es
Feedback
ምስባከ ጳውሎስ (Paul's Pulpit)

ምስባከ ጳውሎስ (Paul's Pulpit)

Ir al canal en Telegram

ይህ የጳውሎስ ፈቃዱ አገልግሎት ሲሆን፣ አብያተ ክርስቲያናትና ክርስቲያኖች በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ዕውቀት እንዲጎለብቱ መትጋትን በዓላማነት አንግቧል። youtube.com/PaulosFekadu fb.com/PaulsPulpit/

Mostrar más
7 686
Suscriptores
+724 horas
+207 días
+10330 días

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
septiembre '26
septiembre '26
+46
en 0 canales
agosto '26
+187
en 2 canales
Get PRO
julio '26
+171
en 2 canales
Get PRO
junio '26
+241
en 4 canales
Get PRO
mayo '26
+245
en 0 canales
Get PRO
abril '26
+339
en 9 canales
Get PRO
marzo '26
+193
en 4 canales
Get PRO
febrero '26
+209
en 1 canales
Get PRO
enero '26
+235
en 1 canales
Get PRO
diciembre '25
+224
en 3 canales
Get PRO
noviembre '25
+133
en 2 canales
Get PRO
octubre '25
+127
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+197
en 4 canales
Get PRO
agosto '25
+150
en 2 canales
Get PRO
julio '25
+129
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+155
en 2 canales
Get PRO
mayo '25
+215
en 3 canales
Get PRO
abril '25
+209
en 4 canales
Get PRO
marzo '25
+332
en 1 canales
Get PRO
febrero '25
+162
en 3 canales
Get PRO
enero '25
+331
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+288
en 1 canales
Get PRO
noviembre '24
+285
en 2 canales
Get PRO
octubre '24
+168
en 1 canales
Get PRO
septiembre '24
+121
en 2 canales
Get PRO
agosto '24
+120
en 2 canales
Get PRO
julio '24
+59
en 3 canales
Get PRO
junio '24
+67
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+53
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+44
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+138
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+273
en 1 canales
Get PRO
enero '24
+162
en 1 canales
Get PRO
diciembre '23
+80
en 1 canales
Get PRO
noviembre '23
+114
en 1 canales
Get PRO
octubre '23
+162
en 0 canales
Get PRO
septiembre '23
+73
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+87
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+85
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+94
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+124
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+133
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+133
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+316
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+106
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+214
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+326
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+853
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+38
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+44
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+28
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+31
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+35
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+43
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+34
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+20
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+34
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+30
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+20
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+32
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+19
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+7
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+26
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+14
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+285
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
08 septiembre+8
07 septiembre+9
06 septiembre+7
05 septiembre+5
04 septiembre+4
03 septiembre+3
02 septiembre+7
01 septiembre+3
Publicaciones del Canal
2
https://youtu.be/x3wdoIrFDIs?si=wekTV2b-MrE_P70M
1
3
https://youtu.be/x3wdoIrFDIs?si=PCDVfodjrETkdvGh
1 062
4
https://www.tiktok.com/@hanaadamu1/video/7680275379000495382?_d=eik60bclh4d1ek&_r=1&preview_pb=0&share_item_id=7680275379000495382&sharer_language=en&source=h5_m&u_code=eik5m59hg6gkh1
1
5
https://www.tiktok.com/@hanaadamu1/video/7680275379000495382?_r=1&u_code=eik5m59hg6gkh1&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=eik60bclh4d1ek&share_item_id=7680275379000495382&source=h5_m
2 139
6
Christological anthropology እያሽኮረመመኝ አለሁ ...
3 906
7
ሳጥናኤል የወደቀው መቼ ነው? ስለ ሳጥናኤል አወዳደቅ ሲነሣ፣ ኢሳይያስ 14 እና ሕዝቅኤል 28 በአብዛኛው በማስረጃነት ይጠቀሳሉ። እነዚህ ክፍሎች እንደ ቅደም ተከተላቸው ስለ “የባቢሎን ንጉሥ” እና “የጢሮስ ንጉሥ” እንጂ በቀጥታ የሚናገሩ ናቸው። ነገር ግን ከጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ጀምሮ ምንባቦቹ በአመስጥሮታዊ ትርጓሜ (allegorical interpretation) እየተወሰዱ ስለ ሰይጣን የሚናገሩ ተደርገው ይቀርባሉ። የዛሬው አሳባችን ከእነዚህ ምንባቦች ጋራ ግጭት የለውም፤ ከምንባቦቹ የምናገኘው እገዛም የለም። 1) ሳጥናኤል ከዘፍጥረት 1፥1 በፊት ወድቆ ይሆን? የዚህ ጥያቄ ምላሽ ከባድ አይደለም። ቀድሞ ነገር ሳጥናኤል በዚያን ወቅት ተፈጥሮ ነበርን? የሚለው ጥያቄ ለዚህ ምላሽ ይሰጠናልና። ከመፈጠሩ በፊት አይወድቅምና። በርግጥ መጽሐፍ ቅዱስ መንፈሳውያን ፍጥረታት መቼ እንደ ተፈጠሩ በግልጽ አይነግረንም። ነገር ግን “በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማያትንና ምድርን ፈጠረ” (አመት) በማለት የሚጀምር መጽሐፍ ቅዱስ ይዘን፣ እግዚአብሔር መላእክቱን “በመጀመሪያ” ከተባለው ጊዜ በፊት እንደ ፈጠረ ማመን የምንችል አይመስለኝም። “በመጀመሪያ” የሚለው በዚህ ስፍራ ያለው ቃል፣ ጊዜ (time) እንኳ የተፈጠረ መሆኑን የሚያስገነዝበን ነው።) እግዚአብሔር በመጀመሪያ የፈጠረው ሰማያትን ነው። የመንፈሳውያኑ ፍጥረታት መኖሪያም ሰማይ በመሆኑ እግዚአብሔር መኖሪያቸውን አስቀድሞ አዘጋጅቶ ይሆናል። ስለዚህ እግዚአብሔር ሰማያትን በሚፈጥርበት ጊዜ፣ መላእክትንም አብሮ እንደ ፈጠረ ብናስብ የተሻለ ነው። ከዚያም ምድርን በሚፈጥርበት ጊዜ መላእክት እያዩ በእልልታ ስለ ማምለካቸው በኢዮብ 38፥4-7 የተነገረው ከዚህ ጋራ መጣጣም ይችላል። 2) ሳጥናኤል የወደቀው በዘፍጥረት ምዕራፍ 1፥1-2 መካከል ይሆን? በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የታተመው “የስኮፊልድ” መጽሐፍ ቅዱስ በስፋት ያስተዋወቀውና ሥር የሰደደ አንድ አሳብ አለ። ይህም አሳብ “gap theory” ተብሎ የሚታወቅ ሲሆን፣ ይኸውም በዘፍጥረት 1፥1 እና 1፥2 መካከል ሰይጣን መውደቁን የሚናገር ነው። ለዚህ መነሻ የተደረገው፣ “ምድርም ባዶ ነበረች፥ አንዳችም አልነበረባትም፤ ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ” ወይም “ምድርም ቅርጽ የለሽና ባዶ ነበረች። የምድርን ጥልቅ ስፍራ ሁሉ ጨለማ ውጦት ነበር” (አመት) መባሉ ነው። በዚህ መላምት መሠረት ከሆነ፣ እግዚአብሔር በመጀመሪያ ሰማይንና ምድርን ሲፈጥር ሁሉ ነገር የተሟላ ነበር። ከዚያ ግን ሳጥናኤል ከሰማይ ሲጣል ምድር ቅርጿ እንደ ተበላሽ ጨለማም በሁሉ ነገር ላይ ተንሰራፋ። ይህ ግን ከምንባቡ አሳብ ጋራ ጨርሶ የማይገናኝ ነው። ምድር “ቅርጽ የሌላት (form less)” እንጂ ቅርጿ የተበላሸ (deformed) እንደ ነበረች እንዳልተጻፈ ልብ ይሏል። በዚህም ላይ “ነበረች” እንጂ “ሆነች” እንዳልተባለችም ግልጽ ነው። የክፍለ ምንባቡ ሰዋስዋዊ መዋቅር በአግባቡ ከተወሰደም ወደዚህ ትርጓሜ አያደርስም። ይህ ዐይነቱ የትርጓሜ አሳብ በአይሁድ ሊቃውንትም ሆነ በቤተ ክርስቲያን አባቶች እንዲሁም በዘመናውያን ሊቃውንት ተቀባይነት የሌለው ለዚህ ነው። አዲስ ኪዳናዊ መነጽራችንን አጥልቀን ስንመለከተው ደግሞ፣ ሳጥናኤል የፍጥረቱ ሁሉ ገዥ ተደርጎ ተሹሞ ነበርን? አለዚያማ እርሱ ሲጣል መላለሙ የሚበለሻሽበት ምክንያት ምንድን ነው? በማለት ጥያቄ እናቀርባለን። 3) ሳጥናኤል በዘፍጥረት 1 ውስጥ ወድቆ ይሆን? እንደ እኔ እንደ እኔ፣ ሳጥናኤል በዘፍጥረት 1 ውስጥ ወድቋል ለማለት የሚያስችል መሠረት የለምም። ዘፍጥረት 1 እግዚአብሔር መላለሙን ስለ ፈጠረበት ሁኔታ ሲያስረዳ፣ የየዕለቱን ክሥተት የሚያጠቃልልበት አገላለጽ አለው፤ “እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ” የሚል። ስድስቱ ቀናት ሲጠናቀቁ ደግሞ፣ “እግዚአብሔርም ያደረገውን ሁሉ አየ፥ እነሆም እጅግ መልካም ነበረ” በማለት ያጠቃልለዋል። ዕለታዊ ዝርዝሩን “መልካም” በማለት ጀምሮ “እጅግ መልካም” በማለት ይደመድማል። በዚህ መልኩ መልካም ሁኔታ የሚዘረዝር ምዕራፍ የሳጥናኤልን የውድቀት ታሪክ ይዟል ማለት እጅግ አስቸጋሪ ነው። የሳጥናኤል በኀጢአት መውደቅ መልካም ተደርጎ ካልተወሰደ በቀር! አለዚያ ግን ሳጥናኤል የወደቀው በዘፍጥረት 1 ላይ ሊሆን አይችልም። እግዚአብሔር መልካም ፍጥረታትን በሚፈጥርበት ሂደት ውስጥ ሳጥናኤል በኀጢአት እየወደቀ፣ ሁኔታውም ሆነ ፍጥረት “እጅግ መልካም ነበረ” በማለት ማጠቃለል አይቻልም። በመሆኑም ሳጥናኤል የወደቀው በዘፍጥረት ምዕራፍ 1 ላይ ሊሆን አይችልም። ታዲይ ሰይጣን የወደቀው መቼ ነው? ከላይ የጠቀስነውን ትንታኔ ከተቀበልን፣ ሳጥናኤል የወደቀው ከዘፍጥረት 1 በኋላ እንዲሁም ከአዳምና ሔዋን መውደቅ በፊት ነው። (ሰይጣን ከመውደቁ በፊት ንጹሕ ነበር አይደል? ለዚህ አጽንኦት ለመስጠት ስል፣ ጥሩ ትርጓሜ ያለውን “ሳጥናኤል” የሚል ስያሜ ተጠቅሜያለሁ።)https://www.facebook.com/PaulsPulpit/posts/pfbid0z41nd9AnvBzhiu3H7YR1obcqB5fd6ZWkEXuWuc61DPCHdu6nSPaigCE7zJrug8GDl
5 336
8
ለፍተሻ .... ሰይጣን የወደቀው ዘፍጥረት 3 ላይ ቢሆንስ? ማለትም፣ ቀዳሚ ኀጢአቱ አዳምንና ሔዋንን ማሳቱ ቢሆንስ? ሌሎቹ መላእክት የወደቁት ደግሞ በኋላ ቢሆንስ? https://www.facebook.com/share/p/1JUY6KchVs/
4 858
9
የወደድሁትና የተማርሁበት ውይይት። https://youtu.be/g0Jzf0Ijs-I?is=vmC1FaHw2-s65BvH
5 817
10
ይገዛል
1
11
የአዲስ ኪዳን ምሁር በሆነችው ስፋኒት ታመነ (ዶ/ር) የተቋቋመ የነገረ መለኮት በኣንላየን መቶ በመቶ ትምህርቱ በኣንላየን ነው። በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ!
የአዲስ ኪዳን ምሁር በሆነችው ስፋኒት ታመነ (ዶ/ር) የተቋቋመ የነገረ መለኮት በኣንላየን መቶ በመቶ ትምህርቱ በኣንላየን ነው። በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ!
5 655
12
ካለፈው የቀጠለ ጌታ ኢየሱስ እንዴት የአዳም ኀጢአት ሳይተላለፍበት ቀረ? ጌታ ኢየሱስ ከእናቱ ከቅድስት ማርያም የሰውነትን ባሕርይ ተካፍሏል፤ የቱም ልጅ ከእናቱ የሚወስደውን ሁሉ እርሱም ከእናቱ ወስዷል። ከሰዎች ጋራ ሥጋና ደምን ተካፍሏል፤ በእናቱ በኩል ተዛምዶናል። ስለዚህም በሰውነቱ ከሰውነት ባሕርይ አንዳችም ያልጎደለው ምሉእ ሰው ነው። (ከመለኮትነት አንዳችም ያልጎደለው ምሉእ አምላክ መሆኑ እንደ ተጠበቀ ሆኖ።) በበርካታ ጥንታውያን ጽሑፎች ውስጥ ከድንግል ማርያም ሥጋና ነፍስ መንሣቱ የተጠቀሰው ይህንኑ ለማለት ነው። ከሥጋዋ ሥጋ ብቻ ሳይሆን፣ ከነፍሷ ነፍስ መንሣቱ የሚነገርበትን ዐውድ እዚህ ላይ ማንሣቱ ጠቃሚ ነው። የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን ከተጋፈጠቻቸው ኑፋቄዎች መካከል አንዱ አቡሊናርዮሳስ (Applonarius) የተባለ ሰው ሲያቀነቅነው የነበረና ጌታ ኢየሱስ መለኮታዊ ነፍስ/መንፈስ እንጂ የሰው ነፍስ/መንፈስ እንደሌለው የሚናገር ነው። እንደ አቡሊናርዮሳዊንት ከሆነ፣ ጌታ አየሱስ የሰው hardware እና የአምላክ software ነው ያለው። የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን፣ ጌታ ኢየሱስ በእናቱ በኩል የሰዎችን ሥጋና ደም ብቻ ሳይሆን ሁለንተናም መውሰዱን ለማስረገጥ ስትል፣ ሥጋና ነፍስ መንሣቱን ደጋግማ ታትት ነበር። ጌታ ኢየሱስ ከእናቱ ከማርያም ሥጋንና ነፍስን ነሥቷል የሚለውን አሳብ በቅጡ መረዳት ግን ያስፈልጋል። የቱም ፅንስ የእናቱን ሥጋም ሆነ ነፍስ ቆርሶ ይወስዳል ማለት አይደለም። የጌታ ኢየሱስም ጉዳይ ከዚህ ጋር ተመሳሳይ ነው። የቱም ሕፃን ከእናቱ የሚወስደውን ሁሉ እርሱም ከእናቱ ወስዷል። ከዚህም የተነሣ፣ በገጽታው ወይም በመልኩ ማንን ይመስላል? ቢባል፣ እናቱንን ወይም የእናቱን ዘመዶች ይመስላል ቢባል ስህተት አይደለም። ጌታ ኢየሱስ በገጽታው የዛሬ 2ሺህ ዓመት በይሁዳና በገሊላ የሚኖሩ ሰዎችን ይመስላል ማለት ነው። ስለዚህ ነጭ ወይም ጥቁር አልነበረም። ጌታ ኢየሱስ የሰውነትን ባሕርይ ከእናቱ ከወሰደ (ወይም በሥጋና በደም ከወንድሞቹ ጋራ ከተካፈለ) ኀጢአት እንዴት ላይተላለፍበት ቻለ? መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረው፣ በአዳም ኀጢአት ምክንያት ክፋት ወደ ዓለም ገብቷል፤ ሰዎችም ሲወለዱ ጀምሮ ወደ ኀጢአት የሚያዘነብሉ ሆነዋል። ሰዎችም መዋቲዎች ናቸው፤ ማለትም የኀጢአት ውጤት የሆነውን ሞት ይዘው ነው የሚወለዱት። ከነዚህ ነገሮች የተነሣ ሰዎች ሁሉ ኀጢአትን ይሠራሉ፤ ኀጢአተኛም ይሆናሉ። የአዳም ኀጢአት ከእርሱ በኋላ የመጡትን ሰዎች ሁሉ ኀጢአት አድራጊዎች ስላደረጋቸው ሰዎች ሁሉ ኀጢአትን ያደርጋሉ። በመሆኑም በመጨረሻው ፍርድ ላይ ሁሉም በየራሱ ኀጢአት ተጠያቂ ይሆናል፤ በራሱም ኀጢአት ይፈረድበታል እንጂ በአዳም ኀጢአት ተጠያቂ የሚሆን አንድም ሰው የለም። እናም ኀጢአተኛነት ሳይሆን ኀጢአት ይወረሳል ወይም ይተላለፋል ማለት የተሻለ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አገላለጽ ነው። (በውስጡ ያለውን ዝርዝር አሳብ ለጊዜው እንዝለለው።) በዚህ አግባብ ኀጢአት ከወላጅ ወደ ልጅ የሚተላለፍ ከሆነ፣ ኢየሱስ ኀጢአት እንዴት ሳይተላለፍበት ቀረ? ምርጫ 1፤ ጌታ ኢየሱስ ከአዳም ጀምሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የነበረው ኀጢአት ያልተላለፈበት እናቱ ኀጢአት ስላልነበረባት ነው። ቅድስት ማርያም በአዳም ኀጢአት ምክንያት የተፈጠረው ምስቅልቅል አንዳችም አልተላለፈባትም፤ ከፅንሰቷ ጀምሮ። Immaculate Conception ተብሎ የሚታወቀው ይህ አስተምህሮ የካቶሊክ ቤ/ክ ይፋዊ አቋም ነው። ምርጫ 2፤ ጌታ ኢየሱስ ኀጢአት ያልተላለፈበት ያለ ወንድ ፈቃድ (ዘር) በመፀነሱ ነው። ይህ ትንታኔ፣ ኀጢአት የሚተላለፈው በወንድ አባለ ዘር በኩል መሆኑን ታሳቢ ያደርጋል። ጌታ ኢየሱስ ደግሞ በወንድና በሴት ሩካቤ ሥጋ ሳይሆን፣ በተአምር የተፀነስ የሴቲቱ ዘር በመሆኑ የአዳም ኀጢአት አልተላለፈበትም። ምርጫ 3፤ ጌታ ኢየሱስ ኀጢአት ያልተላለፈበት ከድንግል ማርያም የነሣውን (የወሰደውን) ነገር መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ ስላነፃው ነው። የምሥራቅ ኦርቶዶክሳውያን እና ኦርየንታል ኦርቶዶክሳውያን (ለምሳሌ የግብፅ እና የሶርያ አብያተ ክርስቲያናት) ከማርያም የነሣውን “ሥጋና ደም” መንፈስ ቅዱስ አስቀድሞ የቀደሰው መሆኑን ያስረዳሉ። አንዳንዶቹ እናቲቱን አስቀድሞ ከኀጢአት እንዳነጻት ሲናገሩ፣ አንዳንዶች ደግሞ ለኢየሱስ መፀነስ አስፈላጊ የሆነውን ነገር ቀድሶ እንደ ወሰደው ይናገራሉ። (በዚህ ውስጥ ያሉትን ዝርዝሮችና ልዩነቶች ለጊዜው እንተወው።) መጽሐፍ ቅዱስ በዚህ ጉዳይ ላይ ዝርዝር ነገር አያስተምርም። ቢሆንም፣ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ድንግል ማርያም ኢየሱስን እንደምትፀንስ ሲያበስራት፣ “መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፤ የልዑልም ኀይል ይጸልልሻል” በማለት የተናገረውን ልብ ማለት የሚያስፈልግ ይመስለኛል (ሉቃ. 1፥34-35)። ወንጌላዊ ሉቃስ በዚህ ስፍራ የተጠቀመው የግሪኩ ቃል “ኤፒስኪያሴ” (ἐπισκιάσει) የሚል ሲሆን፣ ሥሩ “ኤፒስኪያዞ” (ἐπισκιάζω) ነው። ይህ ቃል ሁለት ትርጕሞች አሉት። የመጀመሪያው መጋረድንና መሸፈንን ሲጠቍም፣ ይህም በተለይ ሰዎችን በብሩህ ደመና ወይም ብርሃን ዙሪያቸውን መክበብና መጠቅለልን ያሳያል። ድርጊቱ መለኮታዊ ተግባር አለው። በዚህም የእግዚአብሔርን ሀልዎት ያመለክታል። ጌታ ኢየሱስ በተራራ ላይ ለደቀ መዛሙርቱ በተገለጠላቸው ጊዜ ብሩህ ደመና እንደ ጋረዳቸው ወንጌላቱ ሲነግሩን ይህንኑ ቃል ተጠቅመዋል (ማቴ. 17፥5፤ ሉቃ. 9፥34፤ ማር. 9፥7)። ሁለተኛው ትርጕም ደግሞ በአንድ ነገር ላይ ጥላ ማሳረፍን ያሳያል። ሐዋርያው ጴጥሮስ በሚያልፍበት መንገድ ላይ ሕመምተኞችን የሚያስቀምጡ ሰዎች ነበሩ። ይህንም የሚያደርጉት የእርሱ ጥላ እንዲያርፍባቸው ሲሆን፣ ይህም የተዘገበው በዚሁ ቃል ነው (የሐዋ. 5፥15)። የማደሪያው ድንኳን የእግዚአብሔርን በዚያ ስፍራ መገኘት በሚገልጠው የክብሩ ዳመና (“ሸኺና”) መሞላቱን በሚያመለክት መልኩ የግሪክኛው ብሉይ ኪዳን (ሰብዓ ሊቃናት) ይህን ቃል በዘፀአት 40፥35 ላይ ተጠቅሞታል። የአማርኛ ትርጉሞች የተጠቀሙት “ጸለለ” የሚለው ቃል ከግዕዝ የተወሰደ ሲሆን፣ “በላይ ሁኖ ማጥላት፣ ጥላ መሆን፣ ማልበስ፣ መክደን፣ መሸፈን፣ መከለል፣ መጋረድ፣ ማጨለም” የሚል ትርጕም አለው። ድንግል ማርያም ኢየሱስን ትፀንስ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እንደ ጋረዳት ከዚህ በመነሣት መረዳት ይቻላል። በዚህ ጊዜ የተሠራ ተአምር መኖሩ ግልጽ ነው። እናም በዚህ የፅንሰት ሂደት ውስጥ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፈው ኀጢአት ነክ ነገር እንዳይተላለፍ፣ እግዚአብሔር በኀይሉ ጋርዶ ወይም ከልሎ እንዳስቀረ መረዳት የሚቻል ይመስለኛል። ምርጫ 4፤ ጌታ ኢየሱስ ኀጢአት ያልተላለፈበትን ምክንያት አናውቀውም። እኛ መረዳት በማንችለው መንገድ እግዚአብሔር ኢየሱስ ኀጢአት ሳይተላለፍበት እንዲፀነስ አድርጎታል። በዚህም ሆነ በዚያ ግን፣ ጌታ ኢየሱስ ከኀጢአት ነጻ መሆኑን ለማስረዳት ሲባል ከድንግል ማርያም የሰው-ነትን ባሕርይ እንዳልወሰደ መናገር ሙልጭ ያለ ስሕተት ነው። የቅዱስ መጽሐፍም፣ የቅዱስ ትውፊትም፣ የአመክንዮም ድጋፍ የለውም። “እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፣ እርሱ ደግሞ … በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። … የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም። ስለዚህ የሕዝብን ኀጢአት ለማስተስረይ፣ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ የሚምርና የታመነ ሊቀ ካህናት እንዲሆን፣ በነገር ሁሉ ወንድሞቹን ሊመስል ተገባው።” (2፥14፡17)
6 132
13
የቅዱሳት መጻሕፍት ግብ የቱ ነው? 1) ኀጢአተኛ በእግዚአብሔር ፊት እንዴት እንደሚቆም ማስረዳት? ወይስ 2) እግዚአብሔር ከፍጥረቱ መካከል እንዴት እንደሚኖር ማስረዳት? https://www.facebook.com/PaulsPulpit/posts/pfbid0gukcWzsZrXXTdPPa3oScQaUAGBiCe6Wo87moLcZ87cvJU8kNgYLX5BBoFw2j9Vdql
3 897
14
ተሳስቼ አውቃለሁ። ጉዳዩ 20 ዓመታት ዐልፈዉታል። በMaxwell Whyte የተጻፈ “The power of the Blood” የሚል መጽሐፍ ድሮ አንብቤ ነበር። የመጀመሪያው ምዕራፍ ጌታ ኢየሱስ ደሙን ከእናቱ እንዳላገኘው እና ከሰማይ ያመጣው መሆኑን የሚናገር እንደ ነበር አስታውሳለሁ። አዲስ ነገር ይማርካል አይደል? በዚህም ላይ ትምህርተ ድነትንም የተማርሁት ኢየሱስ ሥጋና ደም ከማርያም እንዳልነሣ በሚያስረዳ መልኩ ነበር። ስለዚህ ያን ምዕራፍ ወደ አማርኛ አመጣሁትና የአዲስ አበባ ሙሉ ወንጌል ልሳን በሆነው “ቀንዲል” የተሰኘ መጽሔት ላይ እንዲታተም ሰጠሁ። “ደም - የሕይወት ሕይወት” የሚል ርዕስ ተሰጥቶት ታተመ። ከብዙ ዓመታት በኋላ “ያልተንኳኩ በሮችን” ላሳትም ስንቀሳቀስ በሰበስብኳቸው ጽሑፎች ውስጥ ያን ጽሑፍ አካትቼው ነበር። ረቂቁን አስቀድሜ ከሰጠኋቸው ሰዎች መካከል የቀንዲል መጽሔት አዘጋጅ የነበረው ወንድም አንዱ ነበር። በመካከል በነበሩት ዓመታት ውስጥ ጥቂት የነገረ መለኮት ትምህርት ቀስሞ ስለ ነበር ጽሑፉ ትክክል ላይሆን እንደሚችል ነገረኝ። መጋቢ በቀለ ወ/ኪዳን እና ዘማሪ ገዛኸኝ ሙሴም አስቀድመው ረቂቁን ሲያነብቡ ያንኑ አጸኑልኝ። ያን ጽሑፍ ነጥዬ አወጣሁና ለተስፋዬ ሮበሌ እና ለተስፋሁን ኀጢያ ሰጠኋቸው። የሁሉም አቋም አንድ ነበር። እናም ጽሑፉን በመጽሐፌ ሳላካትተው ሳላካትተው ቀረሁ። (የታተመው በ2000 ዓ.ም. ነው።) ከዚያማ እኔም የነገረ ክርስቶስ መጻሕፍትን ማንበብ ጀመርሁ። የነገረ መለኮት ሥልጠናም ጀመርሁ። የቤተ ክርስቲያንን ታሪክንም አጠናሁ። ከዚያም ወደ ትክክለኛው አቋም መጣሁ። በዚያ ብቻ ግን አላበቃሁም። የድነት ትምህርት ያስተማረኝን ሰው በብዙ ውይይት አቋሙን አስቀየርሁት። የነገረ መለኮት ጽሑፎችን ማዘጋጀት ገና ሳልጀምር በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማንሣት አገልጋዮች በልከኛ የቅዱሳት መጻሕፍት ትርጓሜና በልከኛ ትውፊት መሠረት አቋማቸውን ዳግም እንዲያጤኑ የማድረግ ጥቂት የማይባሉ ዕድሎችን አግኝቻለሁ። ይህን ስል ግን ወንጌላውያን ክርስቲያኖች በሙሉ ጌታ ኢየሱስ የሰውነትን ባሕርይ ከእናቱ እንዳላገኘ ወይም የትኛውም ጽንስ ከእናቱ የሚወስደውን ነገር ጌታችን ከእናቱ እንዳልወሰደ ያስባሉ ማለት አይደለም። ይህ ጨርሶ ከእውነት የራቀ ነው። ቀላል ማስረጃ ላቅርብ። ታምራት ኀይሌ ቁጥር 7 የመዝሙር ሰንዱቁን ያወጣው መቼ ነበር? በዚያ ሰንዱቅ ውስጥ “ታሪኬ የጀመረው” የሚል መዝሙር አለ። እዚያ ውስጥ፣ “ከወህኒ ከፍርድ እኔኑ ሊያወጣ፣ ከድንግል ማርያም ሥጋ ነስቶ መጣ” የሚሉ ስንኞችን ይዟል። (ያን ጊዜ ዶክትሪን እንዘምር ነበር፤ አይገርምም?) በሌላ በኩል ግን ይህ ጉዳይ በቀላሉ የማይዋጥላቸው ወንጌላውያን ክርስቲያኖች እንደ ነበሩ መናገር እችላለሁ። ለምን? የወንጌላውያኑ አብዛኛው ተዋስኦ ከኦርቶዶክሳውያን ጋራ እንደ ሆነ ይታወቃል። “ማርያም ታማልዳለች ወይስ አታማልድም?” የሚል ዕውቅ ሙግት ለዚህ ዐይነተኛ ማሳያ መሆን ይችላል። እናም በዚህ ውይይት ወይም ንትርክ መካከል “በመስቀል ላይ የተሰቀለው የማርያም ሥጋ፣ የፈሰሰውም የእርሷ ደም ነው” የሚል ንግግር በኦርቶዶክሳውያን እንደሚዘወተር መናገር ይቻላል። ስለዚህ፣ ጭራሹኑ ከእናቱ ምንም አልወሰደም ብሎ በርን ጥርቅም አድርጎ መዝጋት ለዚህ በመፍትሔነት የተመረጠ ይመስላል። ሁለቱም አሳቦች ግን የቅዱሳት መጻሕፍትም፣ የትውፊትም፣ የአመክንዮም ድጋፍ የላቸውም። የእኔ ሥጋ፣ የእኔ እንጂ የእናቴ አይደለም፤ የእኔም ደም፣ የእኔ እንጂ የእናቴ አይደለም። የኢየሱስም ደም የእርሱ እንጂ የእናቱ አይደለም። እንደዚያ ከሆነ፣ የእርሷም ሥጋና ደም የእናቷ እንጂ የእርሷ አይሆንም። የእናቷም ... እያልን አዳምና ሔዋን ዘንድ መድረሳችን ነው። እናም የጌታችን ሥጋና ደም የእርሱ እንጂ የማንም አይደለም። ቅዱሳት መጻሕፍትም ትውፊትም ይህን ትምህርት ያጸናሉ። በሌላ በኩል ደግሞ፣ ጌታ ኢየሱስ ከሰው-ነት አንዳችም ነገር ያልጎደለው ምሉዕ ሰው ነው። የቱም ሕፃን ከእናቱ የሚያገኘውን ነገር ሁሉ እርሱም ከእናቱ ወስዷል። እኛንም የተዛመደው በእርሷ በኩል ነው። ከዚህ በቀር ጌታ ኢየሱስ ከሰማይ ያመጣው ሥጋና ደም የለውም፤ እንዲያ ከሆነ ግን እርሱ ሰው አይደለም። ምናልባትም በሰማይ ያሉ ሌሎች ፍጡራንን እንጂ እኛን የአዳም ልጆችን ሊወክለን አይችልም። እኛንም ወክሎ ጽድቅንም ሊፈጽምም ሊሞትልንም አይችልም። ስለዚህም በእርሱ ማንነትና ሥራ ድነትን አናገኝም። በሌላ በኩል ደግሞ ወንጌላውያንን ከላይ ያነሣነው አሳብ ቀልባቸውን የሚስበው ኀጢአት በሥጋና በደም እንደሚተታተመ። ማሰባቸው ነው። ይህን ደግሞ ምናልባት ሌላ ጊዜ እንመለስበታለን።
5 628
15
አሁንም፤ ከባለፈው የቀጠለ ነው። የእግዚአብሔር ትልቁ ዓላማ ፍጥረቱን ሁሉ በመሲሑ በኩል መዋጀት ሲሆን፣ ለዚህ ክቡር ዓላማው የመረጣቸው ሰዎች አሉ። እነዚህ ሰዎች ምን ዐይነት ሰዎች እንደሚሆኑ ከመወለዳቸውም በፊት ያውቃል። የት ድረስ እንደሚጸኑ፣ የት ድረስ እንደሚወድቁ ያውቃል። እግዚአብሔር ሲመርጣቸው ቅድመ ዕውቀቱን ተጠቅሟል? ወይስ አልተጠቀመም ብሎ መሟገት ግን ይቻላል። (በዚህ ቦታ የምናነሣው ምርጫ ከድነት ጋራ የሚያያዝ አይደለም።) እግዚአብሔር ለዚህ ክቡርና ታላቅ ዓላማው ሰዎችን ሲመርጥ፣ ስለ ሰዎቹ ያለውን ዕውቀት ከግምት ሳያስገባ በዘፈቀደ እንደ መረጣቸው የሚያስቡ ሰዎች አሉ። በተቃራኒው ደግሞ፣ እግዚአብሔር ስለሚመርጣቸው ሰዎች ቅድመ ዕውቀቱን ተጠቅሟል የሚሉ አሉ። ክቡሩን ዓላማውን ለመሸከም ያልመረጣቸው ሰዎች አሉ፤ ዓላማውን እንዲሸከሙ የመረጣቸውም አሉ። ለመረጣቸው ግን ጸጋውን ይሰጣቸዋል። ያዕቆብና ኤሳው ለዚህ ምሳሌ መሆን ይችላሉ። እግዚአብሔር ሆን ብሎ አስቦና አቅዶ ነው የመረጣቸው። ውድቀታቸውንም፣ ብርታታቸውንም ለዓላማው ይጠቀምበታል በማለት ማሰብም ይቻላል። እኔም ይህን እያልሁ ነው። ስለ ምርጫ ሲነሣ፣ ብዙዎች ምርጫ ሁሉ ለድነት እንደሚመስላቸው እየታዘብሁ ነው። ይህን ያልተቀበለ ሰውም ከስም ልጠፋ (labling) አያመልጥም። ምን ማለት ይቻላል? እግዚአብሔር ለመሲሑ መምጣት መንገድ ሲያበጃጅ ከመረጣቸው ሰዎች አንዱ ቂሮስ ነበር። “እግዚአብሔር ለቀባሁት፥ አሕዛብንም በፊቱ አስገዛ ዘንድ የነገሥታትንም ወገብ እፈታ ዘንድ፥ በሮቹም እንዳይዘጉ መዝጊያዎቹን በፊቱ እከፍት ዘንድ፥ ቀኝ እጁን ለያዝሁት ለቂሮስ እንዲህ ይላል። በፊትህ እሄዳለሁ ተራሮችንም ትክክል አደርጋለሁ፥ የናሱንም ደጆች እሰብራለሁ የብረቱንም መወርወሪያዎች እቈርጣለሁ፤ በስምህም የምጠራህ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እኔ እንደ ሆንሁ ታውቅ ዘንድ በጨለማ የነበረችውን መዝገብ በስውርም የተደበቀችውን ሀብት እሰጥሃለሁ። ስለ ባሪያዬ ስለ ያዕቆብ፥ ስለ መረጥሁትም ስለ እስራኤል ብዬ በስምህ ጠርቼሃለሁ፤ በቍልምጫ ስምህ ጠራሁህ፥ አንተ ግን አላወቅኸኝም።” (ኢሳ. 45፥1-4) ቂሮስ በእግዚአብሔር የተመረጠው፣ የተቀባው፣ የተጠራው ለድነት ስለ መሆኑ ምንባቡ አይናገርም። እንዲያውም “አንተ ግን አላወቅኸኝም” ነው የሚለው። “ስለ ባሪያዬ ስለ ያዕቆብ፥ ስለ መረጥሁትም ስለ እስራኤል ብዬ ጠርቼሃለሁ” በማለት ቂሮስ ለምን እንደ ተመረጠ እግዚአብሔር በግልጽ አስቀምጧል። እስራኤል ደግሞ ለመሲሑ መምጫ እግዚአብሔር ያሰባትና የተጠቀመባት መሆኗ ያስማማናል። እግዚአብሔር በመጀመሪያ መጨረሻውን ያውቃል። የሚያውቀውንም ለዓላማውና ለሥራው ይጠቀምበታል። ለመረጣቸው ሰዎች ጸጋውንም ይሰጣል። ይህም ሆኖ ግን የተመረጡት ሰዎች ሊወድቁ ይችላሉ። ሳዖል የእግዚአብሔር ምርጫ ነው፤ ወድቋል። ሳዖል የራሱ ብርታትም ድክመትም ያለው ሰው ነበር። የእርሱ መውደቅ ግን ለእግዚአብሔር ያልታሰበና ያልታወቀ ጉዳይ አልነበረም። አስቀድሞም ያውቀዋል። ለዓላማው (ዳዊትን ለመሥራት) ተጠቅሞበታል። እግዚአብሔር የታሪክ ባለቤት ነውና በዓለም ላይ የሚካሄዱትን ነገሮች አስቀድሞ ያውቃል፤ ለዓላማውም ይጠቀምባቸዋል። የሆነ ነገር ሲከሠት፣ ድንገተኛ ነገር ሆኖበት ለማስተካከል መፍትሔ ፍለጋ የሚንቀሳቀስ አምላክ አይደለም። ቢበቃኝ የሚሻል ይመስለኛል። https://www.facebook.com/PaulsPulpit/posts/pfbid0eSaCSUjpgs8M45qpcAoKdK3WhvMU4qwBMSV7YRXrBKSm9CZiHXQDdSjEERRHxqZ5l
4 614
16
ካለፈው የቀጠለ ... እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ ነው። እያንዳንዳችን ምን ዐይነት ሰው እንደምንሆን ለማወቅ እስክንወለድና ሥራችንን እስክንከውን መቆየት አያስፈልገውም። እግዚአብሔር አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን ... መርጧል። እስማኤልንና ኤሳውን ግን አልመረጠም። በሁለቱም ጎራ ያሉ ሰዎች ምን ዐይነት ሰዎች እንደሚሆኑ ግን አስቀድሞም ያውቅ ነበር። እግዚአብሔር መሲሑን ልኮ ፍጥረቱን የመቤዠት ዓላማው ዓለም ሳይፈጠርም የነበረ ነው። ለአዳምና ለሔዋንም ይህን ቃል ገብቶላቸዋል። ስለዚህ መሲሑ ለእግዚአብሔር “2ኛ ዕቅድ” (Plan B) አይደለም። እስራኤል እንደማትወድቅ ገምቶ፣ ስትወድቅበት መሲሑን ወደ ማምጣት አልሄደም። እስራኤል የት ድረስ እንደምትጓዝ አስቀድሞም ያውቃል። አብርሃም፣ ይስሐቅ፣ ያዕቆብ ... በሚል የጀመረው ጉዞ እስራኤልን ቢያስገኝም እንኳ እስራኤል እንደምትወድቅ እግዚአብሔር አስቀድሞም ያውቃል። እግዚአብሔር መሲሁን የማምጣት ዕቅዱን እንዲሁ በዘፈቀደ ያካሄደው አይደለም። የተመረጡትም ሰዎች በአጋጣሚ የተገኙ አልነበሩም። አስቦ፣ አቅዶ፣ አውቆ ነው ሰዎችን ለዓላማውና ለክቡር ኀላፊነት የመረጠው። የተመረጡት ሰዎች የት ድረስ ኀላፊነቱን እንደሚሸከሙና ዓላማውን እንደሚፈጽሙ፣ የቱጋ ደግሞ እንደሚደናቀፉና እንደሚወድቁ ያውቃል። ሆን ብሎ ነው የመረጣቸው። ይህም ሆኖ ግን እግዚአብሔር በማንም ችሎታና ብቃት ላይ አይታመንም። ለመረጣቸው ሰዎች ሁሉ ጸጋውን ሰጥቷቸዋል፤ በጸጋው ደግፏቸዋል፤ በጸጋው አስችሏቸዋል። እንዲህም ሆኖ ግን የተመረጡቱ ሊወድቁ ይችላሉ። ጸጋ ስለጎደላቸው ሳይሆን፣ ጸጋውን መግፋት ስለሚችሉ። ሳኦል በእግዚአብሔር የተመረጠ ንጉሥ ነበር፤ ነገር ግን ወድቋል። እስራኤል በእግዚአብሔር የተመረጠች ናት፤ ሆኖም ወድቃለች። ማሳሰቢያ፤ ይህ ጉዳይ ድነትን የሚመለከት አይደለም። ለመሲሑ መመጣት እግዚአብሔር የሠራበትን መንገድ የሚመለከት ብቻ እንጂ! https://www.facebook.com/PaulsPulpit/posts/pfbid029inkBVb59yFcUq4MB56TYBD4TVaqQy5iDXWgFbydDrkLNY49Fiw3f5ihvXqJs4s5l
4 031
17
ያዕቆብና ኤሳው ገና ሳይወለዱ፣ በጎ ወይም ክፉ ምንም ሳያደርጉ እግዚአብሔር ከሁለቱ አንዱን ለትልቅ ዓላማና ኀላፊነት መምረጡ ምን ይደንቃል? ያዕቆብ ወይም ዔሳው ምን ዐይነት ሰዎች እንደ ሆኑ፣ ለተመረጡበት ግብና ተልዕኮ ኀላፊነት ብቁ ይሁኑ አይሁኑ እግዚአብሔር ማወቅ የሚችለው ከተወለዱ በኋላ ነውን? ኀላፊነት ለመሸከም መቻላቸውን ለማወቅ በጎ ወይም ክፉ ሲያደርጉ ማየት ያስፈልገዋልን? ሰዎቹ ሲወለዱና ሲያድጉ ምን ምን ዐይነት ሰዎች እንደሚሆኑ እግዚአብሔር አስቀድሞም ያውቅ ነበር። https://www.facebook.com/PaulsPulpit/posts/pfbid0DvmBMbSwrDha8ujD3WQ9nkTAyZKPbxT2WqZ7KSRjMc2WFMLsKLoBGryBZ7KaRQR4l
5 078
18
https://www.youtube.com/watch?v=xjsM81lIEg0
4 871
19
https://www.missuniversegb.co.uk/finalists
5 385
20
Sin texto...
5 229