ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ ( Ethio Beteseb Media)
ይህ ቻናል መንፈሳዊ መልክቶች ፣ ማኅበራዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ጠቃሚ መረጃዎች የሚተላለፉበት ነውና ቤተሰብ ይሁኑ!!
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ ( Ethio Beteseb Media)
El canal ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ ( Ethio Beteseb Media) (@ethiobeteseb) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 12 323 suscriptores, ocupando la posición 7 286 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 732 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 12 323 suscriptores.
Según los últimos datos del 01 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -180, y en las últimas 24 horas de -2, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 30.38%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 12.14% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 746 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 497 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 42.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ይህ ቻናል መንፈሳዊ መልክቶች ፣ ማኅበራዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ጠቃሚ መረጃዎች የሚተላለፉበት ነውና ቤተሰብ ይሁኑ!!”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 02 agosto | +1 | |||
| 01 agosto | 0 |
| 2 | 📝የፍቅር እጃችንን እንዘርጋ — ለታመመችው እህታችን የተስፋ ብርሃን እንሁን
🙏የተከበራችሁ ቤተሰቦች ፣
👉አንዲት እህታችን በከባድ ሕመም ምክንያት በአልጋ ላይ ያለች እህታችን ፣ ወንድሟ ጣሰው ትሑት፣ ቅንና ታማኝ አገልጋይ የሆነው ወንድሟ በፍቅር ከጎኗ ቆሞ እያስታመማት ይገኛል።
👉እርሱም በዚህ በDMV አካባቢ በአብያተክርስቲያኑ እየሄደ በቅንነት የሚያገለግል፣ ትጉህ መልካም ወንድም ነው።
👉ዛሬ ግን የእኛን ጸሎት፣ ፍቅርና ድጋፍ ይፈልጋል። በዚህ ከባድ ወቅት የሕክምናና የተያያዙ ወጪዎችን ለማገዝ GoFundMe ተከፍቷል።
“ለችግረኛው የሚራራ ለእግዚአብሔር ያበድራል።” — ምሳሌ 19፥17
👉በገንዘብ መርዳት የምትችሉ በቻላችሁት መጠን እንድትረዱ፣ መርዳት የማትችሉም በጸሎትና ሊንኩን በማጋራት ከጎናቸው እንድትቆሙ በትሕትና እንጠይቃለን። ትንሽ የምንለው ስጦታ ተሰብስቦ ትልቅ ተስፋ ሊሆን ይችላል።
👉እግዚአብሔር የታመመችውን እህታችንን በምሕረቱ ይጎብኛት፣ ፈውስንም ይስጣት። ወንድሟንና መላውን ቤተሰብ በኃይሉ ያጽናናቸው። የምትረዱትንም ሁሉ መቶ እጥፍ ይክፈላችሁ።
ለመርዳት እባክዎ ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ፦
🔗 https://gofund.me/5c48bec8e
🙏 እባክዎ ይርዱ፣ ይጸልዩ፣ ለሌሎችም ያጋሩ። | 2 144 |
| 3 | Sin texto... | 1 957 |
| 4 | 📝የገዳማውያኑ ጥቃት ሥርዓታዊና ጥላቻን ያዘለው ስልት ቀጣይ ምዕራፍ ነው!
©በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ የአቋም መግለጫ
👉ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ረፋድ 4:00 ላይ በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ቦረና ወረዳ የሚገኘው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም ላይ የድሮን ጥቃት ተፈጽሞ 2(ኹለት) መነኮሳይያት እናቶች ወዲያው ሲገደሉ፣ 14(አሥራ አራቱ) እናቶች ደግሞ ክፉኛ ቆስለው መካነ ሰላምና ደሴ ሆስፒታል ተወስደዋል። በጥላቻና ኾነ ተብሎ በሚመስል መልኩ በተፈጸመው ጥቃት የገዳማውያኑ የዓመት ቀለብ እህልና ጥራጥሬ ሙሉ በሙሉ የወደመ ሲኾን፣ ተግባር ቤት፣ ማብሰያ እቃዎች፣ የውሐ ማጠራቀሚያ የኮንክሪት ታንከር፣ የውሐ ማስተላለፊያ ቱቦዎች ሙሉ በሙሉ ወድማል። "በገዳሙ ሥርዓት የጠዋት 3:00 ፀሎት አድርሰን ኹሉም ወደተመደበበት ሥራ ሲሠማራ ድሮን የምትባለው ስትዞርና ድምጿን ሰምተናል፣ አይተናታል። እኛ ገዳማውያን ነን መቸም ቴክኖሎጂ ነው ያዩናል ምንም የሚያጠራጥርና የሚያስፈራን ነገር የለም ብለን ሥራችንን ቀጠልን" የሚሉት እማኝ "ነገር ግን እኛ እንዳስብነው አልነበረም ቆይተው ለሥራ በተሰበሰብንበት መዓት አወረዱብን፣ ያን የመሰለ ጭካኔ ለምን ማድረግ እንዳስፈለጋቸው ማሰብም ማለምም ይከብዳል። በተለይ የቆሰሉት ሲታዩ የሞቱት ይሻላል ያስብላል" ይላሉ።
👉ገዳሙ እጅግ ከባድ በረሃ ላይ ያለ ነው። በዙሪያው የሚገኝ ታጣቂም ይኹን ወታደር አናውቅም። እንግዲኽ ገዳሙ የቆመውም በእነዚኹ ወጣት መነኮሳይያት እናቶችች ድካም ነበር። ሠሪው ከተገደለ፣ አካሉ ከጎደለና የዓመት ቀለቡ ከወደመ ቀሪውንም የመግደል ያኽል ነው። ተጠንቶ የተደረገ ይመስላል ይላሉ ሌላው እማኝ።
👉እናት ፓርቲ ይኽ እብሪት የተላበሰ ድርጊት ከድግግሞሹ፣ እያስከተለ ከሚገኘው ጉዳትና በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ በታጣቂዎች ሽፋን በእምነቱ ተከታዮች፣ አገልጋዮችና ገዳማት ላይ እየተፈጸመ ያለው ጥቃት ተራ ስህተት ሳይኾን ሥርዓታዊና ከጥላቻ የመነጨ ብሎም የአጥፍቶ መጥፋት ተግባር እንደኾነ በጽኑ ያምናል፤ ድርጊቱንም በጽኑ ያወግዛል። ለሞቱት ገዳማውያንም ሐዘኑን እንገልጻለን።
ስለኾነም፣
1. መላው ኢትዮጵያውያን ይኽን የአጥፍቶ ጠፊ የሽብር ድርጊት በአንድነት እንዲያወግዝ እንጠይቃለን።
2. መንግሥት ለድርጊቱ ሙሉ ኃላፊነቱን እንዲወስድና ድርጊቱ ሲፈጸም የሚያሳይ የፎቶና የቪዲዮ መረጃ ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
3. ሀገርን ከጥቃት ለመጠበቅ የተቋቋሙ ተቋሟት ሕዝብን ጅምላ ጨረሽ ወደመኾን መሸጋገራቸው መላው ሕዝባችንና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲያውቀው እና አጥፊው አካል ተጠያቂ እንዲደረግ አጥብቀን እናሳስባለን፡፡
4. መላው ኢትዮጵያውያን በዚያ ሐሩር ለሀገርና ሕዝብ የሚፀልዩ ገዳማውያን ቀለባቸው እና የመጠጥ ውሐ በጥቃቱ ሙሉ በሙሉ በመውደሙ ቀሪዎቹ በረሃብና ጥም ከማለቃቸው በፊት እንዲደርስላቸው እንጠይቃለን።
ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝባን ይጠብቅ!
©እናት ፓርቲ
ሐምሌ ፲፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
📍 ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ | 3 380 |
| 5 | 📝ሣንባውን ለተሰረቀው ... ሚዲያ !
👉መነኮሳት ተገድለው ፣ ገዳም በመሳሪያ ተደብድቦ፣ ዘገባው ጳጳስ... እከሌ ከባድ አቀባበል ተደረገላቸው ? ፣ ሪባን ቆረጡ ፣ ሕንፃ መረቁ? ፣ ሐዋርያዊ ጉዞ አደረጉ? በነገረችን ላይ ሐዋርያዊ ጉዞ ምንድን ነው ? መልሱን በኮሜንት ላይ ይፃፉ!
👉የሞቱት መነኮሳት ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስን አይወክሉም ፣ አደጋ የደረሰበትን ገዳም ቤተክህነቱ በመዝገብ አያውቀውም ?
👉መተንፈሻ ሣንባው ለተሰረቀው የቤተክርስቲያን ሚዲያ EOTC የቀረበ ምክረ ሀሳብ እና ተግሳጽ ©በአማን ነጸረ https://www.facebook.com/share/1C3qodYpQc/
📍 ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ | 2 719 |
| 6 | በእውነት ልብ ይሰብሯል | 3 174 |
| 7 | 📝ልብን ይሰብሯል ያየነው
👉ዓለም በቃን ብለው መልካሙን የሕይወት ጎዳና መርጠው ከሚታየውም እና ከሚሰማውም እራሳቸውን አርቀው በመነኑ መነኮሳይት ላይ የደረሰው የግፍ ግድያና ጭፈጨፋ ለሰማውም ላየውም ልብ ይሰብሯል ፣
👉በዚህ ዘመነ መንግስት በርካታ የግፍ እና የጭካኔ ተግባሮች ተከናውነዋል ፣ ይኽኛው ግን ይለያል ፣የበቁ መናንያን ፣ በጸሎት የሚተጉ አበው ወእማት ፣ ምስባከ ቅዱሳን የሆነ ለዐይን የሚማርክ ፣ ለሕሊና ረፍትን በሚሰጥ ቅዱስ ቦታ ራሳቸውን በገዳም ሰውረው በምናኔ ሕይወት ውስጥ የሚኖሩ መነኮሳት በዚህ መጠን ሲገደሉ ፣ ይህ የመጀመሪያው ባይሆንም ፣ የኦርቶዶክሳውያን ደም ለሁሉ ነገር መስዋዕት አለበት የተባለ ይመስል በተደጋጋሚ እንዲህ ዐይነቱ የግፍ በኦርቶዶክሳውያን ላይ መፈጸሙ ልብ ሰባሪ ነው ።
👉 ዛሬ ፍትሕ የሚጠይቅ የኦርቶዶክሳውያን አባት መሪ ይህ ለምን ይሆናል ብሎ የሚሞግት ማን ነው? ጉዳዩን ለዓለም ለማሳወቅ የሚጥር የሃይማኖት መሪ የለም? አሁን በሩ ተከፍቷል ፣ ምንም ይፈጠር ምንም የእኛዎቹ ዝምታን መርጠዋል ።
👉ዛሬ ያሉት ዓላማቸው አንድ እና አንድ ገንዘብ ነው ። ሀሳባቸው ሥልጣን ላይ እንዴት መቆየት አለብን ነው !! ለእነዚህ መነኮሳይት ማዘን አበል የለውም !! አዝነናል ብለው ለቅሶ ለመድረስ ቢያስቡም አበል የሚከፍላቸው የለም !! መግለጫ ቢያወጡም መንግስታችን ያዝንብናል ነው ነገሩ !!
👉ስለዚህ ዛሬ ያሉ የሃይማኖት መሪዎቻችን እንዲህ ዓይትነቱ ልብ ሰባሪ ሀዘን አያስጨንቃቸውም ፣ እነሱ ዛሬ ሕንፃ ሥላሴ ይፈርሳል ፣ ሕንፃ ቤተክርስቲያን ታደሰ ብለው በመንግስት በመደበላቸው ካድሬ በከፍተኛ አቀባበል ታጅበው በመብላት በመጠጣት ላይ ናቸው ። ግን ይህም ቀን ያልፋል ...
👉 የቤተክርስቲያኑም ሚዲያ EOTC https://www.facebook.com/share/1DK2DpSBBd የእነሱን ኮቴ እየተከተለ እዚህ ደርሰዋል ፣ እንዲህ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል እያለ የተዋበ ፎቶ እያነሳ ይለጥፋል ፣ ግን እኛ ያልገባን የሞቱት ግን ኦርቶዶክሳውያን አይደሉም ፣ አደጋ የደረሰበት ገዳም ቤተክህነቱ አያውቀውም ? እረ ወገን ምን አይነት ዘመን ላይ ነው የደረስነው ፣
👉የሞቱት ሰማዕታት በረከታቸው ይደርብን🙏 ይህንን መልእክት ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ፣ ላይክ በማድረግ አድርሱ
📍 ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ
| 3 261 |
| 8 | 📝በቁልቢ ገብርኤል ስም ..$$.. ምዝበሯ
👉በቁልቢ ገብርኤል ስም የተበላው ሚሊዮን ገንዘብ ቀላል አይደለም ፣ የሕዝብ ንብረት ነው። መላው የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሆነ መንግሥት በትኩረት ሊያዩት ፣ ምርመራም ሊደረግበት ይገባል ።
👉በሁለት ፣ በሦት ወር የቀለም ቅብ እድሳት ፣ የጉልሏቱን እና የተሰነጠቀውን ዕድሳት ፣ ውጭውን (Waterproof painting) ለማድረግ ፣ ያለ ሕጋዊ ጨረታ በጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጁ እና በቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ መሪነት ጥቂት በሚሆኑ የውስጥ ተባባሪዎች ከ170 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደረግ እና ታደሰ ብለው ነገ ተመረቀ ሊሉን ነው ።
👉ይህ ዕድሳት መደረጉ አስፈላጊ ነው ፣ ቀደም ሲል በብፁ አብነ አብርሃም ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዘመን
አንድ ዓመት አልሞላውን የታላቁ የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም እንዲታደስ ፣ በደብሩ አባት ያላሰለሰ ጥያቄ ቀርቦ ፣ ብፁዕነታቸውም በባለሞያ አስጠንጠው ፣ በጠቅላይ ቤተክህነቱ የቴክኒክ ኮሚቴ አስመርምረው ለዕድሳቱ የቀረበው ዋጋ 59 ሚሊዮን ብር አካባቢ ነበር ፣ ዓመት ባልሞላው ጊዜ ጥናቱ ተሰርዞ ፣ የተመረጠውን የቴክኒክ ኮሚቴ አፍርሶ በማን አለብኝነት ፣ በርካታ ሚሊዮኖችን መዝብሮ እንዲመዘበር ማድረግ ፣ አሳፋሪ ነው ።
👉ይህ ሳያንስ ነገ ሊመረቅ ነው በሚል ሰበብ ለአበል እና ለድግስ በረካታ ሚሊዮን ብር እንደተመደበ የውስጥ የመረጃ ምንጮቻችን ፣ አድርሰውናል ይህ ደግሞ እኛም ከምናውቀው በድግስ ሰበብ ምን እንደሚሰራ ጠንቅቀን እናውቃለን ።
👉ጥያቄው ዛሬ በዚህ ምርቃት ላይ የምትገኙ ጳጳሳት ፣ የተሰራው ሥራ ከ170 ሚሊዮን ብር በላይ ይወስዳል ወይ? የሕዝብ እና የሀገር ንብረት በዚህ ልክ ሲመዘበር ፣ ዝም ብሎ ማየት ኅሊና ላለው ስው ባድ ነው ።
👉ከዚህ በፊት ለግንቦቱ ርክበ ካህናት ሲኖዶስ ተመረቀ የተባለው ሕንፃ ፣ ሙሉ ሕንፃው በባንድሪ አሸብርቆ ያየነው ዛሬ ሕንፃው አገልግሎት ይሰጣል ወይ ? እባካችሁ ብፁዓን አባቶች ሰው ባያየን እግዚአብሔር ያየናል በሉ❗ ይህው ሕንፃው ተመረቀ የተባለው ወፍ የለም ቦዶ ኦናው ሥራው ሳያልቅ ለታይታ ድራማ ተሰራበት አሁን ቆማል ፣
👉በዚህ በሕንፃ የግንባታ ሥራ ቢሊዮን ገንዘቦች እየተመዘበሩ ነው ፣ እያንዳንዱን በመረጃ እና ፣ የተቋራጩን ስም እና አሸነፈ የተባለውን የቢሊዮን እና የሚሊዮን ቁማሮች በቅርቡ ይፋ እናደርጋለን ። ጥያቄው ግን ቅዱስ ሲኖዶሱም ሆነ መንግስት እየተዘረፈ ያለውን የሕዝብ እና የሀገር ንብረት ምርመራ እንዲደረግ እንጠይቃለን ።
👉የዛሬው የቁልቢ ገብርኤል ገዳምን ነው የምናየው ፣ ቁልቢ ታቦቱ ሰሚ ነው ፣ አማኙ ስለት ተስሎ ፣በእግሩ ሳይቀር ከመላው ዓለም ደጁን ይረግጣል ፣ ቦታው የፈውስ ቦታ ነው ፣ ብዙዎቻችንን ያሳደገ ፣ ደገኛ መልአክ ነው ፣ በዚህ ቦታ በርካታ ታአምራቶች ተክናውነዋል ፣ ከቤተመቅደሱ እስከ አፍአ ድረስ ሌቦችን ሳይቀር ሲቀጡ እና በቁማቸው ተዋርደው ያለፉም አሉ ፣ የቁልቢው ቅዱስ ገብርኤል ልዩ ነው ፣ ንግሱ የደመቀ ፣ ታሪካዉ እና ጥንታዊ ቦታ ነው ።
👉ለኦሮምያ ቤተክህነት መመስረት እና ለጨረቃ ጳጳሳት ሹመት ዋንኛ ጥያቄ ሆኖ በወቅቱ የቀረበው ፣" በኦሮሚያ የሚገኘው የቅዱስ ገብርኤል ገዳም ገቢ ውስጥ በኦሮሚያ የሚገኙ አብያተክርስትያናት ተጠቃሚ አይደሉም " የሚል ነበር ፣ ዛሬስ ተጠቃሚው ማን ነው ? ግለሰቦች ወይስ ተቋሙ?
👉ቁልቢ ደብረ ኃይል ገዳም ከዋናው መስራባት ተመድቦ የሄደ ፣በወር የማያገኘውን አበል ይዞ ይመጣል አይደለም አሁን ያኔ ፣ ዛሬ ደግሞ የልማት አርበኛ ተብለው በቀጠሯቸው ሚዲያ እና አጫፋሪዎች ከ170 ሚሊዮን ብር የወጪ የተደረገበትን የቀለም ቅብ በሁለት ሦስት ወር ገደብ ተጠናቋ አለቀ የተባለው ሕንፃ ዕድሳት ሥራ ለመመረቅ የሚጋበዙ ልዑካን ስንት አበል ይከፈላቸዋል? ፣ ወገኔ አሁን መዝናናት ነው ፣ መብላት መጠጣት ነው።
👉 በዓሉ ቅዳሜ ለእሁድ ነው ሠርግ እና ምላሹ ከአዲስ አበባ ድሬደዋ የሚቀበል አለ ፣ ጉዞው በአውሮፕላን ነው ፣ ጨዋታው በሚሊዮኖች እና በመቶ ሺዎች ነው ፣ ጥያቄአችን ሲኖዶሱ ብሎም መንግስት እጁን ያስገባ፣ ምርመራ ይደረግ ፣ አሁንም ነገም ድምፃችን❗ ሌላውም ... ይቀጥላል.....?
📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ
| 3 135 |
| 9 | Sin texto... | 3 264 |
| 10 | 📝ምን እንማር ...❗
👉ያከበረህ ሕዝብ እንዳከበርህ እንዲቀጥል 💤 አክብረው ❗ አልያ ግን..... መውደቂያህን ታፋጥነዋለህ ፦
👉ኮሜዲያ እሸቱ ፣ ካለፈው ስህተቱ ዛሬ ብዙ የተማረ ይመስለናል ፣ ሌሎቻችንም ከዚህ መማር አለብን ፣
👉" ነጋዴ ሁሌ ደንበኛ ንጉስ ነው ይላል " ይህ አባባል ሳይሆን ሀቅ ነው ፣ በዝሕዝብ የበለጸገ መነሻውን መርሳት የለበትም ፣ ስህተት እንኳን ቢሰራ ላከበረው ሕዝን ሲል በፍጥነት ነገሮች ሳይሰፋፉ ይቅርታን ገንዘብ ማድረግ አለበት ። አሁንም መጀመሪያ ያከበረህን ሕዝብ ድረሱልኝ ብለሀል ፦ ፈጣሪ ይርዳህ🙏
📍 ኢትዮ ቤተሰብ ሚዱያ | 4 248 |
| 11 | 🙏Message to parents
👉Today, we celebrate more than the completion of a course we celebrate growth in faith and identity.
👉Over the past four weeks, our students discovered who they are:
✨ Created in the image of God.
✝️ Followers of Jesus Christ.
⛪ Faithful members of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church.
🎓 Students called to honor God through wisdom, character, and excellence.
👉May the lessons learned continue to guide their hearts, strengthen their faith and inspire them to live with purpose wherever God leads them.
🙏🙏🙏 Congratulations to all our graduates! May God bless your journey and help you shine as the light of Christ in your homes, schools, churches, and communities.
"For we are His workmanship, created in Christ Jesus for good works." – Ephesians 2:10 | 4 002 |
| 12 | https://youtu.be/dV7WTxvTvuw?is=UYwYTc1rzt4P3RBT | 3 803 |
| 13 | 📝እጅግ ልብ ይሰብራል
👉የተሰማንን የጠለቀ ሀዘን እየገለጽን ፣ በሚኒሶታ የደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተከርስቲያን በደረሰው ቃጠሎ ፣ በግልጽ ምክንያቱ ባይታወቅም ፣ የደረሰው ቃጠሎ ግን ልብ ይሰብሯል ፣ የደብሩን ካህናት ምእመናን ሁላችንም ልናጽናና ይገባል ፣
👉ሌሎችም በውጭ የምንገኝ አብያተክርስቲያናት ከዚህ ምን እንማራለን ፣ ጥንቃቄ ማድረጉ ሚዛን የደፋ ምርጫ ነው ?
📍ኢትዮ ቤተሰብ ሚዲያ | 4 954 |
| 14 | https://www.youtube.com/live/IfnwCJyx2cg?is=roy6yRlO0GJGHUL5 | 4 396 |
| 15 | Sin texto... | 4 898 |
| 16 | https://youtu.be/XnNgP6QSDhI?is=k5gJMNrxPaayRhac | 5 452 |
| 17 | https://youtube.com/shorts/QDNEnXu0Gss?is=n812ElwRLnYQuX-c | 5 066 |
| 18 | https://youtu.be/2lM3iRTHbK8?is=EldC63kTkfSq4XAV | 3 727 |
| 19 | ✏ታላቅ በዓለ ንግሥ ፦ የፊታችን ቅዳሜ
♣የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዓመታዊ ክብረ በዓል
♣ ቅዳሜ ሐምሌ 4 ቀን 2018ዓ.ም
Saturday , July 11 ,2026
ማኅሌቱ ዓርብ ከሌሊቱ 12AM ጀምሮ ይጀመራል
♣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ መምህራነ ወንጌል ፣ ዘማርያን እና የአድባራቱ የሰንበት ት/ቤት ወጣት መዘምራን ፣ ምዕመናን እና ምዕመናት በሚገኙበት የጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዓዐለ ንግሥ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ይከበራልና ኑ የበረከቱ ተካፋይ ሁኑ🙏
📍አድራሻው ፦ በመካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ቨርጅኒያ
6935 Columbia Pike, Annandale ,VA 22003 | 3 812 |
| 20 | https://youtu.be/HIW4_lqpYTA?is=cdJmXd1-TVaPhzym
የጳጳሱን ቅሌት መጋለጥ የጀመርነዉ ዛሬ አይደለም ሰሚ ጠፍቶ እነጂ ይደመጥ | 3 477 |
