Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 355 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 646,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 354 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 355 名订阅者。
根据 22 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -133,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 11.78% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 562 次浏览,首日通常累积 1 691 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 34。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 23 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 355
订阅者
-324 小时
-387 天
-13330 天
帖子存档
14 355
"እንዴ ግስላ የተቆጣውን ሕዝብ አዘናግታችሁ ያሰብኩትን ዘመቻ የማታሳኩ ከሆነ ከወንበር አንስቼ ወደ መቃብር እንደማወርዳችሁ እወቁ" የሚል ዛቻ ካስተናገዱ የብአዴን አመራሮች "ሕዝቤ ሆይ በሶሻል ሚዲያ የሚወራውን አትስማ" ከማለት ባለፈ "ሕዝቤ ሆይ ጥያቄህን ሰምተናል" የሚል መልስ አይጠበቅም።
አሳዬ ደርቤ
14 355
ሦስት መረጃዎች
1. የዐቢይ ታጣቂ በኮምቦልቻ ከተማ ተኩስ ከፍቶ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ንጹሐንን ገድሏል።
2. ባሕር ዳር ከተማ በተኩስ እየተናጠች ነው
3. የሱማሌ ሕዝብ "ልዩ ሃይላችን ማፍረስ አይታሰብም" የሚል ተቃውሞውን እያሰማ መሆኑን ኦጋዴን ሚዲያ ዘግቧል።
ድል ለኢትዮጵያ
ድል ለአማራ ሕዝብ
14 355
በውጭ አገር ለምትኖሩ የአማራ ልጆች በሙሉ በኦነግ ሸኔ ታጣቂ የአማራን ሕዝብ ጨፍጭፎ መጨረስ እንደማይቻል የተረዳው አረመኔያዊ ሥርዓት ያለ የሌለ ወታደሩን አዝምቶ የአማራን ሕልውና ለማክሰም እየተንቀሳቀሰ ስለሆነ የወገናችሁ ድምጽ እና ክንድ ሁኑ።
14 355
በሱዳን ወታደራዊ ኃይል የተፈፀመብንን ወርራን በተመለከተ መመከቱ ቀርቶ ትንፍሽ አለማለቱም ገሃድ ነው፤ (አንድ ሁለቴ የሰጣቸውን ኢ-ተግባራዊ መግለጫዎች ረስቼያቸው አይደለም፡፡)
ከዚህ ባለፈ፣ ልዩ ኃይሎች በአንዳንድ አካባቢዎች በአነስተኛ በጀት ከመከላከያው በተሻለ ለሕዝብ እና ለአገር ትርጉም የሚሰጥ ድል ማምጣታቸውን ታሪክ መዝግቦታል።
ለማሳያም፣ መከላከያ ሠራዊቱ ላይ ጥቃት በተሰነዘረበት ሰዓት ዛሬ "የሀገር ኢኮኖሚን ይበላል" እየተባለ የሚዘለፈው የዐማራ ልዩ ኃይል እንደደረሰለት መጥቀስ ይቻላል።
መከላከያ፣ አገር የማፍረሱን ዘመቻ ለመመከት ሙሉ በሙሉ ፊቱን ወደ ሰሜን ሲያዞር፤ ዓለም ዐቀፉን አሸባሪ አልሸባብን ሳይቀር ወጥሮ በመያዝ የምስራቁን ድንበር ያስከበረው የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል እንደሆነም ማስታወስ ይቻላል፡፡
ለዚህም ነው፣ ኢትዮጵያ ካለችበት ሁኔታ አኳያ ይህ ምክንያት ውሃ አያነሳም የምንለው። በዚህ ላይ ኢኮኖሚ ከህልውና አይበልጥም፡፡
❺. “ተቋማዊ ባህሪ የለውም (የትጥቅ ምንጩ አይታወቅም፣ ከውጭ ኃይሎች ጋር ግንኙነት አለው)”
አረ አታስቁን?! የሁሉም ክልል ልዩ ኃይል በጀት የሚጸድቀው በክልላቸው ምክር ቤት እንደሆነ እኛ እንንነግራችው እንዴ? በተቀረ፣ ይሄ ጥያቄ መቅረብ ያለበት በፌደራል መንግሥቱ እና በመከላከያ በጀት ከድሮንና ጄት በቀር፤ እስከ አፍንጫው ለታጠቀው የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ብቻ ነው፡፡
❻. “ይህ ሁሉ ወጭ ወጥቶባቸውም በችግር ጊዜ ራሳቸውን ችለው አይቆሙም፤ የፌዴራሉን የፀጥታ ኃይል ድጋፍ ይሻሉ”
ለመሆኑ በየትኛው ችግር? በወለጋው እና በጉጂው ከሆነ እዛው ተነጋገሩበት፡፡ የዐማራ ልዩ ኃይል፣ የመከላከያ ብቻ ሊሆን የሚገባውን ጦርነት በሙሉ ዐቅሙ በመሳተፍ ደርሶላታል፡፡ ከዚህ አኳያም፣ ብዙ ወጪ ወጥቶበት እገዛ የፈለገው ፌደራሉ እንጂ፤ ልዩ ኃይል አይደለም፡፡
❼. “የሕዝብ ቅቡልነት ጥያቄ ይነሳባቸዋል”
ለዚህኛው ምክንያት እንደማሳያ የሚያቀርቡት "የዐማራ ልዩ ኃይል ከሚሴ ላይ አትግባ፤" መባሉን ነው። ይሄ መቼም ሸኔ እና ሕዝብን ያልለየ አደገኛ የሁኔታ ትንተና ነው።
አንደኛ ነገር፣ የዐማራ ልዩ ኃይል የሚባለው ከከሚሴም ከአዊም ከዋግም… ከሁሉም ልዩ ዞኖች ጭምር የተመለመለ ለክልሉ ሰላምና መረጋጋት የሚሰራ ኃይል ነው።
ሁለተኛ፣ በሌሎች ልዩ ዞኖች በአስፈላጊ ጊዜ ገብቶ የሚወጣው፣ ካምፖችንም ያደራጀው የዐማራ ልዩ ኃይል ከሚሴ ላይ ተቃራኒ ድምፆች መሰማቱ ጤነኛም አሳማኝም አይደለም፡፡
በተለይ፣ ከእዚያ ዞን በተደጋጋሚ ጊዜ የተሰነዘሩትን የሽብር ጥቃቶች እዚህ ጋ ስንደምራቸው፤ አስተያየቱ ኦነጋዊ ፍላጎት ያለው አመራር እንጂ፤ የልዩ ዞኑ ንፁሃን ነዋሪዎች እንዳልሆነ አይሳተንም። ዛሬ አጣዬ ላይ የተሰነዘረው ጥቃትም መከራከሪያችን መሬት የረገጠ እንደሆነ ያሳያል፡፡
እስኪ ከተጨባጭ ሁኔታ ተነስተ ደግሞ አጭር ንጽጽር እናድርግ፦
በወለጋ ዞኖች በዐማራ የተፈናቀለ ኦሮሞ የለም፡፡ ከከሚሴ በሚነሳ የሽብር ኃይል ግን በመቶ ሺሕ የሚቆጠር ዐማራ በተደጋጋሚ ተፈናቅሏል፡፡
እናሳ፣ ታዲያ የየትኛው ክልል ልዩ ኃይል ነው የቅቡልነት ችግር ያለበት?
ሌላኛው የክርክራችን ጭብጥ፦ “ቅቡልነት የለውም” የሚለውን ውንጀላ፣ በሁሉም የዐማራ ክልል ከተሞች እየተደረገ ያለው ሰልፍ በበቂ የሚያመክነው መሆኑ ነው።
ከዚህ ባለፈ፣ አገር ሊያፈርስ የሞከረው እና አገርን ከፍርሰት የታደገው ልዩ ኃይል የእኩል ሚዛን ላይ የተቀመጡበት ሁነት የክፍለ ዘመኑ ክህደት ተደርጎ ተመዝግቧል።
ያም ሆነ ይህ የወደቁት የዐማራ ልጆች አፅም በክብር ሳያርፍ፣ በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የዐማራ ልዩ ኃይል ሰማዕታት ቤተሰቦች ጎዳና ላይ በወጡበት ሁኔታ፣ ሰማዕታቱ የተሰውለት ዓላማ ግቡን ሳይመታ የሚፈርስም ሆነ የሚበተን ልዩ ኃይል የለም።
የሁላችንም መተማመን በሚያረጋግጥ አግባብ ሕገ-መንግሥታዊ ማሻሻይ ሲደረግ (ወይም እስካሁን እንደተፋዘዘ የቀጠለው “ብሔራዊ ምክክር መድረክ” የሚባለው ስብስብ ላይ አጀንዳው ቀርቦ ውሳኔ ካገኘ በኋላ) የልዩ ኃይል አደረጃጀት መልክ እንዲይዝ ሊደረግ ይችላል። ይህ እስኪሆንም በትእግስት መጠበቁ ለሁሉም የሚበጅ ነው፡፡
አውቆ መታረም ይመከራል።
ስንጠቀልለው…
ዛሬ እንደ ዐዲስ ሙሽራ እፍ ያሉት ኦሕዴድ እና ወያኔ ስለ ዐማራ ልሂቅም ሆነ ስለ ዐማራ ልዩ ኃይል ሲያወሩ በውስጠ-ዘ ስለ መላው የዐማራ ሕዝብ እንደሆነ ከገባን ሰንብቷል፡፡
ሩቅ ሳንሄድ አዲሱ የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ እንደዛተው ማን ላይ ሒሳብ እንዳወራረዱ በበቂ ያየነው እውነታ ነው፡፡
መቼም የተደፈሩ መነኩሴዎችን፣ ሕጻናትን፣ በጅምላ የተገደሉ አርሶ ዐደሮችን፣ የታረዱ ቀሳውስቶችን፣ የተዘረፉ የድሃ ጥሪቶችን፣ የወደሙ ሕዝባዊ ተቋማትን… ጃል፣ የቱን ጠቅሰን የቱን እንተወው?!
በተረፈ፣ የታሰበው ቀመር ገብቶናል፡፡ አተገባበሩም በአራት የተከፋፋለ ቅደም-ተከተል አለው፡፡
የመጀመሪያው፣ በጦርነቱ ላይ እጃቸውን በጉንጫቸው ያስጫነ ወታደራዊ ድል ያስገኘውን የዐማራ ልዩ ኃይል ፖሊስ ማፍረስ ነው፡፡ ይህ ዘመቻ በበቂ ግቡን ከመታ በኋላ ወደ ቀጣዩ እርምጃ ይሸጋገራሉ፡፡
በሁለተኛው ዙር፣ የሚሊሻውን እና የፋኖን ትጥቅ መግፈፍ ነው፡፡
ሦስተኛው ስቴፕ፣ የክልሉን መደበኛ ፖሊስ ቁጥር በእጅጉ ማመንመን ላይ የሚያተኩር ነው፡፡
ከዚህ በኋላ ማን ቀረ? ከባህልና ከወጉ አኳያ በሬውን ሸጦ ጠመንጃ የሚገዛው ተርታው ሕዝብ፡፡
በመጨረሻም፣ ምሽጎቹን አንድ በአንድ አፍርሰው ብቻውን ያስቀሩትን ሕዝብ ቤት ለቤት እየዞሩ በሃቁ የገዛውን መሳሪያ ያስወርዱታል፡፡
በዚህም፣ የኦሮሞ እና የትግራይ ልሂቃን በኢ-መደበኛ ወጎች “ዐማራ ዱላም ቢሆን መያዝ የለበትም” እያሉ የሚደጋግሙትን ዕቅድ በምልዓት ያስፈጽማሉ፡፡
ስለዚህም፣ ዛሬ ሕዝባችን ከልዩ ኃይል ጎን የሚቆመው፣ አንድም ልጆቹ ስለሆኑ፤ አንድም ደግሞ ለነገ ራሱን መከላከያ ብቸኛው መንገድ በመሆኑ ነው፡፡
እየመጣ ያለው አደጋ ከገመትነውም በላይ አውዳሚ ነው፡፡ ካልተባበርን እንወድቃለን፡፡ በያለንበት እንወጥር።
ዛሬ ክልሉን “ቀራኒዮ” ቢያስመስሉትም-ቅሉ፤ በርትተህ ከቆምክ በሰሞነ-ሕማማት የከፈልከውን ዋጋ፣ በተንሳኤ ትሽረዋለህ፡፡
***
አይዞን ወገን፤ ቀና በል ቀን አለህ!!!
ሙሉዓለም ገ/መድኀን
ከሁመራ-ጎንደር
14 355
የሚነበብ ብቻ ሳይሆን post & Share የሚደረግ
ገራሚ ትንታኔ
የሰሞነ-ሕማማት ፪ኛው መልዕክት
Mulualem G. Medhin
***
በቅድሚያ መታወቅ ያለበት አንድ እውነታ፣ የዐማራን ልዩ ኃይል የማፍረሱ ሴራ ዛሬ የመጣ ዐዲስ ሃሳብ አለመሆኑ ነው፡፡ በሚዲያም በድፍረት ሲነገር የአሁኑ የመጀመሪያው አይደለም፡፡
በከፍተኛ የሐዘን ስሜት በተሰበርንበት ሰኔ 15/2011 ዓ.ም በባህር ዳር የተፈፀመውን የእነ ዶክተር አምባቸው ግድያን "ዐማራ እርስ በርሱ ተበላላ" በሚል እንደዕድል ለመጠቀም የኦሮሞ እና የትግሬ ልሂቃን ስለጉዳዩ በ“መተንተን” ሚዲያዎቹን በሙሉ ተቆጣጥረውት እንደነበረ ይታወሳል፡፡
በርግጥ በዛን ወቅት፣ የኦሕዴድ ዋንኛ ስጋት ወያኔ በመሆኑ የአባ ገዳ ልጆች በግላጭ የዐማራ ልዩ ኃይል እንዲፈርስ መጠየቁ ጊዜው ገና በመሆኑ፣ በገደምዳሜ ከቁጥጥር ውጩ እንዳይሆን የሚያደርግ ሥርዐት እንዲበጅለት ማሳሰብን ብቻ ነበር የመረጡት፡፡
ለትግሬ ልሂቃን ግን ይህ ኃይል የወዲያውኑ ስጋት በመሆኑ በይፋ እንዲፈርስ ከመቀስቀስ አልቦዘኑም፡፡ በተለይ ጄነራል ፃዳቃን ገ/ተንሳኤ በቴሊቪዥን ቀርቦ ያለ ምንም መሸፋፈን “የዐማራ ልዩ ኃይል መፍረስ አለበት” ሲል እንደነበረ ፈጽሞ አይዘነጋም፡፡
በወቅቱ የጄነራሉ ስሌት፣ ወያኔ ወደ አራት ኪሎ ለመመለስ ያለውን ፍላጎት የሚያመክነው የዐማራ ልዩ ኃይል እንደሆነ ከመረዳት የመጣ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህ ላይ፣ ፃድቃን በ1983ቱ አዲስ አበባ ድረስ ማን ተሸክሞ እንዳመጣው የሚረሳ ሰው አይደለም፡፡
ይሁንና፣ በዚያን ጊዜ የፌደራል-ኦሮሚያ ብልጽግና ቁጥር አንድ ስጋት ወያኔ በመሆኑ፤ ባለፉት ሁለት ዐመት ጦርነቶች እንደታየው ገትሮ ሊያቆመው የሚችለው የዐማራ ልዩ ኃይል እንደሆነ ጠንቅቀው አውቀዋል፡፡
ጨፌው በአራት ኪሎ የነገሠውም በኦሮ-ማራ ጥምረት መሆኑን ከማንም በላይ አይዘነጋውም፡፡ ስለዚህም፣ እነ ፃድቃንን “ይፍረስ” እያሉ የሚቀሰቅሱበትን ገፊ-ምክንያት ስለሚያውቁ፣ የዐማራ ልዩ ኃይልን ተንከባክቦ ማቆየት፣ የቤተ-መንግሥቱን ዕድሜ ማራዘም በመሆኑ፣ “ይፍረስ” የሚለውን ሃሳብ ውጉዝ ከመአርዮስ ለማድረግ ማንም አልቀደማቸውም፡፡
ዛሬ ወያኔ ተዳክሟል፡፡ በማይገመት ሁኔታም በፖለቲካ ቁመናውም ያለ ፌደራል መንግሥቱ ድጋፍ ከቁጫ ወይም ከሐረሪ የተለየ ተሰሚነት የለውም፡፡ ብቻውን መቆም ስለማይችልም የኦህዴድ ጁኒየር ፓርትነር ሆኖ ተከስቷል።
ስለዚህም፣ የኦሮሞ ልሂቃን ‹አሁን መመታት ያለበት የዐማራ ኃይል ነው› ብለው መነሳታቸው፣ ለድብቅ ፍላጎታቸው ወሳኙ ሰዓት መሆኑን በማስላት እንደሆነ ለማናችንም አይጠፋንም፡፡
እውነታው ይህ ቢሆንም፤ በመንግሥት በኩል ልዩ ኃይሉን ለማፍረስ የተደረደሩት ምክንያቶች ረብ-የለሽ መሆናቸውን እየጠቀሱ መሞገቱ፣ ጉዳዩ ሳይገባቸው ከአፍራሹ ጎን ለቆሙ ቅን ወገኖች ለማስረዳት አስፈላጊ ስለሆነ ነጣጥለን እንመልከታቸው፡፡
❶. “የስጋት ዐውድ ትንተና የለውም”
የልዩ ኃይል አደረጃጀት ከሚቀርብበት ትችት አንዱ፣ ‹መከላከያ ከአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተነስቶ የዓለምንና የቀጠናውን ሁኔታ ገምግሞ አደጋ ሲመጣበት ወታደራዊ ውሳኔ ላይ ይደርሳል። ልዩ ኃይል ግን ይህ ባህሪ የለውም፤› የሚል ነው፡፡
ይህ መከራከሪያ ፍፁም ስህተት መሆኑን በሦስት አመክንዮዎች እናስረግጠው፡፡
አንደኛ፣ የልዩ ኃይል ፖሊስ ተልዕኮ እንደየ ክልሉ ሁኔታ የሚወሰን ሆኖ መከላከያ እና ፌዴራል ፖሊስ የማይሸፍኗቸውን ግዳጆች የሚፈጽሙ መሆናቸው ነው፡፡
ሁለተኛ፣ የዐማራ ልዩ ኃይልን አብነት ወስደን ካየነው ከውስጥም ሆነ ድንበር ተሻጋሪ ጥቃቶችን በመመከትና በማምከን ረገድ የፌዴራል የፀጥታ ተቋማት አጋዥ ሆኖ ከመሰለፉም በዘለለ፤ ውጤታማ እንደነበረ ከጠቅላይ ሚንስትሩ ጀምሮ ከአናቱ ያሉት ሁሉም ወታደራዊ መኮንኖች በይፋ ምስክርነታቸውን የሰጠለት ሃቅ ነው፡፡
ስለዚህም፣ የስጋት ዐውድ ትንተናው ከመከላከያ በተቃራኒ የቆመ አይደለም፡፡ ሌላ የፖለቲካ ሴራ ከሌለ በቀር፡፡
ሦስተኛ፣ በክልሉ የካቢኔ አባል የሚመራ የሰላምና ደህንነት ቢሮ የተደራጃው በሥሩ የሚገኙ የፀጥታ ተቋማት የስጋት ዐውድን ከመተንተን ጀምሮ የሕዝቡን ሰላም ለማስከበር የተለያዩ እቅዶችን ቀርጾ ለማስፈጸም ነው፡፡
ልዩ ኃይልም በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ስር ሆኖ በተዋረደ ተጠሪነቱ ለዚህ ቢሮ እንደሆነ ልብ ይሏል፡፡
መቼም፣ “ልዩ ኃይል ሕገ-ወጥ ነው” የሚሉትን ውንጀላ በእነዚህ ማሳያዎች ብቻ ዋጋ ቢስነቱን ማስረገጥ ይቻላል፡፡
❷. "ብሔር-ተኮር ነው"
አስቂኙ መከራከሪያ እዚህ ላይ ነው።
አንደኛ ነገር፣ የሀገሪቱ ፖለቲካዊ መዋቅራት ብሔር-ተኮር ናቸው፡፡
ሁለተኛ፣ ይህን የሚሉ አካላት ብሔራቸውን እየጠሩ ነው ወንበር ላይ የተቀመጡት፡፡
ሦስተኛ፣ ብሔር የፖለቲካል-ኢኮኖሚው መዘውር መሆኑ ይታወቃል፡፡… እናም፣ “የልዩ ኃይል አደረጃጀት ብሔር-ተኮር ነው” ማለት የክፍለ ዘመኑ ስላቅ ነው።
ብሔር-ተኮር አደረጃጀትን አለመቀበል የሚጀምረው አጥንትና ጉልጥምት ቆጥሮ ሞት የሚረጨውን ሰነድ በዐዲስ ማኀበራዊ ውል ማደስ ሲቻል እንጂ፤ የክልል ልዩ ኃይል ፖሊስን በመበተን አይደለም። በአናቱም፣ ጠሚው ያውም ጉዳዩ የሕዝብ እንጂ፤ የእሳቸው ሥልጣን እንዳልሆነ እያወቁ “ለአንድ ክልል ብለን ሕገ-መንግሥቱን አናሻሽልም” በማለት የሞት መዘግቡን ዕድሜ ማራዘማቸውን አንዘነጋውም፡፡
ከዚህ ስንነሳ፣ የዐማራ ሕዝብም ‹ለትሕነግ እና ለኦሮሚያ ብልፅግና የመሬት ወረራ እንዲያመች ብዬ ልጆቼን አልበትንም› የማለት ሙሉ መብት አለው፡፡
ምን ያህል ብልጣ-ብልጥነትና ሥልጣን ወዳድነት እንደነገሠ የሚያስረግጠው ደግሞ፣ የብሔር-ኮታ በሚያስተገብር የሀገር መከላከያ ሠራዊት እየመሩ “ልዩ ኃይል ብሔር-ተኮር ነው” ለማለት መድፈራቸው ነው።
❸. "የፌዴራል የፀጥታ ኃይሎችን የሚገዳደር ነው”
ይህ መከራከሪያ ከሰሜኑ ጦርነት መነሻ አንፃር ውሃ የሚያነሳ ቢመስልም፤ ኃይልን የፖለቲካ ቁማር ማስፈፀሚያ የማድረግ ልምምዶች እስከቆሙ ድረስ፣ ክልሎች ከራሳቸው ውስጣዊ ሁኔታ ተነስተው ከውስጥም ይሁን ከውጭ የሚመጣን ወንጀልና ሕገ-ወጥነት ለመከላከል የፀጥታ ዐቅም መፍጠራቸው ለማዕከላዊ መንግሥቱ ስጋት ሊሆንበት አይችልም።
በነገራችን ላይ፣ የአሜሪካ ፌዴሬሽን አባል ስቴቶች ልዩ ኃይል የሚመስል እስከ ሂሊኮፕተር የታጠቀ የክልል አርሚ እንዳላቸው ልብ ይሏል።
ብሔር-ተኮሩ የፌዴራል ሥርዓት እንዲቀጥል ፍላጎት ባላቸው ሰዎች የክርክር መንፈስ መልሰን ብንሞግታቸው ራሱ፦ ኢትዮጵያ እውነተኛ፣ ከፓርቲ ጣልቃ-ገብነት ራሱን የሚጠብቅ፣ ከማዕከል የማይታዘዝ፣ ክልሉን በአገሪቱ ሕግ የሚመራ ጠንካራ አስተዳደርን የሚያነብር የፌደራል ሥርዐት ትከተል ከተባለ፤ የልዩ ኃይል አደረጃጀት ለፌደራል ሥርዐቱ ድጋፍ እንጂ፣ ስጋት አይሆንም።
በተቀረ የዐማራም ሆነ የሶማሌ፣ የጋምቤላም ሆነ የአፋር፣ የደቡብም ሆነ የሲዳማ ልዩ ኃይል ስጋት ሊሆኑ የሚችሉት State Formation ላይ ላለው የኦሮሚያ ክልል እና ለዐቢይ አሕመድ የፌዴራል-ኦሮሚያ መንግሥት እንጂ፤ ለፌደራል ሥርዐቱ አይደለም።
❹. "የሀገር ኢኮኖሚን ይበላል"
የሀገር መከላከያ ሚኒስትር ዓመታዊ በጀት አንድ መቶ ቢሊዮን ተቃርቧል (በየጊዜው አራተኛ ሩብ ዓመት ላይ በተወካዮች ም/ቤት በኩል የሚወሰንለት ተጨማሪ በጀት ሳንዘነጋ፡፡)
በዚህ ደረጃ ግዙፍ በጀት የሚወስድ ተቋም ይሄ ሁሉ ወጭ ወጥቶበትም፡- በትግራይ፣ በወለጋ፣ በከሚሴ የነበረው ደካማ ሚና የሚታወቅ ነው።
14 355
መሳይ መኮነን ይናገራል...
🔸🔸🔸🔸🔸🔸
ተገማች እንቅስቃሴዎች። አሁን የመንግስት እቅድ እርቃኑ ተጋልጧል። ትጥቅ ማስፈታቱና የአማራን ልዩ ሃይል ማፈራረሱ የኦሮሚያ ብልጽግና ተቀዳሚና በአስቸኳይ መፈጸም የሚገባው ጉዳይ ተደርጎ ወደ ተግባር መቀየሩን በተመለከተ ጥርጣሬ የማያስፈልገው ሆኖ በሁሉም ዘንድ የታመነበት ይመስለኛል። አሁን ጨዋታውን መቀየር ተፈልጓል። የተወሰኑ እንቅስቃሴዎች ይኖራሉና ነቅቶ መጠበቁ ግድ ይላል።
ትጥቅ ማስፈታቱ በሌሎችም ክልሎች እንደሚካሄድ አድርጎ ለማሳየት የሀሰት ዜናዎች በመንግስት መገናኛ ብዙሃን በስፋት ይወጣሉ። አንዳንድ ክልሎች ተወያይተው ውሳኔ ማስተላለፋቸውንና ወደተግባር ለመግባት መዘጋጀታቸውን የሚያሳዩ ዜናዎች ከዘሞኑ በብዛት ይለቀቃሉ። ይህን የሚያጎሉ ድራማዎች ተሰርተው ለህዝብ ይቀርባሉ። ግን እውነታው ሌላ ነው። ህዝብን ማደናገርና እርምጃው ከአማራ ክልል ውጪ እንዳለ ተደርጎ ህዝቡ እንዲቀበለው የተለያዩ ሀሰተኛ ዘገባዎች በመንግስት ሚዲያዎችና በብልጽግና ዲጂታል ሰራዊት አማካኘት አየሩን እንዲሞሉት ይደረጋል። እዚህ ላይ መዘናጋትና በፕሮፖጋንዳው መጠለፍ አይገባም። እርምጃው አንድና አንድ ብቻ ነው። የኦሮሚያ ብልጽግና የአማራ ክልል ሽባ ለማድረግ በስውር ያቀደውን መንግስታዊ ሽፋን ሰጥቶት የጀመረው ሀገር አጥፊ እርምጃ ነው። አራት ነጥብ።
ምናልባት ህዝባዊ ንቅናቄው መስመሩን እንዲስት ሊደረግ ይችላል። የሃይማኖት ተቋማት በተለይም መስጂዶች ላይ ጥቃት በመፈጸም ሌላ ቀውስ እንዲፈጠር የመንግስት ደህንነቶች መንቀሳቀሳቸው ይነገራል። የኦሮሞ ህዝብን የሚያጥላሉ ጽሁፎችና መፈክሮች ተዘጋጅተወ ወደ ተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች መበተናቸውንም መረጃው ደርሶኛል። ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ግብግብ እንዲገጠምና በህዝብና በሰራዊቱ መሀል ግጭት እንዲፈጠርም መታቀዱን ከውስጥ የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። ሌሎች በርካታ ሴራዎች ተጎንጉነዋል። ከፍተኛ ጥንቃቄ ያስፈልጋል። በየከተሞቹ የሚደረጉት ህዝባዊ ትዕይንቶችና ንቅናቄዎች በተጠናና የመጣውን መንግስታዊ ሴራ በሚያከሽፍ መልኩ መሆን ይኖርበታል። ጸጉረ ልውጦችን በሚገባ መከታተል፡ የጥላቻና አንድን ማህበረሰብ ነጥሎ የሚያንቋሽሹ መልዕክቶችን በቶሎ ማስወገድና ማጋለጥ ይገባል።
በተረፈ የአብይ መንግስት ከህወሀት ጋር የጀመረውን መርህ አልባ ግንኙነት በአማራውና በተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ኪሳራ ለማሳካት ቆርጦ ተነስቷል። ህወሀት ተጨማሪ ሃይል ከመገንባት ባሻገር ጦሩን እያስጠጋ መሆኑን ዛሬ ያገኙሁት መረጃ ያመለክታል። 5 አርሚ ሰራዊቱ ወደ ወልቃይት ተጠግቷል። በተመሳሳይ 3 አርሚ ጦር ራያ ላይ ሰፍሯል። እጅ እግሩ ታስሮ ለባርነት እንዲማገድ የተፈረደበት የአማራና የአፋር ህዝብ ከፊቱ ትልቅ አደጋ ተደቅኖበታል። ይህ አደጋ የሚቀለበሰው አንድም ከመንግስት አሳሳችና በማታለያዎች የተሸፈኑ ፕሮፖጋንዳዎችን በማጋለጥና አስፈላጊውን እርምጃ በመውሰድ ነው። መደራጀት ያስፈልጋል። መረጃ መለዋወጥ የግድ ነው። ዛሬ የኢንተርኔት መስመሮችን በተለይ በአማራ ክልል ዘግተውታል። ከሰሞኑ ማንኛውም ግንኙነት መቋረጡ የሚጠበቅ ነው። ይህን ታሳቢ ያደረገ ዝግጅት ከወዲሁ ሊኖር ይገባል።
ጠ/ሚር አብይ ታላቅ ጥፋት ሀገሪቱ ላይ ለማምጣት የተዘጋጁ ይመስላሉ። በታሪክ ከተጠያቂነት አያመልጡም። ኢትዮጵያ ላይ አሁን ለሚደርሰው ዕልቂት በግልም ይሁን በሚመሩት ቡድን ለፍትህ መቅረባቸውን አስረግጦ ማሳወቅ ይገባል።
Mesay Mekonnen
14 355
ስልሳ ሚሊዮን ሕዝብ ለታጣቂ አፈሙዝ አሳልፎ ሰጥቶ እራሱን ለማዳን የሚሞክር አስገራሚ ፍጥረት...
በቁሙ የሞተ ሰው "የበላይ አካል ይገድለኛል" ብሎ ሲርበተበት አስበኸዋል።
14 355
የእምነት መሪዎች የአገርና የዜጎች ጉዳይ አያገባንም ብለው የማይሞላ ቀፈታቸውን በገዥዎች ሾረፋ በሚሞሉበት ዘመን የግፉአን ድምጽ ሆኖ የተገኘ ታላቅ ሰው...!!
ክበርልኝ!!
14 355
"ልዩ ሃይሉን ለማፍረስ የተነሳነው ተመካክረን ነው" ለማለት የደፈረው አጋ*ሰስ ይህ እቅዱ ከተሳካለት በቀጣይ የሚያወጣው መግለጫ "ኢትዮጵያን የማፍረስ ተግባር ውስጥ የገባነው በሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ተመካክረን ስለሆነ አርፋችሁ ፍረሱ" የሚል እንደሚሆን አልጠራጠርም።
14 355
"አማራ ክልል ላይ የለኮስከው ጦርነት የማንነት ጥያቄዎችን የመጨፍለቅና ክልሉን የማድቀቅ ዓላማ ያለው ስለሆነ ልዩ ሃይሉ ትጥቅ ቢፈታ እንኳን የማውደም ዘመቻውን እንደማትሰርዘው እርግጥ ነው!" ጎንደር
14 355
የወገን ምክር
➖➖➖➖
አሳዬ ደርቤ
1.በምንም መልኩ ቢሆን ለክፍፍል የሚመች ሴራ ውስጥ ላለመግባት ተጠንቀቁ።
2. የግለሰብ ሐብት ላይ ያነጣጠረ ምንም አይነት ጥቃት ባለመፈጸም ለጎጠኞች ከሚመች ድርጊትና ከስሜታዊነት እራቁ።
3. ቤተ እምነቶችን በትኩረት ነቅታችሁ ጠብቁ።
4. መንጋ በመሆን ፈንታ የጠባቂ አልባው ሕዝብ መንግሥት መሆንን ምረጡ።
5."መሪዎቻችን" ከምትሏቸው ወገኖች ትዕዛዝ አታፈንግጡ።
6. የተሰነዘረብን ወረራ ትጥቅ ከማስፈታት ባለፈ የማንነት ጥያቄዎችን የመጨፍለቅና አማራ ክልልን የማድቀቅ ዓላማ ያዘለ መሆኑን እወቁ።
7. የአማራን ፍትሐዊ ትግል የሚያጠለሹ ምሥሎችን ለመቅረጽ የተዘጋጁ እልፍ አእላፍ ካሜራዎች በዙሪያችሁ መጠመዳቸውን አትዘንጉ!
8. ጥቅምና ጉዳቱን ሳትመረምሩ የምትፈጽሙት ድርጊትም ሆነ የምትናገሩት ቃላት አይኑር።
9. ትግሉን መጥለፍ የሚሹ ኃይሎች በሚፈጽሟቸው ጥቃቶች እንዳትካሰሱ "አንድነታችንን የሚያጠፉ ድርጊቶች ሁሉ የጠላት ሤራዎች ናቸው" የሚል መግባባት ላይ ድረሱ።
Share
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
