ልጅ የሌለው መሆኑ ስለቀጣይ ትውልድ እንዳያስብና የሕፃናት ሞት እንዳይሰማው ያደረገው፤
➔የተሰው ንጹሐንን በገዳይነት ፈርጆ ኦነግ ሸኔን፣ የጉምዝ ታጣቂንና ትሕነግን ሟች ያደረገ፤
➔መንግሥትን ትቶ አንድ ሕዝብን በመታገል ላይ የሚገኝ፤
➔"ከኢትዮጵያ ምድር ላይ አማራ የሚባል ፍጡር መጥፋት አለበት" ብሎ የሚያምን፤
➔"ትዳር ያልመሠረትከው ምን ሆነህ ነው?" ቢባል አማራን ተጠያቂ ከማድረግ የማይመለስ፤
➔በወረደ የጥላቻ አስተሳሰቡ ማንነቱን ከማዋረድ በዘለለ በአማራ ሕዝብ ላይ ቅንጣት ታክል ተጽዕኖ ማምጣት የማይችል፤
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
