es
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram Assaye Derbie

El canal Assaye Derbie (@asayede) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 321 suscriptores, ocupando la posición 2 647 en la categoría Bloques y el puesto 2 347 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 321 suscriptores.

Según los últimos datos del 29 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -125, y en las últimas 24 horas de -9, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 37.52%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 11.99% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 374 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 717 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 34.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 30 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Bloques.

14 321
Suscriptores
-924 horas
-287 días
-12530 días
Archivo de publicaciones
ከስምንት ወር በፊት ይሄንን ትንቢት መጻፌን የምታስታውሱ ስንቶቻችሁ ናችሁ?😁 ማርክ ማይ ወርድ! አሳዬ ደርቤ የአራት ኪሎው መንግሥት ወደ ፈላጭ ቆራጭነት ለመሸጋገርና በወልቃይት መሬት ላይ ለመደራደር ሲያስብ አብን እና ብአዴን የእቅዱ ተገዢ ሆነው ደስ አሰኙት፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ በሶሻል ሚዲያው መድረክ ሕዝባቸውን የሚያነቁ ጦማሪዎችና በጦር ሜዳ ላይ የሚዋደቁ ወጣቶች እንቅፋት ሆነው ታዩት፡፡ እርሱም አለ… ‹‹በወልቃይት ማንነት ዙሪያ ለመደራደርም ሆነ አማራን ለማስገበር የጌታቸው ረዳን ሐሳብ መተግበር ግድ ይላል፡፡ ይሄውም የአማራን ልሳኖችን እና ክንዶች የመስበር ዘመቻ 'ሕግ ማስከበር' ይባል፤›› ከዚህም ውሳኔ በኋላ ከላይ የተዘረዘሩትን ኃይሎች ጠርቶ ወረቀትና ገንዘብ ካቀበላቸው በኋላ "ሕግ አስከብሩ›› አላቸው። እነርሱም ቦርጫቸውን እንደ ጠረጴዛ በመጠቀም የተሰጣቸውን ወረቀት ካስደገፉበት በኋላ ‹‹ጽንፈኛ›› በሚል ርዕስ ‹‹እንቢተኛ እና ሐቀኛ›› የአማራ ልጆችን ሥም መጻፍ ጀመሩ፡፡ እናም አሁን ላይ ፦ ➔አንዳንድ የአብን አመራሮች በብአዴን የሚታፈኑ የአማራ ልጆችን እየጠቆሙ ነው፡፡ ➔አንዳንድ ተከፋይ የአማራ ወመኔዎች ‹‹ወገኔ›› የሚሉትን ሕዝብ ለአፈና ዳርገው ‹‹ወያኔ›› የሚሉትን ጠላት እየጠበቁ ነው፡፡ ➔አብዛኛው የአማራ ሙሕራን እና ፖለቲከኞች ‹‹ተደራጅ›› ብለው ሲቀሰቅሱት የኖሩት ፋኖ ሲሳደድ እያዩ ‹‹ሕግ እንዲከበር እንፈልጋለን፡፡ በወልቃይት ላይ ለመደራደር ያሰባችሁ ቀን ግን እንጣላለን›› እያሉ ነው፡፡ ይሄውም የመጀመሪያ ምዕራፍ ‹‹የሕግ ማስከበር›› ዘመቻ በስኬት መጠናቀቅ ከቻለ ሁለተኛው ምዕራፍ ‹‹ሰላም አስከባሪ›› የሚል ይሆናል፡፡ እናም ‹‹በአንዳንድ አካባቢዎች የሚነሱ የማንነት ጥያቄዎች መልስ እስኪያገኙ ድረስ በፌደራል መንግሥትና በኮማንድ ፖስት ሊተዳደሩ ይገባል›› መባል ይጀመራል፡፡ ያን ጊዜም ከላይ የተጠቀሱት ተላላኪ ኃይሎች ስምምነታቸውን ገልጸው ከወጡ በኋላ ለይምሰል ያህል ከሕዝብ ጎን ቆመው ቁጣቸውንና ተቃውሟቸውን እንዲገልጹ ይፈቀድላቸዋል፡፡ የሕዝብ ጠበቃና ጠባቂ የሆኑ ወጣቶች ወንጀለኛ እና ጽንፈኛ ተብለው እየተመረጡ ሲታፈኑ በዝምታው አማካኝነት ለዘብተኛ መሆኑን ሲገልጽ የከረመው የአማራ ሙሕርም በብልጽግና ውሳኔ የመናደድ መብቱ ይከበርለታል። ከወልቃይት ምድርም ‹‹ማንነቴን የምትወስን አንተ ማን ነህ›› የሚል ትግል ይቀጣጠላል፡፡ ‹‹የወገን ያለህ›› የሚል ቃልም ይሰማል፡፡ ሆኖም ግን ያ ጊዜ እንደሚመጣ አውቀው በሸዋ፣ በወሎ፣ በጎጃምና በጎንደር ሲደራጁ የከረሙ ፋኖዎች ለአፋና እና ለብተና የተዳረጉ በመሆናቸው ፈጥኖ የሚደርስ ኃይል አይኖርም፡፡ ከዚያ በማስከተል በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ የታፈኑ ሁሉ ያለምንም ፍርድ በነጻ ይለቀቃሉ፡፡ ከእነዚህ መሃከል አብዛኞቹ ትግላቸውን ሲቀጥሉ አንዳንዶቹም ዝምታን ተምረው ይወጣሉ፡፡ አሳሪዎቹ ደግሞ የሚታሠሩበት ቀን እስኪመጣ ድረስ የእነሱ ሕልውና በብልጽግና እድሜ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ተረድተው የህውሓትና የመንግሥት ጋብቻ ሲፈጸም እልልታቸውን ያቀልጣሉ። ‹‹የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም›› በሚል አቋምም ዛሬ ላይ የንቁ ዜጎች ማሸማቀቂያ ካደረጉት ጠላት ጎን ተሰልፈው ሕዝባቸው ላይ ይዘምታሉ፡፡ ይህ ቀን እንዳይመጣ የሚሹ ወገኖች ግን አሁን ላይ እንቅልፍ በተጫጫነው ክልል ውስጥ ቆመው ቀን እና ሌሊት በመታገል ላይ ይገኛሉ። "አፈናው ይቁም" ይላሉ።

"ነፍጠኛ" እየተባሉ በጥፊ ሲጠፈጠፉና ከንጹሐን ጋር ሲጨፈጨፉ የከረሙ የሃይማኖት አባቶች "የአማራ ልዩ ሃይል ቢጠፋም እኛ አባቶቻችሁ እያለን ማንም አይነካችሁ" በሚል ምልጃ ሕዝብን የማስተኛት ሥራ እየሠሩ ነው። እናም ለእኒህ አባቶች የምንሰጠው መልስ..."ከእኛ በፊት ሲጨፈጭፉን የከረሙ አሸባሪዎችን ትጥቅ አስፈትታችሁ ከሥጋትና ከጥቃት ገላግሉን" የሚል መሆን አለበት።

የመስከረም አበራ የስልክ ንግግር የሚባለውና በINSA በኩል ተለቀቀ የሚባለው የድምጽ ቅጂ የእርሷ ቢሆን እንኳን በሚዲያ ከምታወራው የተለየ ነገር የያዘ አይደለም። በዚያ ላይ ደግሞ ድምጽ ማቀናበር ከባድ አይደለም። በተረፈ መንግሥት ተብዬው አካል የግለሰቦችን ስልክ ከመጥለፍ ባለፈ በየሪዞርቱና በየሆቴሉ የስለላ ካሜራ አስገጥሞ የዜጎችን ብቻ ሳይሆን የእራሱን ባለሥልጣናትም ጭምር ገመና እየሰበሰበ ብላክ ሜይል እንደሚያደርግ የታወቀ ነገር ነው። ውርጋጥ መራሹ ሥርዓት ከትላልቅ ሆቴሎች መኝታ ቤት ሳይቀር ካሜራ አስገጥሞ የወሲብ ትዕይንት ሲከታተል የሚያድር አሳፋሪ ስብስብ መሆኑን ካወቅን ቆየን። (ለዚያም ነው "ያገራችን ጉዳይ ያገባናል" በሚል ንግግራቸው የሚታወቁ ፖለቲከኞች ሁሉ አንገት ደፍተው የቀሩት 😁

ጧሒር መሐመድ.... ከሌሎች የአብን አመራሮች በተሻለ መልኩ ከሕዝብ ጎን ተሰልፎ የተገኘ!!
ጧሒር መሐመድ.... ከሌሎች የአብን አመራሮች በተሻለ መልኩ ከሕዝብ ጎን ተሰልፎ የተገኘ!!

photo content

"ፌደራሊስት" ብሎ እራሱን ለሚጠራው ጨፍላቂ መንጋ "አቶ ልደቱ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ከእኛ የተለየች አንዲት ሐሳብ አነሳብን" ብለው በጸረ ሕዝብነት የፈረጁትና የሞት ፍርድ የፈረዱበት 'ፌደራሊስት
"ፌደራሊስት" ብሎ እራሱን ለሚጠራው ጨፍላቂ መንጋ "አቶ ልደቱ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ከእኛ የተለየች አንዲት ሐሳብ አነሳብን" ብለው በጸረ ሕዝብነት የፈረጁትና የሞት ፍርድ የፈረዱበት 'ፌደራሊስት' ተብዬዎች "ኤርሚያስ ከኢትዮ 360 የለቀቀው ለየት ያለ ሐሳብ ማስተናገድ ባለመቻላችሁ ነው" እያሉን ነው። እኔ ግን እላለሁኝ... ኤርሚያስ ይሄን ያህል ጊዜ መቆየት የቻለው በወልቃይትና ራያ ማንነት ዙሪያም ሆነ በሄዊ ዙሪያ የሚያራምደውን ሐሳብ ማስተናገድ በመቻላችን ነው።. በተረፈ ኤርሚ በኡቡንቱም ሆነ በርዕዮት ሚዲያ በተቀጠረ ቅጽበት ስለ አዲስ አበባ ያለውን አቋም ካልቀየረ በማግስቱ "ሐጣ*ራው" ብላችሁ እንደምታፈናቅሉት ጥርጥር የለውም። 😁

የኤርሚን ሥም ቀርቶ የሌላውንም ቢሆን ያለምክንያት የማንሳት ፍላጎት የለንም። እናም ባለፈው እንደተነበይነው😁 ኤርሚ ከኢትዮ 360 ለቅቋል። በቀጣይ በሌላ ሚዲያ እንደሚመጣና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ¿ ክ
የኤርሚን ሥም ቀርቶ የሌላውንም ቢሆን ያለምክንያት የማንሳት ፍላጎት የለንም። እናም ባለፈው እንደተነበይነው😁 ኤርሚ ከኢትዮ 360 ለቅቋል። በቀጣይ በሌላ ሚዲያ እንደሚመጣና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ¿ ክቡር ዘበኛ ሆኖ የኖረበት ካምፕ ላይ ሲዘምት እንደሚታይ አልጠራጠርም። ምክንያቱም.... የኤርሚን ሥነልቦና ጠንቅቄ ከተረዳሁ በጣም ቆየሁኝ። በተረፈ ... የብልጽግና እና የሄዊ ጋብቻ ከተፈጸመበት ጊዜ አንስቶ ኤርሚያስና ሽመልስ በተመሳሳይ ማሊያ መሮጥ ጀምረዋል። መልካም ጊዜ ይሁንልህ!!

"እንዴ ግስላ የተቆጣውን ሕዝብ አዘናግታችሁ ያሰብኩትን ዘመቻ የማታሳኩ ከሆነ ከወንበር አንስቼ ወደ መቃብር እንደማወርዳችሁ እወቁ" የሚል ዛቻ ካስተናገዱ የብአዴን አመራሮች "ሕዝቤ ሆይ በሶሻል ሚዲያ የሚወራውን አትስማ" ከማለት ባለፈ "ሕዝቤ ሆይ ጥያቄህን ሰምተናል" የሚል መልስ አይጠበቅም። አሳዬ ደርቤ

የባሕር ዳር ቁጣ እየበረታ መጥቷል። በኮምቦልቻ ከተማም እንቢተኝነቱ በርትቷል።
+2
የባሕር ዳር ቁጣ እየበረታ መጥቷል። በኮምቦልቻ ከተማም እንቢተኝነቱ በርትቷል።

ጄኔራል መስከረም አበራ "ወታደራዊ ሥልጠና ስትሰጥ ነበር" "የሚል ክስ ተመስርቶባታል። 😃🤣
ጄኔራል መስከረም አበራ "ወታደራዊ ሥልጠና ስትሰጥ ነበር" "የሚል ክስ ተመስርቶባታል። 😃🤣

ሦስት መረጃዎች 1. የዐቢይ ታጣቂ በኮምቦልቻ ከተማ ተኩስ ከፍቶ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ንጹሐንን ገድሏል። 2. ባሕር ዳር ከተማ በተኩስ እየተናጠች ነው 3. የሱማሌ ሕዝብ "ልዩ ሃይላችን ማፍረስ አይታሰብም" የሚል ተቃውሞውን እያሰማ መሆኑን ኦጋዴን ሚዲያ ዘግቧል። ድል ለኢትዮጵያ ድል ለአማራ ሕዝብ

የመካነ ሰላም ሕዝብ... "ብልጽግና ሸኔ ፥ በሚመራው ዓለም ትጥቅ ማጥበቅ እንጂ ፥ ትጥቅ መፍታት የለም" እያለ ነው
የመካነ ሰላም ሕዝብ... "ብልጽግና ሸኔ ፥ በሚመራው ዓለም ትጥቅ ማጥበቅ እንጂ ፥ ትጥቅ መፍታት የለም" እያለ ነው

በውጭ አገር ለምትኖሩ የአማራ ልጆች በሙሉ በኦነግ ሸኔ ታጣቂ የአማራን ሕዝብ ጨፍጭፎ መጨረስ እንደማይቻል የተረዳው አረመኔያዊ ሥርዓት ያለ የሌለ ወታደሩን አዝምቶ የአማራን ሕልውና ለማክሰም እየተንቀሳቀሰ ስለሆነ የወገናችሁ ድምጽ እና ክንድ ሁኑ።

በሱዳን ወታደራዊ ኃይል የተፈፀመብንን ወርራን በተመለከተ መመከቱ ቀርቶ ትንፍሽ አለማለቱም ገሃድ ነው፤ (አንድ ሁለቴ የሰጣቸውን ኢ-ተግባራዊ መግለጫዎች ረስቼያቸው አይደለም፡፡) ከዚህ ባለፈ፣ ልዩ ኃይሎች በአንዳንድ አካባቢዎች በአነስተኛ በጀት ከመከላከያው በተሻለ ለሕዝብ እና ለአገር ትርጉም የሚሰጥ ድል ማምጣታቸውን ታሪክ መዝግቦታል። ለማሳያም፣ መከላከያ ሠራዊቱ ላይ ጥቃት በተሰነዘረበት ሰዓት ዛሬ "የሀገር ኢኮኖሚን ይበላል" እየተባለ የሚዘለፈው የዐማራ ልዩ ኃይል እንደደረሰለት መጥቀስ ይቻላል። መከላከያ፣ አገር የማፍረሱን ዘመቻ ለመመከት ሙሉ በሙሉ ፊቱን ወደ ሰሜን ሲያዞር፤ ዓለም ዐቀፉን አሸባሪ አልሸባብን ሳይቀር ወጥሮ በመያዝ የምስራቁን ድንበር ያስከበረው የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል እንደሆነም ማስታወስ ይቻላል፡፡ ለዚህም ነው፣ ኢትዮጵያ ካለችበት ሁኔታ አኳያ ይህ ምክንያት ውሃ አያነሳም የምንለው። በዚህ ላይ ኢኮኖሚ ከህልውና አይበልጥም፡፡ ❺. “ተቋማዊ ባህሪ የለውም (የትጥቅ ምንጩ አይታወቅም፣ ከውጭ ኃይሎች ጋር ግንኙነት አለው)” አረ አታስቁን?! የሁሉም ክልል ልዩ ኃይል በጀት የሚጸድቀው በክልላቸው ምክር ቤት እንደሆነ እኛ እንንነግራችው እንዴ? በተቀረ፣ ይሄ ጥያቄ መቅረብ ያለበት በፌደራል መንግሥቱ እና በመከላከያ በጀት ከድሮንና ጄት በቀር፤ እስከ አፍንጫው ለታጠቀው የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ብቻ ነው፡፡ ❻. “ይህ ሁሉ ወጭ ወጥቶባቸውም በችግር ጊዜ ራሳቸውን ችለው አይቆሙም፤ የፌዴራሉን የፀጥታ ኃይል ድጋፍ ይሻሉ” ለመሆኑ በየትኛው ችግር? በወለጋው እና በጉጂው ከሆነ እዛው ተነጋገሩበት፡፡ የዐማራ ልዩ ኃይል፣ የመከላከያ ብቻ ሊሆን የሚገባውን ጦርነት በሙሉ ዐቅሙ በመሳተፍ ደርሶላታል፡፡ ከዚህ አኳያም፣ ብዙ ወጪ ወጥቶበት እገዛ የፈለገው ፌደራሉ እንጂ፤ ልዩ ኃይል አይደለም፡፡ ❼. “የሕዝብ ቅቡልነት ጥያቄ ይነሳባቸዋል” ለዚህኛው ምክንያት እንደማሳያ የሚያቀርቡት "የዐማራ ልዩ ኃይል ከሚሴ ላይ አትግባ፤" መባሉን ነው። ይሄ መቼም ሸኔ እና ሕዝብን ያልለየ አደገኛ የሁኔታ ትንተና ነው። አንደኛ ነገር፣ የዐማራ ልዩ ኃይል የሚባለው ከከሚሴም ከአዊም ከዋግም… ከሁሉም ልዩ ዞኖች ጭምር የተመለመለ ለክልሉ ሰላምና መረጋጋት የሚሰራ ኃይል ነው። ሁለተኛ፣ በሌሎች ልዩ ዞኖች በአስፈላጊ ጊዜ ገብቶ የሚወጣው፣ ካምፖችንም ያደራጀው የዐማራ ልዩ ኃይል ከሚሴ ላይ ተቃራኒ ድምፆች መሰማቱ ጤነኛም አሳማኝም አይደለም፡፡ በተለይ፣ ከእዚያ ዞን በተደጋጋሚ ጊዜ የተሰነዘሩትን የሽብር ጥቃቶች እዚህ ጋ ስንደምራቸው፤ አስተያየቱ ኦነጋዊ ፍላጎት ያለው አመራር እንጂ፤ የልዩ ዞኑ ንፁሃን ነዋሪዎች እንዳልሆነ አይሳተንም። ዛሬ አጣዬ ላይ የተሰነዘረው ጥቃትም መከራከሪያችን መሬት የረገጠ እንደሆነ ያሳያል፡፡ እስኪ ከተጨባጭ ሁኔታ ተነስተ ደግሞ አጭር ንጽጽር እናድርግ፦ በወለጋ ዞኖች በዐማራ የተፈናቀለ ኦሮሞ የለም፡፡ ከከሚሴ በሚነሳ የሽብር ኃይል ግን በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ዐማራ በተደጋጋሚ ተፈናቅሏል፡፡ እናሳ፣ ታዲያ የየትኛው ክልል ልዩ ኃይል ነው የቅቡልነት ችግር ያለበት? ሌላኛው የክርክራችን ጭብጥ፦ “ቅቡልነት የለውም” የሚለውን ውንጀላ፣ በሁሉም የዐማራ ክልል ከተሞች እየተደረገ ያለው ሰልፍ በበቂ የሚያመክነው መሆኑ ነው። ከዚህ ባለፈ፣ አገር ሊያፈርስ የሞከረው እና አገርን ከፍርሰት የታደገው ልዩ ኃይል የእኩል ሚዛን ላይ የተቀመጡበት ሁነት የክፍለ ዘመኑ ክህደት ተደርጎ ተመዝግቧል። ያም ሆነ ይህ የወደቁት የዐማራ ልጆች አፅም በክብር ሳያርፍ፣ በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የዐማራ ልዩ ኃይል ሰማዕታት ቤተሰቦች ጎዳና ላይ በወጡበት ሁኔታ፣ ሰማዕታቱ የተሰውለት ዓላማ ግቡን ሳይመታ የሚፈርስም ሆነ የሚበተን ልዩ ኃይል የለም። የሁላችንም መተማመን በሚያረጋግጥ አግባብ ሕገ-መንግሥታዊ ማሻሻይ ሲደረግ (ወይም እስካሁን እንደተፋዘዘ የቀጠለው “ብሔራዊ ምክክር መድረክ” የሚባለው ስብስብ ላይ አጀንዳው ቀርቦ ውሳኔ ካገኘ በኋላ) የልዩ ኃይል አደረጃጀት መልክ እንዲይዝ ሊደረግ ይችላል። ይህ እስኪሆንም በትእግስት መጠበቁ ለሁሉም የሚበጅ ነው፡፡ አውቆ መታረም ይመከራል። ስንጠቀልለው… ዛሬ እንደ ዐዲስ ሙሽራ እፍ ያሉት ኦሕዴድ እና ወያኔ ስለ ዐማራ ልሂቅም ሆነ ስለ ዐማራ ልዩ ኃይል ሲያወሩ በውስጠ-ዘ ስለ መላው የዐማራ ሕዝብ እንደሆነ ከገባን ሰንብቷል፡፡ ሩቅ ሳንሄድ አዲሱ የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ እንደዛተው ማን ላይ ሒሳብ እንዳወራረዱ በበቂ ያየነው እውነታ ነው፡፡ መቼም የተደፈሩ መነኩሴዎችን፣ ሕጻናትን፣ በጅምላ የተገደሉ አርሶ ዐደሮችን፣ የታረዱ ቀሳውስቶችን፣ የተዘረፉ የድሃ ጥሪቶችን፣ የወደሙ ሕዝባዊ ተቋማትን… ጃል፣ የቱን ጠቅሰን የቱን እንተወው?! በተረፈ፣ የታሰበው ቀመር ገብቶናል፡፡ አተገባበሩም በአራት የተከፋፋለ ቅደም-ተከተል አለው፡፡ የመጀመሪያው፣ በጦርነቱ ላይ እጃቸውን በጉንጫቸው ያስጫነ ወታደራዊ ድል ያስገኘውን የዐማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ ማፍረስ ነው፡፡ ይህ ዘመቻ በበቂ ግቡን ከመታ በኋላ ወደ ቀጣዩ እርምጃ ይሸጋገራሉ፡፡ በሁለተኛው ዙር፣ የሚሊሻውን እና የፋኖን ትጥቅ መግፈፍ ነው፡፡ ሦስተኛው ስቴፕ፣ የክልሉን መደበኛ ፖሊስ ቁጥር በእጅጉ ማመንመን ላይ የሚያተኩር ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ማን ቀረ? ከባህልና ከወጉ አኳያ በሬውን ሸጦ ጠመንጃ የሚገዛው ተርታው ሕዝብ፡፡ በመጨረሻም፣ ምሽጎቹን አንድ በአንድ አፍርሰው ብቻውን ያስቀሩትን ሕዝብ ቤት ለቤት እየዞሩ በሃቁ የገዛውን መሳሪያ ያስወርዱታል፡፡ በዚህም፣ የኦሮሞ እና የትግራይ ልሂቃን በኢ-መደበኛ ወጎች “ዐማራ ዱላም ቢሆን መያዝ የለበትም” እያሉ የሚደጋግሙትን ዕቅድ በምልዓት ያስፈጽማሉ፡፡ ስለዚህም፣ ዛሬ ሕዝባችን ከልዩ ኃይል ጎን የሚቆመው፣ አንድም ልጆቹ ስለሆኑ፤ አንድም ደግሞ ለነገ ራሱን መከላከያ ብቸኛው መንገድ በመሆኑ ነው፡፡ እየመጣ ያለው አደጋ ከገመትነውም በላይ አውዳሚ ነው፡፡ ካልተባበርን እንወድቃለን፡፡ በያለንበት እንወጥር። ዛሬ ክልሉን “ቀራኒዮ” ቢያስመስሉትም-ቅሉ፤ በርትተህ ከቆምክ በሰሞነ-ሕማማት የከፈልከውን ዋጋ፣ በተንሳኤ ትሽረዋለህ፡፡ *** አይዞን ወገን፤ ቀና በል ቀን አለህ!!! ሙሉዓለም ገ/መድኀን ከሁመራ-ጎንደር

የሚነበብ ብቻ ሳይሆን post & Share የሚደረግ ገራሚ ትንታኔ የሰሞነ-ሕማማት ፪ኛው መልዕክት Mulualem G. Medhin *** በቅድሚያ መታወቅ ያለበት አንድ እውነታ፣ የዐማራን ልዩ ኃይል የማፍረሱ ሴራ ዛሬ የመጣ ዐዲስ ሃሳብ አለመሆኑ ነው፡፡ በሚዲያም በድፍረት ሲነገር የአሁኑ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ በከፍተኛ የሐዘን ስሜት በተሰበርንበት ሰኔ 15/2011 ዓ.ም በባህር ዳር የተፈፀመውን የእነ ዶክተር አምባቸው ግድያን "ዐማራ እርስ በርሱ ተበላላ" በሚል እንደዕድል ለመጠቀም የኦሮሞ እና የትግሬ ልሂቃን ስለጉዳዩ በ“መተንተን” ሚዲያዎቹን በሙሉ ተቆጣጥረውት እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በርግጥ በዛን ወቅት፣ የኦሕዴድ ዋንኛ ስጋት ወያኔ በመሆኑ የአባ ገዳ ልጆች በግላጭ የዐማራ ልዩ ኃይል እንዲፈርስ መጠየቁ ጊዜው ገና በመሆኑ፣ በገደምዳሜ ከቁጥጥር ውጩ እንዳይሆን የሚያደርግ ሥርዐት እንዲበጅለት ማሳሰብን ብቻ ነበር የመረጡት፡፡ ለትግሬ ልሂቃን ግን ይህ ኃይል የወዲያውኑ ስጋት በመሆኑ በይፋ እንዲፈርስ ከመቀስቀስ አልቦዘኑም፡፡ በተለይ ጄነራል ፃዳቃን ገ/ተንሳኤ በቴሊቪዥን ቀርቦ ያለ ምንም መሸፋፈን “የዐማራ ልዩ ኃይል መፍረስ አለበት” ሲል እንደነበረ ፈጽሞ አይዘነጋም፡፡ በወቅቱ የጄነራሉ ስሌት፣ ወያኔ ወደ አራት ኪሎ ለመመለስ ያለውን ፍላጎት የሚያመክነው የዐማራ ልዩ ኃይል እንደሆነ ከመረዳት የመጣ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህ ላይ፣ ፃድቃን በ1983ቱ አዲስ አበባ ድረስ ማን ተሸክሞ እንዳመጣው የሚረሳ ሰው አይደለም፡፡ ይሁንና፣ በዚያን ጊዜ የፌደራል-ኦሮሚያ ብልጽግና ቁጥር አንድ ስጋት ወያኔ በመሆኑ፤ ባለፉት ሁለት ዐመት ጦርነቶች እንደታየው ገትሮ ሊያቆመው የሚችለው የዐማራ ልዩ ኃይል እንደሆነ ጠንቅቀው አውቀዋል፡፡ ጨፌው በአራት ኪሎ የነገሠውም በኦሮ-ማራ ጥምረት መሆኑን ከማንም በላይ አይዘነጋውም፡፡ ስለዚህም፣ እነ ፃድቃንን “ይፍረስ” እያሉ የሚቀሰቅሱበትን ገፊ-ምክንያት ስለሚያውቁ፣ የዐማራ ልዩ ኃይልን ተንከባክቦ ማቆየት፣ የቤተ-መንግሥቱን ዕድሜ ማራዘም በመሆኑ፣ “ይፍረስ” የሚለውን ሃሳብ ውጉዝ ከመአርዮስ ለማድረግ ማንም አልቀደማቸውም፡፡ ዛሬ ወያኔ ተዳክሟል፡፡ በማይገመት ሁኔታም በፖለቲካ ቁመናውም ያለ ፌደራል መንግሥቱ ድጋፍ ከቁጫ ወይም ከሐረሪ የተለየ ተሰሚነት የለውም፡፡ ብቻውን መቆም ስለማይችልም የኦህዴድ ጁኒየር ፓርትነር ሆኖ ተከስቷል። ስለዚህም፣ የኦሮሞ ልሂቃን ‹አሁን መመታት ያለበት የዐማራ ኃይል ነው› ብለው መነሳታቸው፣ ለድብቅ ፍላጎታቸው ወሳኙ ሰዓት መሆኑን በማስላት እንደሆነ ለማናችንም አይጠፋንም፡፡ እውነታው ይህ ቢሆንም፤ በመንግሥት በኩል ልዩ ኃይሉን ለማፍረስ የተደረደሩት ምክንያቶች ረብ-የለሽ መሆናቸውን እየጠቀሱ መሞገቱ፣ ጉዳዩ ሳይገባቸው ከአፍራሹ ጎን ለቆሙ ቅን ወገኖች ለማስረዳት አስፈላጊ ስለሆነ ነጣጥለን እንመልከታቸው፡፡ ❶. “የስጋት ዐውድ ትንተና የለውም” የልዩ ኃይል አደረጃጀት ከሚቀርብበት ትችት አንዱ፣ ‹መከላከያ ከአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተነስቶ የዓለምንና የቀጠናውን ሁኔታ ገምግሞ አደጋ ሲመጣበት ወታደራዊ ውሳኔ ላይ ይደርሳል። ልዩ ኃይል ግን ይህ ባህሪ የለውም፤› የሚል ነው፡፡ ይህ መከራከሪያ ፍፁም ስህተት መሆኑን በሦስት አመክንዮዎች እናስረግጠው፡፡ አንደኛ፣ የልዩ ኃይል ፖሊስ ተልዕኮ እንደየ ክልሉ ሁኔታ የሚወሰን ሆኖ መከላከያ እና ፌዴራል ፖሊስ የማይሸፍኗቸውን ግዳጆች የሚፈጽሙ መሆናቸው ነው፡፡ ሁለተኛ፣ የዐማራ ልዩ ኃይልን አብነት ወስደን ካየነው ከውስጥም ሆነ ድንበር ተሻጋሪ ጥቃቶችን በመመከትና በማምከን ረገድ የፌዴራል የፀጥታ ተቋማት አጋዥ ሆኖ ከመሰለፉም በዘለለ፤ ውጤታማ እንደነበረ ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጀምሮ ከአናቱ ያሉት ሁሉም ወታደራዊ መኮንኖች በይፋ ምስክርነታቸውን የሰጠለት ሃቅ ነው፡፡ ስለዚህም፣ የስጋት ዐውድ ትንተናው ከመከላከያ በተቃራኒ የቆመ አይደለም፡፡ ሌላ የፖለቲካ ሴራ ከሌለ በቀር፡፡ ሦስተኛ፣ በክልሉ የካቢኔ አባል የሚመራ የሰላምና ደህንነት ቢሮ የተደራጃው በሥሩ የሚገኙ የፀጥታ ተቋማት የስጋት ዐውድን ከመተንተን ጀምሮ የሕዝቡን ሰላም ለማስከበር የተለያዩ እቅዶችን ቀርጾ ለማስፈጸም ነው፡፡ ልዩ ኃይልም በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ስር ሆኖ በተዋረደ ተጠሪነቱ ለዚህ ቢሮ እንደሆነ ልብ ይሏል፡፡ መቼም፣ “ልዩ ኃይል ሕገ-ወጥ ነው” የሚሉትን ውንጀላ በእነዚህ ማሳያዎች ብቻ ዋጋ ቢስነቱን ማስረገጥ ይቻላል፡፡ ❷. "ብሔር-ተኮር ነው" አስቂኙ መከራከሪያ እዚህ ላይ ነው። አንደኛ ነገር፣ የሀገሪቱ ፖለቲካዊ መዋቅራት ብሔር-ተኮር ናቸው፡፡ ሁለተኛ፣ ይህን የሚሉ አካላት ብሔራቸውን እየጠሩ ነው ወንበር ላይ የተቀመጡት፡፡ ሦስተኛ፣ ብሔር የፖለቲካል-ኢኮኖሚው መዘውር መሆኑ ይታወቃል፡፡… እናም፣ “የልዩ ኃይል አደረጃጀት ብሔር-ተኮር ነው” ማለት የክፍለ ዘመኑ ስላቅ ነው። ብሔር-ተኮር አደረጃጀትን አለመቀበል የሚጀምረው አጥንትና ጉልጥምት ቆጥሮ ሞት የሚረጨውን ሰነድ በዐዲስ ማኀበራዊ ውል ማደስ ሲቻል እንጂ፤ የክልል ልዩ ኃይል ፖሊስን በመበተን አይደለም። በአናቱም፣ ጠሚው ያውም ጉዳዩ የሕዝብ እንጂ፤ የእሳቸው ሥልጣን እንዳልሆነ እያወቁ “ለአንድ ክልል ብለን ሕገ-መንግሥቱን አናሻሽልም” በማለት የሞት መዘግቡን ዕድሜ ማራዘማቸውን አንዘነጋውም፡፡ ከዚህ ስንነሳ፣ የዐማራ ሕዝብም ‹ለትሕነግ እና ለኦሮሚያ ብልፅግና የመሬት ወረራ እንዲያመች ብዬ ልጆቼን አልበትንም› የማለት ሙሉ መብት አለው፡፡ ምን ያህል ብልጣ-ብልጥነትና ሥልጣን ወዳድነት እንደነገሠ የሚያስረግጠው ደግሞ፣ የብሔር-ኮታ በሚያስተገብር የሀገር መከላከያ ሠራዊት እየመሩ “ልዩ ኃይል ብሔር-ተኮር ነው” ለማለት መድፈራቸው ነው። ❸. "የፌዴራል የፀጥታ ኃይሎችን የሚገዳደር ነው” ይህ መከራከሪያ ከሰሜኑ ጦርነት መነሻ አንፃር ውሃ የሚያነሳ ቢመስልም፤ ኃይልን የፖለቲካ ቁማር ማስፈፀሚያ የማድረግ ልምምዶች እስከቆሙ ድረስ፣ ክልሎች ከራሳቸው ውስጣዊ ሁኔታ ተነስተው ከውስጥም ይሁን ከውጭ የሚመጣን ወንጀልና ሕገ-ወጥነት ለመከላከል የፀጥታ ዐቅም መፍጠራቸው ለማዕከላዊ መንግሥቱ ስጋት ሊሆንበት አይችልም። በነገራችን ላይ፣ የአሜሪካ ፌዴሬሽን አባል ስቴቶች ልዩ ኃይል የሚመስል እስከ ሂሊኮፕተር የታጠቀ የክልል አርሚ እንዳላቸው ልብ ይሏል። ብሔር-ተኮሩ የፌዴራል ሥርዓት እንዲቀጥል ፍላጎት ባላቸው ሰዎች የክርክር መንፈስ መልሰን ብንሞግታቸው ራሱ፦ ኢትዮጵያ እውነተኛ፣ ከፓርቲ ጣልቃ-ገብነት ራሱን የሚጠብቅ፣ ከማዕከል የማይታዘዝ፣ ክልሉን በአገሪቱ ሕግ የሚመራ ጠንካራ አስተዳደርን የሚያነብር የፌደራል ሥርዐት ትከተል ከተባለ፤ የልዩ ኃይል አደረጃጀት ለፌደራል ሥርዐቱ ድጋፍ እንጂ፣ ስጋት አይሆንም። በተቀረ የዐማራም ሆነ የሶማሌ፣ የጋምቤላም ሆነ የአፋር፣ የደቡብም ሆነ የሲዳማ ልዩ ኃይል ስጋት ሊሆኑ የሚችሉት State Formation ላይ ላለው የኦሮሚያ ክልል እና ለዐቢይ አሕመድ የፌዴራል-ኦሮሚያ መንግሥት እንጂ፤ ለፌደራል ሥርዐቱ አይደለም። ❹. "የሀገር ኢኮኖሚን ይበላል" የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ዓመታዊ በጀት አንድ መቶ ቢሊዮን ተቃርቧል (በየጊዜው አራተኛ ሩብ ዓመት ላይ በተወካዮች ም/ቤት በኩል የሚወሰንለት ተጨማሪ በጀት ሳንዘነጋ፡፡) በዚህ ደረጃ ግዙፍ በጀት የሚወስድ ተቋም ይሄ ሁሉ ወጭ ወጥቶበትም፡- በትግራይ፣ በወለጋ፣ በከሚሴ የነበረው ደካማ ሚና የሚታወቅ ነው።

መሳይ መኮነን ይናገራል... 🔸🔸🔸🔸🔸🔸 ተገማች እንቅስቃሴዎች። አሁን የመንግስት እቅድ እርቃኑ ተጋልጧል። ትጥቅ ማስፈታቱና የአማራን ልዩ ሃይል ማፈራረሱ የኦሮሚያ ብልጽግና ተቀዳሚና በአስቸኳይ መፈጸም የሚገባው ጉዳይ ተደርጎ ወደ ተግባር መቀየሩን በተመለከተ ጥርጣሬ የማያስፈልገው ሆኖ በሁሉም ዘንድ የታመነበት ይመስለኛል። አሁን ጨዋታውን መቀየር ተፈልጓል። የተወሰኑ እንቅስቃሴዎች ይኖራሉና ነቅቶ መጠበቁ ግድ ይላል። ትጥቅ ማስፈታቱ በሌሎችም ክልሎች እንደሚካሄድ አድርጎ ለማሳየት የሀሰት ዜናዎች በመንግስት መገናኛ ብዙሃን በስፋት ይወጣሉ። አንዳንድ ክልሎች ተወያይተው ውሳኔ ማስተላለፋቸውንና ወደተግባር ለመግባት መዘጋጀታቸውን የሚያሳዩ ዜናዎች ከዘሞኑ በብዛት ይለቀቃሉ። ይህን የሚያጎሉ ድራማዎች ተሰርተው ለህዝብ ይቀርባሉ። ግን እውነታው ሌላ ነው። ህዝብን ማደናገርና እርምጃው ከአማራ ክልል ውጪ እንዳለ ተደርጎ ህዝቡ እንዲቀበለው የተለያዩ ሀሰተኛ ዘገባዎች በመንግስት ሚዲያዎችና በብልጽግና ዲጂታል ሰራዊት አማካኘት አየሩን እንዲሞሉት ይደረጋል። እዚህ ላይ መዘናጋትና በፕሮፖጋንዳው መጠለፍ አይገባም። እርምጃው አንድና አንድ ብቻ ነው። የኦሮሚያ ብልጽግና የአማራ ክልል ሽባ ለማድረግ በስውር ያቀደውን መንግስታዊ ሽፋን ሰጥቶት የጀመረው ሀገር አጥፊ እርምጃ ነው። አራት ነጥብ። ምናልባት ህዝባዊ ንቅናቄው መስመሩን እንዲስት ሊደረግ ይችላል። የሃይማኖት ተቋማት በተለይም መስጂዶች ላይ ጥቃት በመፈጸም ሌላ ቀውስ እንዲፈጠር የመንግስት ደህንነቶች መንቀሳቀሳቸው ይነገራል። የኦሮሞ ህዝብን የሚያጥላሉ ጽሁፎችና መፈክሮች ተዘጋጅተወ ወደ ተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች መበተናቸውንም መረጃው ደርሶኛል። ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ግብግብ እንዲገጠምና በህዝብና በሰራዊቱ መሀል ግጭት እንዲፈጠርም መታቀዱን ከውስጥ የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። ሌሎች በርካታ ሴራዎች ተጎንጉነዋል። ከፍተኛ ጥንቃቄ ያስፈልጋል። በየከተሞቹ የሚደረጉት ህዝባዊ ትዕይንቶችና ንቅናቄዎች በተጠናና የመጣውን መንግስታዊ ሴራ በሚያከሽፍ መልኩ መሆን ይኖርበታል። ጸጉረ ልውጦችን በሚገባ መከታተል፡ የጥላቻና አንድን ማህበረሰብ ነጥሎ የሚያንቋሽሹ መልዕክቶችን በቶሎ ማስወገድና ማጋለጥ ይገባል። በተረፈ የአብይ መንግስት ከህወሀት ጋር የጀመረውን መርህ አልባ ግንኙነት በአማራውና በተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ኪሳራ ለማሳካት ቆርጦ ተነስቷል። ህወሀት ተጨማሪ ሃይል ከመገንባት ባሻገር ጦሩን እያስጠጋ መሆኑን ዛሬ ያገኙሁት መረጃ ያመለክታል። 5 አርሚ ሰራዊቱ ወደ ወልቃይት ተጠግቷል። በተመሳሳይ 3 አርሚ ጦር ራያ ላይ ሰፍሯል። እጅ እግሩ ታስሮ ለባርነት እንዲማገድ የተፈረደበት የአማራና የአፋር ህዝብ ከፊቱ ትልቅ አደጋ ተደቅኖበታል። ይህ አደጋ የሚቀለበሰው አንድም ከመንግስት አሳሳችና በማታለያዎች የተሸፈኑ ፕሮፖጋንዳዎችን በማጋለጥና አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ ነው። መደራጀት ያስፈልጋል። መረጃ መለዋወጥ የግድ ነው። ዛሬ የኢንተርኔት መስመሮችን በተለይ በአማራ ክልል ዘግተውታል። ከሰሞኑ ማንኛውም ግንኙነት መቋረጡ የሚጠበቅ ነው። ይህን ታሳቢ ያደረገ ዝግጅት ከወዲሁ ሊኖር ይገባል። ጠ/ሚር አብይ ታላቅ ጥፋት ሀገሪቱ ላይ ለማምጣት የተዘጋጁ ይመስላሉ። በታሪክ ከተጠያቂነት አያመልጡም። ኢትዮጵያ ላይ አሁን ለሚደርሰው ዕልቂት በግልም ይሁን በሚመሩት ቡድን ለፍትህ መቅረባቸውን አስረግጦ ማሳወቅ ይገባል። Mesay Mekonnen

ስልሳ ሚሊዮን ሕዝብ ለታጣቂ አፈሙዝ አሳልፎ ሰጥቶ እራሱን ለማዳን የሚሞክር አስገራሚ ፍጥረት... በቁሙ የሞተ ሰው "የበላይ አካል ይገድለኛል" ብሎ ሲርበተበት አስበኸዋል።
ስልሳ ሚሊዮን ሕዝብ ለታጣቂ አፈሙዝ አሳልፎ ሰጥቶ እራሱን ለማዳን የሚሞክር አስገራሚ ፍጥረት... በቁሙ የሞተ ሰው "የበላይ አካል ይገድለኛል" ብሎ ሲርበተበት አስበኸዋል።

የእምነት መሪዎች የአገርና የዜጎች ጉዳይ አያገባንም ብለው የማይሞላ ቀፈታቸውን በገዥዎች ሾረፋ በሚሞሉበት ዘመን የግፉአን ድምጽ ሆኖ የተገኘ ታላቅ ሰው...!! ክበርልኝ!!
የእምነት መሪዎች የአገርና የዜጎች ጉዳይ አያገባንም ብለው የማይሞላ ቀፈታቸውን በገዥዎች ሾረፋ በሚሞሉበት ዘመን የግፉአን ድምጽ ሆኖ የተገኘ ታላቅ ሰው...!! ክበርልኝ!!

መስከረምን ለሶስተኛ ጊዜ አፍነው ወስደዋታል
መስከረምን ለሶስተኛ ጊዜ አፍነው ወስደዋታል

ደብረ ማርቆስ ዛሬም ተሰልፋ ቁጣዋን እየገለጸች ነው
ደብረ ማርቆስ ዛሬም ተሰልፋ ቁጣዋን እየገለጸች ነው