Mattu University Christian Student Fellowship
Ir al canal en Telegram
ይህ ለመቱ ዩኒቨርሲቲ #Mattu_university ክርስቲያን ወንጌላውያን ተማሪዎችን አጠቃላይ ለማግኘት የተከፈተ ነው:: ህብረቱን በገንዘብ ለማገልገል:-1000127166847(CBE) ye mettu university christian team #METTU UNIVERSITY EvaSUE FELLOWSHIP #contact us @Yoohan7 Youtube👉 https://www.youtube.com/@evasuemau
Mostrar más1 068
Suscriptores
+224 horas
+107 días
+1230 días
Archivo de publicaciones
እንኳን ደስ አላችሁ!🎓“እግዚአብሔር ብቻውን መራው፤ ከእርሱም ጋር ሌላ አምላክ አልነበረም።” ዘዳግም 32፥12 ውድ የፈሎአችን ተመራቂዎች👨🎓👩🎓፣ እንኳን ለዚህ የደስታ ቀን አደረሳችሁ! በፌሎሺፕ ያሳለፋችሁት ቆይታ በእግዚአብሔር ፊት ውድና ትርጉም ያለው ነበር። በአምልኮ፣ በጸሎት፣ በኅብረትና በቃሉ ያደጋችሁባቸው ዘመናት ለቀጣይ ሕይወታችሁ ጠንካራ መሠረት ይሁኑላችሁ። በዚህ ፌሎሺፕ የተማራችሁትን እሴቶችና መንፈሳዊ ትምህርቶች ይዛችሁ በምትሄዱበት ሁሉ የክርስቶስ ብርሃን ሁኑ።
ጌታ በፊታችሁ ይሂድ፣ መንገዳችሁን ያቅና፣ በጥበብ፣ በጸጋና በፍቅር ይምራችሁ። የጀመረባችሁን መልካም ሥራ እስከ ፍጻሜው ያድርስ፣ ለብዙዎችም በረከት ያድርጋችሁ። እንኳን ደስ አላችሁ! እግዚአብሔር ይባርካችሁ።
እንኳን ደስ አላችሁ!🎓
“እግዚአብሔር ብቻውን መራው፤ ከእርሱም ጋር ሌላ አምላክ አልነበረም።”
ዘዳግም 32፥12
ውድ የፈሎአችን ተመራቂዎች👨🎓👩🎓፣ እንኳን ለዚህ የደስታ ቀን አደረሳችሁ! በፌሎሺፕ ያሳለፋችሁት ቆይታ በእግዚአብሔር ፊት ውድና ትርጉም ያለው ነበር። በአምልኮ፣ በጸሎት፣ በኅብረትና በቃሉ ያደጋችሁባቸው ዘመናት ለቀጣይ ሕይወታችሁ ጠንካራ መሠረት ይሁኑላችሁ። በዚህ ፌሎሺፕ የተማራችሁትን እሴቶችና መንፈሳዊ ትምህርቶች ይዛችሁ በምትሄዱበት ሁሉ የክርስቶስ ብርሃን ሁኑ።
ጌታ በፊታችሁ ይሂድ፣ መንገዳችሁን ያቅና፣ በጥበብ፣ በጸጋና በፍቅር ይምራችሁ። የጀመረባችሁን መልካም ሥራ እስከ ፍጻሜው ያድርስ፣ ለብዙዎችም በረከት ያድርጋችሁ። እንኳን ደስ አላችሁ! እግዚአብሔር ይባርካችሁ።
“ሔት። ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና።”
ሰቆ. 3፥22
“በታላቅ ድምፅም እንዲህ ብለው ዘመሩ፤ “የታረደው በግ ኀይልና ባለጠግነት፣ ጥበብና ብርታት፣ ክብርና ሞገስ፣ ምስጋናም፣ ሊቀበል ይገባዋል።”
ራእይ 5፥12
Repost from EvaSUE |ኢቫሱ
እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ ! አንተ የርስቴ ድርሻዬ ነህ ። ካንተ የምሻው ሌላ ድርሻ የለም ። ለሌዊ ድርሻው አንተ እንደሆንኸው ፤ ለኔም ድርሻዬ አንተ ነህ ። የማታልፍ ዘላለማዊ ፤ የማትጠፋ ሕያው እና አርጅተህ ማትታደስ ሕያው ርስቴ ፤ ምስጋና ላንተ ይኹን ። የተወለድኹብህ ፣ የኖርኹብህ እና የምኖርብህ የዘላለም ቤቴ ሆይ ተገኔ ነህና አልናወጽም ። አቤቱ አንተ የርስት ድርሻዬ ብቻ ሳትሆን ጽዋዬም ነህ ።
እረኛዬ ነህና ፣ መጋቢዬም ጠባቂዬም እልሃለሁ ። አኗሪዬም ነህና ፣ ዕጣዬ እንኳን ካንተ የተሰወረ ዐይደለም ። ለኔ እጅግ ሩቅ ቢሆንብኝ ፣ ስለራሴ ዕጣ እንኳን የማወቅ ብቃቱ ባይኖረኝ "ነገ ምን እኾን ?"ብዬ ማልሰጋው ዕጣዬ በእጅህ ስለሆነች ነው ። ሁሉዬ ነኽና ፣ ልቤ ያለስጋት ዘላለም ባንተ ያርፋል ። ባንተ እንድኖር ፤ ለራስህ ክብር ሠራኸኝ ። ከአእምሮ በላይ ስለሆነው ማንነትህ ፤ ከልቤ እስከ አርያም ፣ ከዛሬ እስከ ዘላለም ክብር ይሁንልህ !!
✍️ጌታሁን አያኖ
¹ እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በተለያየ ጊዜና በልዩ ልዩ መንገድ በነቢያት በኩል ለአባቶቻችን ተናግሮ፣
² በዚህ መጨረሻ ዘመን ግን ሁሉን ወራሽ ባደረገውና ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ ለእኛ ተናገረን።
ዕብራውያን 1
“ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ።”
ፊልጵስዩስ 4፥4
“ብቻውን አምላክ ለሚሆን ለማይጠፋው ለማይታየውም ለዘመናት ንጉሥ ምስጋናና ክብር እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን፤ አሜን።”
1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥17
“ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች፦ ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።”
1ኛ ሳሙኤል 2፥1
እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤ እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።
1ኛ ጴጥሮስ 5:6-7
የተወደዳችሁ 🎓🎓የGC ተማሪዎቻችን መልካም Exit Exam እግዚአብሔር ከናንተጋር ይሁን🙏
“ባናምነው፥ እርሱ የታመነ ሆኖ ይኖራል፤ ራሱን ሊክድ አይችልምና።”
2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥13
ኢሳይያስ 43¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ አሁንም ያዕቆብ ሆይ፥ የፈጠረህ፥ እስራኤልም ሆይ፥ የሠራህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ተቤዥቼሃለሁና አትፍራ፤ በስምህም ጠርቼሃለሁ፥ አንተ የእኔ ነህ። ² በውኃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፥ በወንዞችም ውስጥ ባለፍህ ጊዜ አያሰጥሙህም፤ በእሳትም ውስጥ በሄድህ ጊዜ አትቃጠልም፥ ነበልባሉም አይፈጅህም። ³ እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክህ እግዚአብሔር መድኃኒትህ ነኝ፤ ግብጽን ለአንተ ቤዛ አድርጌ፥ ኢትዮጵያንና ሳባንም ለአንተ ፋንታ ሰጥቻለሁ። ⁴ በዓይኔ ፊት የከበርህና የተመሰገንህ ነህና፥ እኔም ወድጄሃለሁና ስለዚህ ሰዎችን ለአንተ አሕዛብንም ለነፍስህ እሰጣለሁ። ⁵ እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ ዘርህንም ከምሥራቅ አመጣዋለሁ፥ ከምዕራብም እሰበስብሃለሁ።
የተወደዳችሁ የ ህብረታችን ልጆች ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።
እግዚአብሔር ረድቶን የዚህን ዓመት ቆይታችንን አብዛኞቻችን ጨርሰናል በመሆኑም ግቢ ለምትቀሩ GC እና fresh እንዲሁም ጤና ተማሪዎች ፀሎት ቤት ክፍት ስለሆነ በማንኛዉም ሰዓት መጠቀም ትችላላችሁ::
Repost from EvaSUE |ኢቫሱ
ድካሜን አውቃለሁ ። በጥቂት ነገር ልቤ በፍረኃት ተሸብቦ ሲንገላወድ የምኖር ልልዘሊል ነኝ ። ብርታቴ ሆይ ያላንተ እግሮቼ ጸንተው መቆም ይሳናቸዋል ። የቆምኹ እየመሰለኝ ልወድቅ ምንተፋተፍ ተሰባሪ ነኝና ብርታቴ ሆይ አንተን ተስፋ አደርጋለሁ ። በምኞት ማዕበል ዐይኖቼ ሲናጡ ፣ ልቡናዬም ክፋትን ሲያወጠንጥን ፣ እጆቼ ለነውር ሲዘረጉ ፣ መላአካሌ መሪ እንደሌለው መርከብ እማያውቅበት አገር ሲነጉድ መመለሻ መንገዴ አንተው ነህና ፤ በዚህ ኹሉ አንተን እጠብቃለሁ ። " ሰው እንዴት በዚህ ይወድቃል? "ብዬ ባልኹት ጉዳይ ራሴን አገኛለሁና አቤቱ እጆቼን ይዘኽ ትመራኝ ዘንድ ረድኤትህን እሻለሁ ።
ምትታመን ታማኝ ወዳጅ አምላኬ እግዚአብሔር ሆይ ካንተ በቀር በጎነት የለኝም ። ትናንትና ዛሬም እስከዘላለም ያው ኾነህ በምትኖር ባንተ እንጂ ዛሬ ባለኝ አቋም ፣ ትላንት ባሳለፍኹት ትጋት ታምኜ ነገን ተስፋ አላደርግም ። ባሳልፍኸው ትናንት ፣ ባሳየኸኝ ዛሬ ፣ በእጅህ ባለው ነገ አለመናወጽ ጸንተህ የምትኖር አንተ ነህና ጉልበቴ ሆይ አንተን እጠበቃለሁ ።
ብርታቴ ሆይ ፤ አምላኬም ነህና አንተን እጠብቃለሁ ። በእጆችህ አበጃጅተህ ያቆምከኝ ያንተው ፍጥረት ነኝና ሠሪዬም ነህ ። በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ላይ ጣር ልጅህ አድርገህ የተቀበልኸኝ አባቴም ነህና ፤ ምስጋና ላንተ ይሁን ። ተጠግቼ "እፎዬ "ምለው ። እውነተኛውን ርጋታም ማገኘው ፤ ባንተው ነውና መጠጊያዬ ሆይ ክብር እና ውዳሴ ላንተ ይሁን!! ለዘላለሙ አሜን!
ዛሬ 12 ሰዓት ከናንተ የሚጠበቀዉ በጊዜ መምጣት እና
ID_CARDመያዝ ብቻ ነዉ
✨ የምስጋና | የደስታ | የበረከት ጊዜ ✨ #GC_Wellgo #General_Wellgoእስካሁን ድረስ እግዚአብሔር ረድቶናል ነገ አርብ GC ተማሪዎችን “Wellgo” የምንልበት፣ እንዲሁም የዘንድሮን የፈሎሺፕ ጉዞ በምስጋና የምንዘጋበት ልዩ ፕሮግራም ይኖረናል። በዚህ ዓመት በጸጋው ያጸናንን፣ በፍቅሩ የመራንን፣ በቃሉ የለወጠንን እግዚአብሔር በአንድነት ከፍ እናደርገዋለን።
“እርሱም፦ ሂዱ፥ የሰባውንም ብሉ፥ ጣፋጩንም ጠጡ፥ ለእነዚያም ላልተዘጋጀላቸው እድል ፈንታቸውን ስደዱ፤ ዛሬ ለጌታችን የተቀደሰ ቀን ነው፤ የእግዚአብሔርም ደስታ ኃይላችሁ ነውና አትዘኑ አላቸው።” — ነሀምያ 8፥10ሁላችሁም ተገኝታችሁ ይህን የበረከት ጊዜ ከእኛ ጋር እንድታካፍሉ በክርስቶስ ፍቅር ተጋብዛችኋል። 📅 ቀን፦ አርብ ⏰ ሰዓት፦ 12 📍 ቦታ፦ ሙሉወንጌል
✨ ነገ ፈተና የምትጀምሩ የተወደዳችሁ የህብረታችን Remedial ተማሪዎች ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን::
ለግቢ ቆይታቹ ወሳኝ የሆነ ፈተና የምትወስዱ ስለሆነ እየተዘጋጃችሁ እንደቆያችሁ እናምናለን። በመሆኑም እናንተ ለራሳችሁ ከምታስቡት ይልቅ የሚያስብላችሁ አምላክ አእምሮአችሁን ያብራ፣ የተማራችሁትን በቀላሉ እንድታስታውሱ ጥበቡን ይስጣችሁ። ፍርሃት ይርቃችሁ፣ ሰላሙን ይሞላችሁ፣ ስኬትም ይከተላችሁ። በጣም እንወዳቹአለን አልፋችሁ ቀጣይ አብረን ጌታን እናመልካለን::
ምሳሌ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤ ⁶ በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል። ⁷ በራስህ አስተያየት ጠቢብ አትሁን፤ እግዚአብሔርን ፍራ፥ ከክፋትም ራቅ፤መልካም ፈተና🥰
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
