2 938
Suscriptores
+124 horas
+137 días
+5230 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
Repost from Addis Ababa Education Bureau
Photo unavailableShow in Telegram
ተማሪዎች በበይነ መረብ (Online) መፈተናቸው ያለው ጠቀሜታ
(ሰኔ 3/2016 ዓ.ም)
1. የበይነ መረብ ፈተና ለስህተት በር አይከፍትም
ይህም ለምሳሌ በወረቀት መልስን በማጥቆር ሂደት ተማሪዎች መልስ ሳይሰጡ ሊያልፉና ሊረሱ የሚችሉበት ወይም በመልስ ቅየራ ወቅት የመልስ መስጫ ወረቀት መጎዳት፣ ሁለት መልስ መጻፍ፣ አጋጣሚዎች ሲኖሩ እንዲሁም ከአንዱ ጥያቄ ወደ ሌላኛው ለማለፍ ገጽ ማገላበጥ ወ.ዘ.ተ. ሲኖርባቸው፣ በበይነ መረብ ሲሆን ግን ያልተመለሱ ጥያቄዎች እንዳሉ የሚጠቁም በመሆኑ፣ አንዱን ሳይመልሱ ወደ ፈለጉት ጥያቄ በአንድ “click” የመሄድ እንዲሁም ተመልሰው መስራት የሚፈልጉትን ጥያቄ “flag” በማድረግ ተመልሶ የመስራት እድልን ይሰጣል።
2. ጊዜ ቆጣቢ ነዉ
ወረቀት ላይ መልስ በማጥቆር የሚባክን ጊዜን በማስቀረት በአንድ “click” የፈተና ጥያቄን መልስ ለመስጠት ያስችላል። እንዲሁም ምን ያህል ደቂቃ እንደተጠቀሙ ከመፈተኛ ስክሪን ላይ ማየት ስለሚቻል ጊዜን በአግባቡ ለመጠቀም ያነሳሳል።
3. የተሻሻለ የመረጃ ቋት አለው
የበይነ መረብ ፈተናዎች፡ በቂ የፈተና መረጃዎችን ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ በማከማቸት ለተፈታኞች አመጣጥኖ ያቀርባል፡፡ በአሁኑ ፈተና ተማሪዎች ከሚፈተኑበት አከባቢ አንጻር በ5 ክላስተሮች በመመደብ፤ 5 ወደ ፈተና መግቢያ ማስፈንጠሪያ (URL) ተዘጋጅቷል። ማስፈንጠሪያው የተለያየ የሆነበት ምክንያት በፈተና ወቅት ያለውን የኢንተርኔት መጨናነቅ ለመቀነስ እንጂ በተሰጠው ሊንክ የገባ ማንኛውም ክልል እና ከተማ ላይ ያለ ተማሪ የሚገባበት የፈተና ቋት በሌላ ማስፈንጠሪያ ከገባ ተማሪ ጋር ተመሳሳይ ነው።
Repost from Addis Ababa Education Bureau
Photo unavailableShow in Telegram